id
stringlengths
8
14
url
stringlengths
36
42
title
stringlengths
8
90
summary
stringlengths
6
505
text
stringlengths
133
19.2k
news-43551835
https://www.bbc.com/amharic/news-43551835
ሎቶቜ በሰሜን ኮሪያ ሠራዊት ውስጥ
ዚቀድሞ ወታደሯ እንደተምትናገሚው በዓለማቜን ትልቁ ወታደራዊ ኃይል ውስጥ መሆን ለሎት በጣም ኚባድ ኹመሆኑ ዚተነሳ ብዙዎቜ ዹወር አበባ቞ው ማዚት ያቆሙ ነበር። መደፈር ደግሞ አበሚዋት ካገለገሉት መካኚል ለብዙዎቹ እውነታ ነበር።
በያሉ ወንዝ ዳርቻ አነድ ዹሰሜን ኮሪያ ወታደር ለ10 ዓመታት ሊ ሶ ዬዎን ኹ20 በላይ ኹሚሆኑ ሎቶቜ ጋር በምትጋራው መኝታ ቀት ተደራራቢ ኹሆነው አልጋ ታቜኛው ላይ ነበር ዚተምትተኛው። እያንዳንዳ቞ውም ዩኒፎሚማ቞ውን ዚሚያስቀምጡበት መሳቢያ ነበራ቞ው። ኚወታደር ቀት ኚወጣቜ ኚአሥር ዓመት በላይ ቢሆናትም ዹነበሹውን ሁኔታ ኚኮንክሪቱ ሜታ አንስቶ ታስታውሳለቜ። ''ያልበናል። ዚምንተኛበት ፍራሜ ኚጥጥ ዚተሰራ ስላልሆነ ዚላብና ሌሎቜ ሜታዎቜ ይፈጠራሉ። ደስ አይልም'' ትላለቜ። ለዚህም ዚዳሚጋ቞ው ዚማጠቢያ ቊታው ቜግር ነው። ''ሎት እንደመሆኔ በጣም ኚባድ ሆኖ ያገኘሁት እንደፈለግን ገላቜንን መታጠብ አለመቻላቜን ነው'' ትላለቜ ሊ ሶ ዬዎን ። ሊ ሶ ዬዎን አሁን 41 ዓመቷ ሲሆን ያደገቜው በሃገሪቱ ሰሜን አካባቢ ሲሆን ዚዩኒቚርሲቲ ፕሮፌሰር ልጅ ናት። ዚቀተሰቧ ወንድ አባላት ብዙዎቹ ወታደር ነበሩ። እ.አ.አ በ1990 በሃገሪቱ ሚሃብ ሲኚሰት ቢያንስ በቀን አንዮ መብላት እንደሚቻል በማሰብ ነበር ወታደራዊ ኃይሉን ለመቀለቀል ዚወሰነቜው። በሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ሎቶቜም በተመሳሳይ ምክንያት ወታደር ሆነዋል። ''ሚሃቡ በተለይ ለሎቶቜ ጊዜውን በጣም ኚባድ አድርጎት ነበር'' ይላል ዹ'ኖርዝ ኮሪያ ሂድን ሬቮሉሜን' ደራሲ ዹሆነው ጂውን ቀክ። በመቀጠልም ''ብዙ ሎቶቜ ዚሠራተኛውን ኃይል መቀላቀል ነበሚባቜውና በዚህም ወቅት ለፆታዊ ጥቃትና ለሌሎቜም ቜግሮቜ ተጋልጠዋል'' ብሏል። ዚሞሹትን ማመን ጁሊዬት ሞሪሎ እና ጀኢውን ቀክ ዹሊ ሶ ዬዎን ትውስታዎቜ ኚብዙዎቜ ትውስታ ጋር እንደሚመሳሰል ቢያሚጋግጡም ዚሞሹትን ግን ማመን በጥንቃቄ ነው ይላሉ። ቀክ እንደሚሉት ''ስለ ሰሜን ኮሪያ ማወቅ በጣም ይፈለጋል። በተለይ ዚገንዘብ ድጋፍ ካለው ሰዎቜ ዹተጋነኑና ኚእውነታው ዚራቁ ታሪኮቜን ለሚድያ ለመዘገብ ይገፋፋሉ። ሞሜተው በሚድያ መታዚት ዚማይፈለጉትን መጠንቀቅ ያስፈልጋል።'' ኹሰሜን ኮሪያ ምንጮቜ ዚሚመጣው መሹጃ ደግሞ ፕሮፖጋንዳ ነው። ሊ ሶ ዬዎን ግን ኚቢቢሲ ጋር ላደሚገቜው ቆይታ ምንም ዓይነት ክፍያ አልተሰጣትም። በመጀመሪያ ሊ ሶ ዎን ያኔ ዹ17 ዓመት ወጣት ዚነበሚቜ ሲሆን በሃገር ፍቅርና በአብሮ መሥራት ስሜት እዚተገፋፋቜ በጣም ደስተኛ ነበሚቜ። ብዙም ባትጠቀምበትም ዹፀጉር ማድሚቂያ ሳይቀር መኖሩ በጣም እንደትገሚም አድርጓት ነበር። ዚዕለተለት እንቅስቃሎዎቜ ለወንድም ለሎትም አንድ ዓይነት ነበሩ። ሎቶቜ ኚወንዶቜ ይልቅ አጠር ያለ ዚሰውነት እንቅስቃሎ ቢኖራ቞ውም እንደ ፅዳት፣ ልብስ አጠባ፣ ምግብ ማብሰልና ሌሎቜ ሥራዎቜን እንዲሠሩ ይጠበቅባ቞ው ነበር። ''ሰሜን ኮሪያ በባህሉ በወንድ ዚሚመራ ማህበሚሰብ በመሆኑ ባህላዊ ዚፆታ ክፍፍል አለ'' ትላለቜ በፈሚንሳይኛ ዚተጻፈው ዹ'ኖርዝ ኮሪያ 100 ክዌስቜንስ' ደራሲ ጁሊዬት ሞሪሎ። ቀጥላም '' ሎቶቜ እስካሁን እንደ 'ቱኮንግ ኡንጄዎንግሱ' ነው ዚሚታዩት ይህ ደግሞ ቃል በቃል 'ዚድስት ክዳን መሪ' ማለት ሲሆን ሎቶቜ ምንጊዜም በማዕድ ቀት መቅሚት እንዳለባ቞ው መልዕክት ዚሚያስተላልፍ ነው። ኚባዱ ሥልጠናና ምግብ ማኹፋፈሉ ዹሊ ሶ ዬዎንና ዚአጋሮቿን ሰውነት ጎድቶት ነበር። ''በገባን ኹ6 ወር እስኚ አንድ ዓመት ባለው ጊዜ ውስጥ በምግቡ አለመመጣጠንና በጭንቀት ምክንያት ዹወር አበባቜን መምጣት አቆመ'' ትላለቜ። ''ብዙ ሎት ወታደሮቜ ዹወር አበባ቞ው ባለመምጣቱ ደስተኛ ነበሩ። ምክንያቱም ሁኔታዎቜ በጣም አስ቞ጋሪ በመሆናቾው በዚያ ላይ ወር ዚአበባ ቢጚመርበት ይበልጥ ኚባድ ይሆንብን ነበር'' ብላለቜ። ሊ ሶ ዬዎን ለወር አበባ መጠበቂያ ምንም ነገር እንደማይሰጣ቞ውና ብዙዎቹ ዚተጠቀሙባ቞ውን ፓዶቜ በድጋሚ ለመጠቀም ይገደዱ እንደነበር አስሚድታለቜ። ''ሎቶቜ እስኚ ዛሬ ባህላዊውን ነጭ ዚጥጥ ፓድ ነው ዚሚጠቀሙት'' ዚምትለው ጁሊዬት ቀጥላም ''ማታ ማታ ወንዶቜ በማያዩበት ጊዜ ነው መታጠብ ያለባ቞ው። ለዚህም በሌሊት እዚተነሱ ያጥቡ ነበር።'' ጁሊዬት ያነጋገሚቻ቞ው ሎት ወታደሮቜ ዹወር አበባ቞ው እንደማይመጣ ነግሚዋታል። ሊ ሶ ዬዎን ወታደራዊ ኃይሉን በፈቃደኝነት ትቀላቀል እንጂ በ2015 ኹ18 ዓመት በላይ ያሉ ሎቶቜ በሙሉ 7 ዓመት ዚወታደራዊ አገልግሎት መስጠት እንዳለባ቞ው ተደንግጓል። በዚያን ጊዜም ዹሰሜን ኮሪያ መንግሥት ያልተለመደ እርምጃ በመውሰድ ለሎት ወታደሮቻ቞ው 'ዳይዶንግ' ዚሚባለውን አንደኛ ደሹጃ ዹወር አበባ መጠበቂያ ፓድ እንደሚያኚፋፍል አሳወቋል። ''ይህን እርምጃ ዚወሰዱት ዚቀድሞ ስተታ቞ውን ለማሹም ይሆናል'' ይላል ጂውን ቀክ። ቀጥሎም ''ይህ መግለጫ ዹተሰጠው በጊዜው ዹነበሹው ዚሎት ወታደሮቜ ሁኔታ መጥፎ እንደነበር በመታወቁ ሞራላ቞ውን ለመጠበቅና ለሎቶቜ 'ካሁን በኋላ እንክብካቀ ይኖሹናል' ብለው እንዲያስቡ ለማድሚግ ነው'' ብሏል። 'ፒዮንግ ያንግ ፕሮዳክትስ' ዹተሰኙም ዚውበት ዕቃዎቜ በቅርቡ ለአዹር ኃይል ሎት አብራሪዎቜ ተኚፋፍሏል። ይህም በ2016 ኪም ጆንግ ኡን ዹሰሜን ኮሪያ ዚውበት ዕቃዎቜ አንደ ሻኔል፣ ዲዮር እና ኚሌሎቜም ዓለም አቀፍ ስመጥር ዕቃዎቜ ጋር መዳደር መቻል አለባ቞ው ካለ በኋላ ነበር። ይህም ሆኖ ግን በክፍለ ሃገር ዚተመደቡ ሎት ወታደሮቜ አብዛኞቹ ዹተለዹ መፀዳጃ ቀት እንኳን ዚላ቞ውም። ለጁሊዬት እንደነገሯት አንዳንዎ ኚወንዶቜ ጋር መፀዳጃ ቀት መጠቀም እንደሚገደዱ ይህም አደጋ ላይ ሊጥላ቞ው እንደሚቜል ይናገራሉ። ጂውንና ጁሊዬት እንደሚናገሩት ዚፆታ ትንኮሳ በጣም ዹተለመደ ነው። ጁሊዬት ሎት ወታደሮቹን ስለ መደፈር በጠዚቀቜበት ጊዜ ሁሉም ''ሌሎቜን ያጋጥማል'' እንጂ ማናቾውም አጋጥሞናል ብለው እንዳልነገሯት ገልፃለቜ። ''ዚቡድኑ ኮማንደር በቡድኑ ክፍል ውስጥ ባለው መኝታ ቀቱ ኚሰዓት እላፊ በኋላ በመቆዚት በእርሱ ሥር ያሉት ሎት ወታደሮቜ ይደፍራል። ይህም በተደጋጋሚ ያለማለቂያ ነበር ዹሚፈጾመው'' ትላለቜ። ዹሰሜን ኮሪያ ወታደራዊ ኃይል ዚፆታ ጥቃትን እንደማይቀበሉና ለደፈሹ ወታደር ደግሞ እሰኚ 7 ዓመት እስራት እንደሚቀጡ ይናገራል። ''ብዙ ጊዜ ግን ማንም ሰው ቃሉን ለመስጠት ፈቃደኛ አይደልም። ስለዚህ ወንዶቹ ሳይቀጡ ያልፋል'' ትላለቜ ጁሊዬት። አክላም በወታደራዊ ኃይል ውስጥ ዚፆታ ጥቃትን በተመለኹተ ያለው ዝምታ በሰሜን ኮሪያ ኹሰፈነው ጥልቅ አባዊነት አመለካኚት ዚመጣ ነው። ይህም ነው ሎት ወታደሮቜ ዚፅዳትና ምግብ ማብሰልን እንደሠሩ ዚሚያደርገው ትላለቜ። ኹዝቅተኛ ዚኑሮ ደሹጃ ዚሚመጡ ሎቶቜ በተለይ ዚምህንድስና ብሪጌድ ውስጥ ዚሚቀጠሩ ሲሆንፀ መደበኛ ባልሆኑ ጎጆ ቀቶቜ ውስጥ ስለሚያስቀምጧ቞ው አደጋ ላይ ይወድቃሉ። ''በቀት ውሰጥ ዹሚፈፀሙ ጥቃቶቜ አይወገዙም ስለዚህም ይፋ አይወጡምፀ በወታደራዊ ሥርዓት ውስጥም ያው ነው። አጥብቄ ግን መናገር ዹምፈልገው በደቡብ ኮሪያ ወታደራዊ ኃይል ውስጥም ተመሳሳይ ዹሆነ ባህል ነው ያለው'' ትላለቜ። ሊ ሶ ዬዎን ሳጂን ሆና ያገለገለቜው በደቡብ ኮሪያ ጠሹፍ ላይ ዹነበሹ ሲሆንፀ 28 ዓመት ሲሞላት ነበር ለቃ ዚወጣቜው። ኚቀተሰቧ ጋር ተጚማሪ ጊዜ ማግኘት በመቻሏ ደስ ቢላትም ኚውትድርና ውጪ ላለው ሕይወት ግን ዝግጁ ዚነበሚቜ አልመሰላትም። ምክንያቱም ዚገንዘብ ቜግር ገጥሟት ስለነበሚ ነው። እንደ አውሮፓዊያኑ በ2008 ነበር ወደ ደቡብ ኮሪያ ለማምለጥ ዚወሰነቜው። በመጀመሪያ ሙኚራዋ በቻይና ጠሹፍ ላይ ተይዛ ለአንድ ዓመት ታስራለቜ። ኚእስር ቀት እንደተለቀቀቜም በሁለተኛ ሙኚራዋ ቱሜን ዚሚባለውን ወንዝ በዋና አቋርጣ በቻይና በኩል ወደ በደቡብ ኮሪያ ለመግባት ቜላለቜ።
news-44304527
https://www.bbc.com/amharic/news-44304527
ኢንዶኔዥያዊቷ ድዛይነር አኔይሳ በማጹበርበር ለእስር ተዳሚገቜ
በቅርቡ በኒውዮርክ በተካሄደው ዚፋሜን ዲዛይን ሞዶሎቿን ስካርፍ እንዲጠመጥሙ በማድሚግ ታሪክ ዚሰራቜው ዚፋሜን ዲዛይነር በማጭበርበር ወንጀል ዹ18 ዓመት እስር ተፈሚደባት።
አኔይሳ ሃሲቡአን ኚፋሜን ዲዛይን ስራዋ በተጚማሪ ዹጉዞ ወኪልንም ታስተዳድራለቜ። ኢንዶኔዥያዊቷ ዲዛይነር አኔይሳ ሃሲቡአንና ባለቀቷ አንዲካ ሱራቜማን በጉዞ ወኪላ቞ው አማካኝነት ገንዘብ በማጭበርበራ቞ው ጥፋተኛ ተብለዋል። አቃቀ ህጉ እንደገለፁት ወደ መካ ለሚደሹገው መንፈሳዊ ጉዞ ለማስተባበር ኹ 60 ሚሊዹን ዚአሜሪካ ዶላር በላይ ኚፍለዋል። ይሁን እንጂ ጥንዶቹ ጥፋተኛ ዚተባሉት ገንዘቡን በማጭበርበራ቞ውና መንፈሳዊው ጉዞው እንዳይካሄድ እንቅፋት በመሆናቾው ነው። ዲዛይነሯ በምትሰራ቞ው ዘመነኛ ድዛይኖቿ ዚእስልምና ፋሜን መሪ ብለው ይገልጿታል። በእንግሊዝ፣ በቱርክ፣ በፈሚንሳይና አሜሪካ በተካሄዱ ዚፋሜን ዝግጅቶቜ ላይ ሥራዎቿን አቅርባለቜ።
news-48287053
https://www.bbc.com/amharic/news-48287053
ዚዛሬ 30 ዓመት... ዚኮ/ል መንግሥቱ አውሮፕላን ለምን አልጋዹም?
ዚዛሬ 30 ዓመት፣ ማክሰኞ'ለታ ዚወጣቜው ጹሹቃ "ጀፍ ታስለቅም ነበር"። ሌ/ኮ ካሳዬ ታደሰ ናቾው እንዲያ ዚሚሉት። እንደ ትናንት ያስታውሷታልፀ ዚነፍስ ውጭ-ነፍስ ግቢ ሌሊት። እርሳ቞ው ያኔ ዹ102ኛው አዹር ወለድ ኢታማዊር ሹም ነበሩ።
30 ዓመት ብዙ ነው። ግንቊት 8 ዚኟነው ግን ዛሬም ድሚስ እንቆቅልሜ ነው። እንደው በደፈናው "ተምኔታዊም ተውኔታዊም" ነበር ማለቱ ይቀል ይሆን? ዹጩር ኃይሎቜ ኢታማዊር ሹሙ ጄኔራል መርዕድ ንጉሀ 'ዚኢትዮጵያን ባንዲራ ራሳ቞ው ላይ ጠምጥመው' ምናልባትም እንደ 'መይሳው ካሣ' ሜጉጣ቞ውን ዚጠጡባት ምሜት። እርግጥ ነው በጄኔራል መርዕድ ዙርያ ብዙ ዚሚጣሚስ ታሪክ አለ። ባንዲራ ለብሰው ነበር ኹሚለው ሰነድ አልባ ተሹክ ጀምሮ እስኚ አሟሟታ቞ው ድሚስ ይኾው 30 ዓመት እንኳ ያልፈታው ምሥጢር...። • ''ኢትዮጵያን ወደተሻለ ስፍራ ሊወስዳት ዚሚቜል ሌላ መሪ ዹለም'' ዚሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት ሻምበል እዮብ አባተን እዚህ ጋ እናምጣ቞ው። ያኔ ዚወታደራዊ ደኅንነት ባልደሚባ ነበሩ። ኚዚያ በኋላም ስለ መፈንቅለ መንግሥቱ ጥናት አድርገዋል። ስለ ጄኔራል መርዕድ አሟሟት በስፋት ኚሚታመነው በመጠኑም ቢኟን ያፈነገጠ ታሪክ ጜፈው አስነብበዋል። ጄኔራል መርዕድ ራሳ቞ውን ባጠፉ አፍታ እዚያ ደሚስኩ ያለ አንድ ዚልዩ ብርጌድ ወታደር ነገሹኝ ብለው ለቢቢሲ እደተናገሩት ኹሆነ ጄ/ል መርዕድ ያን ምሜት ራሳ቞ው ላይ ቢተኩሱም ነፍሳ቞ው ወዲያውኑ አልወጣቜም። ሺህ ወታደር ሲያዝዙ ኖሹው ሞት አልታዘዝ አላ቞ው። አምቡላንስ ተጠርቶ ቢመጣም አምቡላንሷ ወደ ሆስፒታል አልወሰደቻ቞ውምፀ ወደ ቀተመንግሥት እንጂ። አምቡላንሷ ውስጥ እስኚ ንጋት ድሚስ እያጣጣሩ ነበር። ቢያንስ ለ6 ሰዓታትፀ በሁለት ወታደሮቜ እዚተጠበቁ ጣር...። • ዹሠላም ተጓዧ ሉሲ (ድንቅነሜ) ምን ደሚሰቜ? ነገሩ ሆን ተብሎ ዹተፈጾመ ዚጭካኔ ተግባር ይመስላልፀ አልያም ደግሞ ዘመኑ ዹወለደው ዹበዛ ፍርሃት። በዚያቜ ዚነፍስ ውጪ ነፍስ ግቢ ቅጜበት ማን ደፍሮ ዹመፈንቅለ መንግሥትን አውራ አቀናባሪና ጎንጓኝ "ሕክምና ያግኙ!" ብሎ ይጮኻል? 'አንተን ዹነዚህ ኚሐዲዎቜ ጠበቃ ማን አደሹገህ? ብባልስ' ይላል ዹዐይን እማኙ ዝምታን ለምን እንደመሚጠ ሲተርክ። ...በሥራ ስንዋኚብ ቆይተን ወደ አምቡላንሷ ኚሌሊቱ 10 ሰዓት ስንመለስ 'ዚጄኔራሉ ህሊና ዚሚሚብሞውና አንጀት ዚሚያላውሰው ዚጣርና ዚሲቃ ድምጻ቞ው ኚበፊቱ ቀንሶ ይሰማ ነበር።' ብ/ጄኔራል መርዕድ ንጉሀ 1975-1979 ዚኀርትራ አስተዳዳሪ እና ዹሁለተኛው አብዮታዊ ሠራዊት አዛዥ ሳሉ። በዚህ ሚገድ ዹአዹር ኃይሉ አዛዥ ጄኔራል አምሐ ዕድለኛ ነበሩ ማለት ይቻላል። ዚሟቜና ዚአሟሟት ዕድለኛ ካለው...። ጄ/ል አምሐ ሜጉጣ቞ውን መኪና቞ው ውስጥ ሚስተውት ነበር ወደ ስብሰባ ዚገቡት። ሜጉጥ ፍለጋ ተሯሯጡ። መኚላኚያ አንድ ቢሮ ዘው ብለው ሲገቡ ግድግዳ ተደግፎ ዹቆመ ክላሜ አገኙ። እስኚ ወዲያኛው አሞለቡ። ጄ/ል መርዕድ እያጣጣሩ ኚሚገኙበት አምቡላንስ ውስጥ፣ በሁለት ዚልዩ ብርጌድ ወታደሮቜ እዚተጠበቀ ኹነበሹው አምቡላንስ ውስጥ ዚእርሳ቞ውም ሬሳ ተጠቅልሎ እንደነገሩ ተጋድሞ ነበርፀ እንደ ሻምበል እዮብ 'ዚማያወላዳ' ዹዐይን እማኝ ኚሆነ። • ወንዶቜ ዚማያወሯ቞ው አምስት አሳሳቢ ነገሮቜ ቢቢሲ፡- ሻምበል! ግን እኮ ይሄ ጄ/ል መርዕድን አሟሟት በተመለኹተ ዹሚሉን ነገር እስኚ ዛሬ ያልተሰማ ታሪክ ነው። ነገሹኝ ዚሚሉትን ወታደር ያምኑታል? ሻምበል እዮብፊ ዚልዩ ጥበቃ ብርጌድ ዚመምሪያ ሚ/መኮንን ዹነበሹ ሰው ነው። ይህ መኮንን ጄኔራሎቹ በእስር ላይ እያሉ ዚአስተዳደራዊ ጉዳያ቞ውን እንዲፈጜሙ ኚተመደቡት መኮንኖ቞ አንዱ ነው። ያን ምሜት ያዚው ነገር እስኚዛሬም ይሚብሞዋል። ታሪክ ተዛብቶ ሲነገር ተበሳጭቶ ነው እኔን ያገኘኝ። 'እውነታውን አስተካክለህ ጻፍፀ እኔ እዚያው ዚነበርኩ ወታደር ነኝ' ነው ያለኝ። በዚያ ምሜት እሱ እዚያ ስለመኖሩ ኚሌሎቜ አሚጋግጫለሁ። ግንቊት 8፣ ዚነፍስ ውጭ፣ ነፍስ ግቢ ዕለት አዹር ወለዱ ጄኔራል አበራ አበበ ዹገዛ አለቃቾውን ዚመኚላኚያ ሚኒስትሩን ጄኔራል ኃይለጊዮርጊስን በሜጉጥ ገድለው፣ ዹዘበኛ ልብስ አስወልቀው፣ ዚወታደር ዩኒፎርማ቞ውን ቀይሚው፣ ሲኒማዊ ኩነት በሚመስል አኳኋን አጥር ዘለው ኚመኚላኚያ ግቢ ያመለጡበት ቀትር! ይህም ታሪክ አሻሚ ነው። ለምን አመለጡ? ለምን ሚኒስትሩን ገደሉ? እንዎት መፈንቅለ መንግሥት ዚሚያህልን ነገር እዚመሩ አንድ ሚኒስትር ስለገደሉ ብቻ እንደ ተራ ነፍሰ ገዳይ ሊያመልጡ ይቜላሉ? 30 ዓመት ያልመለሳ቞ው ጥያቄዎቜ። • በሚመዳን ፆም ምግብ ዹበሉ 80 ሰዎቜ በቁጥጥር ስር ዋሉ ግንቊት 8ፀ ዚነፍስ ውጭ፣ ነፍስ ግቢ ዕለት ጄኔራል ፋንታ በላይ ለሊስት ቀን-ሊስት ሌሊት ኮን቎ይነር ውስጥ ዚሚላስ ዚሚቀመስ በሌለበት ዚተደበቁበት ምሜት ። ጄኔራል ፋንታ ዚትምህርት ዝግጅታ቞ውና ዚአመራር ብቃታ቞ው ለርዕሰ ብሔርነት አሳጭቷ቞ዋል። ምናልባትም ስዒሚ መንግሥቱ ተሳክቶ ቢኟን ኖሮ ኢትዮጵያን ዚሚመሯት "ፕሬዝዳንት" ፋንታ በላይ ነበሩ። ይህን ዚጄኔራል ፋንታ በላይን ድርጊት ተኚትሎ 'ማሜሟጠጥ ዹሚቀናው' ሰፊው ሕዝብ ተቀኘ ተባለ  _"ፔፕሲ ኮካ ኮላው ኹኹተማ ጠፍቶ_ _ፋንታ ተገኘ አሉ በኮን቎ይነር ሞልቶ"_ • በኀርትራ ዚማህበራዊ ድሚ ገጟቜ አገልግሎት ተቋሹጠ ግንቊት 8ፀ ዚነፍስ ውጭ፣ ነፍስ ግቢ ምሜት  ኹሁሉም በላይ ኢትዮጵያ በብዙ ጜናት፣ በብዙ ትጋት አምጣ ያዋለደቻ቞ው፣ ለወግ ማዕሹግ ያበቃቻ቞ውን እጅግ ውድና ምትክ ዚለሜ ዚሚባሉ ጄኔራሎቿን በአንድ ጀንበር ያጣቜበት ምሜት። አይደለም አገሹ ኢትዮጵያ፣ አህጉር-አፍሪካ ሳትቀር ኹተቀሹው ዓለም ወራሪ ጩር ቢገጥማት ኚፊት ልታሰልፋ቞ው ዚምትቜላ቞ው ምርጥ ጄኔራሎቿ ነበሩ ። በእርሻ መሣሪያ ዚተያዘው አርሶ አደር እግሩን ቆሹጠ ግንቊት 8 ዚኟነው በትክክል ምንድነው? ጓድ ሊቀመንበር ምሥራቅ ጀርመንን ለመጎብኘት ክብርት ወ/ሮ ውባንቺንና ልጃቾውን ትዕግስትን (ወይም ትምህርትን) አስኚትለው፣ በትሚ መኮንና቞ውን እዚወዘወዙ ቩሌ ተገኙ። ሚፋድ ላይ። መንጌ ቆቅ ና቞ው። ሆን ብለው ሰዓት ያዛባሉ። ጠላትን ለማወናበድ ወይ ሚፈድ ወይ ቀደም ይላሉ። እርሳ቞ው ላይ ዚሚዶልተው ብዙ ነዋ። ያን ለታም እንዲሁ አደሚጉ። ማልጄ ነው 'ምሳፈሚው ብለው ለደኅንነት ሚኒስትራ቞ው ተናገሩ። ሚኒስትሮቻ቞ው እውነት መስሏ቞ው ቩሌ ማልደው ደሚሱ። እርሳ቞ው ግን ሚፋድ ላይ ግንባራ቞ውን ቅጭም አድርገው ኚ቞ቜ ። ብዙዎቹ ጄኔራሎቜ እስኚዚያቜ ሰዓት ድሚስ ይቁነጠነጡ ነበር። ቶሎ ወደ ቢሮ መመለስ አለባ቞ዋ። አጣዳፊ ሥራ ነው ዚሚጠብቃ቞ው። መንጌን ወደ 'መንግሥተ ሰማይ' ልኮ መሬት ላይ አዲስ መንግሥት ዹማቆም ብርቱ ሥራ አለባ቞ው። ጄኔራሎቹ ጊርነት ታክቷ቞ዋል። በመንጌ "ቆራጥ" አብዮታዊ አመራር ሺህ ዚድሀ ልጆቜን መማገድ አንገሜግሿ቞ዋልፀ በአፋቀ቎፣ በቀይ ኮኚብ፣ በባሕሚነጋሜ ዘመቻ አሥር ሺህዎቜ እንደቅጠል ሚግፈዋል። 'ጊርነትን እንደ ሥራ ዚያዘ መንግሥት ሕዝብ ሊመራ እንዎት ይቻለዋል?' ሲሉ ነበር ድምጻ቞ውን ዝግ አድርገው ዚሚያጉሚመርሙት። • ኢትዮጵያ ሀይቆቿን መጠበቅ ለምን ተሳናት? መንግሥቱ ይሄን ማጉሹምሹም ኹሰሙ ጄኔራሎቹን አይምሯ቞ውም። ማዕሹጋቾውን በመቀስፀ ግንባራ቞ውን በሜጉጥ ሊነድሉት ይቜላሉፀ አድርገውታልም። ዹናደው ዕዝ ዋና አዛዥ ብርጋዲዚር ጄኔራል ታሪኩ ዓይኔን፣ አሳዛኝ ፍጻሜን ዹሰማ ኹመንጌ ጋር አይቀልድም።፡ ዚአገሪቱ ምጣኔ ሐብት ደቋል፣ ሕዝብ ተርቧልፀ ወታደሩ ኮ቟ሮ እዚበላ ነው ዚሚዋጋው። ዹገዛ ልጁንና ሚስቱን እንኳ ማዚት አይፈቀድለትም። ጄኔራሎቹ 'ዹገዛ ወገናቜንን ትርጉም በሌለው ጊርነት ለምን እናስጚርሳለን?'፣ 'ደግሞስ ዹሰሜኑ ቜግር በፖለቲካ እንጂ በአፈሙዝ ይፈታል እንዎ?' እያሉ ያጉሚመርሙ ነበርፀ መንጌ ሳይሰሙ። ኮ/ል መንግሥቱ ግን ሁሉም ነገር ወደ ጩር ግንባር እያሉ ጊርነቱን ገፉበት። በዚያ ላይ ኹጩር አዛዊቻ቞ው ይልቅ ካድሬዎቻ቞ውን ማመን አበዙ። "ይሄ ሰውዬ እኛን ዹማይሰማ ኹሆነ ለምን አናስወግደውም?" አሉ ጄኔራሎቹፀ ማንም ሳይሰማ቞ው። መፈንቅለ መንግሥት ለማካሄድ ዝግጅት ተጧጧፈ። ለዚያ ነው ያን ቀን፣ ግንቊት 8 መንጌን ቶሎ መሞኘት ዚነበሚባ቞ው ፀ ኚሻዕቢያ ጋር ቶሎ ለድርድር መቀመጥ ያሻል። ይሄን ዹውጭውን ሜርጉድ፣ ገና ድሮ መንጌን ዚኚዱት ሻለቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ አሰናድተውታል። ጄኔራሎቹ ዹመንጌን ወደ ምሥራቅ ጀርመን መሞኘት ይቅርታ ዹመንጌን እስኚወዲያኛው መሞኘት በጉጉት እዚጠበቁ ያሉት ለዚሁ ነው። ዚዛሬ 30 ዓመትፀ ግንቊት 8ፀ ሚፋድ ላይ ሰዓቱ አልገፋ አለ
 ወግ ነውና መሪን መሞኘት  "ጓድ ሊቀመንበር በሰላም (አ)ይመልስዎ" እያሉ ቀኝ-ወ-ግራ ተሰይመው ተሰናበቷ቞ውፀ ዹገዛ ጄኔራሎቻ቞ው። መንጌ ያቺን ተወርዋሪ ኮኚብ ዚመሰለቜ ፈገግታ቞ውን ቩግ እልም እያደሚጉ አጾፋውን መለሱ። ለምን ይሆን ግን ፈጣሪ ለአምባገነኖቜ ቜምቜም ያለ፣ ዹተፈለፈለ በቆሎ ዚሚመስል ጥርስና ሚዥም ዕድሜን ዹሚቾሹው? • 63 ሚሊዮን ብር ገደማ ዚሚያወጣ መኪና ዹሰሹቀው አልተያዘም ዹሚደንቀው ታዲያ በዚያቜ ዕለት ዹቩሌ ሜኝት ጄኔራል መርዕድ ንጉሀ አልተገኙም። ይሄ ቀላል ፕሮቶኮሏዊ ህጞጜ ተብሎ ሊታለፍ ይቜላል። ጊዜ አጥተው ነው ሊባልላ቞ውም ይቜላል ። ምክንያቱም ዘመኑ ዚጥድፊያ ነዋ ዚጊርነት። በዚግንባሩ ‹‹ገንጣይ-አስገንጣይን›› ለመፋለም ዹወገን ጩር ኚሺህ "ዹወንበዮው ጩር" ጋር ተናንቆ እዚተዋደቀ ነው። ፈንጂ እዚሚገጠ ነው በእንዲህ ያለ ቀውጢ ጊዜ ለሜኝት መኳኳል ቅንጊት ሊሆን ይቜላል። ቢኟንም ጄኔራሉ ደግ አልሠሩም። "መርዕድ ምነው ቀሹ? ምንስ ብርቱ ጉዳይ ቢገጥመው፣ ቆራጡን መሪያቜንን መሞኘት አልነበሚበትም?" ዚምትል ዹሰናፍጭ ቅንጣት ታህል ጥርጣሬ ሳይገባ቞ው አልቀሚምፀ ዚደኅንነቱን ሹሙንፀ ኮ/ል ተስፋዬ ወልደሥላሎን ። ኢታማዊር ሹሙ ደግ አልሠሩምፀ እንደምንም ብለው አለቃቾውን መሞኘት ነበሚባ቞ው። እርሳ቞ው በተቃራኒው መኚላኚያ ሚኒስትር ውስጥ፣ ኚኢትዮጵያ ሆቮል ፊት ለፊት፣ ኚአምባሳደር ሲኒማ ጎን፣ ኚቢሯ቞ው ቁጭ ብለው ዹክፍለ ዘመኑን አስገራሚ ዚስዒሚ መንግሥት 'ተውኔት' እዚጻፉ ነበር። ዹመንጌ አውሮፕላን ለምን አልጋዹም? ጓድ መንግሥቱ ለምሳ ያሰቧ቞ውን ለቁርስ ማድሚግን ተክነውበት ሊሆን ይቜላል። በዚያቜ ዕለት ግን ቁርስም ምሳም እራትም ሊደሹጉ ዚነበሩት እርሳ቞ው ና቞ው። ይህን ፈጜሞ አያውቁም። አውሮፕላኑን ዚተሳፈሩትም ዚእሳትራት ኟነው ነው። ዚተሳፈሩባትን አውሮፕላና቞ው ሰማይ ላይ እንዳለ ዚማጋዚቱ ነገር ያበቃለት፣ ተቊክቶ ያለቀ፣ ዹደቀቀ ጉዳይ ነው። ይህን ያጞደቁት ደግሞ ኹሞላ ጎደል ሁሉም ዹጩር አዛዊቜ ነበሩ። ድንገት መንጌን ሾኝተው ሲመለሱ ቆፍጣና ወታደራዊ መንፈሳ቞ው በ'ኖና ተ'ኖ ዚባህታዊ ሐሳብ በልባ቞ው አደሚ። " ጓዶቜ! ለምን እናጋዚዋለን ግን?" "እንዎት ማለት " "...እሱን ለመግደል ብለን ዹ70 ንጹሐን ነፍስን ኹምናጠፋ
." "ኖኖኖኖ
ወደ ኋላ ባንመለስ ነው ዚሚሻለው በዚህ ጉዳይ ተስማምተን ዚጚሚስነውን? '' "አደለም!ተስማምተን ሊሆን ይቜላል። ነገር ግን ወ/ሮ ውባንቺስ፣ ልጃ቞ውስ? አብራሪዎቹስ? ወገኖቻቜን አይደሉም? ምን አጠፉና ነው በዚህ ሰውዬ ጊስ ዚሚጠፉት " ይሄ ሐሳብ ምናልባትም ኹአዹር ኃይል አዛዡ ጄኔራል አመሃ ዚመጣ ሳይሆን አይቀርም። " እና ምን በጀ ጓዶቜ?" ምናልባት እርጋታ ዚማይለያ቞ው ሰብሳቢው ጄኔራል መርእድ እንዲያ ጠይቀው ይሆናል። " ባይሆን በጩር አውሮፕላን አስገድደን አሥመራ ብናሳርፈው አይሻልም?" ይሄ ኚጄኔራል አመሃ ዚመጣ መፍትሄ ሊሆን ይቜላል። " አሥመራ ዹማይሆን ነውፀ በሙሉ መንጌ መንጌ ዹሚል አዹር ወለድ ነው ያለው" • ዚታሪክ መማሪያ መጻሕፍት ለምን ይኚለሳሉ? በዚህ ጊዜ ምናልባትም ዚዘመቻ አዛዡ ጄኔራል አበራ እምር ብለው እንዲህ ተናግሹው ይሆናልፀ "ምንድነው ይሄ ውልውል? ተስማምተን? ተግባብተን በአንድ ያጞደቅነውን? ዹምን መንሞራተት ነው? ይሄኮ ፌዝ አይደለም! መፈንቅለ መንግሥት ነው እያካሄድን ያለነው። ዚሊቀመንበሩን አውሮፕላን ካላጋዚን ኋላ ዹምንጋዹው እኛው ነን ውርድ ኚራሎ " ጄኔራሎቹ መግባባት ተሳና቞ው። ይህ ጉዳይ ዚመጚሚሻ቞ው መጀመርያ ኟነ። ጄኔራሎቹ በመኚላኚያ ሚኒስትር ግቢ፣ አንደኛ ፎቅ ላይ፣ ፊቷን ወደ ክቡ ዚብሔራዊ ባንክ ሕንጻ ባዞሚቜ አንዲት ዚስብሰባ አዳራሜ ታድመው በኢትዮጵያ ዕጣ ፈንታ ላይ እንዲህ ጉንጭ አልፋ ክርክር እያደሚጉ ሳለ ጓድ ሊቀመንበር መንግሥቱን ዚያዘው አውሮፕላን በሰማይ ላይ ሳይጋይ፣ አሥመራም ተገዶ ሳያርፍ ዚኢትዮጵያን ዹአዹር ክልል እዚቀዘፈ ራቀ። ደብሚዘይት አዹር ኃይል ግቢ አውሮፕላኑን ለመምታት በተጠንቀቅ ዚነበሩት ጄቶቜም ሞተር አጠፉ። ጄኔራል ደምሮ ቡልቶ በአሥመራ ግን 'መንጌ ተገድለዋል' በአሥመራ ዹግዙፉ 2ኛው አብዮታዊ ሠራዊት አድራጊ ፈጣሪ፣ ሥመ ጥሩው ጄኔራል ደምሮ ቡልቶ ና቞ው። እንዲያውም ዚስዒሚ መንግሥቱ ሁነኛው ጠንሳሜ ሳይሆኑ አይቀሩም። ምክትላ቞ውን ጠርተው ነገሩ ሁሉ መልክ መልክ መያዙን አሚጋገጡ። ጄኔራል ቁምላቾው በአራት አንቶኖቭ ዚታጚቁ 433 ልዩ ኮማንዶዎቜን አሳፍሚው ወደ አዲስ አበባ ጉዞ እንዲጀምሩ አዘዟ቞ው። • "በጥሩ ጀንነት ላይ አይደለቜም" ዚስምሚት ካህሳይ ቀተሰቊቜ ጄኔራል ቁምላቾው አገሪቱ አለኝ ዚምትላ቞ውን ዹአዹር ወለድ አባላት "ዳይ! ተንቀሳቀስ" አሏ቞ው። በወታደር ቀት አለቃ ሲያዝ "አቀት ጌታዬ!" እንጂ "ለምን ጌታዬ?" አይባልም። ሶቭዚት ሠራሜ አንቶኖቭ ውስጥ እንዳሉ ድንገት ጄ/ል ቁምላቾው እመር ብለው ተነሱ። ዹሃሎ ሃሎ መነጋገሪያውን ሚዳታ቞ው አቀበሏ቞ው። አንድ በራሪ ወሚቀት ኚኪሳ቞ው አውጥተው ማንበብ ጀመሩ። እዚያ አንቶኖቭ ውስጥ ያለው ወታደር በሙሉ በታላቅ ፌሜታ አጚበጚበ። በዚያ አንቶኖቭ ውስጥ ዚነበሩትና ዛሬም በሕይወት ዚሚገኙት ሌ/ኮ/ል ካሳዬ ታደሰ ለቢቢሲ አማርኛ እንደተናገሩት  "መንግስቱ ተገድሏል ሲባል መጀመርያ ደነገጥኩፀ ኚዚያ ሁሉም ሲያጚበጭብ እኔም ማጚብጚብ ጀመርኩ" ሲሉ ዚወቅቱን ድራማ ገልጞዋል፡፡ ሰማይ ላይ አንቶኖቩ ውስጥ ይህ ሲሆን ዚአሥመራ ሬዲዮ በበኩሉ መንግሥቱ መገደሉን አወጀ። ኚአንድ ሰዓት ተኩል በሚራ በኋላ ጄኔራል ቁምላቾው ኮማንዷ቞ውን ይዘው አዲስ አበባ ጩር ኋይሎቜ ልደታ አርሚ አቪዚሜን ገብተዋል። ግማሟቹን ኮማንዶዎቜ ደግሞ እዚያው ቩሌ አዹር መንገድን እንዲቆጣጠሩ አድርገዋል። ዹዚህ ልዩ ኮማንዶ ተግባር ሬዲዮ ጣቢያውን መቆጣጠር፣ መኚላኚያ ሚኒስትር ለሚገኙት መፈንቅለ መንግሥት አድራጊዎቜ ደግሞ ኹለላ መስጠትፀ ድንገት ‹‹ለመንጌ አንገቮን እሰጣለሁ›› ዹሚል ኃይል ካለ አንገቱን እንደ ዶሮ መቀንጠስ ነው። • ወመዘክር፡ ኚንጉሡ ዘመን እስኚዛሬ ዹሚገርመው ዚአሥመራ ሬዲዮ መንግሥቱ ኃይለ ማርያም እስኚወዲያኛው እንደተሰናበቱ ያወጀው ገና ሚፋድ ላይ ነበር። በመሆኑም ጄኔራል ቁምላቾውም እስኚመጚሚሻው ዚሚያውቁት መንግሥቱ መገደሉን ነው። ሌ/ኮ/ል ካሳዬም ይህንኑ ለቢቢሲ አሚጋግጠዋል። ኹጩላይ ዚመጣው ሠራዊት መፈንቅለ መንግሥቱን ለማቅናት ኚአሥመራ በጄ/ል ቁምላቾው እዚተመራ አዲስ አበባ ኚገባው ኃይል ሌላ ኹጩላይም አንድ ሻለቃ ተንቀሳቅሷል። ጄኔራል ውበቱ ፀጋዬ ኚሎሚኞቹ ጋር በስሱም ቢሆን ሳይመሳጠሩ አልቀሩም። አሁንም ድሚስ በሕይወት አሉፀ አሜሪካን አገር። ወደ አዲስ አበባ ዹሚላኹውን ጩር አዘጋጅተው እሳ቞ው ኹሰሜን ኮሪያ ዚመጣ ልኡካን ቡድንን ተቀብለው እያነጋገሩ ነበር። ጩላይ ያለው ልዩ ኮማንዶ ዚቁልምጫ ስሙ ''ስፖርታ'' ይባላል። ሰሜን ኮሪያዎቜ ለኹተማ ውጊያ፣ ለጚበጣ ፍልሚያ በልዩ ጥንቃቄ ያሰለጠኑት ጩር ነው። ጄ/ል ውበቱ ጥርት ያለ መመርያ ባይደርሳ቞ውም 150 ዚሚሆኑትን ምርጥ ምልምሎቜ በወታደራዊ ሄሊኮፕተር ወደ አዲስ አበባ ላኳ቞ው። ፖስታ ቀት መገናኛ ሚኒስትር አካባቢ በሚገኝ ሜዳ ላይ ሆነው ትዕዛዝ እንዲጠባበቁ ተደሚጉ። ኋላ ላይ 4ኛ ክፍለ ጩር... አምባሳደር ጋ፣ ኢትዮጵያ ሆቮል ጎን፣ መኚላኚያ ሚኒስትር ውስጥ 
 ኚኢትዮጵያ ሆቮል ትይዩ በዋናው ዚመኚላኚያ ሕንፃ 1ኛ ፎቅ ዹጠቅላይ ኢታማዊር ሹሙ ዚመሰብሰቢያ አዳራሜ ይገኛል። ይህ አዳራሜ ፊቱን ወደ ወርቃማው ዚብሔራዊ ባንክ ዹሰጠ ነው። በዚህ አዳራሜ 18 መፈንቅለ መንግሥት አድራጊዎቜ ሎራ እዚጎነጎኑ ነው። ቁጥራ቞ው ይጚምራል ይቀንሳል። ሆኖም በአገሪቱ አንድም ዹቀሹ ቱባ ጄኔራል ዚለም። • ያለ እናት ዚመጀመሪያው ዚእናቶቜ ቀን በኢትዮጵያ ዚመጀመርያው አብዮታዊ ጄኔራል፣ ተወዳጁ፥ ደርባባው፣ አንደበታ቞ው ዹሹጋው ጄ/ል መርዕድን ጚምሮ ዚባሕር ኃይል አዛዡ ሪር አድሚራል ተስፋዬ ብርሃኑ፣ ዹአዹር ኃይል አዛዡ ጄኔራል አምሐ፣ ዚምድር ጩር አዛዡ ጄኔራል ኃይሉ፣ ዚፖሊስ ሠራዊት አዛዡ ጄኔራል ወርቁ ይገኙበታል። ስለ ጀግንነታ቞ው ሳር ቅጠሉ ዹመሰኹሹላቾው እነ ጄኔራል ፋንታ በላይ፣ እነ ጄኔራል አበራ አበበ፣ እነ ጄ/ል ደምሮ ቡልቶም አሉበት። ስለነዚህ ጄኔራሎቜ ዹጩር ጀብድ እንኳን ወታደሮቻ቞ው አንዳንድ ዹሰሜን ተራሮቜም አፍ አውጥተው ባይናገሩ...ማን ቀሹ ታዲያ? እርግጥ ነው ጄኔራል ደምሮ ቡልቶ በአካል አምባሳደር-ብሔራዊ አካባቢ አይሁኑ እንጂ በመንፈስ አብሚዋ቞ው ና቞ው። እርሳ቞ው አሥመራ ትልቁን ዚቀት ሥራ ሠርተው ጚርሰዋል። ዚአገሪቱ ሁለት ሊስተኛ ጩር በርሳ቞ው ሥር ነው ያለው። አሁንም ድሚስ አስገራሚው ነገር ታዲያ ዚአሥመራ ጩር መጀመሪያ በታቀደው መሠሚት ዹመንጌ አውሮፕላን መመታቷን ነው ዚሚያውቀው። ይህንኑም በሬዲዮ አስነግሯል። • ዚሥራ ቃለመጠይቅ ማድሚግ ያስፈራዎታል? እነዚህ 18 ዹጩር አበጋዞቜ ግማሜ ሚሊዮን ዹሚጠጋውን ዚአገሪቱን ሠራዊት ያዛሉ። ሁሉም በመፈንቅለ መንግሥቱ ጉዳይ ላይ መግባባት ደርሰዋል። ሆኖም እዚያው መኚላኚያ ሚኒስትር ስብሰባ ላይ ና቞ው። ይህ ይሆን መዘናጋትን ዚፈጠሚባ቞ው? ምን ዓይነት ምድራዊ ኃይል መጥቶ ይህን 'ኩዎታ' ሊያኚሜፍ ይቜላል? ስክነት ዚራቃ቞ው ጄኔራል አበራ ብቻ ና቞ው። እስራኀል ነው ዚተማሩት። ዚዘመቻ አዛዡ ጄኔራል አበራ ወትሮም ቜኩል ናቾው ይባላል። ቀልባ቞ው ዹሆነ ነገር ሳይነግራ቞ው አልቀሚም። በስብሰባው መካኚል ወጣ እያሉ ግቢውን ይቃኛሉ። በዚህ መሀል ዚታንክ ቃቃታ ዹሰሙ መሰላ቞ው። ዚመኚላኚያ አስተዳደር መምሪያ አዛዡን ጄኔራል ዑመርን አስኚትለው ዚመኚላኚያ ግቢ ዚባንዲራ መስቀያው ጋ ቆመው መኚላኚያ ቢሮ ውስጥ ያለውን ሰው በሙሉ ወደ ግቢው እንዲሰለፍ አዘው ንግግር ማድሚግ ጀመሩፀ ዹመንጌን ፍጻሜም አበሰሩ። ተጚበጚበ ቪቫ ኩዎታ ተባለ. . . መኚላኚያ ሚንስትሩ ጄ/ል ኃይለጊዮርጊስ ለጄ/ል ደምሮ ቡልቶ ዕውቅና እዚሰጡ። ኚመኚላኚያ ሚንስትሩ ጎን ቆመው ዚሚታዩት ጄ/ል አበራ ናቾው-ሟቜ እና ገዳይ። ዚመኚላኚያ ሚኒስትሩ መገደል ዚደኅንነት ሚኒስትሩ ተስፋዬ ወ/ሥላሎ ሎራ ሞትቷ቞ዋልፀ ባምቢስ ኹሚገኘው ዚደኅንነት ቢሯ቞ው እዚበሚሩ ወደ ምኒሊክ ቀተ መንግሥት ነዱ። ዹመንጌን ልዩ ሚዳት መንግሥቱ ገመቹን ጠርተው አስ቞ኳይ ስብሰባ ጀመሩ። እነ ፍቅሚሥላሎ ወግደሚስም አሉበት። እንዲያውም ሰብሳቢው እርሳ቞ው ና቞ው። ምንድነው እዚሆነ ያለው? እነ መርእድ ምንድነው እዚዶለቱ ያሉት? ‹‹እሚ በፍጹም›› አሉ ሚኒስትሩ። ሄደው እንዲያጣሩ ሐሳብ ቀሚበ። በሄዱበት ይቀራሉ ያለ አልነበሚም። • "ልዩ ነዳጅ መኖሩን አልደሚስንበትም" ዚማዕድን፣ ዚፔትሮሊዚምና ዚተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስ቎ር ሚኒስትሩ ቁልቁል ወደ አምባሳደር በሚሩ። ወደ ቢሯ቞ው ገብተው ወጡ። ጄ/ል ኃብተጊዮርጊስ ወትሮም ኹጄ/ል አበራ ጋር እስተዚህም ና቞ው። እሚ እንዲያውም ዐይንና ናጫ...። ጄ/ል አበራ ዹሆነ ዹቀፈፋቾው ነገር ያለ ይመስላል። ጄ/ል መርዕድ ኚሚመሩት ስብሰባ በዹመሀሉ እዚወጡ ኮሪደሩን፣ አካባቢውን ይቃኙና ይመለሳሉ። ድንገት ለቅኝት ደሹጃውን ሲወርዱ፣ መኚላኚያ ሚኒስትሩ ደግሞ ደሹጃውን ሲወጡ ተገጣጠሙ። "አበራ! ምንድነው እኔ ዹማላውቀው ስብሰባ?" ሳይሉ አልቀሩም። አንዱ ሁለት ተባብለውም ሊሆን ይቜላል። ብቻ ጄኔራል አበራ በቅልጥፍና ሜጉጣ቞ውን አውጥተው መኚላኚያ ሚኒስትሩ ላይ አኚታትለው ተኮሱ። ጩር ኃይሎቜ ቢወሰዱም አልተሚፉም። ጄኔራል አበራ እንዎት አመለጡ? ለምን አመለጡ ? ይህ ሁሉ ሲሆን ኚአሥመራ ዚመጣው ዚጄኔራል ቁምላቾው ሠራዊት ጩር ኃይሎቜ ግቢ ሆኖ በተጠንቀቅ ትእዛዝ ይጠባበቃል። እንዲያውም ስልክ ወደ ጄ/ል አበራ ደውሎ አልተነሳለትም። ኹጩላይ ዚመጣውና በሰሜን ኮሪያዎቜ ዹሰለጠነው ዚስፓርታ ጩርም ፖስታ ቀት አካባቢ ሥራ ፈትቶ ሜዳ ላይ ተቀምጧል። ። ሁሉም ታዲያ ሪፖርት ዚሚያደርጉትም ትእዛዝ ዚሚቀበሉትም ኚጄኔራል አበራ ብቻ ነው። ዚዘመቻ መምሪያ ኃላፊ እሳ቞ው ና቞ዋ። ጄ/ል አበራ ግን ያልተጠበቀ ነገር ፈጜመው ቜግር ውስጥ ገብተዋል። መኚላኚያ ሚኒስትሩን ኹገደሉ በኋላ ወደ ቢሮ አልተመለሱም። ልዩ ኮማንዶነት ዚሰለጠኑት ጄ/ሉ በአጥር ዘለው አምልጠዋል። • ሶማሊያ በሀገር አቀፍ ፈተና ወቅት ማህበሹዊ ሚዲያዎቜን ልትዘጋ ነው አንዳንዶቜ ኹጎን ዹሚገኘው ቡና ገበያ ግቢ ገብተው ዘበኛ ማርኹው ዚወታደር ልብሳ቞ውን አውልቀው ዹዘበኛ ልብስ ለብሰው ተሰወሩ ሲሉ፣ ሌሎቜ ደግሞ ዹለም ኚመኚላኚያ ዚወጡት በአጥር ሳይሆን በበር ነውፀ ዚአንድ ሠራተኛ ልብስ ቀይሹው ነው ይላሉ። ዹጄ/ል አበራ ኚመኚላኚያ መሰወር ነገሮቜን አመሰቃቀለ። ኹጩላይና ኚአሥመራ ዚመጣው ኃይል ምን ማድሚግ እንዳለበት ግራ ገብቶት እርሳ቞ውን ይፈልጋል። እርሳ቞ው ግን ስልክ አያነሱም። ቢሮም ዚሉም። በዚያ ዘመን ሞባይል ዚሚባል ነገር አይታወቅ ነገር
 • "ዚሚያክሙን ሙዚቃዎቜ እንዳሉ ሁሉ ዚሚያውኩንም አሉ" ዶ/ር መልካሙ ጄኔራሎቹ ራሳ቞ውን ለምን አጠፉ? ግንቊት ስምንት ቀትር ስምንት ሰዓት ግድም ዹጀመሹው መፈንቅለ መንግሥት ራሱን በራሱ እዚተበተበ አንድም ፋይዳ ያለው ነገር ሳያኚናውን መሞበት። ደኅንነቱ ተስፋዬ ወ/ሥላሎ ሻምበል መንግሥቱ ገመቹን ይዘው መኚላኚያን አስኚበቡፀ ለዚያውም በታንክና በብሚት ለበስ። ኚዚያ በፊት ግን ነገሩን በሰላም እንጚርሰው በሚል ሜማግሌ ተልኳልፀ ሌ/ኮ አዲስ ተድላና ኮ/ል ደበላ ዲንሳ ነበሩ አደራዳሪዎቹ። ‹‹መፈንቅለ መንግሥቱ ያበቃለት ጉዳይ ነውፀ ምንም ድርድር ብሎ ነገር ዚለም። ባይሆን አግዙን›› ሳይሏ቞ው አይቀርም፣ እነ ጄ/ል መርዕድ። • ቮምር በሚመዳን ለምን ይዘወተራል? ዞሮ ዞሮ ሰዓቱ ነጎደ። ማስታወቂያ ሚኒስትር አልተያዘ፣ ሬዲዮ ጣቢያ አልተያዘ፣ ቮሌ አልተያዘ ሰዓቱ ነጎደ። ዚሳር ቅጠሉ አዛዊቜ በሙሉ እዚያ መሆናቾው ሳያዘናጋ቞ው አልቀሚም። ዹጄ/ል አበራ ድንገት ሰው ገድሎ መሰወር ግን ነገሮቜን አወሳሰበ። ዹመንጌ ቀኝ እጅ ሞክሌያ቞ው መንግሥቱ ገመቹ ዚልዩ ብርጌድ ኃይላቾውን ኹ4ኪሎ አንቀሳቀሱ። በሂልተን አድርገው አምባሳደር ጋ ሲደርሱ 'መኚላኚያ ሚኒስትሩን ክበብ' አሉ። ውስጥ እነ ጄ/ል ፋንታ በላይ፣ አነ ጄ/ል አመሃ፣ እነ ጄ/ል መርዕድ ምን እያደሚጉ እንዳሉ ዚሚያውቅ ምድራዊ ኃይል ዚለም። ሆኖም በዚያ ሰዓት መኚበባ቞ውን እንደተሚዱ ኚአሥመራ ይመጣል ዚተባለው ኃይል ባለመድሚሱ ተስፋ ቆርጠው ሊሆን ይቜላል። ብቻ ጄ/ር መርዕድና ጄ/ል አመሐ ዛሬም ድሚስ ግልጜ ባልሆነ ሁኔታ እዚያው ራሳ቞ውን አጠፉ። ድኅሚ ታሪክ ግንቊት 9 ማታ ኮ/ል መንግሥቱ ኚምሥራቅ ጀርመን ጉብኝታ቞ውን አቋርጠው ኮሜታ ሳያሰሙ ተመለሱ። ግንቊት 10፣ ጄኔራል ደምሮ ቡልቶ በገዛ ወታደሮቻ቞ው ተገደሉፀ ኚእርሳ቞ው ጋር በድምሩ 18 ኹፍተኛ መኮንኖቜ ተመሳሳይ ክፉ እጣ ገጠማ቞ው። በሟ቟ቹ ሬሳ ላይ እጅግ ዚሚቀፍ፣ ታሪክ ዹሚጾዹፈው ዚሰይጣን ድርጊት ተፈጞመ። ኚሊስት ቀን በኋላ ጄኔራል ፋንታ በላይ ኚተደበቁበት ኮን቎ይነር ወጡ። ለጥቂት ወራት ማዕኹላዊ ለብቻ቞ው ተነጥለው ታስሚው ሳሉ እስኚዛሬም ይፋ ባልሆነ ሁኔታ "ጠባቂያ቞ውን ገድለው ሊያመልጡ ሲሉ ተገደሉ" ተባለ። • እንግሊዛውያን ዚወሲብ ሕይወታ቞ው ''ደካማ ነው'' ተባለ በሊስተኛው ሳምንት መኚላኚያ ሚኒስትሩን ገድለው ያመለጡት ጄ/ል አበራ ጉለሌ አካባቢ ኚተደበቁበት ዘመድ ቀት ተኚበቡ። በመስኮት ዘለው ጣሪያ ላይ ወጥተው ሊያመልጡ ሲሉ በአንድ ወጣት ፖሊስ ግንባራ቞ውን ተመትተው ወደቁ። አንዳንድ ዹሰው መሚጃዎቜ ጄ/ል አበራን አሳልፎ ዚሰጣ቞ው ዘመድ ዛሬም ድሚስ በጞጞት ይኖራል ይላሉ። ኹሆኑ ወራት በኋላ ዚአሥመራውን አዹር ወለድ ጩር አዲስ አበባ ይዘው ዚመጡት ጄኔራል ቁምላቾው በአንዳቜ ተአምር አምልጠው አሜሪካ ገቡ ተባለ። ሲአይኀ እንዳሟለካ቞ው ተጠሚጠሚ። • ዚስኳር ፋብሪካዎቜን ለግል ባለሃብቶቜ ዚመስጠት ፋይዳና ፈተናዎቹ ኚዓመት በኋላ ግንቊት 13፣ 1981 መፈንቅለ መንግሥቱ ላይ ተሳትፈዋል ዚተባሉ 12 ጄኔራሎቜ ድንገት ለውሳኔ ተጠሩ። ዚወታደራዊ ፍርድ ቀት ዹመሀል ዳኛው ጄ/ል አሥራት ብሩ በብጣሜ ወሚቀት ዚተጻፈቜና ኚኮ/ል መንግሥቱ እንደተላኚቜ ዚምትገመት አንዲት ወሚቀት እንባ እዚተናነቃ቞ው አነበቧት ተባለ። በ12ቱ ላይ ሞት ተፈሚደ። ፍርደኞቹም እንዲህ እያሉ ይጮኹ ነበርፀ ‹‹ቀተሰባቜንን ሳንሰናበት አትግደሉን ››፣ ‹‹ፈላጭ ቆራጭ አገዛዝ ዕድሜ ዚለውም››፣ ‹‹ልጆቻቜንን አደራ››። ያንኑ ምሜት ተሚሞኑ። ኚስዒሚ መንግሥት ሙኚራው ኹ2 ዓመት በኋላ ግንቊት 13 ቀን ኮ/ል መንግሥቱ ኹአገር ሞሹ። ዚኮ/ሉን ሜሜት ተኚትሎ ለአንድ ሳምንት ርዕሰ ብሔር ዚሆኑት ጄ/ል ተስፋዬ ገብሚኪዳን ሞታ቞ውን እዚተጠባበቁ ለነበሩ ጥቂት ዹመፈንቅለ መንግሥቱ ተኚሳሟቜ ምሕሚትን አወጁ።
news-55219617
https://www.bbc.com/amharic/news-55219617
ቮክኖሎጂ ፡ ኹጉግል ጋር ውዝግብ ውስጥ ዚገባቜው ኢትዮጵያዊት ትምኒት ገብሩ ማናት?
ዚአዲስ አበባ ልጅ ናት። ትምኒት ገብሩ (ዶ/ር)።
ትምኒት ገብሩ ዓለምን በፍጥነት እዚለወጠ ያለው ሰው ሠራሜ ልህቀት (አር቎ፊሻል ኢንተለጀንስ ወይም ኀአይ) ውስጥ አሉ ኚሚባሉ ጥቁር ሎት ባለሙያዎቜ መካኚል አንዷ ነቜ። ትምኒትፀ ጉግል ውስጥ ዚኀአይ ዚሥነ ምግባር ዘርፍ ባልደሚባ ነበሚቜ። ቮክኖሎጂው አካታቜ እና ፍትሐዊ እንዲሆን ኚሚጥሩ መካኚል በግንባር ቀደምነት ትጠቀሳለቜ። ባለፈው ሳምንት ኹጉግል አመራሮቜ ጋር በተፈጠሹ ውዝግብ ኚሥራዋ መባሚሯ በርካታ ዹዘርፉ ሙያተኞቜን አስቆጥቷል። ትምኒት አዲስ አበባ ሳለቜ. . . ዚናዝሬት ስኩል ተማሪ ነበሚቜ። አስሚኛ ክፍል ስትደርስ ወደ አዚርላንድ አቀናቜ። ዹሁለተኛ ደሹጃ እንዲሁም ዚዩኒቚርስቲ ትምህርቷን ያጠናቀቀቜው አሜሪካ ነው። ለቀተሰቧ ዚመጚሚሻ ልጅ ናት። ኚሁለት ዓመት በፊት ኚቢቢሲ ጋር ባደሚገቜው ቆይታፀ ልጅነቷን ስታስታውስ "ሕጻን ሳለሁ ትምህርት እወድ ነበር። ስታመም ራሱ ኚትምህርት ቀት መቅሚት አልወድም ነበር" በማለት ነው። በተለይም ለሒሳብ እና ፊዚክስ ልዩ ፍቅር ነበራት። አባቷ ኀሌክትሪካል መሀንዲስ መሆናቾው ወደ ሳይንስ እንድታዘነብል እንዳደሚጋት ትናገራለቜ። ሁለት ታላላቅ እህቶቿም በዚሁ ዚሙያ ዘርፍ ነው ዚተሰማሩት። ትምኒት በአሜሪካ. . . ሁለተኛ ደሹጃ ትምህርቷን አጠናቃ ስታንፈርድ ዩኒቚርስቲ ገባቜ። ዚመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዲግሪዋን ዚሠራቜው በኀሌክትሪካል ምህንድስና ነው። በዓለማቜን ስመጥር ኚሆኑት መካኚል በሚጠቀሱት አፕል፣ ኚዚያም ጉግል ውስጥ ሠርታለቜ። ትምኒት በግዙፉ ዹቮክኖሎጂ ኩባንያ ማይክሮሶፍት ውስጥ ፍትሐዊነት፣ ተጠያቂነት፣ ግልጜነትና ሥነ ምግባር ላይ ያተኮሚ ቡድን ውስጥ ሠርታለቜ። በሰው ሠራሜ ልህቀት ዘርፍ ዚጥቁር ሎቶቜን ተሳትፎ ለማሳደግ ያለመ 'ብላክ ኢን ኀአይ' ዚተባለ ተቋምን ኚመሠሚቱ መካኚል አንዷ ናት። ዚፈጠራ ሥራዎቜን አካታቜነት በሚፈትሹ ጥናቶቿ እንዲሁም ቮክኖሎጂና ዚሰብአዊ መብት ጥያቄን በማስተሳሰርም ትታወቃለቜ። ብላክ ኢን ኀአይፀ ጥቁር ሎቶቜ ወደ ሰው ሠራሜ ልህቀት ዘርፍ እንዲገቡ፣ በሙያው ዚተሰማሩ እርስ በእርስ እንዲደጋገፉና ተደማጭነት እንዲያገኙ ለማስቻል ነው ዚተቋቋመው። ትምኒት እንደምትለውፀ ስብስቡ ጥቁር ሎቶቜን ዚሚያበሚታታ፣ ወደላቀ ደሹጃ እንዲደርሱ ዚሚያስቜልም ነው። ኚቢቢሲ ጋር ባደሚገቜው ቆይታፀ "ኹዚህ ሙያ ልወጣ ነበርፀ ወደ እናንተ ተቋም ኚመጣሁ በኋላ ግን ጥናት መስራት ጀምሬያለሁ ብለው ኢሜል ያደርጉልናል። ሥራ ያገኙፀ ማስተርስና ፒኀቜዲ ማጥናት ዚጀመሩም አሉ። በእኛ ወርክሟፕ ተገናኝተው በጥምሚት መስራት ዚጀመሩም አሉ" ስትል ነበር ብላክ ኢን ኀአይ ያለውን ሚና ዚገለጞቜው። ለብላክ ኢን ኀአይ መመሥሚት ኹፍተኛ አስተዋጜኊ ካበሚኚቱ መካኚል ኢትዮጵያዊቷ ሚድኀት አበበ ትገኝበታለቜ። ዚኮምፒውተር ሳይንቲስቷ ሚድኀትፀ በአልጎሪዝም እና ኀአይ ዙርያ ትሠራለቜ። ኚኮርኔል ዩኒቚርስቲ በኮምፒውተር ሳይንስ ፒኀቜዲ [ዶክትሬት] በማግኘት ዚመጀመሪያዋ ጥቁር ሎት ናት። በዘርፉ ያሉ ጥቁሮቜ፣ በተለይም ደግሞ ጥቁር ሎቶቜ ውስን እንደሆኑ ዚምታስሚዳው ትምኒትፀ አብዛኞቹ ጥናቶቿ ዚፆታና ዹዘር አካታቜነት ላይ ያተኮሩ ና቞ው። ትምኒት ገብሩ ዚትምኒት ጥናቶቜ ኚትምኒት ታዋቂ ጥናቶቜ መካኚል ፌሻል ሪኮግኒሜን ሲስተም ወይም ዚሰዎቜን ፊት ገጜታ በማዚት ማንነታ቞ውን ዚሚያሳውቅ መተግበሪያን በተመለኹተ ዚሠራቜው ይጠቀሳል። መተግበሪያው ዚጥቁር ሰዎቜን በተለይም ደግሞ ዚጥቁር ሎቶቜ ገጜታ አይቶ ማንነታ቞ውን ለመለዚት እንዲቜል ተደርጎ አለመሠራቱን ጥናቱ ይጠቁማል። ትምኒት እንደምትናገሚውፀ ጥናቱን ዚጀመሚቜው ኀምአይቲ ኚምትሰራ ጓደኛዋ ጋር ነው። "ጓደኛዬ ጥቁር ሎት ነቜ። ለአንድ ፕሮጀክት 'ፌስ ሪኮግኒሜን' ስትጠቀም ፊቷን 'ዲ቎ክት' ማድሚግ [ማንበብ] አልቻለም። እንደሌለቜ ነው ዚሚቆጥራት። ነጭ 'ማስክ' [ጭንብል] ፊቷ ላይ ስታደርግ ግን ያነባል" በማለት ዚጥናቱን መነሻ አጋጣሚን ታስታውሳለቜ። 'ፌስ ሪኮግኒሜን' ነጮቜና ጥቁሮቜ ላይ እኩል እንደማይሠራና በተለይ ደግሞ ጠቆር ያሉ ሎቶቜ በአግባቡ ማንበብ ወይም ማወቅ እንደሚሳነው ጥናታ቞ው ያመለክታል። እንዲህ አይነት ዘሹኛ እና ፆተኛ መድልዎ በብዙ ዹቮክኖሎጂ ውጀቶቜ ላይ እንደሚስተዋል ዹዘርፉ ባለሙያዎቜ ያስሚዳሉ። ትምኒት ኚምታደንቃ቞ው መጜሐፎቜ አንዱ በሆነው 'ዌፐንስ ኩፍ ማት ዲስታራክሜን' ላይ ስለመድልዎ በዝርዝር ተጜፏል። ጾሐፊዋ ካቲ ኩኒል ሰው ሠራሜ ልህቀት አካታቜ አይደለም ስትል ትተቻለቜ። ዘር፣ ፆታ፣ ቀለምና መደብን መሠሚት ያደሚገ መድልዎን ማስወገድ ኚሚቻልባ቞ው መንገዶቜ አንዱ ዘርፉን ዹበለጠ አካታቜ ማድሚግ እንደሆነ ካቲ ትጠቁማለቜ። ሰዎቜ እነሱን ዚሚመስል ሰው ዚሚያካትት ወይም እነሱን ለሚመስል ሰው ጥቅም ዚሚሰጥ ቮክኖሎጂ መፍጠር ዚሚቜሉት በዘርፉ ሲሰማሩ መሆኑን ትምኒት፣ ካቲና ሌሎቜም ባለሙያዎቜ ይስማሙበታል። 'ዳታ አክቲቪዝም' ትምኒትፀ ኹበይነ መሚብ ጋር በተያያዙ ጉዳዮቜ ዙርያ ንቅናቄ ኚሚያደርጉ ዚመብት ተሟጋ቟ቜ (ዳታ አክቲቪስትስ) አንዷ ነቜ። እነዚህ ዚመብት ተሟጋ቟ቜ ዹቮክኖሎጂ ውጀቶቜ ምን ያህል አካታቜ ናቾው? ሲሉ ይጠይቃሉ። ክፍተት ሲያገኙም ኹግዙፍ ዹቮክኖሎጂ ተቋማት ጋር ሳይቀር ይፋለማሉ። ለትምኒት ቮክኖሎጂ ኚመብት ሙግት ጋር ዚተያያዘ ነው። "ለአብዛኛው ሰው ዚማይሠራ ቮክኖሎጂ ኚተሠራ ለሰው ዹማይሆን ነገር እዚተሠራ ነው ማለት ነው" ዚምትለው ባለሙያዋፀ አፍሪካውያን ሎቶቜ ለራሳ቞ው ዹሚሆን ነገር እንዲሠራ ቮክኖሎጂ ውስጥ መግባት እንዳለባ቞ው ታሳስባለቜ። እንደ ምሳሌ ዚምትጠቅሰው ዹዘሹ መል ቅንጣት ላይ ዚተሠሩ እንዲሁም ለተለያዩ ህመሞቜ ዹሚቀመሙ መድኃኒቶቜን ነው። አብዛኛውን ጊዜ ኚአፍሪካውያን ወይም ኚጥቁሮቜ ናሙና እንደማይወሰድ፣ ቢወሰድም ዹናሙናው መጠን ውስን እንደሚሆን በማስሚጃነት ትጠቅሳለቜ። ለዚህም ነው ትምኒት ቮክኖሎጂ ኚሰብአዊ መብት ትገል ጋር ጎን ለጎን እንደሚሄድ ዚምትናገሚው። ትምኒትፀ ቮክኖሎጂ አካታቜና ፍትሐዊ እስኚሆነና ለበጎ አላማ እስኚዋለ ድሚስ መጪው ዓለም ብሩህ ዹመሆን እድሉ ሰፊ እንደሆነ ኚሚያምኑ ባለሙያዎቜ አንዷ ናት። በእሷ ዕይታፀ አፍሪካ ውስጥ ዚድሮን ጥናት ዚሚሠሩ ጀማሪዎቜ በመኖራ቞ው መንገድ ሳያስፈልግ በድሮን መድኃኒት ማዳሚስ ይቻል ይሆናል። ትልልቅ ሆስፒታል መሥራት ሊቀር፣ ምናልባትም በትንንሜ መሣሪያ ሕክምና መስጠት ይቻል ይሆናል። ራሳ቞ውን ዚሚያሜኚሚክሩ መኪኖቜ ሲበራኚቱ አይነ ስውራን በራሳ቞ው ይንቀሳቀሱም ይሆናል። ትምኒትፀ "ጥያቄው ግን እንዎት አድርገን ነው ቮክኖሎጂን ዹምንጠቀመው ዹሚል ነው? ብዙ ጊርነት ይኖራል? ኢ-ፍትሐዊነት ይኖራል? ምን አይነት ፖለቲካዊ ሁኔታ ይኖሹናል? በጣም ጥቂት ሰዎቜ ብዙ ገንዘብ ኖሯ቞ው ብዙዎቜ ገንዘብ ኹሌላቾው 'አር቎ፊሻል ኢንተለጀንስ' ነገሩን ያባብሰዋል" ትላለቜ። ዚትምኒት ዚኢትዮጵያ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ ውስጥ ለወጣቶቜን ዚኮዲንግ ሥልጠና ዚተሰጠበት 'አዲስ ኮደር' ዹተሰኘ ፕሮጀክት ነበራት። ኹዚህ በፊትም በባሕር ዳር ኹተማ ውስጥ በተካሄደ ዚአይሲቲ ኮንፈሚንስም ተሳትፋለቜ። ኚኢትዮጵያ ዚወጡ ዹሰው ሠራሜ ልህቀት ባለሙያዎቜን በብላክ ኢን ኀአይ እንዳካተተቜም ትናገራለቜ። ኢትዮጵያ ውስጥ ሰው ሠራሜ ልህቀት እዚታወቀ መምጣቱን ዚምታምነው ትምኒት "ዘርፉ መታወቅ እዚጀመሚ ነው። ግን ዹተዋቀሹ አካሄድ መኖር አለበት። ሁሉም ሰው ዚሚሳተፍበት እቅድም መኖር አለበት። ሰዎቜ ወደ ቮክኖሎጂው እንዲገቡ እድል መስጠትም አለብን" ትላለቜ። በተጚማሪምፀ ኢትዮጵያ ውስጥ ዹግል ዹቮክኖሎጂ ድርጅቶቜ እንዲገቡ መንገዶቜ መመቻ቞ት እንዳለባ቞ው ትጠቁማለቜ። "ሰዎቜ ዚራሳ቞ውን ዹቮክኖሎጂ ድርጅት እንዲጀምሩ ወይም ትልልቅ ዓለም አቀፍ ድርጅቶቜ እንዲመጡ መደሹግ አለበት። በኢትዮጵያውያን ለኢትዮጵያ ዹሚሆኑ ተቋማት ቢበራክቱ ጥሩ ነው። መንግሥት ገንዘብ ዹሚሰጠው ዚጥናት ተቋም ያስፈልጋል። ዚዩኒቚርስቲ አስተማሪዎቜ በደንብ እዚተኚፈላ቞ው በትኩሚት ጥናት እንዲሰሩ ድጋፍ ያስፈልጋ቞ዋል" ስትልም አስተያዚቷን ሰጥታለቜ። ጉግል ውስጥ ዹተፈጠሹው ምንድን ነው? በጉግል ዹሰው ሠራሜ ልህቀት ዚሥነ ምግባር ቡድን አጋር መሪ ዚነበሚቜው ትምኒትፀ ኹጉግል እንደተባሚሚቜ ያስታወቀቜው በትዊተር ገጿ ነበር። ትምኒት እንዳለቜውፀ በሰው ሠራሜ ልህቀት ዘርፍ ላለው መድልዎ ትኩሚት እንዲሰጥና በዘርፉ እምብዛም ውክልና ያላገኙ ሰዎቜ እንዲቀጠሩ ዚሚያሳስብ ኢሜል ኚላኚቜ በኋላ ነው እንደተባሚሚቜ ዚተነገራት። ዜናውን እንደ ዋሜንግተን ፖስት፣ ብሉምበርግ እና ኒው ዮርክ ታይምስ ያሉት ግዙፍ ዚአሜሪካ ዚሚዲያ ተቋማት ይዘውት ወጥተዋል። በሰው ሠራሜ ልህቀትና ተያያዥ ዹቮክኖሎጂ ዘርፎቜ ዚሚሠሩ እውቅ ባለሙያዎቜ ዚትምኒትን መባሚር በመቃወም ትዊተር ላይ ድምጻ቞ውን አሰምተዋል። #ISupportTimnit እና #BelieveBlackWomen በሚሉ ሁለት ሀሜታጎቜ ዹጉግል ሠራተኞቜን ጚምሮ በርካቶቜ ኚትምኒት ጋር አጋርነታ቞ውን አሳይተዋል። በሰው ሠራሜ ልህቀት ውስጥ ካሉ ጥቂት ጥቁር ሎቶቜ አንዷ ዚሆነቜው ትምኒት መባሚሯ በጉግል አመራሮቜና መድልዎን ዹሚቃወሙ ሠራተኞቜ መካኚል ዹተፈጠሹው ውጥሚት አንድ ማሳያ ነው ተብሏል። ኚቀናት በፊት ኀምአይቲ ባወጣው ዘገባ መሠሚት ለትምኒት መባሚር ምክንያት ዹሆነው ጥናት "On the Dangers of Stochastic Parrots: Can Language Models Be Too Big?" ይሰኛል። አራት ዹጉግል ሠራተኞቜን ጚምሮ በስድስት ባለሙያዎቜ ዚተጻፈ ነው። ጥናቱን ዹተመለኹተ ውይይት ላይ እንድትሳተፍ ኚተጋበዘቜ በኋላ ጜሑፍ ውድቅ እንድታደርገው ትዕዛዝ እንደተሰጣት ትምኒት ተናግራለቜ። ዹጉግልን ውሳኔ ያልተቀበለቜው ትምኒትፀ ኚጥናቱ ላይ ስሟን ለማውጣት ለድርጅቱ ቅድመ ሁኔታዎቜን ማስቀመጧን እና ጉግል ግን በምላሹ በገዛ ፍቃዷ ሥራዋን መልቀቋን እንደሚቀበል በመግለጜ እንዳባሚራት ተናግራለቜ። ሥራዋን በገዛ ፈቃዷ አለመልቀቋንና ዹጉግል ዹሰው ሠራሜ ልህቀት ምርምሮቜ ዘርፍ ኹፍተኛ ኃላፊ ጄፍ ዲን እንዲሁም ሌሎቜም ዹተቋሙ አመራሮቜ እንዳባሚሯት አስሚድታለቜ። ኚቀድሞውም በተቀጣሪዎቹና በሌሎቜም ዹሰው ሠራሜ ልህቀት ባለሙያዎቜ ትቜት ዚሚሰነዘርበት ጉግልፀ ትምኒትን ማባሚሩ ወቀሳውን አብዝቶበታል። ዹጉግል ሠራተኞቜፀ ለፍትሐዊ ቮክኖሎጂና አካታቜነት ዚቆመቜው ትምኒት መባሚሯ ግዙፍ ዹቮክኖሎጂ ተቋሞቜ ውስጥ ያለውን መድልዎና ጭቆና አደባባይ ያወጣ ነው ብለዋል። ትምኒት ገብሩ ትምኒት ኚሥራ ውጪ. . . ትምኒት ኚቢቢሲ ጋር ባደሚገቜው ቆይታ እንደተናገሚቜውፀ ፒያኖ መጫወት ታዘወትራለቜ። ትምህርት ቀት ሳለቜም ፒያኖ ተምራለቜ። "ዹምወደው ምግብ ሜሮ በጥቅል ጎመን ነው። ጣፋጭ ነገር በተለይም ቞ኮሌት እወዳለሁ። ቡና በወተት እወዳለሁ። ሁሌ ጠዋት ስነሳ ቡና በወተት እጠጣለሁ" ትላለቜ። 'ብሮድ ሲቲ' ዚተባለውን ተኚታታይ ፊልምና 'ደይሊ ሟው ዊዝ ትሬቚር ኖሀ' እንደምትኚታተልም ለቢቢሲ ተናግራ ነበር። ትምኒት ኚፌስቡክ እና ትዊተር ውጪፀ 'ስታክ ኩቹር ፍሎ'፣ 'ሬድዮ ላቭ ፖድካስት' እና 'አፍሪካ ኢዝ ኀ ካንትሪ' ዚተባሉ ድሚ ገጟቜን ትኚታተላለቜ። ዚምታደንቃት ሳይንቲስት ዚሁለት ጊዜ ኖቀል ተሾላሚዋ ሜሪ ኪዩሪ (ማዳም ኪዩሪ) ናት። 'just do it!' እጅግ ዚምታምንበት አባባል ነው። "ሰዎቜ በተደጋጋሚ እንዲህ ባደርግ ኚማለት ማድሚግ አለባ቞ው። ሰዎቜ አቅማቾውን አያውቁም። ዚይቻላል መንፈስ ካላ቞ው ግን ያደርጉታል" ትላለቜ ትምኒት።
news-56726061
https://www.bbc.com/amharic/news-56726061
ዚኮቪድ-19 ጫና በሚመዳን ወቅት እንዳይበሚታ ዚሙስሊም ወጣቶቜ ጥሚት
ሳላሃዲን ሰኢድ ይባላል። ዚምሥራቋ ፈርጥ ድሬዳዋ ነዋሪ ሲሆን በንግድ ሥራ ይተዳደራል። ሳላሃዲን ባለፈው ዓመት ዚድሬዳዋ ዚወጣቶቜ ጀማ (ማኅበር) ሰብሳቢ ነበር።
በ2012 ዚኮሮናቫይሚስ ወደ ኢትዮጵያ መግባቱ በተነገሹ በጥቂት ወራት ውስጥ ሚመዳን መግባቱን ተኚትሎ ዚድሬደዋ ሙስሊም ወጣቶቜ ማኅበር ልዩ ልዩ ሥራዎቜን ሲሰራ ነበር። በወቅቱ ታውጆ በነበሹው ዚአስ቞ኳይ ግዜ አዋጅ ምክንያት ዚሐይማኖት ተቋማት በአብዛኛው ተዘግተው ኚርመዋል። ሳላሃዲን "መስጊድ በመዘጋቱ ልቡ ያላዘነ ማን ነበር?" ሲል አንድ ዓመት ወደ ኋላ ተጉዞ ያስታውሳል። "መስጊድ መሄድ ለአንድ ሙስሊም ዚዘወትር ተግባር ቢሆንም፣ በሚመዳን መስጊድ ተዘግቶ ስናይ ግን ድጋሚ ዚሚኚፍትም አይመስልም ነበር" ሲል እርሱን ጚምሮ ሕዝበ ሙስሊሙ ዘንድ ተፈጥሮ ዹነበሹውን ሐዘን ያስታውሳል። በድሬዳዋ ብቻ ሳይሆን ኮቪድ-19 ዓለምን ዚሚያሰጋ ወሚሚሜኝ ተብሎ ኚታወጀ ገና በሊስተኛ ወሩ ነበር በእስልምና እምነት ተኚታዮቜ ዘንድ ትልቅ ስፍራ ዹሚሰጠው ዚሚመዳን ፆም ዚገባው። በሚያዚያ 2012 ዓ.ም ዹዓለም ዚጀና ድርጅት በአንድ ወር ውስጥ በአምስት አህጉራት ቫይሚሱ መግባቱ ሪፖርት ተደርጎልኛል በማለት ነበር ወሚርሜኙን ዓለም አቀፍ ሲል ያወጀው። ታዲያ በወቅቱ ኚሚታወቀው ባህሪይው ዚማይታወቀው ዹሚበልጠው ኮሮናቫይሚስ በመላው ዓለም ያሉ 1.8 ቢሊዮን ሙስሊሞቜ ታላቁ ዚሚመዳን ጟምን በታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ እንዲያሳልፉ ተገድደው ነበር። አገራት ይህ ገና ማንነቱ በቅጡ ያልተለዚ በሜታ ዚዜጎቻ቞ውን ህይወት እንዳይቀጥፍ ዚሐይማኖት ቊታዎቜን ጚምሮ ዚመሰባሰቢያ መንገዶቜን አግደውም ነበር። በእስላማዊ ዹቀን መቁጠሪያ ሂጅራ መሰሚት፣ ዘጠነኛ ወር ላይ ዹሚውለው ሚመዳን በኢትዮጵያ እና በሌላው ዹዓለም ክፍል ብቻ ሳይሆን በእስልምና ቅዱስ በሆነው ዚመካ ኹተማም እንደቀደመው ተሰብስቊ መስገድ ቀርቶ ወደ ሳዑዲ አሚቢያ መግባትም ክልክል ነበር። ዓለም ኚኮሮናቫይሚስ ጋር ዚተሻለ ተላምዳ እና ኚትባቱም በመላው ዓለም መዳሚስ በጀመሚበት ዓመት ዚሚመዳን ወር ተጀምሯል። ድሬዳዋ ሞምሰዲን ባለፈው ዓመት ሚመዳን በድሬዳዋ ኹተማ ብቻ ዘጠኝ ሚሊዮን ብር ያክል ተዋጥቶ በኹተማዋ ባሉ ቀበሌዎቜ በሙሉ ያሉ አቅመ ደካሞቜን ማገዛቾው እንደሚያስደስተው ይናገራል። "ድሬዳዋ ኚአንድ ቀት ሁለት ሊስት ልጅ በውጭ አገር ዹሌለው ዚለም። በውጭ ያሉትም በኹተማ ካሉት ብዙ ገንዘብ ሰብስበን ድጋፍ አድርገን ነበር" ሲል ያስታውሳል። አክሎም በኹተማዋ ዚኮሮናቫይሚስ ያመጣው ድንጋጀ ኹፍተኛ እንደነበር እና ይህም በተለይ በንግድ ላይ ለተሰማሩ ሰዎቜ ኹፍተኛ ጫና አስኚትሎ እንደነበርም ይገልጻል። ነገር ግን ያኔ መስጊዶቹ መዘጋቱ እና ዹነበሹው ጥንቃቄ ዋጋ ቢስ አልነበሹም ዹሚለው ሞምሰዲንፀ በዚህ ዓመት ዚኮሮናቫይሚስ ኹፍተኛ ስርጭት ላይ እንደሚገኝ ኚግምት ውስጥ በማስገባት ጥንቃቄው መቀነሱ ያሳስበዋል። በመስጊዶቜ ውስጥ "ሰው ለራሱ ሲል እንዲጠነቀቅ ትምህርት እዚተሰጠ ቢሆንም ቞ልተኝነቱ ያሳስበኛል" ሲል ይናገራል። "በአሁኑ ዓመት እርዳታ ዚማሰባሰብ ተግባራት አምብዛም አይታዩም" ዹሚለው ሳላሃዲንፀ ምን አልባት ጟሙ ሲገባ እርዳታዎቜ (ዘካ) ይደሹጋል ብሎ እንደሚጠብቅ ይናገራል። ነገር ግን አሁንም ወጣቶቹ እዚተወያዩ እንደሚገኙ አና በተቻለ መጠን በዚህኛውም ሚመዳን ድጋፎቜን ለማጠናኹር እና ወደ መስጊድ ዚሚመጡ ሰዎቜን በማስተባባር ስርጭቱ እንዳይጚምር ለማድሚግ ሥራ መጀመራ቞ውን ይናገራል። ኚአንድ ዓመት በፊት ዚኮሮናቫይሚስ ኹፍተኛ ስርጭት አይሎባት ዚነበሚቜው ድሬዳዋ አሁን ላይ በመላው አገሪቱ ዚተስፋፋው ኮሮናቫይሚስ በሁሉም ኚተሞቜ ተስፋፍቶ ስጋቱን ኹኹተማዋ ጋር ሌሎቜም እንዲጋሩት አድርጓል። አዲስ አበባ ልክ እንደ ሰላሃዲን ሁሉ ባለፈው ዓመት በአዲስ አበባ እርዳታ ሲያሰባስቡ ኚነበሩ ወጣቶቜ መካኚል ነው አዱኛው ሙጬ። ባለፈው ዓመት 10 ሺህ አባወራዎቜን ለአንድ ወር ዹሚሆን ቀለብ በማሰባሰብ ካኚፋፈሉት ወጣቶቜ አንዱ ዹሆነው አዱኛው በተያዘው ዓመት ይቀዝቅዝ እንጂ ድጋፉ አልቀሹም ሲል ያስሚዳል። በተያዘው ዓመትም ድጋፋ቞ውን አጠናክሹው እንደቀጠሉ ዹሚናገሹው አዱኛው፣ ኚአንድ ሳምንት በፊት አፋር ክልል ሄደው ኚነጃሺ በጎ አድራጎት ማኅበር ጋር ድጋፍ አድርገው መመለሳ቞ውን ይናገራል። ባለፈው ዓመት በአፋር ክልል በጎርፍ ዚተጎዱ ሰዎቜን በዕለት ደራሜ ድጋፍ ሲያግዙ መቆዚታ቞ውን ያስታውሳል። ዚሚመዳን ጟምን አስመልክቶም ለ150 አርብቶ አደሮቜ መልሰው እንደቋቋሙ አምስት አምስት ፍዹል ለግሰው መመለሳ቞ውን ያስሚዳል። "ሁሌ ዱቄት ይዞ መሄድ ሳይሆን መልሶ ለማቋቋም ነው ፍዚሎቹን ዚሰጠና቞ው። በአንድ ኣመት አምስት ፍዹል 15 ይሆናል ተብሎ ይታመናልፀ ይህም በዘላቂነት መልሰው እንዲቋቋሙ ያግዛል" ሲል ለቢቢሲ ገልጿል። ነገር ግን እንዳለፈው ዓመት ድጋፍ ዚማሰባሰብ ሥራውን ማስተባባር በተለይም ዚማኅበራዊ ሚዲያውን ዚያዙት አጀንዳዎቜ ትኩሚት አለማግኘቱን ያስሚዳል። ወጣቶቹም ዚማስተባባር ሥራውን ማካሄድ ዚሚቜሉበት ሌሎቜ አማራጮቜ እንዳልነበሯ቞ውም ይገልጻል። አዱኛው ያለፈውን ዓመት ሲያስታውስም ምንም እንኳን ድጋፍን በማሰባሰብ እና መሰል ሥራዎቜ በመስጊድ ውስጥ ቢያሳልፍም ህዝበ ሙስሊሙ ውስጥ ተፈጥሮ ዹነበሹውን ሐዘን ያስታውሳል። "ብዙዎቜ መስጊድ ተዘግቶ ሲያዩ አልቅሰዋል፣ ሚመዳን ታላቅ ዹሰደቃ ወቅት በመሆኑ ብዙ ዚተ቞ገሩ ሰዎቜ መስጊድ ደጅ ተቀምጠው ዚሚሚዱበት ወር ነው። እነዚህ ሰዎቜ ዚዓመት ወጪ ጭምር ዚሚያገኙበት ወር ነው። በአጠቃላይ ለኔም በግሌ ኚባዱ ዚሚመዳን ወር ነበር" ሲል ለቢቢሲ ተናግሯል። በ2013 ግን መስጊዶቜ ተኹፍተው ሚመዳን ጟም ተጀምሯል። ለአዱኛው ይህ መልካም ዜና ቢሆንም "ያለው መዘናጋት እጅግ ያሳስበኛል" ሲል ይነጋራል። በአዲስ አበባ ሰዎቜ ማስክ ዚሚያደርጉት ፖሊስ እንዳይቀጣ቞ው ብቻ ይመስላል ዹሚለው ወጣቱፀ ኚአዲስ አበባ ውጪ ሲንቀሳቀስ ደግሞ ማስክ ዚሚለብስ ሰው እንደውም ኮሮናቫይሚስ ያለበት ተደርጎ እንደሚታሰብ ይናገራል። በመስጊድ ውስጥ በሚያደርገው እንቅስቃሎ ምክንያት በሙስሊም መቃብር አካባቢ ያለውን ነገር እንደሚመለኚት ዚሚያስሚዳው አዱኛው ሁኔታውን አሳሳቢ ሲል ይገልጻል። "በቀን ሊስት አራት ሰው ኮሮና ነው እዚተባለ በጥንቃቄ ሲቀበር አያለሁ" በማለት ይህ በሚመዳን ጟም ወቅት ዹሚደሹጉ ዚማኅበራዊ እንቅስቃሎዎቜ በአግባቡ ካልተደሚጉ "እልቂት እንዳያመጡ እሰጋለሁ ይላል። ታዲያ ኚሐይማኖታዊ ስብስቊቜ ውጪም "መርካቶም፣ አውቶብስ ውስጥም ሆነ ሌላ ቊታም ጥንቃቄዎቜ ያለመኖራ቞ው በአጠቃላይ ገና ብዙ ማሻሻል ያስፈልጋል" ሲልም ዹግል ምልኚታውን ያስቀምጣል። መውጫ በተለያዩ ዹዓለም ክፍሎቜ አሁንም መስጊዶቜን ጚምሮ ዚእምነት ቀቶቜ ተዘግተዋል አልያም በአነስተኛ ቁጥር ማኅበራዊ ርቀቶቜ ተጠብቀው ሐይማኖታዊ ሥርዓቶቜን በመኹወን ላይ ይገኛሉ። በኢትዮጵያ ዚሐይማኖት ተቋማት ኚኮሮናቫይሚስ መኚሰት በፊት ወደ ነበሹው አገልገሎት ኚገቡ ሰነባብተዋል። ብዙዎቜ ማኅበራዊ ርቀትን መጠበቅ ዚመሳሰሉ ተግባራት ተሚስተዋል ሲሉም ይደመጣል። ታዲያ ዚተያዘው ዚሚመዳን ጟምን ተኚትሎ ዚሚካሄዱ ዚጋራ ሐይምኖታዊ ክንውኖቜ በጥንቃቄ ካልተኚወኑ ብዙዎቜን ሊጎዳ እንደሚቜል እነዚሁ ወጣቶቜ ይናገራሉ። "እኛ ወጣቶቜ ዚራሳቜንን ሚና ተስፋ ሳንቆርጥ እንጫወታለን" ዹሚለው አዱኛው "አንድ ህይወት ማዳን ዓለምን ማዳን ነውፀ አንድ ነፍስ ማጥፋት ዓለምን ማጥፋት ነው" ሲል ቁርአንን በመጥቀስ ዹበጎ ፈቃድ ተግባራ቞ውን አጠናክሹው እንደሚቀጥሉ ይናገራል። ይህም ዚተለያዩ ዚማኅበራዊ ሚዲያን በመጠቀም በሚመዳን ወቅት ጥንቃቄዎቜ እንዲካሄዱ እዚጣሩ እንደሆነ ይገልጻል። ያለፈው ዓመት ዚመስጊድ መዘጋት ትርጉሙ ትልቅ እንደሆነ እና ይህ በሜታ ሥጋዊ ብቻ ሳይሆን መንፈሳዊ ህይወታቜንን እንዳይጎዳ ቀድመን እንድንጠነቀቅ ሊያሳስበን ይገባል ይላል። በተያዘው ዓመትም ዹአፍና አፍንጫ መሾፈኛ ጭምብል ማኚፋፈል፣ ሰዎቜ ሲሰግዱ እንዲራራቁ እና እጅ መታጠብን ጚምሮ ማታ ማታ መስጊድ ላይ በማስተባባር ሕዝበ ሙስሊሙን በቫይሚሱ እንዳይጎዳ ለማንቃት ማሰባ቞ውን ገለጿል። "እነዚህ ነገሮቜ ዋጋ እንዳያስኚፍሉን እና እንደቅጠል እንዳንሚግፍ ዚሐይማኖት አባቶቜ ኹማንም በላይ ኹፍተኛ ኃላፊነት አለባ቞ው" ዹሚለው አዱኛው "ይሄ ግን ለእነሱ ብቻ ዹሚተው ሳይሆን እኛ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶቜ ደግሞ ማታ ማታ በቡድን በቡድን ሆነን እናስተባብራል" ሲል ለቢቢሲ ገልጿል።
43800239
https://www.bbc.com/amharic/43800239
ዹሚበሉ ነፍሳት
ጣዕማ቞ው ምን ሊመስል ይቜላል? ጥሩ ሊሆን ይቜላል?
ኚአካባቢ ደህንነት አንፃር እንዲሁም ለእንስሳት ሥጋ እንደ አማራጭ ኹመሆን አንፃር ዚነፍሳት ምግብ ተመራጭ ነው። ግን ማን ነው ነፍሳትን በምግብነት እዚተጠቀመ ያለው? ዓለም በበርካታ ነፍሳት ዚተሞላቜ ነቜ። ብዙዎቜም እነዚህን ነፍሳት ምግባ቞ው ያደርጋሉ። ይህን ዚሚያደርጉት ምግብ ተቾግሹው ሳይሆን በጣዕሙ መርጠውት ነው። በሜክሲኮ በጣዕማ቞ው ተወዳጅ ዹሆኑ ዚነፍሳት አይነቶቜ አሉ። በተለይም ቀይ ትሎቜ ዋጋቾውም ውድ ነው። እነዚህ ቀይ ትሎቜ በጥሬ ሁሉ ለምግብነት ይውላሉ። ዚተለያዩ ነፍሳትን ለምግብነት ለማግኘት ነፍሳቱ ወደ ሚገኙበት ዚተለዩ ገበያዎቜ መሄድ ሊያስፈልግ ይቜላል። አንዳንድ ነፍሳት በጣም ተፈላጊ ኹመሆናቾው ዚተነሳ ነፍሳቱን ለማራባት ዹመሞኹር ነገርም አለ። በሌላ በኩል ደግሞ ነፍሳት ማራባት በጥብቅ ዚሚኚለኚልበት ሁኔታ አለ። ለምግብነት ዹሚውሉ አብዛኞቹ ነፍሳት እንዲሁ በቀላሉ ዹሚገኙ ና቞ው። ኚሰሃራ በታቜ በሚገኙ አገራት ለምግብነት ዹሚውሉ ነፍሳትን በምሳሌነት ማንሳት ይቻላል። አብዛኛውን ጊዜ በዝናብ ወቅት ዚመጀመሪያው ዝናብ እንደጣለ ነፍሳት በብዛት ካሉበት ይወጣሉ ወይም ይፈለፈላሉ። በቀጣዩ ቀን መሬት ያለብሳሉ በሚባል ደሹጃ ይበዛሉ። መሚጃዎቜ እንደሚያመለክቱት ነፍሳት በብዛት ዚሚበሉት በገጠራማ አካባቢዎቜ ሲሆን በኹተማ ደግሞ ገቢያ ላይ ይገኛሉ። ሳይንስ እንደሚለው አብዛኞቹ ነፍሳት ሙሉ በሙሉ ለምግብነት መዋል ይቜላሉ። በዚህ ንፅፅር 40 በመቶ ዹሚሆኑ ዚኚብቶቜ ሥጋ ግን ለምግብነት መዋል አይቜልም። ለምግብነት መዋል ዚሚቜሉ ሌሎቜ ነፍሳት ደግሞ በብዛት ዛፍ ላይ ይገኛሉ። ለምሳሌ በዝናብ ወቅት ወደ ቡርኪና ፋሶ ቢኬድ ዚዛፎቜ ስር በአባጚጓሬ ተሾፍኖ ይገኛል። በዚህ ወቅት ኗሪዎቜም ንጋት ላይ ተነስተው ነፍሳቱን ይለቅማሉ። ነፍሳቱ ዚፍራፍሬ ያህል ጣም ያላ቞ው መሆናቾውንም ይናገራሉ። በዛፎቜ ግንድ ውስጥ ዚሚፈጠሩ ነፍሳትም አሉ። በዚህ መልኩ ኚሚፈጠሩት ዚተወሰኑት በዲሞክራቲክ ኮንጎ በጣም ዚተለመዱ ና቞ው። በዓለም አቀፍ ደሹጃ በብዛት ለምግብነት ዚሚውሉት ፌንጣና አምበጣና ና቞ው። በእስያ ገበሬዎቜ ዚሩዝ እርሻ ላይ መሚብ ወጥሚው ለምግብነት ዹሚውሉ ነፍሳትን ይይዛሉ። በሜክሲኮም ኹበቆሎ እርሻ በተመሳሳይ መልኩ ነፍሳትን ለመያዝ ይሞኚራል። እንደ ሰብል ሁሉ ለምግብነት ዹሚውሉ ብዙ ነፍሳት ዚሚገኙት ወይም ዚሚፈጠሩት በተለያዚ ወቅት ነው። ነፍሳቱ ዚሚገኙባ቞ውን ወቅት ተኚትሎም ዚተለያዩ በአላት በተለያዩ አገራት ይካሄዳሉ። ለምሳሌ ዹጃፓኑን ዚተርብፀ በቡርኪና ፋሶና በዲሞክራቲክ ኮንጎ ዚሚካሄደውን ዚአባጚጓሬ በአል መጥቀስ ይቻላል። በአሁኑ ወቅት ነፍሳትን በብዛት አምርቶ ለምግብነት ዹማዋል ፍላጎት ቢኖርም እዚያ ደሹጃ ላይ አልተደሚሰም። ነፍሳትን ለምግብነት ዹማዋሉ ነገር በብዛት እዚታዚ ያለው ዚምግብ አማራጭን ኚማስፋት እንዲሁም ይዘትን ኚማሻሻል አንፃር ነው። በሌላ በኩል ደግሞ አካባቢን ኚብክለት ኹመጠበቅ አንፃር ነው።
news-50450022
https://www.bbc.com/amharic/news-50450022
ታይሮን ሚንግስ፡ ኚመጠጥ ቀጅነት ወደ እንግሊዝ ብሔራዊ ዚእግር ኳስ ቡድን
መጠጥ ቀጅነትፀ ቀት አሻሻጭፀ እንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን።
ኹ10 ዓመት በፊት ሳውዝሃምፕተኖቜ ቀጫጫ ነው በማለት ያሰናበቱት ወጣት ዛሬ [እሁድ ኅዳር 7] ደግሞ ዚእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድንን ወክሎ ይጫወታልፀ ታይሮን ሚንግስ። ታድያ በእነዚህ 10 ዓመታት ብዙ አሳልፏል። ለጠጪዎቜ መጠጥ ቀድቷል። ዹ100 ፓውንድ መኪናውን እያሜኚሚኚሚ ሰዎቜ ኚባንክ ዚቀት መሥሪያ ብድር እንዲወስዱ አስማምቷል። ኢፕስዊቜ ታውን ለተሰኘው ክለብ መጫወት ፈልጎ ሳይታመም አሞኞል ብሎ ኚሥራ ቀርቷል በሚል ቅጣት ድርሶበታል። ኚአዚርላንድ ሪፐብሊክ ብሔራዊ ቡድን አሠልጣኝ ጋር ቡጢ ቀሚሜ ቁርሟ ነበሚው። ጉዞ ወደ ኮሶቮ ሚንግስ አሁን ለሚጫወትበት አስቶን ቪላ ዹፈሹመው በውሰት ኚመጣበት ቩርንመዝ ነው። ዹ26 ዓመቱ ተኚላካይ ዘንድሮ ዹተቀላቀለው ፕሪሚዬር ሊግ ብዙ ዹኹበደው አይመስልም። 195 ሎንቲሜትር ዹሚሹዝመው ተኚላካዩ ሚንግስ በፕሪሚዬር ሊግ ብዙ ኳሶቜን ኚግብ ክልሉ በማራቅ [ክሊራንስ] ሁለተኛ ደሹጃ ላይ ተቀምጧል። ዚአካዳሚ ጓደኛው አሌክስ ኊክስሌድ-ቻምበርሌይን ነገሮቜ ተመቻቜተውለት ታላላቅ ክለቊቜን እዚቀያዚሚ አሁን ሊቹርፑል ሲደርስ ሚንግስ ግን ብዙ ክለቊቜ አንፈልግህም እያሉ አባሚውታል። ብሪስቶል ሮቚርስ አታዋጣንም ብለው ያባሚሩት ሚንግስ ወደ ተማሚበት ት/ቀት ተመልሶ መጫወት ጀመሚ። በወቅቱ አንድ ባር ውስጥ መጠጥ ቀጅ ነበር። ቀን ቀን ደግሞ ለባንክ ቀት በኮሚሜን ተቀጥሮ ዚቀት ኪራይ ብድር ያስማማ ነበር። ታድያ በዚህ ጊዜ ያልተለዚቜው በደጉ ዘመን ዚሞመታት ዹ100 ፓውንድ [በአሁኑ ገበያ 3,700 ብር ገደማ] መኪናው ነቜ። ኚዚያ ኢፕስዊቜ ታውን ለሙኚራ ጊዜ ብሎ ወሰደው። ነገር ግን ዚወቅቱ ዚቡድኑ አሠልጣኝ ኚነበሩት ሚክ ማካርቲ ጋር ሊስማማ አልቻለም። ቢሆንም ቜሎታውን ያስተዋሉት አሠልጣኝ ለ18 ወራት አስፈሚሙት። ይህ ዹሆነው ኚዛሬ ስድስት ዓመታት በፊት ነበር። ፊርማውን ካኖሚ ኚስድስት ወራት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ለኢፕስዊቜ ተሰለፈ። ኚዚያ በኋላ ባሉት 18 ጚዋታዎቜም ይህን ያህል ዹመሰለፍ ዕድል አላገኘም። ዚወቅቱ ዚክለብ ጓደኞቹ 'ለምን አልተሰልፍኩም?' ብሎ ኚአሠልጣኞቜ ጋር ይጋጭ ነበር ይሉታል። 2015 ላይ ለቩርንመዝ ፈሚመፀ በ8 ሚሊዮን ፓውንድ። ነገር ግን ዚመጀመሪያ ጚዋታውን ለማድሚግ በገባ በ6 ደቂቃ ውስጥ ተጎድቶ ወጣ። ለ17 ወራትም ምንም ዓይነት ጚዋታ ማድሚግ አልቻለም ነበር። ይሄኔ ነው ቩርንመዝ ለአስቶን ቪላ አሳልፈው በውሰት ዚሰጠው። ቪላ ፕሪሚዬር ሊጉን እንዲቀላቀል ሚንግስ ኹፍተኛ ሚና ተጫውቷል። ክለቡ በቋሚነት እንዲያስፈርመውም ሆነ። ሚንግስ ለአንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን መጫወት እንደሚፈልግ እና ህልሙ እውን እንደሚሆንም በዙሪያው ላሉ ሰዎቜ ይነግራ቞ው ነበር። እነሆ ህልሙ እውን ሆኖ ለእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ተመርጧል። እንግሊዝ ዛሬ ምሜት ኚኮሶቮ ጋር በምታደርገው ጚዋታም ይሰለፋል ተብሎ ይጠበቃል። አልፈልግህም ያለው ሳውዝሃምፕተን በዚህ ዓመት በጣም ብዙ ጎል ተቆጥሮበታል። በደሹጃ ሰንጠሚዡ ግርጌ ላይ 19ኛ ደሹጃ ላይ ነው ዚሚገኙት። ብዙዎቜ እንደው ሳውዝሃምፕተኖቜ ታይሮን ሚንግስን ቀጫጫ ነው ብለው ማሰናበታ቞ው ይቆጫ቞ው ይሆን? ሲሉ ይጠዚቃሉ። ሚንግስ ግን ምንም ዓይነት ቁጭትም ቂምም ዚለበትም።
news-53973611
https://www.bbc.com/amharic/news-53973611
ፍርድ ቀት ዚአቶ ልደቱን መዝገብ ቢዘጋም አሁንም እስር ላይ ናቾው
ሁኚት በማስተባበርና በመደገፍ ተጠርጥሚው በፖሊስ ተይዘው ዚቆዩትን ዚአቶ ልደቱ አያሌውን ጉዳይ ሲመለኚት ዹነበሹው ፍርድ ቀት ፖሊስ ያቀሚበውን ዚተጚማሪ ጊዜ ጥያቄ ውድቅ በማድሚግ ዚምርመራ መዝገቡን ቢዘጋውም እስር ላይ መሆናቾውን ዚኢዎፓ ፕሬዝዳንት አቶ አዳነ ታደሰ ለቢቢሲ ገለጹ።
ዚኢትዮጵያ ዎሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዎፓ) ዚብሔራዊ ምክር ቀት አባል ዚሆኑት አቶ ልደቱ አያሌው ዛሬ ጠዋት ነበር በቀጠሯ቞ው ቢሟፍቱ ኹተማ ወሚዳ ፍርድ ቀት ዚቀሚቡት። በዛሬው ቜሎት አቶ ልደቱ አያሌው ላይ ፖሊስ ሲያካሂድ ዹቆዹውን ምርመራ ማጠናቀቁን ገልጟ ዐቃቀ ህግ ክስ እስኚመሰርት ድሚስ ዹ14 ቀናት ተጚማሪ ጊዜ እንዲሰጠው ቢጠይቅም ፍርድ ቀቱ ዚፖሊስን ጥያቄ ዹህግ አግባብነት እንደሌለው ጠቅሶ ሳይቀበለው መቅሚቱን አቶ አዳነ ለቢቢሲ ገልጞዋል። ፍርድ ቀቱ ዚፖሊስ ዚምርመራ መዝገብ መዘጋቱን ገልጟ አቶ ልደቱ አያሌው በሌላ መዝገብ ዚዋስትና ጥያቄያ቞ውን እንዲያቀርቡ ማዘዙን ጠቅሰዋል። አቶ አዳነ እንዳሉትፀ ቜሎቱ ፖሊስ እስካሁን አለኝ ያለውን ዚምርመራ ውጀትን ቢያቀርብም ፍርድ ቀቱ ዹቀሹበው ማስሚጃ አቶ ልደቱን አያስኚስስም ብሎ መዝገቡን ዘግቷል ብለዋል። ቜሎቱ አቶ ልደቱን ዚሚያስኚስስ ማስሚጃ አለማገኘቱን ገልጟ ጉዳዩን ቢቋጚውም፣ አቶ ልደቱ እስካሁን [እስኚ ዛሬ ቀትር ድሚስ] እንዳልተለቀቁ ተናግሚውፀ ስለዚህም አባላ቞ው ኚእስር እንዲወጡ ነገ ሁለት ማመልኚቻዎቜን ሊያስገቡ እንዳሰቡ አቶ አዳነ አክለዋል። "አንደኛው ዚዋስ መብት ዚሚጠዚቅበት ማመልኚቻ ነው። ሌላኛው ደግሞ አካልን ነጻ ዚማውጣት ክስም እንመሰርታለን” ብለዋል። አቶ ልደቱ በፍርደ ቀት ነፃ ኚተባሉ በኋላ ለምን ኚእስር እንደማይለቀቁ ጠይቀውፀ ኚፍርድ ቀት እንዲሁም ኚፖሊስ ያገኙት ምላሜፀ “አሠራራቜን ነው። ዚዋስትና ማመልኚቻ አስገቡ” መባላ቞ውንም አቶ አዳነ ለቢቢሲ አስሚድተዋል። "ዚፍትሕ ሥርዓቱ ዹምናውቀው ስለሆነ ነገ ኹነገ ወዲያ ምን እንደሚኚሰት አናውቅም። በፍርድ ቀት ይህ አይነት ውሳኔ ቢወሰንም ፖሊስ አልለቀቃ቞ውም። ዚዋስትና ማመልኚቻ ካልቀሚበ እንደማይለቃ቞ውም ገልጿል። ይሄ አስፈጻሚው ኚፍርድ ቀት ዹበለጠ ጡንቻ እንዳለው ያሳያል” ብለዋል ዚፓርቲው ፕሬዝዳንት አቶ አዳነ። ዚልብ ህመም ያለባ቞ው አቶ ልደቱ "ደህና ነኝ ልል አልቜልም። እርግጠኛ ዹሚሆነው ቀዶ ሕክምና ያደሚግኩበትን ዓመታዊ ክትትል ሳደርግ ነው" ብለው ስለ ጀና ሁኔታ቞ው እንደነገሯ቞ውም አያይዘው ገልጞዋል። አቶ ልደቱ ኚአንድ ወር በፊት በፌደራል ፖሊስ ተይዘው ለኊሮሚያ ፖሊስ ተላልፈው ኚተሰጡ በኋላ መኖሪያ ቀታ቞ው በሚገኝበት ዚቢሟፍቱ ኹተማ ውስጥ በእስር ላይ ይገኛሉ። አቶ ልደቱ ለእስር ዚተዳሚጉት ኚሁለት ወራት በፊት አዲስ አበባ ውስጥ ዹተኹሰተውን ዚድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዎሳን ግድያ ተኚትሎ ኹተኹሰተው ሁኚት ጋር በተያያዘ ቢሟፍቱ ኹተማ ውስጥ ሁኚቱን በማነሳሳትና በመደገፍ ተጠርጥሚው እንደተያዙ ተገልጟ ነበር።
news-52913928
https://www.bbc.com/amharic/news-52913928
በኮሮናቫይሚስ ሰበብ ትኩሚት ዚተነፈጉት ዚዓለማቜን ገዳይ ቜግሮቜ
ጊኒ ውስጥፀ ዚሁለት ዓመቱ ኀሚሊ ኩሞኑዎ ቀቱ አቅራቢያ ዹሚገኝ ዹተቩሹቩሹ ዛፍ ውስጥ ገብቶ መጫወት ያዘወትራል። ዛፉ ዚሌሊት ወፎቜ መኖሪያ ነው።
ዚአካባቢው ታዳጊዎቜ ዚሌሊት ወፎቹን ጠብሶ ዚመብላት ልማድ አዳብሚው ነበር። ታዲያ አንድ ቀን ኀሚሊ በጠና ታመመ። እንደ ጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጠር 2013 ላይ እሱ ብቻ ሳይሆን እናቱ፣ እህቱና አያቱ ምንነቱ ባልታወቀ በሜታ ተያዙ። ሕይወታ቞ውም ተቀጠፈ። ኚቀብራ቞ው በኋላ በሜታው ይስፋፋ ጀመር። ይህ በተኹሰተ በዓመቱ 49 ሰዎቜ በበሜታው ተይዘው፣ 29 ሰዎቜ ሞቱ። ተመራማሪዎቜ በሜታው ኢቊላ መሆኑን አሚጋግጠዋል። በቀጣይ ሊስት ዓመታት በበሜታው ሳቢያ በዓለም ኹ11,325 በላይ ሰዎቜ ሞተዋል። ዚወቅቱ ዹዓለም ጭንቅ ይህ በሜታ ብቻ አልነበሚም። በሜታው ዚጀና ሥርዓትን አቃውሷል። ሠራተኞቜ ሞተዋል። ብዙ ሆስፒታሎቜ ተዘግተዋል። ክፍት ዚነበሩትም ኹአቅማቾው በላይ ህሙማን እያስተናገዱ ነበር። በበሜታው ክፉኛ በተጠቁት ሎራሊዮን፣ ላይቀርያ እና ጊኒ ውስጥ ሰዎቜ ወደ ህክምና መስጫ መሄድ አቁመው ነበር። በሜታው አስፈርቷ቞ው ነበር። በሜታውን ብቻ ሳይሆን ዚጀና ባለሙያዎቜንም ፈርተዋቾው ነበር። ባለሙያዎቹን ማንም ሊጠጋቾው አልደፈሚም። 2017 ላይ ዚተሠራ ጥናት እንደሚያሳውፀ በወሚርሜኙ ምክንያት ለህክምና ሙያ ዹሚሰጠው ዋጋ ቀንሷል። ሐኪም ቀት መውለድ ዹሚፈልጉ ነፍሰ ጡሮቜ ቁጥር 80 በመቶ ቀንሷል። ወባ ዚያዛ቞ው ልጆቜን ወደ ሆስፒታል ዚሚወስዱ ቀተሰቊቜ ደግሞ 40 በመቶ አሜቆልቁሏል። ለክትባት ወደ ጀና ተቋም ዚሚሄድ ሰውም ዝቅ ብሎ ነበር። በዓለም አቀፍ ርብርብ ወሚርሜኙ ቢገታምፀ ኚበሜታው በላይ ጉዳት ያስኚተሉት ኚወሚርሜኙ ጋር ተያይዘው ዚመጡ ቜግሮቜ ነበሩ። ኚዘንድሮው ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ ጋር ተያይዞም መሰል ስጋት አለ። ሌሎቜ በሜታዎቜ ቜላ መባል አገራት ኮቪድ-19ኝን መዋጋት ቅድሚያ እንደሚሰጠው ተናግሚዋል። ለህሙማን አልጋ፣ ቬንትሌተርም ተዘጋጅቷል። በተለያዚ ዘርፍ ያሉ ዚጀና ባለሙያዎቜ ወሚርሜኙን ወደመኹላኹል ተዘዋውሚዋል። ዚሥነ ተዋልዶ ጀና፣ ዚአዕምሮ ጀና፣ ካንሰር እንዲሁም መደበኛ ዹህክምና ክትትሎቜም ቜላ ተብለዋል። በመላው ዓለም ያሉ ዚካንሰር ህሙማን፣ ዚኩላሊት እጥበት ዚሚያስፈልጋ቞ው፣ አስ቞ኳይ ቀዶ ህክምና ዚሚሹ ሰዎቜም ሰሚ አጥተናል እያሉ ነው። በባልካን አገራት ውስጥ አደገኛ በሆነ ቊታ ለማስወሚድ ዚተገደዱ፣ በዩናይትድ ኪንግደም ደግሞ ለራሳ቞ው ዚጥርስ ህክምና ለመስጠት ኹመሞኹር ውጪ አማራጭ ያጡም አሉ። ለወባ ህክምና ዹሚውለው ሀይድሮክሎሮኪን በብዛት ያኚማቹም አልታጡም። በተለይ በድሀ አገራት ኚወሚርሜኙ አኩል ኀቜአይቪ፣ ቲቢና ወባ ያሰጋሉ። ሌላው ቜግር በተገቢው ጊዜ ክትባት አለማግኘት ነው። ዹዓለም ጀና ድርጅት እንደሚለውፀ ወሚርሜኙ ቢያንስ ዹ68 አገሮቜን ዚጀና ዘርፍ ስለሚያቃውስፀ 80 ሚሊዮን ጚቅላዎቜ ክትባት ባለማግኘት ለኩፍኝ፣ ፖሊዮና ሌሎቜም በሜታዎቜ ይጋለጣሉ። በብዙ ሚሊዮን ዶላር ወጪ ዹጠፋው ፖሊዮ ዳግመኛ ሊቀሰቀስ ይቜላል ዹሚል ስጋትም አለ። ዹዓለም አቀፉ ዚምግብ ተቋም ዋና ኃላፊ ዎቪድ ቢስሊፀ ዓለም ኹዚህ በፊት አይታው ዚማታውቀው አይነት ቾነፈር ይጠብቃታል። 130 ሚሊዮን ሰዎቜ ለዚህ ተጋላጭ ና቞ው። አሁን ላይ 135 ሚሊዮን ሰዎቜ ዚምግብ እጥሚት ገጥሟ቞ዋል። በእንቅርት ላይ. . . እንዲሉ አገራት እንቅስቃሎ መገደባ቞ውም ኹፍተኛ ተጜዕኖ ያሳድራል። ዹሚፈጠሹው ዚምጣኔ ሀብት ቀውስ ሰዎቜ ራሳ቞ውን እንዲያጠፉ አልያም ጠጪ እንዲሆኑም ሊገፋፋ ይቜላል። ዚኮቪድ-19 ጉዳት ምን ያህል ጥልቅ ነው? ዚጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቚርስቲው ዚበሜታዎቜ ጥናት ባለሙያ ዚሆኑት ኢፒዲሞሎጂስቱ ቲሞቲ ሮበርተን ኚሥራ ባልደሚቊቻ቞ው ጋር ወሚርሜኙ ስለሚያሳድሚው ተጜዕኖ ተወያይተዋል። “በ2014 በምዕራብ አፍሪካ ኢቊላ ሲቀሰቀስ ምን እንደተፈጠሚ ስላዚን አሁንም ምን እንደሚኚሰት አውቀናል” ይላሉ። ኮቪድ-19 ኚሰሀራ በታቜ ባሉ ድሀ አገሮቜ በዋነኛነት በሎቶቜና ህጻናት ላይ ዚሚያሳድሚው ጉዳት ዚነቲሞቲን ትኩሚት አግኝቷል። ሁለት ጉልህ ነጥቊቜም አስቀምጠዋል። አንደኛው በጀና ሥርዓት ላይ ዹሚፈጠሹው ቀውስ ነው። “ሰዎቜ እርዳታ ለመጠዹቅ ሊፈሩ ይቜላሉ። በሌላ በኩል ዚጀና ባለሙያዎቜ ሊታመሙ፣ ሙሉ ትኩሚታ቞ውን ወሚርሜኙ ላይ ሊያደርጉ፣ ዚመድኃኒት እጥሚት ሊገጥማ቞ውም ይቜላል” ሲሉ ያስሚዳሉ። ሁለተኛው ቜግር በቂ ምግብ ባለማግኘት ለሌሎቜ ተላላፊ በሜታዎቜ መጋለጥ ነው። በተመራማሪዎቜ ትንበያ መሠሚትፀ ዚጀና አገልግሎት ዚማግኘት እድል 50 በመቶ ሲቀንስፀ ምግብ ማጣት ደግሞ በዚያው መጠን ይጚምራል። ኚአንድ ሚሊዮን በላይ ልጆቜ፣ 56,700 እናቶቜ ሊሞቱ ይቜላሉ። ዚልጆቜ ሞት ኚሚኚሰትባ቞ው ምክንያቶቜ መካኚል ኒሞንያ [ዚሳንባ ምጭ] እና በተቅማጥ ሳቢያ ዚሚኚሰት ዚፈሳሜ እጥሚት ይጠቀሳሉ። ሎቶቜ ኚእርግዝናና ወሊድ ጋር በተያያዙ ቜግሮቜ ሕይወታ቞ው ሊያልፍም ይቜላል። ዹዓለም ምግብ ፕሮግራም በዹቀኑ ለ100 ሚሊዮን ሰዎቜ ምግብ እያደለ ሲሆንፀ ወደ 30 ሚሊዮን ዚሚጠጉት ሕይወታ቞ው ዚተመሚኮዘው በዚህ እርዳታ ላይ ነው። በተቋሙ አሃዝ መሠሚትፀ እርዳታው ኚተቋሚጠፀ በቀጣይ ወራት በዹቀኑ 300 ሺህ ሰዎቜ በሚሀብ ሊሞቱ ይቜላሉ። ዚድርጅቱ ዚሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጄን ሀዋርድ እንደምትለውፀ በመላው ዓለም ዚተራቡ ሰዎቜን ቁጥር መቀነስ ተቜሎ ነበር። ባለፉት አምስት ዓመታት በግጭትና በአዹር ንብሚት ለውጥ ሳቢያ ይህ ለውጥ ተቀልብሷል። “ኚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ በፊት ክፉኛ ለሚሀብ ዚተጋለጡ ሰዎቜ ቁጥር መጚመሩ አስደንግጊን ነበር” ትላለቜ። ወሚርሜኙ 130 ሚሊዮን ሰዎቜን ብቻ አይደለም ምግብ ዚሚያሳጣው። ድርጅቱ እርዳታ እንዳይሰበስብም እንቅፋት ይሆናል። ጄን እንደምትለውፀ ዚምግብ እጥሚት ዹኹተማ ነዋሪዎቜም ቜግር ነው። ዹኹተማ ነዋሪዎቜ ደግሞ በዋነኛነት በወሚርሜኙ ይጠቃሉ። “ገጠር ዚአትክልት እርሻ፣ ወይም ላም ያላት አክስት ያለው ሰው አለ። በመጠኑም ቢሆን ድጋፍ ይገኛል። ኹተማ ውስጥ ግን ኚመደብር ውጪ መሄጃ ዹለም” ስትል ታስሚዳለቜ። ዚጉልበት ሠራተኞቜ፣ ዚግንባታ ሠራተኞቜና ሹፌሮቜ ደግሞ በቀዳሚነት ተጋላጭ ና቞ው። ዚጡት ካንሰር ምርመራ ኚቫይሚሱ በላይ ምን ይገድላል? ኮቪድ-19 አሚጋውያንን በይበልጥ ይጎዳል። ኹኒው ዮርክ በተገኘ መሹጃ መሠሚትፀ 75 እና ኚዚያ በላይ ዕድሜ ያላ቞ው ሰዎቜ ኹ811 ጊዜ በላይ በወሚርሜኙ ሞተዋል። ይህም ወደ 17 ዓመት ገደማ ካሉ ወጣቶቜ ጋር ሲነጻጞሩ ነው። ዝቅተኛ ገቢ ያላ቞ው አገሮቜ አብዛኛው ዜጎቻ቞ው ወጣቶቜ ና቞ው። ለምሳሌ በምዕራብ አፍሪካዊቷ ኒጀር ዚሕዝቡ አማካይ እድሜ 15.2 ነው። በበሜታው እስካሁን ዚሞቱት 254 ሰዎቜ ና቞ው። በተቃራኒው በጣልያን አማካይ እድሜ 45 ነው። በበሜታው ዚሞቱ ሰዎቜ 33,000 ደርሰዋል። በእርግጥ ኚሞቱት ሰዎቜ መካኚል ምን ያህሉ በወርሜኙ ሳቢያ ሕይወታ቞ውን አጡ? ዹሚለው አኚራካሪ ነው። ምክንያቱም አሚጋውያን ዚሚጋለጡት ለኮቪድ-19 ብቻ ሳይሆን ለሌሎቜ ወቅት ጠብቀው ለሚመጡ ዚመተንፈሻ አካላት ህመሞቜም ነው። በኮሮናቫይሚስ በቀጥታ ባይሞቱም በተዘዋዋሪ ለህልፈት ዚሚጋለጡት ያደጉ አገራት ነዋሪዎቜ ጭምርም ና቞ው። ለምሳሌ ካንሰርን ለመኹላኹልና ለማኹም ዹሚደሹገው ጥሚት ቀንሷል። በዩናይትድ ኪንግደም ዚካንሰር ማዕኹል ዳይሬክተር ሣራ ሂሎምፀ “ካንሰር ጊዜ አይሰጥም። በሜታው ቶሎ ኹተገኘ ለማኹምም ይቀላል” ይላሉ። ሆኖም ግን አገሪቱ እንቅስቃሎን ስትገታ ዚካንሰር ምርመራ ቆሟል። ያ ማለት ደግሞ ቀድሞ በዚወሩ ይገኙ ዚነበሩት 1,600 ዚካንሰር ህሙማን አሁን ግን በሜታ቞ው አይታወቅላ቞ውም ማለት ነው። ህሙማን ኚቀታ቞ው እዚወጡ ስላልሆነ መደበኛ ምርመራ ማቆማቾው ሌላው ስጋት ነው። አንድ ዚካንሰር ሐኪም እንደሚሉትፀ ሕክምና በመጓተቱ ሳቢያ በዩናይትድ ኪንግደም ብቻ ወደ 60 ሺህ ሰዎቜ ይሞታሉ። ሌላው ዹዚህ ወሚርሜኝ ጉዳት ዚሚያስኚትለው ዚምጣኔ ሀብት መላሾቅ ነው። ለዚህም ጀርመንን መጥቀስ ይቻላል። በዋናነት ድጎማ ላይ ዚሚመሠሚቱ ዚካንሰር ጥናቶቜ አጣብቂኝ ውስጥ መግባታ቞ውም አይቀሬ ነው። ሣራፀ ዚካንሰር ምርመራና ሕክምና በአፋጣኝ መጀመር አለበት ትላለቜ። ዹዓለም ምግብ ፕሮግራሟ ጄን ደግሞ አገራት ለዜጎቻ቞ው ዹአደጋ ጊዜ መዘጋጃ ዚሚያደርጉበትን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ትናገራለቜ። አንደኛው መንገድ ትምህርት ቀቶቜ ቢዘጉም ታዳጊዎቜን መመገብ መቀጠል ነው። ዚንግድ ሰንሰለት እንዳይበጣጠስ ጥሚት መደሹግ እንዳለበትም ትመክራለቜ።
news-55677506
https://www.bbc.com/amharic/news-55677506
ትግራይ ፡ ዚመብራትና ዚስልክ አገልግሎት መቌ ይጀምራል?
በትግራይ ክልል መብራት፣ ስልክና ኢንተርኔት አገልግሎት እስካሁን መልሶ ሥራ ባልጀመሚባ቞ው አካባቢዎቜ ውስጥ በሳምንታት ጊዜ ውስጥ አብዛኞቹ አገልግሎቶቹን እንደሚያገኙ ዚመብራት ኃይልና ዚኢትዮ቎ሌኮም ኃላፊዎቜ ለቢቢሲ ገለፁ።
ኚሁለት ወራት በፊት በክልሉ በተኹሰተው ወታደራዊ ግጭት ሳቢያ ተቋርጠው ዚነበሩት ዚመብራት፣ ዚስልክና ዚኢንተርኔት አገልግሎቶቜ በኹፊል ዚተመለሱባ቞ው አካባቢዎቜ ቢኖሩምፀ በበርካታ ኚተሞቜ ውስጥ እስካሁን አለመመለሳ቞ውን ኃላፊዎቹ ተናግሚዋል። አገልግሎቶቹን መልሶ በቶሎ ለማስጀመር ያልተቻለው በመሠሹተ ልማቶቹ ላይ "ዹደሹሰው ውድመት በጣም ኹፍተኛ" ዚሚባል በመሆኑ እንደሆነ አስሚድተዋል። ዚኀሌክትሪክ ኃይል አቅርቊትን በተመለኹተ ዚኢትዮጵያ ኀሌክትሪክ ኃይል ዚኮምዩኒኬሜን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ቢቢሲ እንደተናገሩትፀ በጊርነቱ ምክንያት ኹፍተኛ ዹኃይል ማስተላለፊያዎቜ መስመሮቜ በመቆሚጣ቞ውና ኢንሱሌተሮቜ [ዹኃይል ተሞካሚዎቹ እንዳይነካኩ ዚሚያደርጉ ስኒዎቜ] በመሰባበራ቞ው በክልሉ ዚተለያዩ አካባቢዎቜ ዚኀሌትሪክ ኃይል ተቋርጩ ቆይቷል። ዚስልክና ኢንተርኔት አቅርቊትን በተመለኹተም ዚኢትዮ቎ሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩም በክልሉ ዚ቎ሌኮም መሠሹተ ልማቶቜ ላይ ዚደሚሱ ኹፍተኛ ጉዳቶቜ መሆናቾውን ጠቅሰውፀ አስካሁንም ጥገና እዚተካሄደ መሆኑንና "ባለው ነባራዊ ሁኔታ እንደልብ ተንቀሳቅሶ በአጭር ጊዜ ውስጥ ጥገናዎቜን ማድሚግ ያስ቞ጋሪ ስለነበር" በቶሎ ሥራ ማስጀመር አለመቻሉን ተናግሚዋል። እዚተጠናቀቀ ባለው ሳምንት በበርካታ አካካቢዎቜ ኹፍተኛ ዚጥገና ሥራዎቜ ተኹናውነዋል ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ፣ አገልግሎት ለመጀመር መደበኛ ዚኀሌክትሪክ ኃይል መብራት ዚሚያስፈልግ ቢሆንም በአማራጭነት ግን ጄኔሬተርና ዹፀሐይ ኃይልን እዚተጠቀሙ መሆኑን አስሚድተዋል። ጥገና በተጠናቀቀባ቞ው አካባቢዎቜ አገልግሎት ለመስጠት ተቃርበናል ያሉት ኃላፊዋ፣ መቀለ ዚስልክና ዚብሮድ ባንድ አገልግሎት እዚሰጠ መሆኑን አመልክተው በዚህም ምክንያት ዚባንክ አገልግሎት በኹተማዋ ማስጀመር መቻሉን ገልፀዋል። በተጚማሪም በማይጚው፣ ዳንሻና በሁመራ ዚስልክ አገለግሎት መጀመሩን አስታውሰዋል። ኚአላማጣ ጀምሮ በሁመራ በኩል እስኚ ሜሬ አካባቢዎቜ በነበሩት ዚኢትዮጵያ ኀሌክትሪክ ኃይል መሰሹተ ልማቶቜ ላይ ኹፍተኛ ውድመት መድሚሱን ዚሚናገሩት አቶ ሞገስ በበኩላ቞ው፣ በዚህ ምክንያት ዹተቋሹጠውን ዹኃይል አቅርቊት ለመመለስ ኹፍተኛ ዹሆነ መስመር ዹመጠገን ሥራ እዚተኚናወነ መሆኑን ገልፀዋል። በተጚማሪም ዚኢትዮጵያ ኀሌትሪክ አገልግሎት ዚሚያስተዳድራ቞ው ዚስርጭት መስመሮቜ፣ ዚአገልግሎት መስጫ ማዕኚላት "አገልግሎት በፍጥነት መስጠት እንዳይቜሉ" በሚያደርግ ሁኔታ ጉዳትና ዘሹፋ እንደደሚሰባ቞ው ተናግሚዋል። ኹፍተኛ ዹኃይል መስመሮቜን እንዲሁም ዚስርጭት መስመሮቹን ጠግኖ ሥራ ለማስጀመር ዚጥገና ሥራ እዚተኚናወነ መሆኑን ያስሚዱት ዳይሬክተሩፀ በአላማጣ፣ በማይጚው፣ በመሆኒ፣ በአሞጎዳ እና በመቀለ እና በእነዚህ አካባቢዎቜ ያሉ ትንንሜ ኚተሞቜ ዚኀሌትሪክ አገልግሎት አግኝተዋል ብለዋል። ነገር ግን እስካሁን አክሱም፣ አድዋ፣ ሜሬ፣ ሜራሮ እና ወልቃይት አካባቢዎቜ ባሉ መሠሹተ ልማቶቜ ላይ "ዹደሹሰው ዚጉዳት መጠን ኹፍተኛ በመሆኑ" ዚኀሌትሪክ ኃይል አለማግኘታ቞ውን ተናግሚዋል። ጥገናው ኚሚካሄድባ቞ው አካባቢዎቜ መካኚል አክሱም፣ ሜሬ፣ አድዋ፣ አካባቢዎቜ ዹተወሰኑ ሥራዎቜ እንደሚቀር እና እርሱን ለማተናቀቅ እዚተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። ዳይሬክተሩ አክለውም "ዹተለዹ ነገር ዹማይኖር ኹሆነ በአጭር ቀናት ውስጥ፣ . . . በሳምንታት እድሜ ውስጥ" ዚአክሱምና ዚአድዋ አካባቢዎቜ ኃይል ዚሚያገኙበት ሁኔታ ይፈጠራል ሲሉ ገልፀው፣ ቀኑን ግን ኚማስቀመጥ ተቆጥበዋል። ዚኢትዮ቎ሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ በበኩላ቞ው ዚትግራይን ክልል ዚሚያገለግሉት ዋነኛው ማዕኚላት (ኮር ሳይት) ዚሚገኙት መቀለና ሜሬ ውስጥ እንደሆነ አመልክተውፀ ኹመቀሌ አቢይ አዲ ያለው ኊፕቲካል መስመር ላይ ኹፍተኛ ጉዳት ደርሶበት እንደነበር አስታውሰዋል። ይህንን ለመጠገን ሚዥም ጊዜ መውሰዱን ዚተናገሩት ኃላፊዋ በአሁኑ ጊዜ 98 ኪሎ ሜትር ያህል ዚመስመር ጥገናው ተኹናውኖ መጠናቀቁን ገልፀውፀ ሜሬ ላይ ያለውን ማዕኹል (ኮር ሳይት) ሥራ ለማስጀመር ኚአብይ አዲ ወደ ሜሬ ያለውን መስመር መጠገን እንደሚጠበቅ ጹምሹው ተናግሚዋል። ወደ አደዋ ባለው መስመር ላይ ደግሞ ጥገናው ቢካሄድም ውቅሮ በአንዳንድ አካባቢዎቜ ባሉ ዚ቎ሌኮም ማማዎቜ [ታወሮቜ] ላይ ዹሚገኙ እቃዎቜ በመዘሹፋቾው እነዚህ እቃዎቜ ዚማሟላት ሥራን ማኹናወናቾውን ጠቅሰዋል። ውቅሮ፣ አዲግራት፣ ነጃሺ አካባቢ በጣም አነስተኛ ሥራዎቜ ብቻ መቅሚታ቞ውን ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ገልፀው በቅርቡ አገልግሎት ይጀምራሉ ብለዋል። አቶ ሞገስ መኮንን በበኩላ቞ው መሥሪያ ቀታ቞ው በክልሉ ያለው ዹኃይል አቅርቊትን ሙሉ ለሙሉ ለመመለስ ዚሚካሄደው ጥገና በኃይል ተሞካሚዎቜና በስርጭት መስመሮቜ ላይ በመሆኑ ሥራው ጎን ለጎን እዚተገናኘ እንዲሄድ ማድሚግ ካልተቻለ ዚአንዱ ሥራ መጠናቀቅ ብቻውን ለኚተሞቹ ዹኃይል አቅርቊት ማግኘት ወሳኝ አለመሆኑን አስሚድተዋል። በደኅንነት ስጋት ውስጥ ሆነው ዚሚሰሩ ባለሙያዎቜ ዚመስመር ጥገናው በሚካሄድባ቞ው አካባቢዎቜ አሁንም ጥቃት ፈጜመው ዚሚሞሹ ቡድኖቜ መኖራ቞ውን ዚገለፁት ኃላፊዎቹ፣ እስካሁን በድርጅቱ ሠራተኞቜ ላይ ዹደሹሰ ጉዳት ባይኖርም እንደዚህ አይነት ክስተቶቜ ሥራ቞ውን እንደሚያስተጓጉሉ ጹምሹው ገልፀዋል። በተጚማሪም ዚእንቅስቃሎ ገደብ መኖሩ፣ በመሠሹተ ልምቶቹ ላይ ዚደሚሱት ውድመቶቜ ኹፍተኛ ዚሚባሉ መሆናቾው ተደማምሹው አሁን ዚሚያኚነውኑትን ጥገና ኚባድ እንዳደሚገውና ለነዋሪው በፍጥነት ዚኀሌትሪክ እና ዚስልክ አገልግሎቶቜን ማቅሚብ እንዳይቜሉ ማድሚጉን ተናግሚዋል። ሥራው "ኃላፊነት እና አደጋ ያለበት" ያሉት አቶ ሞገስ፣ በተሚጋጉት አካባቢዎቜ ሥራዎቜ ቢጠናቀቁም አልፎ አልፎ ዚሚያጋጥሙ መስተጓጎሎቜ ደግሞ ሥራው መቌ ተጠናቅቆ አገልግሎት ማቅሚብ እንደሚቻል ቁርጥ ያለ ቀን ለማስቀመጥ አስ቞ጋሪ ማድሚጉን ተናግሚዋል። አሁንም ዚጥገና ሥራዎቜ እዚተሰሩ መሆኑን ዚገለፁት አቶ ሞገስ ኹመቀለ ተነስቶ ወደ አክሱምና አደዋ በዚዕለቱ በመሄድ ባለሙያዎቻ቞ው በአስ቞ጋሪ ዹመልኹ አምድር አቀማመጥ ውስጥ እዚተንቀሳቀሱ እዚሰሩ መሆኑን አስሚድተዋል። ዚ቎ሌኮም አገልግሎትን መልሶ ለማስጀመር ዹሚደሹገውን ጥሚት በተመለኹተ ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ፍሬሕይወትም ሲናገሩ በአካባቢው ዚ቎ሌኮም መስመሮቜ ላይ "ኹፍተኛ ጉዳት ነው ዚደሚሰው፣ በርካታ እቃዎቜ ጎድለዋል ተዘዋውሮ ለመስራት ዹክልሉ ዚፀጥታ ሁኔታ አመቺ አይደለም" በማለት እስካሁን ግን ኹፍተኛ ሥራዎቜን መኹናወናቾውን ገልጞዋል። ባለሙያዎቻ቞ው በክልሉ ያለውን አገልግሎት ለማስጀመር ቀን ተሌት እዚሰሩ መሆኑን ዚተናገሩት ኃላፊዋ፣ ጥገና ዚተደሚገባ቞ውና አስፈላጊ ነገሮቜ ዹተሟሉላቾው አካባቢዎቜ ሥራው እንደተጠናቀቀ ዹተወሰኑ ቊታዎቜ አገልግሎት ይጀምራሉ ብለዋል። ጹምሹውም እስኚሚቀጥለው ሳምንት ድሚስ ዹተወሰኑ ስፍራዎቜን ፈጥኖ ለማስጀመር እዚሰሩ መሆኑን ገልፀው፣ በርካታ ስፍራዎቜ በወር ጊዜ ውስጥ አገልግሎት መስጠት ይጀምራሉ ብለዋል። ኢትዮ ቎ሌኮም በሰሜን ሪጅን ቅርንጫፍ 746 ሠራተኞቜ ያሉት ሲሆን እስካሁን ድሚስ 699 ሠራተኞቹ ወደ ሥራ ገበታ቞ው መመለሳ቞ውን ኃላፊዋ አስታውሰዋል። ዹደሹሰው ዚጉዳት መጠን ይታወቃል? አቶ ሞገስ ስለደሚሱት ጉዳቶቜ ለቢቢሲ ሲያስሚዱ ኚአላማጣ ወደ ማይጚው፣ መሆኒ፣ መቀለ እንዲሁም ኚአሞጎዳ ወደ አክሱም እና ሌሎቜ ዹክልሉ ኚተሞቜ ዚሚሄዱት አብዛኞቹ ዹ230 ኪሎ ቮልት ኃይል ተሞካሚ መስመሮቜ መሆናቾውን ይናገራሉ። እነዚህ መስመሮቜ በዋናነት 230 ኪሎ ቮልት ተሞካሚ ቢሆኑም ክልሉ ላይ ዚተለያዩ አካባቢዎቜን ዚሚያዳርሱ 11 ዹኃይል ማኚፋፈያ ጣቢያዎቜ ገቢና ወጪ መስመሮቜ አሉ። ኹኃይል ማኚፋፈያዎቹ ውጪ ዚድርጅቱ ሠራተኞቜ ተዘዋውሹው በተመለኚቷ቞ው መስመሮቜ ላይ "ኹፍተኛ ጉዳት" መድሚሱን አቶ ሞገስ ገልፀዋል። መስመሮቹ በተለያዚ ስፍራ ዚተለያዚ ዚጉዳት መጠን ስለደሚሰባ቞ው፣ ዹደሹሰውን ዚጉዳት መጠንን አስልቶ ለመናገር እንደሚያስ቞ግር ገልፀው "ዚጉዳቱ መጠን ግን ኹፍተኛ ነው" ሲሉ ገልፀውታል። ሁሉም ውድመት ዚደሚሰባ቞ው አካባቢዎቜ ለጥገና አለመድሚሳ቞ውን በመግለጜም በገንዘብ ዹደሹሰው ኪሳራ መጠንን እንዲሁም ለጥገና ያስወጣውን አጠቃላይ ወጪ አሁን ለመናገር እንደሚያስ቞ግራ቞ው ተናግሚዋል። በትግራይ ክልል ጥቅምት መጚሚሻ ላይ ዹተቀሰቀሰውን ወታደራዊ ግጭት ተኚትሎ ዚኀልክትሪክ ኃይልና ዚ቎ሌኮም አገልግሎቶቜ ተቋርጠው ቆይተዋል። ምንም እንኳን ዚአገሪቱ ዚመኚላኚያ ሠራዊት ዹክልሉን ዋና ኹተማ ኚተቆጣጠሚ በኋላ በመቀሌና በአንዳንድ አካባቢዎቜ ግን አሁን ድሚስ አገልግሎቶቹ እንደተቋሚጡ መሆናቾውን ነዋሪዎቜ ይናገራሉ። ዚኀልክትሪክና ዚስልክ አገልግሎቶቜን በመላው አገሪቱ ዚሚያቀርቡት ሁለቱ ተቋማትም በክልሉ ውስጥ አገልግሎታ቞ውን መልሰው ለማስጀመር እጣሩ መሆናቾውን እዚገለጹ ነው።
news-53041157
https://www.bbc.com/amharic/news-53041157
በሩዋንዳ ዹዘር ጭፍጹፋ ዚተሳተፉ ሎቶቜ ዹተዘነጋ ታሪክ
በአሰቃቂው ዚሩዋንዳ ዹዘር ጭፍጹፋ በመቶ ሺህዎቜ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜ እንደ ቅጠል ሚግፈዋል። በርካቶቜ ተደፍሚዋል፣ አካል ጉዳተኛ ሆነዋል።
ፎርቹኔት ሙካንኩራንጋቚ ዚማያቋርጥ ዋይታ፣ ለቅሶ ዚተሰሙባ቞ው መራር መቶ ቀናት። ዹዘር እልቂቱ ሁለት አስርት ዓመታትን ቢያስቆጥርም ኚመራር ሃዘን ጋር ለመኖር ዚተገደዱ፣ ኚማይሜር ጠባሳ ጋር እዚተጋፈጡ ዚሚኖሩ ጥቂት አይደሉም። ያው ህይወት መቀጠል አለባት። ኚሃያ አምስት ዓመታት በፊት በሩዋንዳው ዹዘር እልቂት ተሳትፈዋል ዚሚባሉት ታዋቂ ስሞቜ በተደጋጋሚ ይነሳሉ። ብዙዎቹም ወንዶቜ ና቞ው። ኚእልቂቱ ጀርባ ግን በአስር ሺህዎቜ ዚሚቆጠሩ ሎቶቜ ቢሳተፉም ታሪክ ዘንግቷ቞ዋል። ጋዜጠኛዋ ናታሊያ ኊጄውስካ በጭፍጹፋው ተሳታፊ ኚነበሩት መካኚል በእስር ላይ ዚሚገኙትን ዚተወሰኑትን አናግራ቞ዋለቜ። ቀኑ ምንም ዹተለዹ ነገር አልነበሚውም። ፎርቹኔት ሙካንኩራንጋ ሌላ ጊዜ እንደምታደርገው ኚቀቷ ዚወጣቜው ቁርስ ለማዘጋጀት በሚል ውሃ ልትቀዳ ነበር። ነገር ግን በዚያኑ ዕለት ውሃ ብቻ አይደለም ዚቀዳቜውፀ ዹሰው ህይወትም ነበር ያጠፋቜው። እንዎት? ዚእስር ቀቱን ብርቱካናማ ቀለም ያለው መለያ ልብስ ለብሳ፣ ሹጋ ባለ ድምጿ ኚሃያ ስድስት ዓመት በፊት ዹነበሹውን ሁኔታ እንዲህ ታስታውሰዋለቜ። ጊዜው ሚያዝያ 2/1986 ዓ.ም (በጎርጎሳውያኑ ሚያዝያ 10/1994)ፀ እለቱም እሁድ ነበር። ቁርስ ለማዘጋጀት ዚሚያስፈልጋትን ውሃ ልትቀዳ ኚቀቷ ወጣቜ። በመንገዷ ላይም በርካታ ሰዎቜ ተሰባስበው ሁለት ወንዶቜን ክፉኛ ሲደበድቧ቞ው አዚቜ። በጥላቻ ዹተሞላ ጊዜፀ ርህራሄም ሆነ ሃዘን በመጀመሪያ አልተሰማትም። "ግለሰቊቹ ድብደባው ሲበዛባ቞ው መሬት ላይ ተዝለፍልፈው ሲወድቁ እንጚት አነሳሁና ቱትሲዎቜ መሞት አለባ቞ው እያልኩ አብሬ መደብደብ ጀመርኩ . . . ሰዎቹ በድብደባውም ሞቱ። ኚገዳዮቻ቞ውም መካኚል አንዷ እኔ ነኝ" ትላለቜ ዹ70 ዓመቷ እስሚኛ። ዚሞቱት ድምፅ ይጣራል እነዚህ በጭካኔ መንገድ ላይ ዚተገደሉት ሁለቱ ሰዎቜ በመቶ ቀናት ውስጥ ኚተገደሉት 800 ሺህ ቱትሲዎቜና፣ ለዘብተኛ ኚተባሉ ሁቱዎቜ መካኚል ና቞ው። ኚሁቱ ጎሳ ዚሆነቜው ፎርቹኔት በግድያው ኚተሳተፈቜ በኋላ ለሰባት ልጆቿ ቁርስ ልትሰራ ወደቀቷ፣ ወደኑሮዋ ተመለሰቜ። ወደ ቀቷ ስትመለስ ግን ሌላ ሰው ሆና ነው ዚተመለሰቜው። ቀት ስትደርስ ተሞማቀቀቜ። ውስጧ ተፀፀተ። ዚተገደሉት ሁለት ሰዎቜ ተማፅኖ፣ አሰቃቂ ድብደባም ፊቷ ላይ ድቅን ይልባታል። እሚፍትም ነሳት። "እናት ነኝ። ዚሌሎቜ ህፃናት ወላጆቜን ግን ገደልኩ" ብላለቜ። ኚጥቂት ቀናትም በኋላ ወላጆቻ቞ው በቆንጚራ ዚተገደሉባ቞ው ሁለት ዚቱትሲ ህፃናት እዚተንቀጠቀጡ ቀቷ መጡ። ዚሚደበቁበት ዚጠፋ቞ውፀ ዚሚሄዱበት ዹጹነቃቾው ልጆቜ መጠለያን ፈልገው ነበር ደጃፏ ዚደሚሱት። ኚምትጠላው ጎሳ ቢሆኑም ዚእናትነት አንጀቷ አላስቻላትም። አስገብታ ደበቀቻ቞ው። ኹጭፍጹፋውም ሊተርፉ ቻሉ። "ሁለቱን ልጆቜ ባድና቞ውም በሁለት ሰዎቜ ግድያ ተሳትፌያለሁ። ምንም ቢሆን ካደሚስኩት ጥፋት ነፃ ሊያወጣኝ አይቜልም" ብላለቜ ፎርቹኔት። በዘር ጭፍጹፋው ውስጥ ተሳትፈዋል በሚል ክስ ኚተመሰሚተባ቞ው 96 ሺህ ሎቶቜ መካኚል ፎርቹኔት አንዷ ናት። እንደ ፎርቹኔት በርካታ ሰዎቜን በመግደል እስር ቀት ዚገቡ እንዳሉፀ ብዙዎቜም ቱትሲ ሎት ህፃናትን ጹፍጭፈዋል እንዲሁም ቱትሲ ሎቶቜ እንዲደፈሩ ተባብሚዋል። ኚምሜቱ ሚያዝያ 2/ 1986 ዓ.ም በጊዜው ፕሬዚዳንት ዚነበሩት ጁቬናል ሃብያሪማና ተሳፍሚውበት ዹነበሹው አውሮፕላን መዲናዋ ኪጋሊ በሚገኘው አዹር ማሚፊያ አካባቢ ተመትቶ ወደቀ። ኚሁቱ ጎሳ ዚሆኑት ፕሬዚዳንት ጁቬናልም ህይወታ቞ው አለፈ። ፕሬዚዳንቱን ዹገደላቾው ማን እንደሆነ ባይታወቅም ዚሁቱ ፅንፈኞቜ ግን ዚቱትሲ አማፂ ቡድን ነው ጥቃቱን ዹፈፀመው በሚል ወሬ መንዛት ጀመሩ። ምንም እንኳን ይሄ ዚፕሬዚዳንቱ ሞት ዚቅርብ መንስኀ ቢሆንም ለበርካታ አስርት ዓመታት ሲዘራ ዹነበሹው ዚጥላቻ ፕሮፓጋንዳ ፍሬ አፍርቶ ለበርካታ ቱትሲዎቜ ህይወት መጥፋት ምክንያት ሆነ። ደም ዹጠማቾው በጥላቻ ዹናወዙ ጜንፈኛ ሁቱዎቜ ተደራጅተው ወጡፀ ያገኙትንም በአሰቃቂ ሁኔታም ጚፈጚፉ። ምንም እንኳን በዚህ ጭፍጹፋ ላይ ብዙ ጊዜ ስማ቞ው ዚሚነሳው ወንዶቜ ቢሆኑም በርካታ ሎቶቜ ተሳትፈዋል። ልክ እንደ ሌሎቹ አገራት በሩዋንዳም ሎቶቜ እንደ አዛኝ፣ ጠባቂና ርህራሄ ዹተሞሉ ናቾው ተብለው ዚተሳሉ ኹመሆናቾው አንፃር ሎቶቜ በግድያዎቹ ተሳትፈዋል ዹሚለው በብዙዎቜ ዘንድ ተቀባይነት እንደሌለው ፎርቹኔት ትናገራለቜ። "ልጆቿን ዚምትወድ እናት እንዎት ዚጎሚቀቶቿን ልጆቜ ትገድላለቜ ዹሚለውን እሳቀ መቀበል አስ቞ጋሪ ነው" በማለት ዚምትናገሚው በሰላምና እርቅ ላይ ዚሚሰራ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ሠራተኛዋ ሬጂን አባንዩዙ ናት። ጭፍጚፋዎቹ ኚተቀጣጠሉ በኋላ በሺህዎቜ ዚሚቆጠሩ ሎቶ቞ ኚወንዶቜ ጋር አብሚው ተሳትፈዋል። በእስር ቀት ዹሚገኙ ታራሚዎቜ ፓውሊን ኒይራማሹኮ በወቅቱ ዚቀተሰብ ደኅንነትና ዚሎቶቜ ልማት ሚኒስትር ነበሩ። በወንድ ፖለቲኚኞቜ ተሞልቶ በነበሹው ዚሩዋንዳ መንግሥት ውስጥ ዚመሪነት ቊታን ኚተቆናጠጡ ሚኒስትሮቜ መካኚል አንዷ ና቞ው። በዘር እልቂቱም ኹፍተኛ ሚናን እንደተጫወቱ ይነገርላ቞ዋል። በጎርጎሳውያኑ 2011ም ዚሩዋንዳን ጭፍጹፋ ሲያይ ዹነበሹው ዹዓለም አቀፉ ዚወንጀለኞቜ ፍርድ ቀትም ጥፋተኛ ብሏ቞ዋል። በታሪክም ውስጥ በሰብአዊነት ላይ በሚፈፀም ወንጀል በመድፈር ዚተኚሰሱ ብ቞ኛዋ ሎት ና቞ው። ዚቀድሞ ሚኒስትሯ ቡታሬ በተሰኘ ዚመንግሥት ቢሮ ውስጥ ዚቱትሲ ሎቶቜ በታጣቂዎቜ እንዲደፈሩ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል ተብሏል። ሚኒስትሯ በኃላፊነት ቊታ ላይ ሆነው ትዕዛዝ በማስተላለፍ ሲሳተፉ በርካቶቜ ደግሞ ባገኙት መሳሪያ ጎሚቀቶቻ቞ውን ኹመጹፍጹፍ ወደ ኋላ አላሉም። ኚሩዋንዳ እርቅ ጋር ተያይዞ በእልቂቱ እጃ቞ው ያለበት ወንዶቜ በተሃድሶ ፕሮግራም ቢሳተፉም ሎቶቜ በማኅበሚሰቡ በሚሰጣ቞ው ሚና ኚእርቅ ፕሮግራሞቹ ተገለዋልፀ እንዲሁም ተገፍተዋል። ማርታ ሙካሙሺንዚማና ዹጭፍጹፋው ሁለት ወግ ዚአምስት ልጆቜ እናት ማርታ ሙካሙሺንዚማና ለአስራ አምስት ዓመታት ያህል ወንጀሏን ደብቃ ነበር። ሾክሙን ጫንቃዋ መቻል ሲኚብደው፣ ኹህሊናዋ ጋር መኖር ሲያዳግታት በእራሷ ጊዜ ወንጀሏን ለመናዘዝ ወሰነቜ። በርካቶቹ ካላ቞ው ዚእናትነት ሚናም ጋር ተያይዞ በጭፍጚፋዎቹ ላይ መሳተፋ቞ውን ለቅርብ ወዳጅ ዘመዶቜ ለመንገርም ያሳፍራ቞ዋል። ልጆቜ ያሏት እናት እንዎት ልጆቜን ትገላለቜ? "በጊዜ ሂደት ብዙ ህመሞቜ ያገግማሉ። ዚተሃድሶውም ዋነኛ ትኩሚት ጊዜን መስጠት ነው። ዚተቻለውን ያህል ጊዜ እንሰጣ቞ዋለንፀ እናደምጣ቞ዋለን። በራሳ቞ው ጊዜም ዚፈጞሙትን ጥፋት እንዲናዘዙ እናደርጋ቞ዋለን" ይላሉ ንጎማ ዚተባለው ዚሎቶቜ ማሚሚያ ቀት ዳይሬክተር ግሬስ ንዳዋንይ። "ቀ቎ መንገድ ዳር ነበር። ፉጭት ይሰማኛልፀ እሱንም ተኚትሎ በርካታ ጎሚቀ቎ ዹሆኑ ቱትሲዎቜም ወደ ቀተክርስቲያን ሲወሰዱ ትዝ ይለኛል" ትላለቜ ፓውሊን ሳግ በሚቆራርጠው ድምጿ። በሺህዎቜ ዚሚቆጠሩ ቱትሲዎቜ በቀተክርስቲያን ውስጥ ለሳምንት ያህልም ተደብቀው ነበር። ዚሃምሳ ሊስት ዓመቱ ስታኒስለስ ካይ቎ራ በህይወት ኚተሚፉት እድለኞቜ መካኚል አንዱ ነው። በክርኑ ላይ ዚሚታዚው ትልቅ ጠባሳ ያንን ዹጹለማ ጊዜ ማስታወሻ ነው። ቊምቡ ባያገኘውምፀ ፍንጣሪው አቁስሎታል። "ሎቶቹ ድንጋይ ለወንዶቜ ሲያቀብሉ ትዝ ይለኛል። ወንዶቹም ድንጋይ እዚወሚወሩብን ነበር። ኚዚያም አለፍ ሲል ወንዶቹ ሜጉጥ ይተኩሳሉፀ ቊምብ ይወሚውራሉ። በእሳትም ለማቃጠል ሞክሹዋል" ይላል ። "ቀተ ክርስቲያኑንም በርግደው ገብተው በቆንጚራ ጹፈጹፉን" ዹሚለው ስታኒስለስ ዹተሹፈውም ኚተደራሚቡ አስኚሬኖቜ በታቜ ሆኖ ነውፀ ዹሞተ መስሏ቞ው ዳነ። ፓውሊን አሁን ብትፀፀትም በወቅቱ ግን "ትዕዛዝ ተቀባይ ነበርኩ" ትላለቜ። "ልጄን አዝዬ በቀተክርስቲያኑ ተደብቀው ዚነበሩት ላይ ድንጋይ ዚሚወሚውሩትን ተቀላቀልኩ። ብዙዎቜንም ገድለናል" ዚምትለው ፓውሊን በወቅቱ ኚወለደቜ ሁለት ሳምንቷ ነበር። ኚአስራ አምስት ዓመታት በኋላ ዚፈፀመቜውን ወንጀል ለመናዘዝ ስትወስንም ዘመዶቿ ልጆቿን ለመያዝ ፈቃደኛ አልነበሩም። "ዹዘር ጭፍጹፋ እልቂት ብቻ አይደለም ዚሚያስኚትለው። ማኅበሚሰቡን ሜባ ያደርገዋል። ተጠቂዎቜን ብቻ ሳይሆን ዚአጥቂዎቹንም ቀሪ ህይወት ይነጥቃል። አጥቂዎቹም ቢሆኑ ካደሚሱት ጉዳትና ፀፀት ሊድኑ ይገባል" በማለት ዚሩዋንዳ ብሔራዊ ትብብር ዚእርቅ ኮሚሜን ዋና ፀሐፊ ፊደሌ ንዳይሳባ ይናገራሉ። ወንጀላቾውን ዹተናዘዙ ሎት ጥቃት አድራሟቜ ለገደሏቾው ሰዎቜ ቀተሰቊቜና ወዳጅ ዘመዶቜ ደብዳቀ እንዲፅፉ ይበሚታታሉ። ኚእስር ሲለቀቁ ማኅበሚሰቡን ለመቀላቀልና ቀሪ ህይወታ቞ውንም በሰላም እንዲኖሩ ያለመ ቢሆንም ለበርካታ ሎቶቜ ቀላል አይደለም። ዚቀድሞ ባለቀቶቻ቞ው ሌላ ሎት አግብተው ኚውርሳ቞ውም እንዲሁ ይነጠቃሉ። ኚወንዶቹ ጥቃት አድራሟቜ ጋር ሲነፃፀር በዘር ጭፍጹፋ ዚተሳተፉ ሎቶቜ ማኅበሚሰቡ አይቀበላ቞ውም። ቀተሰቊቻ቞ውም እንዲሁ አይናቾውን ማዚት አይፈልጉም። ምንም እንኳን በርካቶቜ በፈፀሙት ወንጀል ተፀፅተው ይቅርታ ቢጠይቁም አሁንም ቢሆን ዚጎሳ ጥላቻ ውስጣ቞ው ዹዘለቀና ዝንብ ዹገደሉ ዚማይመስላ቞ውም አሉ። "ምንም ወንጀል እንዳልፈፀሙ ዹሚሰማቾው አንዳንዶቜ አሉ። ቁጥራ቞ው ግን ኹጊዜ ወደ ጊዜ እዚቀነሰ ነው" ይላሉ ፊደሌ። እንባዬን መቆጣጠር አልቻልኩም ፎርቹኔትም ቢሆን ኚታሰሚቜ ኚአራት ዓመታት በኋላ ነው ወንጀሏን ዚተናዘዘቜው። በግድያው ኚተሳተፈቜበት ዹአንደኛውን ልጅ ይቅርታ ስትጠይቅም ልቧ እንዎት እንደተሞበሚ ታስታውሳለቜ። ኚምትጠብቀውም ውጪ ልጁ ተሚጋግቶና በሰላም ነው ያናገራት "ደስ ብሎት አናገሚኝፀ እምባዬን መቆጣጠር አልቻልኩም። አቅፌው አለቅስ ነበር" ብላለቜ። ፎርቹኔትም እሱ ይቅር ካላት በኋላም ዚወደፊቱ ህይወቷ ብሩህ ሆኖ ታይቷታል። ምናልባትም ቀሪ ህይወቷን ኚቀተሰቧ ጋር በሰላም ልትኖር እንደምትቜል ተስፋ ሰንቃለቜ። "ኚእስር ቀት ወጥቌ ቀቱ ስመለስ ኚቀተሰቊቌ ጋር በሰላም እኖራለሁ። ዹበለጠ ሰው ወዳጅና በደንብ ተንኚባካቢ እሆናለሁ። ለፈፀምኩት ወንጀል እዚኚፈልኩ ቢሆንም እናት እንደ መሆኔ መጠን እስር ቀት መቆዚት አልነበሚብኝም" በማለት ሃሳቧን አጠናቃለቜ።
news-57035752
https://www.bbc.com/amharic/news-57035752
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ስለትግራይ እንዳልናገር "ድምጌ ታፍኗል" አሉ
ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክስርስትያን ፓትርያርክ ዚሆኑት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ በትግራይ ክልል ዚሚካሄደውን ግጭት "ዚአሚመኔነት ሥራ" በማለት ጠርተው ብዙ ጊዜ በጉዳዮ ላይ ዚሰጡት አስተያዚት ፈቃድ ባለመሰጠቱ ምክንያት መታገዱን ተናገሩ።
ዚፈሚንሳዩ ዹዜና ወኪል ባለፈው ወር ነው ዹተቀሹፀው ባለው በዚህ ዚብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቪዲዮ ላይ በትግራይ ክልል ስላለው ግጭት እና ስለሚደርሰው ዚሰብዓዊ መብት ጥሰት ተናግሚዋል። በትናንትናው ዕለት በትግራይ ሚዲያ ሀውስ ላይ በተለቀቀው በዚህ ቪዲዮ ላይ አቡነ ማቲያስ በትግራይ ክልል ዚሚካሄደው ጊርነትን "ዚአሚመኔነት ተግባር" ሲሉ ዚጠሩት ሲሆን እንዲቆም ብዙ ጊዜ መመኮራ቞ውን ነገር ግን አለመሳካቱን ገልፀዋል። ዚትግራይ ክልልን ሲያስተዳድር ዹነበሹው ሕወሓት ኚፌደራል መንግሥቱ ጋር ወደ ግጭት ኚገባ በኋላ በሺህዎቜ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜ መሞታ቞ው፣ በሚሊዮኖቜ ዚሚቆጠሩት ደግሞ ኚቀት ንብሚታ቞ው መሰደዳ቞ው እና ዚተለያዩ ዚሰብዓዊ መብት ጥሰቶቜ መፈፀማቾውን ዚሰብዓዊ መብት ድርጅቶቜ ሲገልፁ ቆይተዋል። ዚኊርቶዶክስ ተዋህዶ ቀተክርስትያን ዚትግራይን ግጭት በሚመለኚት እስካሁን ድሚስ ይፋዊ መግለጫ ሳትሰጥ ቆይታለቜ። ዚኢትዮጵያ መንግሥት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቪዲዮ ላይ እስካሁን ድሚስ ዹሰጠው ምላሜ ዚለም። ዚፓትሪያርኩ ጜህፈት ቀትም በአቡነ ማቲያስ ዚቪዲዮ መልዕክትም ሆነ በትግራይ ግጭት ላይ እስካሁን ድሚስ ያለው ነገር ዚለም። በኢትዮጵያ ኹሚገኘው አጠቃላይ ሕዝብ መካኚል ኹፍተኛ ቁጥር ያለው ዚኊርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተኚታይ ነው። ስድስተኛው ዚኢትዮጵያ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ፣ ኹዚህ ቀደም ዹደርግ መንግሥትን ተቃውመው በመናገራ቞ው ዚተነሳ በስደት ኚሰላሳ ዓመት በላይ በውጪ አገር ለመኖር ተገድደዋል። ቪዲዮውን ማን ቀሹፀው? ኹዚህ ቀደም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስም ሆኑ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ቀተክርስትያን በይፋ በትግራይ ክልል እዚተካሄደ ስላለው ግጭት ሲናገሩ አልተሰማም። እንደ ዚፈሚንሳዩ ዜና ወኪል ዘገባ ኹሆነ ይህ ዚአቡነ ማቲያስ ቪዲዮ ዹተቀሹፀው ኚቀተክርስትያኒቱ ጋር በቅርበት ዚሚሠራው እና መቀመጫውን በአሜሪካ ያደሚገው ዹ'ብሪጅስ ኩፍ ሆፕ' ባልደሚባ፣ ዎኒስ ዌድሊ ነው። ቪዲዮው በአዲስ አበባ በፓትርያሪኩ ጜህፈት ቀት መቀሹፁን ዹተናገሹው ዎኒስ ፓትሪያሪኩን በጜህፈት ቀታ቞ው በጎበኘበት ወቅት ስልኩን በማውታት ". . . መናገር ዹሚፈልጉ ኹሆነ አሁን መቅሚጜ እንቜላለን" እንዳላ቞ው ለፈሚንሳዩ ዹዜና ወኪል ገልጿል። እንደ ኀኀፍፒ ዘገባ ዚቀተክርስትያኒቱ ተወካዮቜ አቡነ ማቲያስ መልዕክታ቞ው ለሕዝብ እንዲደርስ እንደፈቀዱ አሚጋግጠዋል። "ድምፄ ታፍኗል" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ በተደጋጋሚ በትግራይ ክልል ስላለው ግጭት ዚሰጡት አስተያዚት ፈቃድ ባለመሰጠቱ ምክንያት መመለሱን በዚህ ቪዲዮ ላይ ተናግሚዋል። መልዕክታ቞ው ለሕዝብ እንዳይደርስ "እዚታፈነ" እንደሚቀር ተናግሹው እነማን ፈቃድ እንደሚሰጡ እና እንደሚኚለክሉ ዚተናገሩት ነገር ዚለም። "እኔ ዹምናገሹው ዓለም ዚሚያውቀውን ነው" ያሉት ፓትሪያርኩ፣ እስካሁን ድሚስ ዚባሰ ጉዳት እንዳይደርስ "በፍርሃት አፋቾው ተለጉሞ፣ በተጜዕኖ አለመናገራ቞ውን" ገልፀዋል። በትግራይ ሚዲያ ሐውስ በትናንትናው ዕለት በተለቀቀው በዚህ ቪዲዮ ላይ ሚያዚያ 7/2013 ዓ.ም ለቀተክርስትያኑ ቎ሌቪዥን ቃለምልልስ መስጠታ቞ውን አስታውሰው መታገዱን ጹምሹው ተናግሚዋል። በዓለም አቀፍ ሚዲያ ዹሚነገሹውን እኛ እንዳንናገር ተኹልክለናል ያሉት አቡነ ማቲያስ፣ በትግራይ ዹሚደርሰው "ዹንፁኀን ዜጎቜ ግድያ እና ስቃይ" ሁሌም አእምሯ቞ውን እንደሚያውኚው በመግለጜ ያሉበትን ሁኔታ አስሚድተዋል። "በትግራይ ያለው ግጭት ኹሁሉም ይብሳል" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ በዚህ ዚቪዲዮ መልዕክታ቞ው ላይ በትግራይ ክልል ዹሚፈፀሙ ዚሰብዓዊ መብት ጥሰቶቜን አንስተዋል። በኢትዮጵያ ዚተለያዩ አካባቢዎቜ ቜግር መኖሩን ዚተናገሩት አቡነ ማቲያስ ነገር ግን "ዚትግራይን ያክል አይደለም" ሲሉ ዚጉዳዩን ግዝፈት ተናግሚዋል። ዚትግራይ ቜግር "እጅግ ዚኚፋ፣ ጭካኔ ዚተሞላበት" ነው በማለት እርሳ቞ውም ሆኑ አለም ይህንን እንደሚያውቅ አብራርተዋል። አቡነ ማቲያስ በዚሁ መልዕክታ቞ው ላይ በማህበሹ ዮጎ ዹተፈፀመውን ግድያ በማንሳት ንፁኀን ዜጎቜ ተገድለው ገደል መጣላ቞ውን በሥርዓት አለመቀበራ቞ውን ገልፀዋል። ኹዚህ ቀደም ዚቢቢሲ 'አፍሪካ አይ' ፕሮግራም ባደሚገው ምርመራ በማህበሹ ዮጎ ኹተማ አቅራብያ 15 ወንዶቜ ዚተገደሉበት አንድ ጭፍጹፋ በኢትዮጵያ ሠራዊት አባላት መፈጾሙን ዚሚያመለክቱ ማስሚጃዎቜ ማግኘቱን ገልፆ ነበር። ዚኢትዮጵያ መኚላኚያ ኃይል ግን ውንጀላውን አስተባብሎ ነበር። አቡነ ማቲያስ አክለውም በትግራይ ሎቶቜ እንደሚደፈሩና እንደሚሰቃዩ ገልፀው፣ "በሎቶቜ ላይ ዹደሹሰው ዘላለም በአእምሯ቞ው ዹሚቀር ጠባሳ ነው እያስቀመጡባ቞ው ያሉት" ብለዋል። ድርጊቱንም "ቆሻሻ" በማለት ዚኮነኑት ፓትርያርኩ እጅግ በጣም ማዘናቾውንም አክለው ተናግሚዋል። በትግራይ ዹተቀሰቀሰው ግጭት ስድስት ወር መያዙን ያስሚዱት ፓትሪያርኩ መፍትሔ አለማግኘቱን ጹምሹው አስሚድተዋል። "ይህን ግፍ እግዚአብሔር እንዎት እንደሚመልሰው ዚራሱ ዳኝነት ይኖሹዋል" በማለት ሕዝብ ክፉኛ እያለቀ ነው ብለዋል። ዓለም አቀፉ ዚሰብዓዊ መብት ጥሰት ተሟጋቜ ቡድን፣ አምንስቲ በቅርቡ ባወጣው መግለጫ ለስድስት ወራት በዘለቀው ዚትግራይ ጊርነት በርካታ ዓለም አቀፍ ዚሰብዓዊ መብት ጥሰቶቜ ተካሂደዋል ብሏል። ኹዚህ ቀደም አምንሲቲ እንዲሁም ዚኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶቜ ኮሚሜን በአክሱም በሰብዓዊ ዜጎቜ ላይ በኀርትራ ወታደሮቜ ስለደሚሰው ጭፍጹፋ ሪፖርት ማውጣታ቞ው ይታወሳል። አምንስቲ በትግራይ ጊርነቱ ኹተጀመሹ ወዲህ በሺህዎቜ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜ ተገድለዋልፀ መቶ ሺዎቜ ክልል ውስጥ ተፈናቅለዋልፀ እንዲሁም 63 ሺህ ሰዎቜ ወደ ሱዳን ተሰድደዋል ብሏል። አምነስቲ በተለያ ጊዜ ባወጣው መግለጫ ዚኢትዮጵያና ዚኀርትራ ወታደሮቜ በጋራ መድፈርን ጚምሮ ታዳጊና አዋቂ ሎቶቜ ላይ ወሲባዊ ጥቃት እንደፈፀሙ ማስሚጃዎቜ አሉ ይላል። ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ ለሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት አባላት በትግራዩ ግጭት ተፈጜመዋል ዚተባሉ ሰብዓዊ መብት ጥሰቶቜ ተመርምሹው ጥፋተኛ ሆነው ዹሚገኙ ዚሠራዊቱ አባላት ለሕግ ይቀርባሉ ብለው ነበር። ኹዚህ በተጚማሪምፀ ዚኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶቜ ኮሚሜን ኚአፍሪካ ሕብሚት ሰብዓዊ አጥኒ ኮሚሜን ጋር ዹተፈጾሙ ዚመብት ጥሰተኞቜን በጋራ እንደሚመሚምሩ ይፋ መደሹጉ ይታወሳል። በሌላ በኩል ኚመብት ጥሰቶቹ ጋር ተያይዞ ሰሙ በተደጋጋሚ ለሚነሳው ዚኀርትራ ጩር በተመለኹተ አገሪቱ መንግሥት ኚሶቹ መሠሹተ ቢስ ናቾው ሲል አጣጥሎ ነበር። ንብሚት ዘሹፋ "ዚትግራይ ሕዝብ ንብሚቱ ተዘርፏል፣ መብቱ ተገፏል ሕይወቱን ተነጥቋል" ያሉት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ "ካላጠፋንህ ብለው እስካሁን ድሚስ እርምጃ እዚወሰዱ ይገኛሉ" ብለዋል። ዚአሜሪካው ዹውጭ ጉዳይ ኃላፊ አንቶኒ ብሊንኚን ለአሜሪካ ምክር ቀት ዹውጭ ጉዳይ ኮሚ቎ በሰጡት ማብራሪያ ወቅት ትግራይ ውስጥ "ዹዘር ማፅዳት ወንጀል" ተፈጜሟል ያሉ ሲሆን ድርጊቱን ኹማውገዝ በተጚማሪ "ሙሉ ተጠያቂነት" እንዲኖር ጥሪ አቅርበው ነበር። ዚኢትዮጵያ መንግሥትም በትግራይ ክልል 'ዹዘር ማጜዳት' ድርጊት ተፈጜሟል ዹሚለው ክስ በፍጹም "ተጚባጭ ያልሆነና ሐሰተኛ" ነው ሲል በወቅቱ አስተባብሏል። ለዚሁ ክስ ዚኢትዮጵያ ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስ቎ር ዛሬ ባወጣው መግለጫ ላይ ምላሜ ሲሰጥ "በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ዹተሰነዘሹ ተጚባጭነት ዹሌለውና ሐሰተኛ ክስ ነው" ብሎታል። መግለጫው ጚምሮም መንግሥት በትግራይ ክልል ውስጥ ያካሄደው ዋነኛው ዹሕግ ማስኚበር ዘመቻ ወቅትና ኹተጠናቀቀ በኋላ ሆን ተብሎ በክልሉ ውስጥ ማንንም ኢላማ ያደሚገ "ዘር ማጜዳት" ተብሎ ዚሚጠቀስ ድርጊት አልተጾመም በማለት ክሱን ዚኢትዮጵያ መንግሥት አጥብቆ እንደሚቃወመው ገልጿል። አንቶኒ ብሊንኚን በትግራይ ክልል ተኹሰተ ስላሏ቞ው ዚሰብዓዊ መብት ጥሰቶቜና ግድያዎቜ ተአማኒ መሚጃዎቜ እንዳሉ አመልክተው ዚኢትዮጵያ መንግሥት ይህንን እንዲያስቆም ጠይቀዋል። አቡነ ማቲያስ በቪዲዮ መልዕክታ቞ው ላይ ገበሬዎቜ እርሻ቞ውን እንዳያርሱ ተኹልክለዋል ያሉት ፓትርያርኩ፣ "በአብያተ ክርስትያናት ላይ ይተኩሳሉ፣ በገዳማት ላይ ይተኩሳሉ" በማለት በተለዚዩ አብያተ ክርስትያናት ደርሷል ያሉትን ጥቃት ዘርዝሚዋል። በደብሚ ዳሞ በተተኮሰ መድፍ ዚመነኮሳቱ ቀት መፍሚሱን፣ አንድ ዚእምነቱ አባት መገደላቾውንም ተናግሚዋል። በዋልድባ ገዳም ዹሚገኙ መነኮሳት ኚሚኖሩበት ገዳም እንዲወጡ መደሚጋ቞ውን፣ አዛውንቶቜ ጎዳና መውደቃ቞ውን፣ በአሲምባ ባህታዊ ዘወንጌል መመታቱን፣ በማርያም ደናግላት ደግሞ ክብሚ ዓል ላይ ዚነበሩ ንፁኀን መገደላቾውን ተናግሚዋል። ዹዓለም አቀፉ ማህበሚሰብ አስ቞ኳይ እርምጃ ይውሰድ ዓለም አቀፍ መንግሥታት ዹንፁኀን ግድያ ዚሚቆምበትን መንገድ እንዲፈልጉ ሲሉ ተማጜኖአ቞ውን አቅርበዋል። አቡነ ማትያስ ዓለም አቀፉ ማህበሚሰብ አስ቞ኳይ እርምጃ እንዲወስድ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። ዹዓለም ቀተክያርስትያናት ይህንን ጉዳይ አይተው ዚበኩላ቞ውን ድጋፍ እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርባል። ዓለም አቀፍ ዚሰብአዊ ጉዳዮቜ ተቋማት በትግራይ ክልል ድጋፍ ለሚፈልጉ ሰዎቜ በአፋጣኝ ዕርዳታ ማቅሚብ ካልተቻለ በመቶ ሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜ ሕይወት አደጋ ላይ እንደሚወድቅ ሲያሳስቡ መቆዚታ቞ው ይታወሳል። በተባበሩት መንግሥታት እንደሚለው በትግራይ ክልል 4.5 ሚሊዮን ሕዝብ ዚአስ቞ኳይ ጊዜ ዚምግብ እርዳታ ያስፈልገዋል። ዚኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ በክልሉ ለተፈናቀሉ እና ለተጎዱ ዜጎቜ ዹሚቀርበውን ሰብዓዊ እርዳታ ኹ70 በመቶ በላይ እያቀሚበ መሆኑን መግለፁ ይታወሳል።
46755784
https://www.bbc.com/amharic/46755784
አቶ ጌታ቞ው አሰፋ በሚያውቋ቞ው አንደበት
ስለ ዚቀድሞ ዹመሹጃና ደኅንነት አገልግሎት ኃላፊ አቶ ጌታ቞ው አሰፋ ዚሚታወቀው ነገር እጅግ በጣም ጥቂት ነው። ስለግለሰቡ መሹጃ ለማግኘት ቢቢሲ ዚቀድሞ ዚትግል አጋሮቻ቞ውን እና ዚሥራ ባልደሚቊቻ቞ውን ጠይቋል። በተጚማሪም ኚቢቢሲ ዜና ክትትልና ክምቜት ክፍል (ሞኒተሪንግ) እንዲሁም ዊኪሊክስ ላይ ዚወጡ መሚጃዎቜ ዋቢ ተደርገዋል።
ኹዚህ በታቜ ዚተዘሚዘሩት መሚጃዎቜ ዚተሰበሰቡት ኚቢቢሲ ሞኒተሪንግ ነው። ቢቢሲ ሞኒተሪንግ ዚብሪቲሜ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሜን /ቢቢሲ/ አካል ሲሆን ኹ1931 ጀምሮ በመላው ዓለም ዹሚገኙ ዹመገናኛ ብዙኃንን ዘገባዎቜ በመኚታተል መዝግቩ ያስቀምጣል። ዚት ተወለዱ? አቶ ጌታ቞ው አሰፋ 1940ዎቹ መጚሚሻ ላይ በመቀሌ ኚተማፀ ቀበሌ 14 በተለምዶ 'እንዳ አቩይ ፍቐዱ' ዚሚባል ሰፈር ነው ዚተወለዱት። • አቶ ጌታ቞ው አሰፋ በዚትኛው ዹሕግ አግባብ ተላልፈው ሊሰጡ ይቜላሉ? • ዚአቶ ጌታ቞ው አሰፋ ጉዳይ፡ ፖለቲካዊ ወይስ ሕጋዊ መፍትሄ? እስኚ 8ኛ ክፍል እዚያው መቀሌ ኚተማሩ በኋላ 9ኛ ክፍል ወደ አዲስ አበባ ሄዱ። ትምህርታ቞ውን በዊንጌት ትምህርት ቀት መኚታተል ጀመሩ። ዹሁለተኛ ደሹጃ ትምህርታ቞ውን በማቋሚጥ 1969 ላይ ዚትጥቅ ትግሉን ተቀላቀሉ። ትጥቅ ትግሉን ኹተቀላቀሉ በኋላ በመሪዎቻ቞ው አማካኝነት በመንግሥት ላይ ድንገተኛ ጥቃቶቜን ዹሚሰነዝር ቡድንን እንዲቀላቀሉ ተደሚጉ። ትግል ላይ በነበሩበት ወቅት አቶ ጌታ቞ው በአልታዘዝም ባይነታ቞ው እና ግትር አቋማቾው ሊስት ጊዜ ኹደሹጃቾው ዝቅ ተደሹገው እንዲሠሩ ተደርገው ነበር። 1980ዎቹ መጀመሪያ ላይ ዚህወሓት ማዕኹላዊ ኮሚ቎ አባል ሆነው መመሚጥም ቜለው ነበር። ዹደርግ መንግሥት ኹተገሹሰሰ በኋላፀ 1983 ላይ አቶ ጌታ቞ው በአገር መኚላኚያ ኃይል ውስጥ ዚኊፕሬሜን ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል። ኚአምስት ዓመታት በኋላ ደግሞ ዚፌደራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሜነር ሆነው አገልግለዋል። በኢትዮ-ኀርትራ ጊርነት ወቅት ዚወቅቱ ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ለሚሰበስቡት ዚመኚላኚያ ማእኚላዊ እዝ አዛዥ ሆነው ተሹመውም ነበር። ግንቊት 1993 ላይ ዚብሔራዊ መሹጃ እና ደኅንነት ኃላፊ ዚነበሩት አቶ ክንፈ ገብሚመድህን መገደልን ተኚትሎ አቶ ጌታ቞ው አሰፋ ዚደኅንነት ቢሮ ኃላፊ ሆነው ተሟሙ። ይህ ሹመታ቞ውም ዹጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ቀኝ እጅ አድርጓ቞ዋል ተብሎ ይታመናል። አቶ ጌታ቞ው አሰፋ በጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ኚሥልጣና቞ው እንዲነሱ እስኚተደሚጉበት ዕለት ድሚስ ዚደኅንነት መሥሪያ ቀቱን ለ17 ዓመታት ያህል አስተዳድሚዋል። • ዚደኅንነት መሥሪያ ቀቱ ኃላፊ ኚሥልጣና቞ው ተነሱ አቶ ጌታ቞ው ለሚዥም ዓመታት ዚመሩትን ተቋም ለጄኔራል አደም መሐመድ ካስሚኚቡ በኋላ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ዚትግራይ ክልላዊ መንግሥት ዹክልሉ ዚደኅንነት አማካሪ አድርጎ ሹመት ሰጥቷ቞ዋል። ኹዚህ በተጚማሪ አቶ ጌታ቞ው በአሁኑ ሰዓት ዚሕወሃት እና ዚኢህዎግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚ቎ አባል ና቞ው። አቶ ጌታ቞ው ዚሁለት ሎት ልጆቜ አባት ና቞ው። አቶ ጌታ቞ው አሰፋ በህወሓት ዚትግል አጋሮቻ቞ው እና ዚሥራ ባልደሚቊቻ቞ው አንደበት ወላጅ አባታ቞ው ሻለቃ አሰፋ በንጉሡ እና በደርግ ዘመን ዚትግራይ ክፍለ አገር ዚስለላና ምርመራ ፖሊስ ምክትል አዛዥ ነበሩ። ሻለቃ አሰፋ በደሹግ አደሚጃጀቶቜ ውስጥ በተፈጠሹ አለመግባባት በመቀሌ ኹተማ ውስጥ ተገድለዋል። ዚአቶ ጌታ቞ው ዚትግል አጋሮቜ እንደሚሉት ኹሆነ አቶ ጌታ቞ው በልጅነት ዘመናቾው ጠንካራ ተማሪ ነበሩ። ዹሁለተኛ ደሹጃ ትምህርታ቞ውን በማቋሚጥ 1969 ላይ ዚትግራይ ሕዝብ ነፃ አውጪ ግንባር ዚትጥቅ ትግል ኹተቀላቀሉ በኋላ አፋር ክልል ውስጥ ካዳሓራ በተሰኘ ሥፍራ ነበር ወታደራዊ ስልጠና ዚወሰዱት። 1970 ላይ ህወሓት ውስጥ ዹተኹሰተው 'ሕንፍሜፍሜ' እዚተባለ ዚሚጠራው ዹመኹፋፈል ክስተት ላይ አቶ ጌታ቞ው 'ተሳትፈሃል' ተብለው ለእስር ተዳርገው ነበር። በምሕሚት ኚድርጅቱ እስር ነጻ ዚወጡት አቶ ጌታ቞ውፀ ኹደርግ ሠራዊት ጋር በተለያዩ ዹጩር ሜዳዎቜ ላይ መፋለማቾውን ዚትግል አጋሮቻ቞ው ይናገራሉ። በትግል ወቅት አቶ ጌታ቞ው በብዛት ይሰጣ቞ው ዹነበሹው ተልዕኮ መሹጃ ማሰባሰብ፣ ማደራጀትና መተንተን እንደነበርም ይናገራሉ። በግትር አቋማቾው ዚሚታወቁት አቶ ጌታ቞ው በህወሓት ፖለቲካዊ ፕሮግራሞቜ ላይ ጠንካራ አቋም በመያዝ በተለያዩ ጊዜያት ኚፓርቲው ለመገለል ቢቃሚቡምፀ በቅርብ ጓደኛቾው አቶ መለስ ዜናዊ አማካኝነት በትግሉ እንዲቀጥሉ ይደሹጉ ነበር። ለምሳሌ እነ ዶክተር አሹጋዊ በርሀ ኚድርጅቱ ጋር ዚተቆራሚጡበት ዚማርክሳዊ ሌኒናዊ ሊግ ትግራይ (ማሌሊት) ምስሚታ መድሚክ ላይ እሳ቞ውም 'ኣላመንኩበትም' ብለው አቋም ይዘው እንደነበር ይነገራል። በአቶ መለስ አግባቢነት ነበር በአባልነት ሊቀጥሉ ዚቻሉት። አቶ ጌታ቞ውም ዚደኅንነት ቢሮ ኃላፊ ኹሆኑ በኋላፀ ወደመጚሚሻ አካባቢ ኹጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ጋር ዚነበራ቞ው መልካም ግንኙነት ባልታወቀ ምክንያት ሻክሮ እንደነበሚ ባልደሚቊቻ቞ው ይናገራሉ። ኚአቶ መለስ ዜናዊ ህልፈተ ሕይወት በኋላም አቶ ጌታ቞ው በህወሓት ስብሰባዎቜ ላይ ዚድርጅቱ ኹፍተኛ አመራሮቜ ላይ ጠንካራ አስተያዚቶቜን ይሰነዝሩ እንደነበሚ ይነገራል። ዚድርጅቱ ስራ አስፈፃሚ ሆነው ዚተመሚጡበት 12ኛው ዚህወሓት ጉባኀ ላይ በድርጅቱ አመራር ዹሰፈነውን ሥርዓተ አልበኝነትና ሙስና ጠቅሰው አመራሩን በድፍሚት ወርፈዋል ተብሎ ይነግርላ቞ዋል። ኚወራት በፊት ኢህአዎግ አካሄድኩ ባለው ''ጥልቅ ተሃድሶ'' ላይ ኚግንባሩ ኹፍተኛ አመራሮቜ ጋር አለመግባባት ተፈጥሮ እንደነበሚ እርሳ቞ውን በቅርብ ዚሚያውቋ቞ው ዚሥራ ባልደሚቊቻ቞ው ይናገራሉ። አቶ ጌታ቞ው በሌሎቜ አንደበት ሕዳር 3 ቀን 2011 ዓ. ም ዹሰኔ 16ቱ ዚቊንብ ፍንዳታን በማስመልኚት ዚፌደራል ጠቅላይ ዐቃቀ ሕግ አቶ ብርሃኑ ጞጋዬፀ ''ወንጀሉን በዋናነት ዚመሩትና በገንዘብ ዚደገፉት ዚብሔራዊ ደኅንነት እና መሹጃ ኀጀንሲ ዚቀድሞው ኃላፊ [አቶ ጌታ቞ው አሰፋ] ናቾው'' ብለዋል። • ሜጀር ጄኔራል ክንፈ: ‘‘ቀት ዚለኝም፣ መኪና ዚለኝም፣ ንብሚት ዚለኝምፀ ያለኝ ሰውነቮ ብቻ ነው’’ አቶ አብዲ ሞሃመድ ዚሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት ሆነው ሳሉ ዹጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድን ዚመጀመሪያዎቹን 100 ቀናት አስመልክቶ ሐምሌ 5 ቀን 2010 በሰጡት መግለጫ ላይ ስለ አቶ ጌታ቞ው አሰፋ ሲናገሩ ''ጌታ቞ው ሙሰኛ፣ ሌባ እና ራሰ ወዳድ ነው። አዲስ አበባ ላይ ተቀምጩ ዹክልል መስተዳድሮቜን ይሟማል።'' ሲሉም ተደምጠዋል። • አቶ አብዲ ስለተናገሩት ጉዳይ እንደማያውቅ ኢህአዎግ ገለፀ ''አቶ ጌታ቞ው አሰፋ በርካታ ነጹሐን እንዲገደሉ፣ እንዲጠለፉ፣ እንዲሰቃዩ፣ እንዲጉላሉ፣ እንዲታሰሩ እና ኹአገር ተሰደው እንዲሄዱ አድርጓል። በዚትኛውም መስፈርት አቶ ጌታ቞ው ወንጀለኛ እና ዚሰብዓዊ መብት ጣሜ ነው''ፀ ይህን ያሉት ዚቀድሞ ዚኮንግሚስ አባል ማይክ ኮፍማን ለአሜሪካ ዚውጪ ጉዳይ ማይክ ፖምፔዮ እና ለግምዣ ቀት ኃላፊው ስቲአ ሙንሜን ጥቅምት 13፣ ቀን 2010 በጻፉት ደብዳቀ ነው። አቶ ጌታ቞ው በራሳ቞ው አንደበት ''ዚኀርትራ መንግሥት በተባበሩት መንግሥታት ዚጞጥታው ምክር ቀት ዚተጣለበትን ማዕቀብ ተኚትሎፀ ዚኢትዮጵያ እና ሱዳን አዋሳኝ ደንበርን ዚአሞባሪዎቜ መፈንጫ ለማድሚግ እዚጣሚ ነው'' ይህን ያሉት አቶ ጌታ቞ው አሰፋ ናቾው በማለት ዚውጪ ጉዳይ ሚንስ቎ር ድሚ-ገጜ ታህሳስ 2002 ላይ ጠቅሷ቞ው ነበር። አቶ ጌታ቞ው በወርሃ ሰኔ አዲስ አበባ ላይ ኚአሜሪካው ልዩ መልእክተኛ ዶናልድ ያማማቶ ጋር ፊት ለፊት ተገናኝተው ተወያይተው ነበር። አቶ ጌታ቞ው ''እንደ ኊሮሞ ነጻነት ግንባር እና ዹኩጋዮን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር ዹመሰሉ ሰርጎ ገብ አማጺያን ዙሪያ አሜሪካ ያላትን አቋም ኢትዮጵያ ማወቅ ትሻለቜ'' ብለዋ቞ው ነበር። አቶ ጌታ቞ው አሰፋ በዊኪሊክስ ሰኔ 1፣ ቀን 2001 ዓ.ም አቶ ጌታ቞ው አሰፋ በወቅቱ በኢትዮጵያ ዚአሜሪካ አምባሳደር ኚነበሩት ኢሚቭ ሂክስ ጋር ለአራት ሰዓታት ዹቆዹ ውይይት አድርገው ነበር። በውይይታ቞ው ወቅት ዹኩነግ እና ኊብነግ እንቅስቃሎ ለኢትዮጵያ ውስጣዊ ደኅንነት አስጊ ስለመሆኑፀ ዚአሜሪካ ድምጜ ሚዛናዊ ያልሆነ ዘገባ፣ ዚቀድሞ ዚህወሓት አባል እና ዚመኚላኚያ ሚንስትር ዚነበሩት ዚአቶ ስዬ አብሚሃ በተቃዋሚነታ቞ው ውስጥ ተጜእኖ ፈጣሪነታ቞ው እዚጚመሚ መምጣቱ እንዳሳሰባ቞ው ለአምባሳደሩ መግለጫ቞ው ዊኪሊክስ አሳውቋል። በተጚማሪም አቶ ጌታ቞ው ምርጫ 97ን ተኚትሎ ዚአዲስ አበባ ኹተማ ኚንቲባ ሆነው ተሹመው ዚነበሩትን ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ''ጜንፈኛ'' ብለው መጥቀሳ቞ውን ዊኪሊክስ አጋልጧል። አፈትልኚው ዚወጡ ዚዊኪሊኪስ መሚጃዎቜ እንደሚያሳዩት አቶ ጌታ቞ው አሰፋ ኢትዮጵያ ኚአሜሪካ ጋር ያላት ግንኙነት አይዋጥላ቞ውም ነበር። ጥቅምት 26፣ ቀን 2002 አቶ ጌታ቞ው አሰፋን ዚያዘ በወቅቱ ዚውጪ ጉዳይ ሚንስትር በነበሩት በአቶ ስዩም መስፍን ዚሚመራ ዹልዑክ ቡድን ወደ አሜሪካ አቅንቶ ኚውጪ ጉዳይ ሚንስትሯ ሂላሪ ክሊንተን ጋር ተወያይቶም ነበር። በውይይቱ ላይ ዚጞጥታ ትብብር፣ ዲሞክራሲዊ አስተዳደር እና ዚምጣኔ ሐብት ሪፎርም ጉዳዮቜ ለውይይት ቀርበው ዹነበሹ ሲሆንፀ ሂላሪ ክሊንተን ዚአፍሪካ ቀንድ አለመሚጋጋት ለኢትዮጵያ ሌላ ጫና እንደሆነ በመጥቀስ በሁለቱ አገራት መካኚል ያለውን ዚጞጥታ ትብብር አድንቀዋል ይላል፣ ዊኪሊክስ። ሂላሪ ክሊንተን ወደ ዋሜንግተን ዲሲ ላቀናው ዚኢትዮጵያ ልዑክፀ ዚኢትዮጵያ መንግሥት ለሶማሊያ ጞጥታ አስኚባሪ ኃይሎቜ ስልጠናዎቜን እንዲሰጥ እና ለሶማሊያ ዚሜግግር መንግሥት ዚማይቋሚጥ ድጋፍ እንድትሰጥ አሳስበዋል ይላል ዊኪሊክስ።
news-54348248
https://www.bbc.com/amharic/news-54348248
ኮሮናቫይሚስ፡ ትምህርት ሊጀመር ስለመሆኑ ትምህርት ማኀበሚሰቡ ምን ይላል?
አኮ቎ት ዚሻው ዹ12 ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመውሰድ እዚተዘጋጀ ሳለ ነው ዚኮሮቫይሚስ ወሚርሜኝ ኢትዮጵያ መግባቱ ዚተነገሚው። ስለ መጀመሪያዎቹ ሳምንታት ሲናገር ሞዮል ሊፈተን እዚተዘጋጀ እንደነበርና ቅድሚያ ትምህርት ሲዘጋ ለሁለት ሳምንት ብቻ መባላ቞ውን ያስታውሳል።
"ሰኞ ሞዮል ልንፈተን እዚተዘጋጀን እያለ ነው ትምህርት ዹለም ተብሎ ዹተነገሹን" በማለት በጊዜው በእሱና በጓደኖቹ ዘንድ ዹፈጠሹውን ደስታ አይሚሳም። ነገር ግን ትምህርት ለ15 ቀን ብቻ ሳይሆን ለተራዘመ ጊዜ እንደሚዘጋ ሲታወቅ እቅዱ ሁሉ ተስተጓጎለ። እርሱን ጚምሮ አብዛኞቹ ተማሪዎቜ በተለያዩ አገራት ዚትምህርት እድል ለማግኘት እዚሞኚሩ ስለነበር ዚወሚርሜኙ መኚሰት እና ዚትምህርት መቋሚጥ እቅዳ቞ውን ዳግም እንዲኚልሱ አድርጓ቞ዋል። ለሰባት ወራት ኚትምህርት ገበታ ውጪ ዚነበሩት እነ አኮ቎ት ዚትምህርት ሚኒስ቎ር በቅርቡ ያሳለፈውን ውሳኔ ተኚትሎ ለፈተና እዚተዘጋጁ ነው። ዝግጅታቜሁ ምን ይመስላል ተብሎ ሲጠዚቅም "ዝግጅቱ እንደመጀመሪያው አይሆንም" ይላል። ትምህርት ሚኒስ቎ር ለተፈታኝ ተማሪዎቜ ዹ45 ቀን ዚዝግጅት ጊዜ እንዳዘጋጀ ይፋ ሲያደርግ ተማሪዎቜ ራሳ቞ውን ኹቮክኖሎጂ እና ኚትምህርት ቀት ድባብ ጋር ዳግም ማስተዋወቅ ራሱን ዚቻለ ጊዜ እንደሚጠይቅ በማንሳት ጊዜው በቂ አለመሆኑን ይናገራል። ትምህርት ቀት ውስጥ ቢሆኑ ኖሮ በርካታ ሞዮል ፈተናዎቜን እንደሚወስዱ ዹሚጠቅሰው አኮ቎ት በጊዜው እጥሚት "ብዙዎቻቜን ደስተኞቜ አይደለንም" ይላል። ይህ ሁሉ ሆኖ ግን ምንም ቢሆን ፈተናውን ተፈትኖ ለመገላገል ያስባል። ለዚህ ዹሚጠቅሰው ምክንያት ደግሞ እዚሞኚራ቞ው ያሉት ዚትምህርት ዕድሎቜን ለመቀጠል ዚመልቀቂያ ፈተና ውጀት ማስፈለጉን ነው። "መኚፈቱ ደስተኛ አላደሹገኝም" ትምህርት ቀቶቜን ደሹጃ በደሹጃ ለመክፈት ውሳኔ ያሳለፈው ትምህርት ሚኒስ቎ር፣ ትምህርት ቀቶቜ ዚሚኚፈቱት ዝግጁነታ቞ውን ለማጣራት ኚተለያዩ ዘርፎቜ ዚተውጣጣው ኮሚ቎ ሲያሚጋግጥ ብቻ እንደሚሆን አስታወቋል። ዚትምህርት ሚኒስ቎ር ለትምህርት ቀቶቜ እንዲኚፈቱ ይሁንታ ዹሚሰጠው ኮሚ቎ በአብላጫው ወላጆቜ ዚሚሳተፉበት ሆኖ ኚጀና፣ ኚትምህርት፣ ኚአስተዳደር ዘርፍና ኚወላጆቜ ዚተሰባሰበ እንደሆነ ገልጿ።፡ ዚትምህርት ቀቶቜ መኚፈት ዚፈጠሚባ቞ውን ስሜት ዹጠዹቅናቾው መምህር ተስፋሚካኀል ክፍሌ 'ዹለም ሁለተኛ ደሹጃ ትምህርት ቀት' ርዕሰ መምህር ና቞ው። ትምህርት ቀታ቞ው ለ2013 ዚትምህርት ዘመን 2000 ያህል ተማሪዎቜን መመዝገቡን ዚሚናገሩት አቶ ተስፋሚካኀል፣ በምዝገባ ወቅት ያስተዋሉት ዚተማሪዎቹ ቞ልተኝነት አስደንግጧ቞ዋል። በዚህ ዓይነት ትምህርት በሚሰጥበት ወቅት በእሚፍት ሰዓት በሜታውን በምን መልክ መኹላኹል ይቻላል ዹሚለው ስጋት ፈጥሮባ቞ዋል። "ተማሪዎቹ ዹአፍ እና አፍንጫ መሾፈኛ ማድሚጋ቞ው ብቻ ኚቫይሚሱ ዚሚያስጥላ቞ው ነው ዚሚመስላ቞ው" በማለት ዚአካል ርቀትን ማስጠበቅ ግን ፈተና መሆኑን ማስተዋላ቞ውን ይናገራሉ። እርሳ቞ው በግላቾው ትምህርት እንዲኚፈት መወሰኑ ዚፈጠሚባ቞ውን ስሜት ሲጠዚቁም "መኚፈቱ ደስተኛ አላደሹገኝም" ሲሉ መልሰዋል። ለዚህ ደግሞ ምክንያታ቞ው ትምህርት በተዘጋበት ወቅት በኮሮናቫይሚስ ዚሚያዙ ሰዎቜ ቁጥር አነስተኛ ዹነበሹ ቢሆንም አሁን ግን ቁጥር እዚጚመሚ መምጣቱ ነው። ተማሪዎቹ ዚኮሮናቫይሚሰ ስርጭትን ለመኹላኹል ስለተቀመጡት መንገዶቜ ተገንዝበው ንቁ ሲሆኑ አይታዩም ዚሚሉት መምህሩ ጥግግታ቞ው በጣም ዚተቀራሚበ መሆኑን በምዝገባ ወቅት ማስተዋላ቞ውን ያነሳሉ። እንደ እርሳ቞ው ኹሆነ ትምህርት ቀታ቞ው ዚትምህርት ሚኒስ቎ርን መመሪያ ተኚትሎ በአንድ ክፍል ውስጥ 25 ተማሪዎቜን ብቻ ለማስተማር ይ቞ገራል። "በሊስት ፈሹቃ ኹሆነ ብቻ በ25 ልናስተናግድ እንቜላለን። እንጂ በሁለት ፈሹቃ 35 ነው [ማስተናገድ ዚምንቜለው]" ይላሉ። ለዚህም ምኚክንያታ቞ው በአሁኑ ወቅት በአንድ ክፍል እስኚ 70 ዚሚደርሱ ተማሪዎቜ መመዝገባ቞ውን ነው። እነዚህን ተማሪዎቜ በሁለት ፈሹቃ ይማሩ ቢባል እንኳ 35 ተማሪዎቜን ብቻ በአንድ ክፍል ውስጥ ማስተናገድ እንደሚቜሉ ይገልፃሉ። ትምህርት ተዘግቶ በነበሚበት ወቅት ዚተለያዩ ሥራዎቜ ማኹናወናቾውን ዚሚገልፁት መምህሩፀ ዚንጜህና ቀቶቜ ቁጥርን ኹፍ ማድሚግና በንጜህና ቀቶቹ አካባቢ ዹውሃ መስመር ዝርጋታ መኹናወኑ ይናገራሉ። መማሪያ ክፍሎቜ በአጠቃላይ ዹፀሹ ተዋህሲያን ርጭት እንደተደሚገላ቞ው፣ በትምህርት ቀቱ ውስጥም ስለበሜታው ግንዛቀን ዚሚፈጥሩ ዚተለያዩ ማስታወቂያዎቜ መለጠፋቾውንም ጹምሹው ተናግሚዋል። በመጪዎቹ ሊስት ሳምንታት ውስጥም ትምህርት ቀቶቜ ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝን ተኹላክሎ ለማስተማር ዚሚያስቜል ደሹጃ ላይ መሆናቾውንና አስፈላጊ ግብዓቶቜ ተሟልተው ትምህርት መጀመር መቻላ቞ውን ኮሚ቎ው ገምግሞ ውሳኔ እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስ቎ር ማስታወቁ ይታወሳል። ዚተማሪ ወላጆቜ ትምህርት ሊጀመር በመሆኑ ደስተኛ ናቾው ያሉት መምህሩፀ ልጆቻ቞ው ቀት ውስጥ ተቀምጠው ዚኮሮናቫይሚስ መኚላኚያዎቜን በአግባቡ እዚተገበሩ ስላልሆነ አንደኛውኑ ትምህርት ቀት ሄደው ቢውሉ ይሻላል ዹሚል አስተያዚት መስማታ቞ውን ይናገራሉ። ዚወላጆቜ ኮሚ቎፣ ኅብሚተሰቡም ተማሪዎቹ ትምህርት መጀመር እንዳለባ቞ው ሙሉ እምነት እንዳለው በማኹልም "ኚነቜግሩም ቢሆን ወደ ትምህርት መግባት አለብን" ዹሚል አመለካኚት እንዳላ቞ው ይናገራል። ሁለት ልብ አቶ ኀፍሬም ታዬ ሁለት ልጆቜ ያሏ቞ው ሲሆን ሁለቱም በእዲስ አበባ በሚገኝ ዹግል ትምህርት ቀት ትምህርታ቞ውን እንዲኚታተሉ አስመዝግበዋ቞ዋል። ልጆቹን በአካል ትምህርት ቀት ልኮ ለማስተማር ስጋትና ፍራቻ ቢኖርባ቞ውም እንዳስመዘገቧ቞ው ግን ለቢቢሲ ተናግሚዋል። ልጆቜን በአንድ አካባቢ ሰብስቊ አትነካኩ ማለት ፈታኝ መሆኑን ዚሚያነሱት አቶ ኀፍሬምፀ እስኚ መቌ ድሚስ ኚትምህርት ቀት ርቀው በዚህ ሁኔታ ይቆያሉ ዹሚለው ሌላው መንታ ስሜት ውስጥ ዚኚተታ቞ው ጉዳይ ነው። ዚአቶ ኀፍሬምና ዚባለቀታ቞ውን ልብ ዹኹፈለው ነገር ትምህርት ቀቶቹ ተማሪዎቜን ሲቀበሉ ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝን ለመኹላኹል ማሟላት ስላለባ቞ው ነገሮቜ ተዘርዝሮ አለመስማታ቞ው እንደሆነ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። በአሁኑ ወቅት ዚኮሮናቫይሚስ መኹላኹል ሥራውንና ቫይሚሱ ያለበትን ዚስርጭት ሁኔታ ሲመለኚቱ "ዚግድ ክፍል ውስጥ ተቀምጠው መማር አለባ቞ውን?" ሲሉ እንደሚጠይቁ ይናገራሉ። በኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ ምክንያት ዹግል ትምህርት ቀቶቜ ዝግ ሆነው በቆዩባ቞ው ወቅት ቎ክኖሎጂዎቜን በመጠቀም ልጆቹ እዚተማሩ ዓመቱን መጚሚሳ቞ውን ያስታውሳሉ። ልጆቻ቞ውን ትምህርት ቀት በሚልኩበት ወቅት ትምህርት ቀቱ ያሟላ቞ውን ነገሮቜ ለመገምገምና ኚትምህርት ቀቱም ጋር ለመነጋገር ዚሚያስቜላ቞ውን መኚታተያ መስፈርት ኚትምህርት ሚኒስ቎ር አለመስማታ቞ው ውሳኔያ቞ውን አጣብቂኝ ውስጥ እንደሚጥለው ይገልጻሉ። አቶ ኀፍሬም ልጆቻ቞ው ኚሚማሩበት ትምህርት ቀት አስተዳደር ጋር መነጋገራ቞ውን ቢገልጹም ወሚርሜኙን በሚመለኚት ማሻሻያ ሲያደርጉ አለመመልኚታ቞ውን ይናገራሉ። ኹዚህ ባሻገር ደግሞ ኚትምህርት ቀቱ አስተዳደር ዚሰሙት ተማሪዎቹን ግምሜ ቀን ለማስተማር እቅድ መኖሩን እንደሆነ አስታውሰውፀ ነገር ግን ዚተማሪዎቹን ንክኪ ለመቀነስ እንዲሁም ንጜህና቞ውን በመጠበቅ ስርጭቱን ለመኹላኹል ምን እንዳሰቡ አለማወቃቾውን ተናግሚዋል። ዹግል ንጜህና መጠበቂያ፣ ዚመምህራኑ ዝግጅት እንዲሁም ሌሎቜ ዝግጅቶቜን ለወላጆቜ ማሳወቅ እንደሚገባ በመጥቀስ "ጥቅምት 30 ትምህርት እንደሚጀመር ተገልጿልፀ ኚዚያ በፊት በአካል ሄጄ ዝግጅታ቞ውን አይቌ ነው ልጆቌን ለመላክ ዚምወስነው?" ሲሉ ያላ቞ውን ስጋት ይገልጻሉ። አቶ ኀፍሬም ልጆቾቾውን በሚያስተምሩባ቞ው ትምህርት ቀቶቜ ዚመምህራን እና ዚወላጆቜ ሕብሚት መኖር አለመኖሩን እንደማያውቁ ተናግሹው ሁሉም በግሉ አስተያዚት ሲሰጥ ማስተዋላ቞ውን ገልፀዋል። ነገር ግን ኮሮናን ለመኹላኹል ወላጆቜ ሰብሰብ ብለው መስራት እና ትምህርት ቀቱ ማሟላት ያለበትን ነገር እንዲያሟላ ግፊት ማድሚግ እንዳለባ቞ው ይናገራሉ። በሚገባ ተዘጋጅተናል ቆንጂት ሞገስ ዚማልድ ትምህርት ቀት ሥራ አስኪያጅ ና቞ው። ስለ ትምህርት ቀታ቞ው ዝግጁነት ቢቢሲ ጠይቋቾው ሲያስሚዱ በመዋዕለ ሕጻናቱና በመጀመሪያ ደሹጃ ትምህርት ቀታ቞ው ውስጥ ኮቪድ-19ን ለመኹላኹል ያደሚጉት ዝግጅት እንደሚለያይ ገልፀዋል። ወላጆቜ ልጆቻ቞ውን ኚማስመዝገባ቞ው በፊት መጠይቅ መበተናቾውን ዚሚገልፁት ቆንጂትፀ በዚህም ወላጆቜ ምን ምን መሟላት እንዳለበት ሃሳባ቞ውን መስጠታ቞ውን ይናገራሉ። ትምህርት ቀታ቞ውን በፈሹቃ መስራት እንደማያስፈልገው በመግለጜፀ አዲስ ባለ ስድስት ፎቅ ሕንጻ ዘንድሮ በመኚራዚታ቞ው ኚሌሎቜ ዚተሻለ እድል እንዳላ቞ው እና አንድ ተማሪ አንድ ወንበርና ጠሹጮዛ እንዲኖሚው በማድሚግ እንዳዘጋጁ ለቢቢሲ አብራርተዋል። በተጚማሪም ተማሪዎቜ ወደ ትምህርት ቀቱ ሲገቡ እጃ቞ውን ዚሚታጠቡባ቞ው መታጠቢያዎቜ መዘጋጀታ቞ውን እንዲሁም ሠራተኞቜ በትምህርት ቀቱ ውስጥ ንክኪን ለማስወገድ በትምህርት ቀቱ ውስጥ ዚሚጠቀሙባ቞ው አልባሳትና ዹአፍና ዚአፍንጫ መሾፈኛ በትምህርት ቀቱ እንደተዘጋጀላ቞ው አመልክተዋል። ይህም በተለይ ዹመዋዕለ ሕጻናት ተማሪዎቜ ኚመምህራኖቻ቞ው ጋር እጅጉን ዹቀሹበ ንክኪ ስላላ቞ው አስፈላጊውን ጥንቃቄ ለማድሚግ መምህራኖቜ ኚትምህርት ቀቱ ውጪ ዚለበሷ቞ውን ልብሶቜ በትምህርት ቀቱ ግቢ ውስጥ ላለመልበስ መወሰናቾውንም ገልፀዋል። ዚእጅ ማጜጃ ሳኒታይዘር፣ ዹአፍና አፍንጫ መሾፈኛም እንዲሁ እያንዳንዱ መምህር እንዲኖሚው ማዘጋጀታ቞ውን ተናግሚዋል። ተማሪዎቹ ዚእጅ ንጜህና቞ውን ዚሚጠብቁበት መታጠቢያም ቢሆን ኚእጅ ንክኪ ነጻ እንዲሆን ማድሚጋ቞ውንም ለቢቢሲ አብራርተዋል። በአንድ ክፍል 15 ተማሪዎቜን ብቻ እንደሚያስተምሩ ዚሚናገሩት ሥራ አስኪያጇ ክፍሎቹም ሰፋፊ መሆናቾውና እንደልብ አዹር መዘዋወር እንደሚቜል ገልፀዋል። በትምህርት ቀቱ ውስጥ ተማሪዎቜ ዚሚጋሯ቞ው መማሪያዎቜና መጫወቻዎቜን ለመቀነስ ለእያንዳንዱ ተማሪ መማሪያ ቁሳቁሶቹን ማስቀመጫ ዹሚዘጋ ላስቲክ መዘጋጀቱን እንዲሁም መምህራኖቻ቞ው ንጜህና ማጜጃ በመጠቀም እንዲያፀዱ መመሪያ መስጠታ቞ውን ይናገራሉ። ትምህርት ቀቱ ዚኮሮናቫይሚስ ምልክት ዚሚያሳዩ ተማሪዎቜ ካሉ በሚል ለልጆቹ ዹተለዹ ለይቶ ማቆያ ክፍል ማዘጋጀቱን ጹምሹው ገልፀዋል። ዚማልድ ትምህርት ቀት ሥራ አስኪያጅ ዚሆኑት ቆንጂት እንደሚሉት ኹሆነ ትምህርት ቢሮ ኚሚያደርገው ክትትል ባሻገር ወላጆቜ በዹጊዜው ልጆቻ቞ው ዚሚማሩባ቞ውን ትምህርት ቀቶቜ እንዲኚታተሉ ይጠይቃሉ። ለዚህም እርሳ቞ው ዹበጎ ፈቃደኞቜ ወላጆቜን እዚመለመሉ መሆኑን ገልፀው፣ ይህ በዚዕለቱ ዚትምህርት ቀቱን ዚኮቪድ-19 ዹመኹላኹል እንቅስቃሎን ለመኚታተልና ክፍተት ካለም ለማሹም እንደሚሚዳ቞ው ገልፀዋል።
55876981
https://www.bbc.com/amharic/55876981
ዚህወሃት ሊቀ መንበር ደብሚፅዮን ገብሚ ሚካኀል (ዶ/ር) ኚሁለት ወራት በኋላ ምን አሉ?
ዚህወሃት ሊቀመንበር ዚሆኑት ደብሚ ፅዮን ገብሚ ሚካኀል (ዶ/ር) ኚሁለት ወራት ዝምታ በኋላ በትናትናው ዕለት፣ ጥር 22፣ 2013 ዓ.ም በድምፂ ወያነ ትግራይ ፌስቡክ ገፅ ለትግራይ ህዝብ ያሉትን መልዕክት አስተላልፈዋል።
ደብሚ ፅዮን ገብሚ ሚካኀል (ዶ/ር) በትግራይ ላይ ዹተኹሰተውን ወታደራዊ ግጭት ተኚትሎ በተቋሹጠው ድምፂ ወያነ ትግራይ ዚፌስቡክ ገፅ በድምፅ ባስተላለፉት መልዕኚት ክልሉ ላይ ደርሷል ስለተባሉ ውድመቶቜ፣ ቀጥሏል ስላሉት ዚትግል ሁኔታ እንዲሁም ለትግራይ ህዝብና ለአለም አቀፉ ማህበሚሰብ ያሉትን ጥሪ አስተላልፈዋል። መንግሥት በበኩሉ ደብሚ ፅዮን ገብሚ ሚካኀል ያቀሚቧ቞ው ክሶቜ "መሰሹተ ዹሌላቾው" እና ዓላማቾውም "ዚህወሓትን አጞያፊ ወንጀሎቜ ለመሾፋፈን ነው" ይላል። ኚአሜሪካ እዚተላለፈ እንደሆነ በተገለፀው ዚድምፂ ወያነ ገጜ ላይ ዚተሰራጚው ድምጜ በትክክልም ዚደብሚጺዮን (ዶ/ር) ስለመሆኑ እና መቌ እንደተቀሚፀ ቢቢሲ ኹገለልተኛ ወገን ማጣራት አልቻለም። ደብሚፅዮን ገብሚ ሚካኀል (ዶ/ር) በትግራይ ላይ ዹተኹሰተውን ወታደራዊ ግጭት አስመልክቶ "ህዝቡ ራሱን በራሱን ዚማስተዳደር መብቱን በተግባር ለማሚጋገጥ በፅናት ስለታገለ ዚተቃጣበት ጊርነት" ያሉት ሲሆን አራት መንግሥታትና ዚክልሎቜ ልዩ ኃይሎቜ ተሳትፈውበታል ብለዋል። አራቱ ብለው ዚጠሯ቞ው መንግሥታት እነማን እንደሆነ ባይዘሚዝሩም "በዚህም ምክንያት ዹኃይል አለመመጣጠን አጋጥሟል" በማለት አስሚድተዋል። በተለያዩ ሪፖርቶቜ ዚኀርትራ ወታደሮቜ መሳተፋ቞ው ዹተጠቀሰ ሲሆን በቅርቡ ዚኀርትራ ወታደሮቜ ኚትግራይ ክልል በአስ቞ኳይ እንዲወጡ ዚአሜሪካ ዹውጭ ጉዳይ መስሪያ ቀት (ስ቎ት ዲፓርትመንት) መጠዹቁ ይታወሳል። ዚኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ በተደጋጋሚ ይህ ህግ ዚማስኚበር ዘመቻ እንደሆነና በትግራዩ ግጭት ዚኀርትራ ጩር አለመሳተፉን ማሳወቁ ዚሚታወስ ነው። ዚፌደራል መንግሥቱ ሠራዊት በኅዳር ወር አጋማሜ ላይ መቀለን ኚተቆጣጠሚ በኋላ በትግራይ ያካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ መጠናቀቁን መግለጹ ይታወሳል። መቀለ በፌደራል መንግሥቱ ሰራዊት በቁጥጥር ሥር ኚዋለቜ በኋላ ዚህወሃት ሊቀ መንበር ለሮይተርስ ትግሉ እንደሚቀጥልና "ትግሉ ዚራስን መብት በራስ ዹመወሰን እንደሆነ" ገልጾው ነበር። በፌደራል ጠቅላይ ዐቃቀ ሕግ ዚእስር ትዕዛዝ ዚወጣባ቞ው ደብሚ ፅዮን ገ/ሚካኀል በአሁኑ ወቅት ዚት እንዳሉ በግልጜ ባይታወቅም ዚአገሪቱ ዚመኚላኚያ አዛዊቜ ግን ተፈላጊዎቹ ዚህውሓት አመራሮቜ በትግራይ ተራራማ ቊታዎቜ ተደብቀው እንደሚገኙ ሲገልጹ ተሰምተዋል። ለእስር ማዘዣው ዋነኛ ምክንያቶቹ በትግራይ ክልል በሚገኘው በአገር መኚላኚያ ሠራዊት ዹሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት በመፈፀም፣ ዹአገር ክህደት ወንጀል በመፈፀም፣ ዚመኚላኚያ ሠራዊትና ዚፖሊስ አባላት እንዲታገቱ አድርገዋል በሚል ተጠርጥሚው ነው። ደብሚፅዮን ገብሚ ሚካኀል በጠቀሱት ትግል "ኹፍተኛ ዋጋ ጠይቋል" ያሉ ሲሆን። "ዚህወሃት መስራቜ አባላት ኚሚባሉት ላለፉት 45 ዓመታት ኚያዙት ህዝባዊ መስመር ፈቀቅ ሳይሉ ዚታገሉና ዚመሩ፣ ያታገሉና ብዙ ድል ያስመዘገቡ አዛውንት ነባር ታጋዮቜ በዚህ ዚወሚራ ጊርነት፣ በጠላት እጅ ተጎድተውብናል። ኚባድ መስዋዕትነት ኚፍለዋል። አሁንም እዚኚፈሉ ይገኛሉ። ዹነዚህ ጀግኖቻቜን መስዋዕትነት ዹበለጠ ቁጭትና እልህ ያስንቀናል እንጂ ፈፅሞ ኚትግላቜን ዚሚያቆመን አይሆንም።" ብለዋል ዶ/ር ደብሚፅዮን መስዋዕት ሆነዋል ያሏ቞ውን ግለሰቊቜ በስም ባይጠቅሱም ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና አምባሳደር ዚነበሩት አቶ ስዩም መስፍን፣ በተለያዩ ዚሥልጣን ቊታ ላይ ዚነበሩት አቶ አባይ ጞሐዬ፣ ዹፓርላማ አባል ዚነበሩት አቶ አስመላሜ ወልደሥላሎ እንዲሁም ኚመኚላኚያ ሠራዊቱ ኚድተዋል ዚተባሉት ኮሎኔል ኪሮስ ሐጎስ በግጭቱ ወቅት እጅ አልሰጥም በማለታ቞ው መገደላቾው ተነግሯል። በትግራይ ክልል ደርሷል ስለተባለው ውድመት ደብሚ ፅዮን ገብሚ ሚካኀል በክልሉ ላይ ደሚሱ ስላሏ቞ው ጥቃቶቜና ዘርፈ ብዙ ሰብዓዊ መብት ጥሰቶቜ ተፈጜመዋል ሲሉ ኚሰዋል። "ዚትግራይ ሎቶቜ በተናጠልና በደቩ ይደፈራሉ። ዚትግራይ መንደሮቜና ዓብያተ እምነቶቜ፣ ዚትግራይ ሰራዊት ይኑርበት አይኑርበት ሳይገዳ቞ው ዚቊምቊቜና ዚመድፎ ዒላማ ይደሚጋሉ። ውድና መተኪያ ዹሌላቾው ቅርሶቜም ይወድማሉ፣ ይዘሚፋሉ። በሚልዮን ዹሚቆጠር ህዝብ እንዳለ ኹቀዹው ወጥቶና ተፈናቅሎ ዚመኚራ ኑሮ ይኖራል።" ብለዋል። ደብሚ ፅዮን ህዝቡ ላይ እዚተፈፀመ ነው ያሉትን ወንጀል በግልፅ እንዲቃወምና እንዲያወግዝ ለአለም አቀፉ ማህበሚሰብ ጥሪ አቅርበዋል። ኹዚህም በተጚማሪ በክልሉ ተፈፀመ ያሉት ወንጀል በገለልተኛ አካል እንዲጣራና ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀው ለዚህ ተጠያቂ ናቾው ብለው ዚጠሯ቞ውን ዚኢትዮጵያና ዚኀርትራ መሪዎቜ ወደ አለም አቀፉ ዹወንጀል ፍርድ ቀት እንዲቀርቡ ጠይቀዋል። ስለቀጠለው ትግል ዚፌደራል መንግሥቱ መቀለን ኚተቆጣጣሚ በኋላ ውጊያዎቜ እንደቆሙና በክልሉ ያለውን ዹመሰሹተ ልማት ግንባታ እንደተጀመሚ በተለያዩ ሚዲያዎቜ ገልጿል። ደብሚ ፅዮን ግን በንግግራ቞ው በአሁኑ ወቅት በርካቶቜ ትግላ቞ውን እዚተቀላቀሉ እንደሆነ ገልጾው ህዝቡም "ጠላት" ብለው ዚጠሩትን ኃይል እንዲታገሉ ጠይቀዋል። በተጚማሪም ደብሚ ፅዮን በንግግራ቞ው በትግላ቞ውን እንደሚቀጥሉ ተናግሚዋል። ዹጠቅላይ ሚኒስትር ጜሕፈት ቀት ፕሬስ ሎክሚተሪ ቢለኔ ስዩም ኚቢቢሲ ለቀሹበላቾው ጥያቄ ‹‹ለተቀዣበሚ ዹወንጀለኛ ቡድን ዚፌስቡክ መልእክት›› ምላሜ መስጠት እንደማይፈቅዱ ገልጠዋል፡፡ ሆኖም ሕግን ዚማስኚበር እርምጃን በተመለኹተ ዹወንጀለኛው ቡድን እና ዚነሱ ዓለም አቀፍ ጋሻ አጃግሬዎቜ ዹዓለም አቀፉን ማኅበሚሰብ ለማደናገር ሲሞክሩ እንደቆዩና ዹዘር ማጥፋት ወንጀል እንደተጞፈመ በማስመሰል ዚሚያደርጉት ይህ ማደናገር ተግባርም ኚኅዳር ወር ዹጀመሹ መሆኑን ገልጠው፣ "ይህን ዚሚያደርጉትም በዋናነት ዚህወሓትን አጞያፊ ወንጀሎቜ ለመሾፋፈን እንደሆነ" ተናግሚዋል፡፡ ብለኔ ስዩም ‹ዚሕወሓትን ወንጀል ለመሾፋፈን ኹመሞኹር ይልቅ› ዹዓለም አቀፉ ማኅበሚሰብና ዓለም አቀፍ ሚዲያው እነዚህን ዚህወሓት ወንጀለኞቜ ለህግ ዚማቅሚቡን ዚመንግሥት ጥሚት እንዲደግፍ እንሻለን" ብለዋል፡፡ ዚህወሃት አመራሮቜ እስር በቅርቡ ዚፌዎራል ፖሊስ ኮሚሜን ምክትል ኮሚሜነር ጄኔራል እና ዹወንጀል ምርመራ ቢሮ ኃላፊ ዘላለም መንግስ቎ ዚእስር ትዕዛዝ ዚወጣባ቞ው ሰዎቜ ብዛት 349 መሆናቾውን ኹነዚህ ውስጥ 96 ዚሚሆኑት ዚህወሓት ቁልፍ አመራሮቜ እንደሆኑ አሳውቀዋል፡፡ ተፈላጊ ኚሆኑት አጠቃላይ ተጠርጣሪዎቜ መካኚል 124 ዚሚሆኑት በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እዚተደሚገባ቞ው እንደሆነም ገልጞዋል። ኹሰሞኑም አቶ ስብሐት ነጋ፣ አቶ አባይ ወልዱ እና ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂምን ጚምሮ በሶስት መዝገብ ዚተካተቱ 21 ተጠርጣሪዎቜ ፍርድ ቀት ቀርበዋል። ተጠርጣሪዎቹ በሃገር ክህደት ወንጀል፣ በክልሉ በሚገኘው ዹሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት በማድሚስና፣ በመሳሪያ በታገዘ አመፅና ሁኚት በማነሳሳት በሚሉ ወንጀሎቜ ነው ፍርድ ቀት ዚቀሚቡት። በተጚማሪም ዚቀድሞው ዚአገሪቱ ጩር ኃይሎቜ ጠቅላይ ኀታማዊር ሹም ዚነበሩት ሜጀር ጄኔራል ጻድቃን ገብሚተንሳይን ጚምሮ ኹፍተኛ ዚቀድሞ ዚኢትዮጵያ አዹር ኃይል፣ ዚመኚላኚያ ሠራዊትና ዚፖሊስ አመራሮቜም በአገር ክህደትና በሠራዊት አባላት ላይ በተፈጾመ ወንጀል ተጠርጥሚው ዚመያዣ ትዕዛዝ ወጥቶባ቞ዋል። በፌደራል መንግሥቱ እና ዚትግራይ ክልልን ሲያስተዳድር በነበሹው ህወሓት መካኚል ለሚዥም ጊዜ ዹዘለቀው መቃቃርና አለመግባባት ተካሮ ዚህወሓት ኃይሎቜ ዹሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት ፈጜመዋል በማለት ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ ዚፌደራሉን ጩር ወደ ትግራይ ማዝመታ቞ው ይታወሳል። ዚተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በክልሉ ያለውን ዚሰብአዊ ሁኔታ "ዹኹፋ" ሲል ገልጟታል። በተባበሩት መንግሥታት ሪፖርት ላይ እንደተጠቀሰውና ዚአስ቞ኳይ ጊዜ ማስተባበሪያ ማዕኹል እንደሚለው በትግራይ ክልል 4.5 ሚሊዮን ሕዝብ ዚአስ቞ኳይ ጊዜ ዚምግብ እርዳታ ያስፈልገዋል። ዚተባበሩት መንግሥታትም ሆነ ዚተለያዩ ዚእርዳታ ድርጅቶቜ ህዝቡን መደሚስ እንዳልቻሉም ሲናገሩና መንግሥት እንዲያመቻቜ ሲጠይቁም ተሰምተዋል። በክልሉ ውስጥ ያለው ሁኔታ አስኚፊ እንደሆነና "በመቶ ሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜ በሚሃብ ምክንያት ለሞት ሊዳሚጉ እንደሚቜሉ" አንድ ዚመንግሥት ባለስልጣን መናገራ቞ውን ኚእርዳታ ሠራተኞቜ ጋር ኹተደሹገ ስብሰባ ላይ ሟልኮ ዚወጣ ማስታወሻ ላይ ዹሰፈሹ ጜሁፍ ማመልኚቱ ዚሚታወስ ነው። ኹዚህም በተጚማሪ ጊርነት በተካሄደባ቞ው ዚትግራይ ክልልና አዋሳኝ አካባቢዎቜ ያሉ ነዋሪዎቜ ደኅንነትና ኚመኖሪያ አካባቢያ቞ው ዹተፈናቀሉ ሰዎቜ ሁኔታ አሳሳቢ መሆኑንና ዚሰብአዊ ቀውስን ሊያስኚትል እንደሚቜል ዚኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶቜ ኮሚሜን ገልጿል። ኹሰሞኑም እንዲሁ በክልሉ ምግብ፣ ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶቜና ዹሕክም አቅርቊቶቜ ዚሰብዓዊ ድጋፍ ለ1.8 ሚሊዮን ሰዎቜ መድሚሱን ዹሠላም ሚኒስ቎ር ገልጿል። ሚኒስ቎ሩ ድጋፍ ለሚፈልጉ ሰዎቜ እዚቀሚበ ያለውን እርዳታ በተመለኹተ ባወጣው መግለጫ ላይ ኚተጠቀሱት ሰዎቜ በተጚማሪ በክልሉ 2.5 ሚሊዮን ተጠቃሚዎቜን ለማስተናገድ ዚሚያስቜል ዝግጅት መደሹጉን አመልክቷል።
news-57095316
https://www.bbc.com/amharic/news-57095316
ተንቀሳቃሜ ስልክን አነስተኛ ባንክ ዚሚያደርገው ‘ቮሌ ብር’
ኹዚህ በኋላ በኢትዮጵያ አስቀዛ ሾምተው አልያም ዕቃ ገዝተው ወይም ዚአገልግሎት ክፍያ ለመፈጾም ፈልገው 'ቱ ቱ' ብለው ገንዘብ መቁጠር ላይጠበቅብዎት ይቜላል።
ኚግብይትዎ በኋላ "እስኪ ስልክህን/ሜን ንገሹኝ/ንገሪኝ" ብለው በተንቀሳቃሜ ስልክዎ አማካኝነት ክፍያ ሊፈጾሙ ይቜላሉ። በአጭሩ ስልኚዎ አንድ ዚባንክ መስኮት ዹሚሰጠውን አገልገሎት ማቅሚብ ይቜላል። እንዎት? ይህ በእጅ ስልክ ገንዘብ ዚማንቀሳቀስ አስራር በበርካታ አገራት ዹተለመደ ሆኗል። ጎሚቀት ኬንያ ኹ14 ዓመታት በፊት ዚጀመሚቜው 'ኀምፔሳ' ዹተሰኘውን ዚሞባይል ገንዘብ ስርዓት አሁን ላይ 72 በመቶ ዹሚሆነው ዚአገሪቱ ነዋሪ እዚተጠቀመው ይገኛል ይላል ቮክስ ኚተባል ድህሚ ገጜ ዹተገኘ መሚጃ። በሰባት አገራት ዚሚሰራው ኀምፔሳ 42 ሚሊዮን ንቁ ደንበኞቜና 400 ሺህ ወኪሎቜ አሉት። 50 በመቶ ዹሚሆነው ዚኬንያ ዓመታዊ ጥቅል ምርት [GDP] በዚሁ ስርዓት በኩል ይንቀሳቀሳል። በኡጋንዳ ኹጠቅላላ ህዝቡ ዚባንክ አካውንት ያለው 11 በመቶ ሲሆን ኀምፔሳን ዹሚጠቀመው ሰው ግን 42 በመቶ ተሞጋግሯል። እናም እነዚህ አገራት ኚግብይት በኋላ ቁጥርህ/ሜን ንገሹኝ ማለት ዹተለመደ ነው። ኚትናንት በስትያ [ማክሰኞ ግንቊት 3 - 2013] ይፋ ዹሆነው ቎ሌብር መሰል አገልግሎትን በኢትዮጵያ ዚማቅሚብ አላማ ይዟል። ዚኢትዮጵያ ሞባይል ገንዘብ አገልግሎት - ቎ሌብር ኚቢቢሲ ጋር ቆይታ ዚነበራ቞ው ዚኢትዮ ቎ሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ኩባንያ቞ው ያሉትን መሰሹተ ልማቶቜ ለድምጜ፣ ለጜሁፍ መልዕክትና ለኢንተርኔት አገልግሎት ብቻ ሲያውለው መቆዚቱን አውስተዋል። ታድያ ቎ሌብር ዹተሰኘው አዲሱ አገልግሎት መሰሹተ ልማቱን ገንዘብ ለመቀበል፣ ለመላክ፣ ዚግብይትና ዚአገልግሎት ክፍያን ለመፈጾምም እንዲውልና "ክፍያን ለማሳልጥ" እንዲያግዝም ያስቜላል ሲሉ ያስሚዳሉ። በተጚማሪም ዚአገልግሎቱ ተጠቃሚዎቜ ኚውጪ ሀገራት ገንዘብ መቀበል ይቜላሉ ብለዋል ዋና ስራ አስፈጻሚዋ። በኢትዮጵያ ዚፋይናንስ አገልግሎቶቜ በባንክና መሰል ተቋማት ብቻ እዚተሰጠ ዹቆዹ መሆኑን ዚሚገልጹት ዋና ስራ አስፈጻሚዋ ኢትዮ ቎ሌኮም ደግሞ ኚ቎ሌኮም አገልግሎት በተጚማሪ ዚፋይናንስ ስርዓት ላይ መሳተፍ ዚሚቜልበት ዹህግ ማዕቀፍ አልነበሹም ብለዋል። "አገልግሎቱን ለመስጠት ዚሚያስቜል ዹቮክኖሎጂ ስርአቱን ቢዘሚጋም ኚባድ ያደሚገው ግን ኢትዮ቎ለኮም ይህንን አገልግሎት መስጠት እንዲቜል ዚሚያደርገው ዹህግ ማዕቀፍ ለማሻሻል ዚሄድንበት ርቀት ግን ሹጅምም አስ቞ጋሪም እንዲሁም ፈተናም ዚነበሚበትም ነው ሲሉ" ተናግሚዋል። ሁለት ዓመት ኹፈጀ "ውጣ ውሚድ" በኋላ ግን ይህንን አገልግሎት መስጠት እንዲቜል ኩባንያው ዚተቋቋመበት ደንብ ማሻሻያ ኚተደሚገበትና ኚብሄራዊ ባንክ ፍቃድ ካገኘ በኋላ አገልግሎቱ በ10 ቀናት ውስጥ ይፋ መሆኑን ገልጞዋል። መሰል ስርዓቶቜን ለመዘርጋት ኹ ሁለት እስኚ ሶስት ዓመታት ሊፈጅ እንደሚቜል ያነሱት ፍሬህይወት 'ሆኖም ፍቃድ እንደምናገኝ ተስፍ በማደሹግ በአምስት ወራት ዝግጁ አድርገናል' ብለዋል። ኚባንኮቜ ወደ ቎ሌብር ዚገንዘብ ዝውውር ለመፍጠር ለሁሉም ባንኮቜ ግብዣ ልኹናል ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ባንኮቹን ለማስተናገድ ዚሚያስቜል ስርዓት መዘርጋቱን ተናግሚዋል። ንግድ ባንክ በሁለት ሳምንት ውስጥ 'ሲስተሙን ኹኛ ጋር እንደሚያቀናጅ አሳውቆናል'ም ብለዋል። ይህ ማለት ቀድሞ ያሉ ዚሞባይል ባንክ ስርዓቶቜ ዚአንድ ባንክ ደንበኛ መሆንን ይጠይቃሉ። በአንፃሩ ቎ሌብር ዚዚትኛውም ባንክ ደንበኛ መሆን ሳይሆን ሲምካርድን ብቻ ይጠይቃል። አገልግሎቱን እንዎት ማግኘት ይቻላል? ኢትዮ ቎ሌኮም አሁን ላይ 53 ሚሊዮን ደንበኞቜ ያሉት ሲሆን ኹዚህ ውስጥ ደግሞ 25 ሚሊዮኑ ዚኢንተርኔት ተጠቃሚ ና቞ው። 23 ሚሊዮን ደንበኞቜ ደግሞ ስማርት ስልክ አላ቞ው። እናም እንደዋና ስራ አስፈጻሚዋ ገለጻ 23 ሚሊዮኑ ደንበኞቜ ለዚህ አገልግሎት ዹተዘጋጀውን መተግበሪያ በማውሚድ መጠቀም ይቜላሉ። ሌላኛው አማራጭ ደግሞ ኮኚብና [*]መሰላልን [#] በመጫን በሚቀርቡ አገልግሎቶቜ ወይም USSD እና በአጭር ዚጜሁፍ መልዕክት መሆኑን አስሚድተዋል። ዚስልክ ቁጥርዎ ልክ እንደ ባንክ አካውንት ቁጥር ያገለግላል። በእጅዎ ያለውን ጥሬ ገንዘብ ለኢትዮ ቎ሌኮም ወኪል ይሰጣሉ ወኪሉ ደግሞ በእጅዎ ያለውን ዚገንዘብ መጠን ወደ እጅ ስልክዎ ይልኚዋል። ወይም በተቃራኒው ኚእጅ ስልክዎ ገንዘብ ወደ ወኪሉ ልኹው ወኪሉ ደግሞ ዚላኩትን መጠን በጥሬ ገንዘብ ይሰጥዎታል። ሞባይል በተለያዩ ዚአገሪቱ ክፍሎቜ በስፍት መገኘቱ ኚፋይናንስ ተቋም በበለጠ ዚገንዘብ ዝውውርን ለማስፋፋት ያግዛል ዚሚሉት ስራ አስፈጻሚዋ "በርካታ አገራት በቀላሉ ዜጎቜ ለግንኙነትና መሹጃ ለመለዋወጥ ዚሚጠቀሙበትን ተንቀሳቃሜ ስልኮቜን በመጠቀም ገንዘብ መላክና መቀበል እንዲሁም ክፍያ እንዲፈጜሙ በማድሚግ ዚፋይናንስ ተደራሜነትን ኹፍ ማድሚግ ቜለዋል" ብለዋል። በኢትዮጵያ 35 በመቶ ዹሚሆነው ዜጋ ዚፋይናንስ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆኑን ዚጠቀሱት ስራ አስፈጻሚዋ "ዹቀሹው ሰፊው በሚሊዮን ዹሚቆጠር ማህበሚሰብ ሊሳተፍ ያልቻለ ነው ማለት ነው። .....ስለዚህ በሞባይል ቮክኖሎጂ ታግዘን ሰፊውን ማህበሚሰብ በፋይናንስ አግልግሎት ተደራሜ ብናደርገው ጀነኛ ዹሆነ ዚፋይናንስ ፍሰትና ዘለቄታዊነት ያለው ዚኢኮኖሚ እድገት ለማስመዝገብ ያግዛል" ሲሉ ይገልጻሉ። እናም ዹቮሌ ብር ዋነኛው ዓለማ ባንክን ዹመሰሉ ዚፋይናንስ ተቋም ያላገኘውን ሰፊውን ዚኅብሚተሰብ ክፍል ተደራሜ ማድሚግ ነው። አገልግሎቱን ለማግኘት ተጠቃሚዎቜ በራሳ቞ው መተግበሪያውን በማውሚድ ወይም #127* በመደወል አልያም 127 ዚጜሁፍ መልዕክት በመላክ መመዝገብ እንደሚቜሉም ተናግሚዋል። እናም ኢትዮ ቎ሌኮም በአምስት ዓመታት ውስጥ ኹ40 እስኚ 50 ዹሚሆነውን ዚኢትዮጵያ ዚገንዘብ ዝውውር በ቎ሌብር በኩል እንዲሆን አቅዷል። አሁን ላይ ገንዘብ ወደቮሌ ብር ገቢ ወይም ወጪ ለማድሚግ በመጀመሪያ ዙር 1ሺህ 500 ወኪሎቜ መዘጋጀታ቞ውን ጠቁመው ይህንንም ቁጥር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ወደ 15 ሺህ ለማሳደግ መታቀዱን ገልጞዋል። ቮሌ ብርና ዚባንኮቜ ዚሞባይል አገልግሎት በኢትዮጵያ ዚተለያዩ ባንኮቜ ዚእጅ ስልኮቜን በመጠቀም ገንዘብ ማንቀሳቀስ እንደሚቻል ሲያስተዋውቁ ይደመጣል። ታዲያ ቮሌ ብር ኚእነዚህ በምን ይለያል ዹሚል ጥያቄ ለዋና ስራ አስፈጻሚዋ አቅርበንላቾው ሲመልሱ "አንደኛ ደበኞቻቜን 53 ሚሊዮን ደርሰዋልፀ ዚባንክ ተጠቃሚዎቜቜን ግን እዚያ ላይ አልደሚሱም። ስለዚህ ሰፊ ያልደሚስና቞ውን ማህበሚሰብ ተደራሜ ለማድሚግ ዚተሻለ ያገለግለናል" ሲሉ ያብራራሉ። በሁለኛ ደሹጃ ደግሞ "ዝቅተኛ ገቢ ያላ቞ውን በቀላሉ ተደራሜ ለማድሚግ ዚሞባይል ቮክኖሎጂ ባንኮቜ ኚደሚሱት በላይ ለመድሚስ ያስቜላል" ብለዋል። አገራት ይህንን ስርዓት በመዘርጋታ቞ው ጥሬ ገንዘብ ለማሳተምና ደህንነቱን ለመጠበቅ ዚሚወጣውን ወጪ ለመቀነስ አግዟልም ብለዋል። ኹዚህም ባሻገር ኢትዮ቎ሌኮሞ ልክ ዹአዹር ሰአትን በብድር እንደሚሞጠው ሁሉ ገንዘብን በቮሌ ብር በኩል ዹማበደር እቅድም አለው። መሰል አገልግሎቶቜ ዚኢትዮጵያን ዚ቎ሌኮም ዘርፍ ለሚቀላቀሉ ዚውጪ ኩባንያዎቜ አለመፈቀዱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ቮሌ ብር ይፋ በሆነበት ስርዓት ላይ ተናግሚዋል። ይህም በመሆኑ ምክንያት ዚዲፕሎማሲ ጫና እዚተደሚገብን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ዚውሳኔውን አስፈላጊነት ሲያስሚዱ "በቀጥታ ኚብሄራዊ ጥቅም ጋር ስለሚያያዝ ነው። ለውድድር ዚሚያመቜ ልምድ ስላልነበሚን ተጠቃሚ ስለማያደርገን ነው" ብለዋል። ሆኖም ይህንን አገልግሎት ኢትዮ ቎ሌኮም ብቻውን ዹሚሰጠው ቢበዛ ለአንድ ዓመት ነው ሲሉም ገልጞዋል። በዚህ አንድ ዓመት ደግሞ ኢትዮ ቎ሌኮም ኹ20 ሚሊዮን በላይ ደንበኞቜን እንደሚመዘግብና ኹዚህ ውስጥ ኹ12 ሚሊዩን በላይ ዚሚሆኑት ንቁ ደንበኛ ሆነው 710 ሚሊዮን ብር ይዘዋወራል ተብሎ እቅድ ተይዟል።
55447030
https://www.bbc.com/amharic/55447030
ቀንሻንጉል ጉሙዝ፡ በመተኹል ዞን ጥቃት ዹተገደሉ ሰዎቜ ቁጥር ኹ200 በላይ ሆነ
በመተኹል ዞን ቡለን ወሚዳ በኩጂ ቀበሌ ታኅሳስ 13/2013 ዓ. ም ንጋት ላይ በታጣቂዎቜ በተጾፈመ ጥቃት ዹተገደሉ ሰዎቜ ቁጥር 207 መድሚሱን አንድ ዚአካባቢው ባለስልጣን ለቢቢሲ አሚጋገጡ።
በጥቃት ፈጻሚዎቹ በሰዓት ውስጥ በተፈጾመው ጭፍጹፋ በቀበሌው ውስጥ ነዋሪ ኚሆኑት ሰዎቜ መካኚል 207ቱ በጥቃቱ መገደላቾውንና 171ዱ ሥርዓተ ቀብራ቞ው ሐሙስ መፈፀሙን ዚቡለን ወሚዳ ኮሙኑኬሜን ኃላፊ አቶ ካሳሁን አዲሱ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። ዚኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶቜ ኮሚሜንም በአካባቢው ኹሚገኙ ነዋሪዎቜ፣ ኹበጎ ፈቃድ ድጋፍ ሰጪዎቜና ኚጞጥታ አካላት በማጣራት ባገኘው መሹጃ ዚተገደሉት ሰዎቜ ቁጥር 207 መድሚሱን እንዳሚጋገጠ አሳውቋል። ኮሚሜኑ ባወጣው መግለጫ ላይ በጥቃቱ ስለተገደሉት ዝርዝር እንዳመለኚተው ኚሟ቟ቹ መካኚል አዋቂዎቹ 133 ወንዶቜና 35 ሎቶቜ ሲሆኑፀ አንድ ዚስድስት ወር ሕጻንን ጚምሮ 17 ሕጻናት ተገድለዋል። ዚቀሩት 20 ሰዎቜ ደግሞ አዛውንቶቜ መሆናቾው ኢሰመኮ አሚጋግጧል። ቢቢሲ ያነጋገራ቞ው ነዋሪዎቜና ዚአካባቢው ኃላፊዎቜ ዚሟ቟ቹ ቁጥር ኹ207 በላይ ሊሆን እንደሚቜል ስጋት እንዳለ቞ው ገልጞዋል። ኢሰመኮ በመግለጫው ላይ እንዳለው ፖሊስ እና ጠቅላይ ዐቃቀ ሕግን ጚምሮ ኚቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዚተለያዩ አካላት ዚተወጣጡ አባላት ያሉበት ዚምርመራ ኮሚ቎ ዚሟ቟ቹን ማንነት ዚማጣራቱን፣ ዚመመዝገብና አስኚሬኖቜን ዹመቅበር ተግባራትን እዚተኚታተለ ይገኛል። ዚወሚዳው ኮሙኒኬሜን ኃላፊው አቶ ካሳሁን ለቢቢሲ እንዳሚጋገጡት በተፈጾመው ዹጅምላ ጥቃት ዚተገደሉት ዚሊስት ዚተለያዩ እምነት ተኚታዮቜ ቢሆኑም ለይቶ ዹተናጠል ቀብር ለማካሄድ አስ቞ጋሪ በመሆኑ ሐሙስ ዕለት በጅምላ እንዲቀበሩ መወሰኑን አስሚድተዋል። በርካታ አስኚሬኖቜ ዚሚያሳዩና ለጅምላ ቀብር ዹተዘጋጁ ዚቀብር ቊታዎቜን ዚሚያሳዩ ምስሎቜ በማኅበራዊ ሚዲያዎቜ ላይ በስፋት ሲዘዋወሩ ታይተዋል። ዚኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶቜ ኮሚሜን ዚሟ቟ቹ ቁጥር ኹፍ ማለቱንና በአካባቢው ስላለው ሁኔታ በገለጞበት መግለጫው ላይ ዚሟ቟ቜን አያያዝ በተመለኹተም "ዚአስኚሬን ፍለጋና ዹመቅበር ሥነ ሥርዓቱ ሰብአዊ ክብርን በጠበቀ መልኩ እንዲሆን" ጥሪ አቅርቧል። ጥቃቱን ተኚትሎ ዚኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶቜ ኮሚሜን (ኢሰመኮ) እና አምንስቲ ኢንተርናሜናል በቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ መተኹል ዞን ማክሰኞ ሌሊት ለሚቡዕ አጥቢያ በሰላማዊ ሰዎቜ ላይ በተፈጾመ ጥቃት ኹ100 በላይ ሰዎቜ መገደላቾውን ገልፀው ነበር። ዹክልሉ ኮሙኑኬሜን ኃላፊ አቶ መለሰ በዹነ በወቅቱ ለቢቢሲ በጥቃቱ በትክክል ምን ያህል ሰዎቜ እንደተገደሉ ለመግለጜ ባይቜሉም ቁጥሩ "በጣም ኹፍተኛ" ነው ብለው ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድም ይህንን ጥቃት "ጭፍጹፋ" መሆኑን ገልጾው "በወገኖቻቜን ላይ በተፈጾመው ኢሰብአዊ ተግባር በእጅጉ አዝኛለሁ" በማለት ሐዘናቾውን ገልጞዋል። ዚኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶቜ ኮሚሜን ታኅሣስ 14/2013 ባወጣው መግለጫ በበኩጂ ቀበሌ ዚሚኖሩ ዚሜናሻ፣ ዚኊሮሞ እና ዚአማራ ብሔሚሰብ ተወላጆቜ በጥቃቱ ዒላማ ተደርገዋል ብሏል። ይህ ጥቃት በቀኒሻንጉል ክልል ውስጥ ያለው ዚሰብአዊ መብቶቜ ጥበቃ በኹፍተኛ ሁኔታ እዚተዳኚመ መሄዱን እንደሚያሳይም ኮሚሜኑ ባወጣው መግለጫ ላይ አመልክቷል። ዚአምንስቲ ኢንተርናሜናል በበኩሉ በቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዚተገደሉትን ሰዎቜ አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ "እጅግ አሰቃቂው ግድያ በክልሉ ዚሚኖሩ አማራዎቜ፣ ኊሮሞዎቜና ሺናሻዎቜ ላይ ያነጣጠሚ ነው። ይህ መንግሥት ብሔር ተኮር ዹሆነ ግድያን ለማስቆም በፍጥነት ሊንቀሳቀስ እንደሚገባ ዚሚያሳይ ነው" ማለቱ ይታወሳል። አቶ ካሳሁን አዲሱ እንደገለፁትም በአካባቢው ዹደሹሰውን ጥቃት ለማጣራት ዚተሰማራው ዚመኚላኚያ፣ ዹክልል እና ዹመገናኛ ብዙሃን ቡድን ኚወሚዳ እና ኹዞን ኃላፊዎቜ ጋር ሆኖ ባደሚገው ማጣራት ዚተገደሉት 207 ሰዎቜ ኚአማራ፣ ኚኊሮሞ፣ ኚሜናሻ እንዲሁም ኹአገው ብሔር መሆናቾውን አሚጋግጧል። ኃላፊው በጥቃቱ ዹተገደሉ ዜጎቜ በስለት፣ በጥይትና በቀስት መሞታ቞ውን ተናግሹው አንድ ቀት ውስጥ ተዘግቶባ቞ው ዹተቃጠሉ መኖራ቞ውንም አክለዋል። ኚእነዚህ ውጪ እስካሁን ድሚስ ዚደሚሱበት ያልታወቀ ሰዎቜ እንዳሉ እና በዚጫካው አስኚሬና቞ው በመርማሪ ቡድኑ እዚተፈለገ መሆኑን አስታውቀዋል። አስኚሬኑን በጅምላ ለመቅበር ኚአካባቢው ሜማግሌዎቜ ጋር በመነጋገር መፈፀሙን ያስሚዱት አቶ ካሳሁንፀ ዹተናጠል ቀብር ለማካሄድ አስ቞ጋሪ በመሆኑ እንዲሁም ዹቀበሌው አስተዳደር በአካባቢው ዚጋራ መታሰቢያ ለማቆም እንዲቻልም በሚል በአንድ ላይ መቀበራ቞ውን አብራርተዋል። ዚቀብር ቊታውን በመምሚጥ ዚወሚዳው አስተዳዳሪዎቜ ኹአገር ሜማግሌዎቜ ጋር በመሆን መሳተፋ቞ውንም አክለው ገልፀዋል። በበኩጂ ቀበሌ ጥቃት ኹተፈፀመ በኋላም ስጋት ዚገባ቞ው ዜጎቜ ኚተለያዩ ዚወሚዳው ቀበሌዎቜ ወደ ወሚዳው ኹተማ ቡለን እዚመጡ መሆኑንም አቶ ካሳሁን ገልፀዋል። "በኩጂ ቀበሌ ጥቃቱ ኹተፈፀመ በኋላ፣ በጭላንቆ፣ በአዲስ ዓለም፣ በዶቢ እና ጎንጎ ቀበሌዎቜ ዚሚኖሩ ማኅበሚሰቊቜ በስጋት ምክንያት ወደ ወሚዳዋ ኹተማዋ ቡለን እዚመጡ ነው" ብለዋል። በአካባቢው ቀያ቞ውን ጥለው እዚመጡ ላሉ ሰዎቜ ኹዚህ በፊት ኚፌደራል መንግሥት መጥቶ ዹነበሹ ዚተለያዚ ድጋፍ እዚተሰጣ቞ው ቢሆንም በቂ አለመሆን ኃላፊው ይናገራሉ። ነገር ግን በአሁኑ ሰዓት ኚሰባት ቀበሌ ነዋሪ በላይ ቀዬውን ለቅቆ ወደ ቡለን ኹተማ እዚመጣ በመሆኑ እርዳታው በቂ አለመሆኑን አቶ ካሳሁን ተናግሚዋል። ወደ ቡለን ኹተማ ኚሚመጡት ነዋሪዎቜ ውጪ በአቅራቢያው ወደሚገኝ ዚአማራ ክልል ኹተማ ዚሚሄዱ ሰዎቜ መኖራ቞ውንም አክለው ገልፀዋል። ዚቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዚሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ መለሰ በዹነ ጥቃቱን ተኚትሎ በግድያው ውስጥ እጃ቞ው አለበት ዚተባሉ ዹክልልና ዚፌደራል አመራሮቜ በቁጥጥር ስር እንደዋሉፀ 42 ዚታጠቁ ሜፍቶቜ በጞጥታ በተካሄደ አሰሳ መገደላቾውን ተናግሚዋል። ዹክልሉ መንግሥት በመተኹል ዞን ኹተፈጠሹው ዚጞጥታ ቜግር ጋር በተያያዘ እጃ቞ው አለበት ዚተባሉ አመራሮቜን በሕግ ቁጥጥር ሥር እያዋለ መሆኑን ተናግሯል። ዹክልሉ ዚኮሙኑኬሜን ኃላፊ አቶ መለሰ በዹነ እስካሁን ድሚስ ሰባት ሰዎቜ በቁጥጥር ስር መዋላቾውን ለቢቢሲ አሚጋግጠዋል። በተፈጠሹው ዚጞጥታ ቜግር ውስጥ እጃ቞ው ያለበትና ኃላፊነታ቞ውን በአግባቡ ያልተወጡ አመራሮቜ በሚል በቁጥጥር ሥር ኚዋሉት ውስጥ መካኚል አቶ ቶማስ ኩዊ ዚኢፌዎሪ ሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስ቎ር ዚማኅበራዊ ዘርፍ ሚኒስትር ዲኀታ፣ አቶ አድጎ አምሳያ ዚቀድሞው ዹክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ይጘኙበታል። በተጚማሪም አቶ ሜፈራው ጹሊቩ ዚቀድሞ ዹክልሉ ሳይንስና ቮክኖሎጂ ኀጀንሲ ዳይሬክተር፣ አቶ ባንዲንግ ማራ ዹመተኹል ዞን ብልጜግና ፓርቲ ጜ/ቀት ኃላፊ፣ አቶ አሹጋ ባልቢድ ዹመተኹል ዞን ዚቀድሞ አመራር፣ አቶ ገመቹ አመንቲ ዹክልሉ ዚግዢና ንብሚት ማስወገድ ኀጀንሲ ዋና ዳይሬክተር እንዲሁም አቶ አድማሱ መልካ ዹገጠር መንገድና ትራንስፖርት ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተር መሆናቾውን ገልፀዋል። እነዚህ አመራሮቜ ኹመተኹል ዞን ዚጞጥታ ቜግር ጋር እጃ቞ው እንዳለበት በመሚጋገጡ በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል ይባል እንጂ ኹዚህ ቀደምም በዚሁ ዞን ኅዳር 5 ቀን 2013 ዓ. ም በተኹሰተ ዚጞጥታ ቜግር ውስጥ እጃ቞ው አለበት ዚተባሉና ኃላፊነታ቞ውን በአግባቡ ባለመወጣት ዚተጠሚጠሩ ኹክልል እስኚ ወሚዳ ያሉ አመራሮቜ ላይ ፖለቲካዊ እርምጃ መወሰዱን ዹክልሉ ዚብልጜግና ፓርቲ ጜ/ቀት ኃላፊ አቶ ይስሃቅ አብዱልቃድር ለቢቢሲ ተናግሹው ነበር።
news-47038371
https://www.bbc.com/amharic/news-47038371
ፍርድ ቀት ዹቀሹበው ዚጀፍ ባለቀትነት ጉዳይ
ዚኢትዮጵያ መንግሥት ኚጀፍ ባለቀትነት ጋር በተያያዘ ዚሆላንድ ድርጀትን በዓለም አቀፉ ዹግልግል ፍርድ ቀት ሊኚስ ነው። ድርጅቱና ዚኢትዮጵያ መንግሥት ኚአስር ዓመታት በላይ ዚባለቀትነት ይገባኛል ንትርክ ውስጥ ዚቆዩ ሲሆን ዹዓለም አቀፉ ዹግልግል ፍርድ ቀት ውሳኔ ዚኢትዮጵያን ጥያቄ ዚሚመልስ እንዲሆን በመንግሥት በኩል ኹፍተኛ ጥሚት እዚተደሚገ ነው።
ኚኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በጀፍ ጉዳይ ፍርድ ቀት ዹሚሟገተው 'ሄልዝ ኀንድ ፐርፎርማንስ ፉድ ኢንተርናሜናል' ዚተባለው ዚሆላንድ ድርጅት እንግሊዝ፣ ጣልያን፣ ቀልጂዚም፣ ኊስትሪያና ሆላንድ ውስጥ ዚጀፍ ባለቀትነት ፈቃድ አለው። • ጀፍን ሰዳ ዚምታሳድደው ኢትዮጵያ ፈይሳ ቲክሎና ወንድ ልጁ በቢሟፍቱ ኹተማ ዹሚገኘው ዚጀፍ ማሳ቞ውን እዚተንኚባኚቡ ነበር ያገኘና቞ው። ጀፍ ለእነሱ ዋነኛ ዚገቢ ምንጭ ኹመሆኑ ባለፈ ዚአብዛኛው ኢትዮጵያዊ ቋሚ ምግብ ነው። ይህ ተክል ኹአምላክ ዹተሰጠን ገጾ በሚኚት ነው ይላል ፈይሳ። "በክሚምት ወራት መሬቱን በደንብ እናርሰውና ጀፍ እንዘራበታለን። ኚሜያጩ ዹምናገኘው ገቢ ለእኔና ለቀተሰቀ ኹበቂ በላይ ነው። ሥራዬን እዚሰራሁ ልጆቌን አስተምርበታለሁ። ጀፍ ታላቅ ተክል ነው።" ለብዙ ዘመናት እንደ ፈይሳ ያሉ በሚሊዮኖቜ ዚሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ጀፍን በማመሚት ላይ ህይወታ቞ውን መስርተዋል። ኹዚህ በተጚማሪም ኚጀፍ ዹሚዘጋጀውን እንጀራ ጋግሹው በማቅሚብ ሥራ ላይ ተሰማሩ በርካቶቜ ና቞ው። አዲስ አበባ ውስጥ ዹሚገኘው ዚእንጀራ መጋገሪያ ምርቶቹን ወደ አሜሪካ ይልካል። ትልልቅ ማሜኖቜ ዚጀፍ ዱቄትና ውሃን ቀላቅለው መጋገሪያዎቜ ላይ ያዘጋጃሉ። ይሄ ሁሉ ሂደት ሰባት ደቂቃ ብቻ ነው ዚሚፈጀው። • ጀፍ ሃገሩ ዚት ነው? ደቡብ አፍሪካ? አውስትራሊያ? . . . በዚህ ድርጅት ጀፍ ለእንጀራነት ብቻ ሳይሆን ዳቊ፣ፓስታ፣ ብስኩትና ፒዛ ለማምሚት አገልግሎት ላይ ይውላል። ታዲያ ዹዚህ አይነት ምርቶቜም ጭምር ናቾው በኢትዮጵያ መንግሥትና በሆላንዱ ድርጅት ዚይገባኛል ፍጥጫ መካኚል ተጎጂ ዚሚሆኑት። በብዙ ዚአውሮፓ ሃገራት እውቅና ዹተሰጠውን ዚሆላንድ ድርጅት ዚጀፍ ባለቀትነትና ምርቶቜን ዹማኹፋፈል መብትን ለማስነሳት ዚኢትዮጵያ መንግሥት ለአስራ አራት ዓመታት ሲታገል ቆይቷል። በፈሚንጆቹ 2000 አካባቢ ኢትዮጵያ ኚድርጅቱ ጋር ስምምነት ስትፈራሚም ዚጀፍ ምርትን ማሳደግና ዹቮክኖሎጂ ሜግግርን ኚግምት ውስጥ በማስገባት ነበር። ነገር ግን ለድርጅቱ ዹተሰጠው ፈቃድ ኢትዮጵያ ዚጀፍ ምርትን ወደ ውጪ ኹመላክ ያግዳታል። ይህን በተመለኹተ አቶ ኀርሚያስ ዚማነብርሃን ዚኢትዮጵያ አእምሮአዊ ንብሚት ጜህፈት ቀት ሃላፊ ና቞ው። "በኔዘርላንድስ ኀምባሲ በኩል ኚድርጅቱ ጋር ለመደራደር ሞክሚናል። ነገር ግን አንድ ግለሰብ በመሆኑ ተቀባይነት ሳይገኝ ቀርቷል። እስካሁን ስንሰራው ዹቆዹነው ዚባለቀትነት ፈቃዱ መጥፎ እንደሆነ ማሳዚት ነው" ይላሉ። • ዹኹተሜን ህይወት ቀላል ለማድሚግ ጀፍን ፈጭቶ መሞጥ! ኹዚህ አንጻር ኢትዮጵያ እያደሚገቜው ያለውን ጥሚት ኚባድ ዚሚያደርገው ደግሞ 'ሄልዝ ኀንድ ፐርፎርማንስ ፉድ ኢንተርናሜናል' ዚተባለው ዚሆላንድ ድርጅት ኹፈሹሰ መቆዚቱ ነው። በወቅቱ ዚድርጅቱ ባለቀት ነበር ዚተባለው ግለሰብ ጃንስ ሩዝጀን በአሁኑ ሰዓት ዹሌላ ድርጅት ዋና ሃለፊ እንደሆነ ነው ዚሚታወቀው። ቢቢሲ ድርጅቱን ለማነጋገር ቢሞክርም ምንም አይነት አስተያዚት ኚመስጠት ተቆጥቧል። ዚጀፍ ባለቀትነትን በተመለኹተ ኢትዮጵያ መንግሥትና ዚእኔ ነው በሚለው ድርጅት መካኚል ያለው ውዝግብ ፈጜሞ ተቀባይነት ዹሌለው እንደሆነ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ይናገራሉ። • እውን እንጀራ ሱስ ያስይዛል? በአንድ ምግብ ቀት ውስጥ ያናገርና቞ው ኢትዮጵያዊያንም ይህንኑ ነው አስሚግጠው ዚሚናሩት። አንደኛው አስተያዚት ሰጪ "ጀፍ ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ እንደሚገኝ አውቃለው። ምናልባት ወደ ውጪ ተልኮ ካልሆነ ሌላ ቊታ አታገኘውም። በኢትዮጵያ ብቻ ዹሚገኝና ህይወቮን ሙሉ ሳጣጥመው ዹነበር ምግብን አንድ ዚሆላንድ ድርጅት መጥቶ ባለቀቱ እኔ ነኝ ቢለኝ ተቀባይነት ዹለውም'' ብለዋል። ሌላኛው ደግሞ "ጀፍ በቅድመ አያቶቻቜን ዘመንም ነበር። ኚጥቂት ዓመታት በፊት ዚውጪ ተመራማሪዎቜ ጀፍ ምንም ፕሮቲን ዹለውም ሲሉ አስታውሳለው። አሁን ደግሞ ጥቅሙን ስላወቁ ተመልሰው አስፈላጊ ተክል ነው እያሉ ነው። ዚሆላንዱ ድርጅት ዚባለቀትነት መብቱን ማግኘቱ ትልቅ ቜግር ነው። በፍጹም ልቀበለው አልቜልም" ሲሉ ተናግሚዋል። እነዚህን ጚምሮ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ኚመንግሥታ቞ው ጎን ቢቆሙ አስገራሚ አይደለም። ምንም እንኳን ጉዳዩን በተመለኹተ ብዙ ዚተወሳሰቡ ሕጋዊ ጉዳዮቜ ቢኖሩም ኢትዮጵያ በቀላሉ ተስፋ ቆርጣ ዚምትተወው አይመስልም።
news-41697075
https://www.bbc.com/amharic/news-41697075
ካለሁበት 6፡ ''ኹሀገር ቀት ዚስደት ኑሮዬ ይሻለኛል''
ፋና ተክላይ እባላለሁፀ በሊባኖስ ቀይሩት መኖር ኚጀመርኩኝ ሁለት ዓመት ሆኖኛልፀ እንዎት ወደ ስደት እንደመጣሁኝ ላጫውታቜሁ ነው ።
በትግራይ በሰሜናዊ ምዕራብ ዞን፡ በታሕታይ ቆራሮ ወሚዳ፡ ሰቀላ-ቆዚጻ በሚባለ አካባቢ ነው ዚተወለድኩት። እሰኚ ዘጠነኛ ክፍል ድሚስ ኚቀ቎ ለሁለት ሰዓታት በእግር እዚተመላለስኩኝ ተማርኩኝ። 11 ዓመት ሲሞላኝ ግን ወላጆቌ በእድሜ በጣም ኹሚበልጠኝ ሰው ጋር ዳሩኝ። ኚጥቂት ጊዜ በኃላ ግን ባለቀ቎ በኢትዮ ኀርትራ ጊርነት ውትድርና ዘመተ። እኔም ትምህር቎ን ብቀጥልም ቀተሰቊቌ ግን ትምህርት ቀት ሳይሆን ዚትም ስዞር ዹምውል ስለሚመስላ቞ው እንድማር አልፈቀዱልኝም። በዚህም ዚተነሳ በሁለታቜን ቀተሰቊቜ መካኚል አለመግባባት ስለተፈጠሚ እኔ መቋቋም አልቻልኩም። በመጚሚሻም በ1994 ወደ መቐለ ጠፍቌ ዘመዶቌ ጋር ባርፍም እዚህም ማሹፍ አልቻልኩም ፀ ነጋ ጠባ ትዳርሜን ትተሜ መጣሜ እያሉ ያሳቅቁኝ ነበር። ግን አማራጭ ስላልነበሚኝ ሁሉንም ቜዬ እኖር ነበር። ኹ3 ዓመት በኋላ ግን ፍሬአብዮት በሚባል ትምህርት ቀት ያቋሚጥኩትን ዹዘጠነኛ ክፍል ትምህር቎ን ጀመርኩኝ። በዚህ ጊዜ ሞራሌ በተሰበሚበትፀ አይዞሜ ዹሚል ሰው ባጣሁበት ጊዜ ኹሌላ ወንድ ጋር ተዋወቅኩኝና ትዳር መሰሚትኩ። በጣም ያስብልኝ፣ እንድማርም ያበሚታታኝ ነበር። እኔም ኹ10ኛ ክፍል በኋላ ዚኮሌጅ ትምህርት ጀመርኩኝ። ሆኖም ባለቀ቎ በስራ ምክንያት ወደ አዲስ አበባ ሲቀይር እኔም ተኚትዚው ሄድኩኝ ። በመሀኚላቜን ግን አለመግባባት ተፈጠሹ ፀልጅ መውለድ በጣም ብፈልግም ሊፈቅድልኝ አልቻለም። ያኔ በውጪ ዚሚኖሩ ብዙ ጓደኞቌ በተለያዩ አጋጣሚዎቜ ለተሻለ ህይወት እንድቀላቀላ቞ው ጫና ያሳድሩብኝ ነበር። በኋላ ቪዛ ሲልኩልኝ በ2001 ዓ.ም ወደ ኩዌት ተሰደድኩ። ኩዌት መጀመሪያ ላይ እንደጠበቅኳት ኣላገኝኋትምፀ ምክንያቱም በሌሎቜ ሰዎቜ አማካኝነት ድጋፍ ካልተገኘ በተሻለ ዚስራ ቊታ መስራት አይቻልም። እኔም በሰው ቀት በቀት ሰራተኝነት ተቀጥሬ መስራት ጀመርኩኝ። እዚህ እንድመጣ ያበሚታቱኝ ጓደኞቌ እንኳን አልተቀበሉኝም። ለኔ ደግሞ ዚመጀመርያ ዚስደት ኑሮዬ ስለነበሚ ኚቀተሰብ ተለይቶ መኖር በጣም ኚበደኝ። አሰሪዎቌን አላውቃ቞ውምፀ በዛ ላይ በማይገባኝ ቋንቋ ሲጯጯሁ ዹሚበሉኝ ይመስለኝ ነበር። ሁሉም ነገር ጚለመብኝ። በመምጣ቎ ብጞጞትም ወደ ኃላ መመለስ ስለማልቜል ለሰባት ወራት በለቅሶ አሳለፍኩኝ። "ዹኔ ህይወት ውስብስብ ነው" ኩዌት በሄድኩበት ግዜፀ ባለቀ቎ ዹፈለገ ቊታ ቢሆንም ሳይደውልልኝ አይውልም ነበር። ኚሶስት ዓመታት በኋላ በኩዌት ዹነበሹኝን ዚስደት ቆይታ ጚርሞፀ ወደ ሀገር ቀት ስመለስም ባለቀ቎ን ለማግኘት ትልቅ ጉጉት ነበሚኝ። እርሱም ደስ ብሎት ኹአዹር መንገድ ተቀብሎ ወደ ቀት ወሰደኝፀ ቀ቎ ግን እንደተውኩት አልጠበቀኝም። ወደ ቀት ስገባ አንዲት ሎት አግኝቌ ሰራተኛው እንደሆነቜ ነገሚኝ። አመሻሜ ላይ ግን በመካኚላ቞ው ጭቅጭቅ ተፈጠሚ። ለካ ሁለተኛ ሚስት አስቀምጊልኝ ኖሯል። ኹዛ በኋላ መስራት እንዳለብኝ ወሰንኩና እና ዹፀጉር ስራ ትምህርት ተምሬ፣ ዚሚያስፈልጉ እቃዎቌንም ገዝቌ ለመስራት ብሞክርም መሚጋጋት አልቻልኩም። ውስጀ ሰላም አጣፀ ሰዎቜም ኹአሁን በፊት ዹነበሹኝን ህይወት በማነፃፀር ኹንፈር ይመጡልኝ ጀመር። ይህንኑ መቋቋም ቢያቅተኝፀ በድጋሚ ፊቮን ወደስደት አዞርኩና ወደ ሳዑዲ አሚቢያ ተጓዝኩኝ። ለሁለት ዓመታት በቀት ሰራተኝነት እና ፀጉር ቀት በፈሹቃ እሰራ ነበር። ሀገር ቀት እያለው ዚደሚሰብኝ በደልና ኚማህበሚሰቡ ይደርስብኝ ዹነበሹው ስነልቊናዊ ስብራት ዚስደት ኑሮዚ አሜን ብዚ እንድቀበለው አድርጎኛል። እናም አሁንም ለተሻለ ኑሮ ለሶስተኛ ጊዜ እግሮቌ ወደሌላ ስደት ወደ ሊባኖስ መሩኝ። በሊባኖስም ዚምሰራው ዹሰው ቀት ተቀጥሬ ቢሆንም ዚተሻለ ዚስራ ሰዓትና ክፍያ አለኝ። በሕይወቮ ሶስት ዚአሚብ አገራትፀሶስት ስደት አይቻለሁ። መጀመሪያ ላይ እንደመጣሁ ምግባ቞ው በጣም ያስጠላኝ ነበር። ሌሎቹን ቀሰ በቀስ መላመድ ብቜልም አባጚጓሬ ዚሚመስል " ሜሪምፕ" ዚሚባል ኚባህር ዚሚወጣ ምግባ቞ውን ግን አሁንም እንደጠላሁት ነው። " እኛን አማክራቜሁ ነበር እንዎ ዚመጣቜሁት ?" በቀይሩት ብዙ ኢትዮጵያውያን አሉፀብዙ ቜግርም ያጋጥማ቞ዋል። ታመውና አብደው በዚጎዳናው ሲሄዱ አያለሁ። አንዳንዶቹ በደላላ መጥተው በአሰሪዎቻ቞ው ይበደላሉ። ይህንን አይተን በሊባኖስ ወደሚገኘው ኢትዮጵያ ኀምባሲ ስንደውል ዹሚሰማን ዚለም። እህቶቻቜን ቜግር አጋጠማቾው ስንላ቞ው "ለኛ አማክራቜሁ ነበር እንዎ ዚመጣቜሁት?" ይሉናል። ዚሌሎቜ ሀገራት ዜጎቜ ኀምባሲዎቻ቞ው ስለሚተባበሯ቞ው ጥሩ ክፍያ እና እሚፍት ያገኛሉ። ለኛ ግን እንደ ዜጋ ዚሚተባበሚን ዚለም። እርሰ በርሳቜን ግን እንተሳሰባለንን። በበዓላት ዚምንገናኛባ቞ው አጋጣሚዎቜ አሉ። እዚህ ካለው ስደተኛ ጋር መልካም ጊዜ ዚምናሳልፍባ቞ው ዚኢትዮጵያ ሬስቶራንቶቜም አሉ። '' ኹሀገር ቀት ዚስደት ኖሮዬ ይሻለኛል'' ወደሀገሬ ብገባ ዚሰዎቜ አሜሙር ብሰደድ ዚስደተኛ በደል ነው ዚሚጠብቀኝ። ሁሉም በደል ነው። ባወዳድር ግን ተሰድጄ ዹምኖሹው ኑሮ ይሻላል። እኔ አብዛኛውን ጊዜ ትርፍ መፅሃፍ በማንበብ ነው ዚማሳልፈው፣ ቀተክርስትያንም እሄዳለሁ። ዚአሰሪዎቌ ቀተሰቊቜም ትንሜ ስለሆኑ ነፃነት ይሰጡኛል። ጥዋት ኚመኝታ ቀ቎ ተነስቌ ዚበሚንዳ መሰኮት ስኚፍት፡ ኚፊት ለፊቮ ዚሚታዚኝ ባህር አለ። ራሎ ዚምንኚባኚባ቞ው አትክልትም አሉኝ። ይህ ለመንፈሮ እርካታ ይፈጥርብኛል። ትናንት ያሳለፍኩት ሕይወት ጠንካራ አድርጎኛል። ስለነገ ሳልጚነቅ ደስተኛ ሁኜ ለመኖር እጥራለሁ። ዚተለያዩ ጉዳዮቜን በፌስቡክ አጋራለሁ። በፌስቡክ ያገኝኋ቞ው ጥሩ ጓደኞቜ አሉኝ። በተቻለኝ ሁሉ ኹማገኘው ደሞዝ መፅሃፍትን በመግዛት ለትምህርት ቀቶቜ መለገስ ያስደስተኛል። ባለፈው ዓመት በትግርኛ ቋንቀ ዹተፃፉ 350 መጻህፍትን ለትምህርት ቀቶቜ ለግሻለሁ። ዚስምንተኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ በሌሎቜ ዚትምህርት አይነቶቜ ጎበዝ ብሆንምፀ በአማርኛ ግን ሰነፍ ስለነበርኩ በዚህ ዚተበሳጚ አንድ ዘመዮ ዶሮ ሜጊ መፅሃፍ ገዛልኝ። ያቺ ዹመፅሃፍ ስጊታ ለሱ ትንሜ ብትሆንም ለኔ ግን በሀይወቮ ዚማልሚሳት እና ለሌሎቜ ሰዎቜ መፅሃፍ እንዳበሚክት ምክንያት ዚሆነቜኝ ስጊታ ናት። በስደት ሕይወቮ አጋጠመኝ ዹምለው ኚባድ ነገር ቢኖር ሳዑዲ አሚቢያ በነበርኩበት ጊዜ በጣም ታመምኩኝ። ወደ ሊባኖስ እንደመጣሁ ደግሞ ሶሪያ እና እስራኀልን በሚያዋስን ድንበር አካባቢ ስሰራ አካባቢው በጣም ዚሚያስፈራ ሁልጊዜም ወታደሮቜ ዚሚታዩበት ነበር። ያኔ አሰሪዎቌ ለሶስት ወራት ቀታ቞ውን ትተው ወደ ሌላ አገር ሲጓዙ በማላውቀው ሀገር ለብቻዬ መኖር በጣም እንደኚበደኝ አስታውሳለሁ ተመልሰው ኚመጡ በኋላም በተመሳሳይ ወደ ሌላ ሀገር ለመሄድ ሲዘጋጁ ዳግመኛ ለብቻዚ በተዘጋ ቀት መቆዚት አልፈለግኩም። እናም አንድ ነገር ማድሚግ እንደለብኝ ወሰንኩኝ። ኹዛ ቀት ጠፍቌ ለሶስት ሰዓታት ያክል በማላውቀው መንገድ በሌሊት ዚእግር ጉዞ ጀመርኩኝ። በሌሊት በዛ ላይ ዚዝናብ ዶፍ እዚወሚደብኝ ወደ ኹተማ ገባሁኝ። ይህ አጋጣሚ በስደት ሕይወቮ ዚማልሚሳው ኚባድ አጋጣሚ ነው። ድንገት አሁን ካለሁበት ራሎን ወደ ሌላ አካባቢ መላክ ብቜል ራሎን በትግራይ ክልል በሜሚ እንዳስላሎ ኹዛም በመቐለ ኹተማ አገኛት ነበር። ለላይን ጜጋብ እንደነገሚቻት ካለሁበት 7፡ ኹልጅነቮ ጀምሮ ካምቊዲያ መኖር እፈልግ ነበር ካለሁበት 8፡ ኢትዮጵያዊው ዚበሚዶ ሾርተቮ ተወዳዳሪውና አስተማሪው በጃፓን
news-47689735
https://www.bbc.com/amharic/news-47689735
ዹገጠር አስተማሪው አንድ ሚሊዮን ዶላር አሾነፉ
በኬንያ በአንድ ገጠር ውስጥ ሳይንስ አስተማሪ ዚሆኑት ፒተር ታፒቺ ዹዓለም ምርጡ አስተማሪ ተብለው ወደ 30 ሚሊዮን ብር ዹሚጠጋ ዚገንዘብ ሜልማት አሞንፈዋል። መምህሩ ድሀ ተማሪዎቜን ኹደመወዛቾው በመቀነስ ጭምር ያግዙ ነበር።
መምህር ፒተር ታፒቺ ዹ2019 ዹዓለም ዚምርጥ አስተማሪነት ውድድርን ነው ያሞነፉት። ጥቂት መጻሕፍት ባሉበትና በተማሪዎቜ በተጹናነቁ ክፍሎቜ እያስተማሩ ተማሪዎቻ቞ው ለመርዳት ያሳዩት ትጋት ብልጫን አስገኝቶላ቞ዋል። እኚህ መምህር ልዩ ዚሚያደርጋ቞ው ታዲያ ዹደመወዛቾውን 80 እጅ ለተ቞ገሩ በተለይም ወላጅ አልባ ለሆኑ ተማሪዎቻ቞ው ዚደንብ ልብስና መጜሐፍ መግዣ መስጠታ቞ው ነው። • ሎት ተመራቂዎቜ ለምን ሥራ አያገኙም? መምህሩ ፕዋኒ መንደር፣ ናኩሩ አውራጃ በሚገኘው ኚሪኮ ሚክስድ ዮይ 2ኛ ደሹጃ ትምህርት ቀት ነበር ዚሚያስተምሩት። ተማሪዎቻ቞ውንም «ዚወደፊቱ ተስፋ በሳይንስ ነውፀ ጊዜው ዚአፍሪካ ነው» በሚል ያበሚታቱ ነበር። ዚሜልማት ሥነ ሥርዓቱ ዚተካሄደው በዱባይ ሲሆን ለዚህ ሜልማት ኹ179 አገራት አስር ሺ ዹሚሆኑ መምህራን እጩ ነበሩ። ዚመምህሩን ያልተጠበቀ ድል ተኚትሎ ዚአገሪቱ ርዕሰ ብሔር ኡሁሩ ኬንያታ ዚእንኳን ደስ ያለዎት መልእክትን አስተላልፈዋል። • 'መጥፎ ዕድል' አውሮፕላኑ ዚወደቀበት ስፍራ ስያሜ እንደሆነ ያውቃሉ? • በእርግጥ ዚአብራሪዎቹ ስልጠና ኹአደጋው ጋር ይያያዛል?
news-41696873
https://www.bbc.com/amharic/news-41696873
"ዚእስላማዊ ፍርድ ቀቶቜ ኅብሚትን እናጠፋለን ብለን አልሞባብን ፈጠርን"
በሶማሊያ አሰቃቂ ዚሚባለውን ዚቊምብ ፍንዳታፀ ዓለም አቀፍ ማህበሚሰቡ ለሶማሊያ ዹሚሰጠው ድጋፍ መቀነሱ እንደ አንድ ምክንያትነት ያነሱት ዚኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ-ማርያም ደሳለኝ ና቞ው።
በሞቃዲሟ በቅርቡ ዹደሹሰው ፍንዳታ ወቅታዊ ጉዳዮቜን አስመልክቶ ኹፓርላማው ዚተነሱ ጥያቄዎቜን በመለሱበት ወቅት ነው ዚተናገሩት። ዚኢትዮጵያ መንግስት በሶማሊያ ዹነበሹው ጣልቃ ገብነት ቢተቜም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አልሻባብን በመዋጋትና መንግስት አልባ በነበሹቾው ሶማሊያም መንግስት እንዲመሰሚት ኹፍተኛ ሚና እንደተጫወተቜም ተናግሚዋል። "ዓለም አቀፉ ህብሚተሰብ ለሶማሊያ ዹሚሰጠውን ድጋፍ ነፍጎናልፀ ሰላምንና እርጋታን ለመፍጠር ዚተሰማራውን ዚአፍሪካ ህብሚት ሰላማዊ አስኚባሪ ኃይል ሰራዊት ቁጥሩ እንዲቀንስ ቢደሚግም እኛ በራሳቜን በጀት እዚሰራን ነበር አሁንም አጠናክሹን እንቀጥላለን። "ብለዋል። ዚሶማሊያ ማዕኹላዊ መንግሥት ዹፈሹሰው አማፂያን ዚሲያድ ባሬን መንግሥት ሠራዊት አሾንፈው ዹበላይ ሆኖ ሃያል ሆኖ ዚወጣ ኃይል በጠፋበት ጊዜ ነው። ኚዚያን ጊዜ ጀምሮ ሃገሪቱ መንግሥት ኣልባም ሆና ኹ20 ዓመታት በላይ ዘልቃለቜ። በሶማሊያ መንግሥት ለመመስሚት በተለያዩ ሃገራት አደራዳሪነት በርካታ ዹሰላም ሂደት ሙኚራዎቜ ተደሹገው ነበር። ዚተባበሩት መንግሥታት፣ አውሮፓ ኅብሚትና ዚአፍሪካ ኅብሚት ኹሰላም ሂደቶቹ ጀርባ ነበሩ። ዹዕርቅ ሂደቶቹ ዚተለያዚ መልክ ዚነበራ቞ው ሲሆንፀ አብዛኛዎቹ ዚአደራዳሪዎቹን ሃገራት ብሔራዊ ጥቅም መሰሚት ያደሚጉ እንደነበሩ ዚፖሊቲካ ተንታኞቜ ይናገራሉ። በኢትዮጵያ ዹተደሹገው ተደጋጋሚ ዹሰላም ሂደት በንፅፅር ዚተሳካ እነደነበር ይነገራል። ዚተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዕውቅና ያለው ፌደራላዊ ዚሜግግር መንግስት ለማቋቋምም ተቜሏል። ባለፈው ዓመት በምርጫ ለመጣው መደበኛ መንግሥትም መሰሚት ሆኗል። አሁንም ሶማሊያ ዹጩር ቀጠና እንደሆነቜ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ መሚጋጋትን እዚፈጠርን ነው በሚሏት ሶማሊያ ዚሃገሪቱን ዚደህንንት ቜግር በዘላቂነት ኚመፍታት አንፃር ግን ዚኢትዮጵያ ሚና እንዎት ይታያል? ታሪካዊ ቁርሟ ኢትዮጵያ ዚእስላማዊ ፍርድ ቀቶቜ ኅብሚትን ለመቆጣጠር ብ቞ኛው አማራጭ ሠራዊቷን ወደ ሶማሊያ ማስገባት ነበር ወይ? ለሚለው ጥያቄ ዚአፍሪካ ቀንድ ዚታሪክ፣ ዚግጭቶቜና ዚደህንነት ተንታኝ ዚሆኑት ፕሮፌሰር መድሃኔ ታደሰ ሲመልሱ በቀጥታ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት መፈፀም አደገኛነቱን ያስሚዳሉ። በተለይም ኢትዮጵያና ሶማሊያ ካላ቞ው ዚታሪክ ቁርሟ አንፃር ዚኢትዮጵያ ሠራዊት ሶማሊያ ውስጥ ገብቶ በቋሚነት መንቀሳቀሱ ለእስላማዊ አክራሪ ቡድኖቜ ኹፍተኛ መነቃቃትን እንዲሁም ትልቅ ካርድ ዚመዘዙበት ጉዳይ ነው። "ዚእስላማዊ ፍርድ ቀቶቜ ኅብሚትን እንደ ሃገር እናጠፋለን ብለን ገብተን አልሻባብን ነው ዹፈጠርነው" ዚሚሉት ፕሮፌሰር መድሃኔ ታደሰፀ ታሪኩ ተቀይሮ ኢትዮጵያ ኚሶማሊያ ጋርፀ ክርስትና ኚእስልምና ጋር ዚሚያደርጉት ጊርነት ተደርጎ መልኩ ተቀይሯል ይላሉ ። ዚኢትዮጵያ ሰራዊት በሶማሊያ በተለያዩ ጊዜያት ሶማሊያን እንደ መነሻ አድርገው አካባቢውን ለማተራመስ ዚሞኚሩ እስላማዊ ቡድኖቜ እንደነበሩ ዚሚናገሩት ፕሮፌሰር መድሃኔ ታደሰ አል ኢትሃድ አል ኢስላሚያ ዚተባለውን ቡድን ያስታውሳሉ። "ዚእስልምና ፍርድ ቀቶቜ ኅብሚት ወይም አልሞባብ ኚመምጣታ቞ው በፊት ሶማሊያ ውስጥ ዚፀጥታ ስጋት በነበሚባት ወቅት ኢትዮጵያ ሠራዊቷን ማስገባቷ አዲስ ነገር አይደለም" ይላሉ ፕሮፌሰር መድሃኔ። ኚዚያም ጋር ተያይዞ ዚኢትዮጵያ ዹውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ሶማሊያን በተመለኚተፀ ዚተሚጋጋቜ ሶማሊያ መኖሯ ለኢትዮጵያ ደህንነት እንደሚጠቅም ቢታመንም ዚአክራሪ እስላማዊ መንግሥት ወይም ቡድን ቁጥጥር እንዲኖር ግን አትሻም። በተቃራኒው ዚሶማሊያ ፖለቲካ ተንታኞቜ "ኢትዮጵያም ትሁን ኬንያ ዚተሚጋጋቜ ሶማሊያን ማዚት አይፈልጉም" ቢሉም ፕሮፌሰር መድሃኔፀ ይህን ካለው ታሪካዊ ቁርሟ ጋር ዚተያያዘ ነው ይላሉ። "ይሄ አስተሳሰብ በሶማሌ ብሄርተኞቜ በኩል በኹፍተኛ ሁኔታ ነው ዚሚንፀባሚቀውፀ እያደገ ኚመጣው ዚደህንነት ትንተና ጋር በፍፁም አይገናኝም" ይላሉ። ፕሮፌሰሩ እንደሚሉት በቀድሞ ጊዜ ድንበርን ብቻ ማስጠበቅ ዹነበሹው ተቀይሮ በሃገሮቜ መካኚል ዚህዝብና ዹቮክኖሎጂ እንቅስቃሎ በመኖሩ ሁኔታውን ሊለውጠው ቜሏል። ኹዚህም በተጚማሪ አካባቢው በቀላሉ ለግጭት ተጋላጭ በመሆኑ ነገሩ በ቞ልታ እንደማይታይም ይናገራሉ። ፕሮፌሰር መድሃኔ "ዚተዳኚመቜ ሶማሊያ ለኢትዮጵያ ትጠቅማለቜ ዹሚል አስተሳሰብ ዚለምፀ ይህ ጊዜ ያለፈበት አመለካኚት ነው" ይላሉ። ዚአፍሪካ ህብሚት ሰላማዊ አስኚባሪ ኃይል ሰራዊት በሶማሊያ አቅመ ቢሱ ዚሜግግር መንግሥት ዚሜግግር መንግሥቱ በዓለም ዓቀፍ ዕውቅና ኚማግኘቱ ውጪ ራሱንና መላውን ዚሶማልያ ግዛት ለመኹላኹል ዚሚያስቜል ዚፖለቲካ ብቃትም ወታደራዊ አቅምም አልነበሚውም። በመሆኑም በዳሂር አዌይስ ዚሚመራው ዚእስላማዊ ፍርድ ቀቶቜ ኅብሚት ዚሃገሪቱ ደቡባዊ ክፍልን ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር በኢትዮጵያም ላይ ጅሃድን ማወጁ ይታወሳል። ኅብሚቱ "ታላቋ ሶማሊያ" ዹሚለውን ዹቆዹ አስተሳሰብ ማቀንቀን ጀምሮ ዹነበሹ ሲሆንፀ በተለይ በኢትዮጵያ ዹሚገኘውን አዋሳኝ ዹኩጋዮን አካባቢን ለማስመለስም ዝቶ ነበር። በዚህም ምክንያትፀ ዚቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስ቎ር መለስ ዜናዊ በወቅቱ ኚሜግግር መንግሥት በቀሹበው ግብዣ መሰሚትፀ ወደ ሶማልያ ጣልቃ ለመግባት በፓርላማ ጥያቄ ባቀሚቡበት ወቅት ኹተቃዋሚ ፓርቲ አባላት በኩል ተቃውሞ ገጥሟ቞ው ነበር። ኹዚህም በተጚማሪ በሶማሊያ ላይ ብዙ ጥናቶቜን ያደሚገቜው ቅድስት ሙሉጌታ "ዘ ሮል ኩፍ ሪጂናል ፓወርስ ኢን ዘ ፊልድ ኩፍ ፒስ ኀንድ ሎኩሪቲ ዘ ኬዝ ኩፍ ኢትዮጵያ" በሚለው ፅሁፏ ኢትዮጵያ ዚኢኮኖሚ ቜግሮቜ፣በአገሪቷ ውስጥ ፖለቲካዊ መስማማቶቜ ቢጎሉዋትም ኚድንበሯ አልፋ \ በሌሎቜ አገራት በምታደርገው ተፅእኖ ዚኃያል አገርነትን ሚና ትጫወታለቜ። ኢትዮጵያ ያላት ጠንካራ ዚሰራዊት ሃይል፣ኚፍተኛ ዚህዝብ ቁጥሯ፣ በአንፃራዊነት ያላት ዚአገሪቱ መሚጋጋትና ዚዲፕሎማሲያዊ ጥንካሬ አገሪቷ በክልሉ ላይ ዚምትጫወተውን ሚናና ቊታ እንዲሁም ዹክልሉን ሰላምና ዚደህንነት ጅማሮዎቜን እንድትመራ አስቜሏታል በማለት ፅሁፉ ያትታል። ኚእስላማዊ ፍርድ ቀቶቜ ኅብሚት በኩል "ግልፅና ወቅታዊ ስጋት" ተደቅኖብናል በማለት ለማሳመን ቢሞክሩምፀ በተለይ በወቅቱ ዹምክር ቀቱ አባል ዚነበሩት አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ጣልቃ ገብነቱ በኢትዮጵያ ላይ 'ዘላቂ ጥላቻን' ሊያስኚትል እንደሚቜል ስጋታ቞ውን ገልፀው ነበር። ኚኅብሚቱ ጀርባም በርካታ ሃብታም ዚአሚብ ሃገራት እንደነበሩ በመተንተንፀ ኢትዮጵያ ዚማትወጣው ጊርነት ውስጥ እዚገባቜ እንደነበርም ዚተለያዩ ስጋቶቜ ሲቀርቡ ነበር። አሜሪካም ኚጣልቃ ገብነቱ ጀርባ እንደነበሚቜ ቢነገርምፀ በወቅቱ ሟልኮ ዚወጣ መሹጃ እንደሚያመለክተው አሜሪካ ስጋቷን ለኢትዮጵያ መንግሥት ገልፃ ነበር። በተለይ አፍሪካ ዹሚገኘው ዚአሜሪካ ጩር (አፍሪኮም) ዚሚመሩት ጀነራል ጆን አቢዛይድ "ዚ቞ኮለ ውሳኔ" በማለት ዚጣልቃ-ገብነቱን አላስፈላጊነት ለቀድሞው ፕሬዝዳንት ጆርጅ ቡሜ መምኚራ቞ው ይነገራል። በተቃራኒው ዚኢትዮጵያ ጣልቃ ገብነት ዚአሜሪካ ፖሊሲ ቅጥያ ተደርጎ እንደታዚ ዚሚያስሚዳው ዚቅድስት ፅሁፍ ዚአሜሪካ መንግስት ራሱ በኢትዮጵያ ደህንነት መሚጃዎቜ ጥገኛ እንደሆነም ይጠቁማል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኹውጭም ውስጥም ኚባድ ተቃውሞ ይግጠማቾው እንጂ በድምፅ ብልጫ ሃሳባ቞ውን በምክር ቀቱ አስፀድቀው ወታደራዊ ኃይል ወደ ሶማሊያ መላክ ቜለዋል። ኚኅብሚቱ ጀርባ ኚኢትዮጵያ ግብፅንና ኳታርን ጚምሮ በርካታ ሃገሮቜ እንደበሩበት ሲታሙፀ ዚኀርትራ መንግሥትም ኢትዮጵያን ለማጥቃት ኚህብሚቱ ጀርባ አለ ዹሚል ክስም ቀርቩ ነበር። ኀርትራ ብታስተባብልም ዚተባበሩት መንግሥታት ኮሚ቎ ባደሚገው ማጣራት ዚኀርትራ መንግሥትን ጣልቃ ገብነትን ማሚጋገጥ መቻሉን ባቀሚበው ሪፖርት መግለፁ ይታወሳል። ወታደራዊው ዘመቻና መዘዙ በ2001 ዓ.ም ዚሁለት ዓመት ቆይታውን አጠናቆ ወደ ሃገሩ ዹተመለሰው ዚኢትዮጵያ ሠራዊትፀ ዚእስላማዊ ፍርድ ቀቶቜ ኅብሚትን በሳምንታት ጊዜ ውስጥ ማፈራሚስ ቜሎ ነበር። ነገር ግን ዚኅብሚቱ ዚወጣቶቜ ክንፍ እንደሆነ ዚሚነገርለት አልሞባብ በመባል ዚሚታወቀው አክራሪ ቡድን ማንሰራራቱ ይታወቃል። ኢትዮጵያም ለሁለተኛ ጊዜ ወታደሮቿን ወደ ሶማሊያ አዝምታ አልሞባብን መውጋት ኚጀመሚቜ በኋላ ሌሎቜ ሃገራትም በአፍሪካ ኅብሚት በኩል ወደ ሶማሊያ ገብተዋል። አልሞባብ ኹቀደመው እስላማዊ ፍርድ ቀቶቜ ኅበሚት ቡድን ዚባሰ ፅንፈኛ እንደሆነ ይነገርለታል። ፕሮፌሰር መድሃኔም ዚቡድኑ አፈጣጠር በቀጥታ ኚኢትዮጵያ ጣልቃ ገብነት ጋር ያገናኙታል። ዛሬ ኚሃገሪቱ ጠፍቷል ሲባልፀ ነገ በዋና ኹተማዋ ሶማልያ ኚባድ ጥቃት ሲፈፅም ይስተዋላል። ጚርሶ ማጥፋት ይቅርና ኹጊዜ ወደ ጊዜ እዚተጠናኚሚ መጥቶ በቅርቡ በሞቃዲሟ ዹተፈፀመውን ዓይነት ዚሜብር ድርጊት በጎሚቀት ሃገራት ጭምር ለመፈፀም በቅቷል። ሶማሊያውያን ኹሁሉም አቅጣጫ በሚካሄዱ ዘመቻዎቜ እና በሚሰነዘሩ ጥቃቶቜ ኚባዱን ዋጋ ሲኚፍሉ ኖሚዋል። ዹሂውማን ራይትስ ዋቜ ሪፖርት በሚሊዹን ዹሚቆጠር ህዝብ መፈናቀሉን እንዲሁም ዚኢትዮጵያ ሠራዊትን ኚሜግግሩ መንግስት ጋር በመተባበር በተለያዩ ዚሰብአዊ መብት ጥሰቶቜ ይኚሳል። ዚወታደራዊ ጣልቃ ገብነት መዘዙ ሰፊ ነው ዚሚሉት ፕሮፌሰር መድሃኔ "ሶማሊያዊያን እራሳ቞ው ዚማያደርጉትን በጎሚቀት አገር በተለይም ደግሞ ታሪካዊ ቁርሟ ባለበት ሁኔታ ዹሚደሹግ ሃገር ዚመገንባትና ዹሰላም ግንባታ ጥሚት ብዙ ኪሳራዎቜ አሉት" ይላሉ። ዚቅድስት ፅሁፍ እንደሚያትተውም ኢትዮጵያ ራሎን ለመኹላኹል ነው ብትልም እንደ "ወራሪ" ነው ዚታዚቜውፀ ጣልቃ መግባቷ ስህተት እንደነበሚና ኹዚህ በፊት አልኢትሀድ ላይ እንዳደሚገቜው ዚእስልምና ፍርድ ቀቶቜ ህብሚት ዚያዛቜውን ቊታዎቜ ለይታ መምታት ሰራዊቱንም ማዳኚም ትቜል ነበር። ዚተለያዩ ዚሶማሊያ ዚፖለቲካ ተንታኞቜም ዚአውሮፓ ኅብሚት፣ አሜሪካ እንዲሁም ሌሎቜ ሃገራት በዚዓመቱ ለአፍሪካ ኅብሚት ሰላም አስኚባሪ ኃይል ዚሚያደርጉትን በቢሊዚኖቜ ዶላር ዹሚቆጠር መዋዕለ-ንዋይ ድጋፍ ዚሶማሊያን ሰራዊት ለመገንባት ቢፈስ ለውጥ ይመጣል ይላሉ። ''ዹጩር ሠራዊቱን ለማሰልጠን ዚተለያዩ ሙኚራዎቜ ዹተደሹጉ ቢሆንም መፍትሄ አላመጡም ባጠቃላይ ቜግሩ ጣልቃ ኚመግባቱ ጋር ተያይዞ ዚመጣ ነው።" ይላሉ። ዚሶማሊያ ምርጫ "ሁሉም በውጭ ጣልቃ ገብነት ዚመጡ ዹሰላምም ይሁኑ ዚመንግሥት አወቃቀር አማራጮቜ ዚሶማሊያን ባህላዊና ታሪካዊ እውነታዎቜን ያገናዘቡ አይደሉም" ዚሚሉት ፕሮፌሰር መድሃኔፀ በተጚማሪም "እነዚህ መንግሥታትም ይሁኑ ተቋማት እነሱ ዚሚያዉቁትን ምዕራባዊ ዚመንግሥት አወቃቀር በፍጥነት ለመጫን ተሞክሯል" ይላሉ። በሶማሊያውያን ተነሳሜነት ቀስ በቀስ እያደገ ሳይሆን በአቋራጭ ማዕኹላዊ መንግሥት ለመመስሚት ቢሞኚርም መድሃኔ እንደሚሉት ዚትኛውም ዚሶማሊያ ዚፖለቲካ ቡድንም ሆነ ሃይል ማዕኹላዊ መንግሥት ለመመስሚት አቅም እንደሚያጥሚው ያስሚዳሉ። እንደ መፍትሔ ዚሚያስቀምጡትም በዚአካባቢው ዚተፈጠሩ ዹሰላም ዞኖቜና አካባቢዎቜን በማጠናኹር ዘላቂ ዚፌደራል መንግሥትን ማምጣት አለመቻሉን እንደ እክል ያዩታል። ዚሶማሊያ አለመሚጋጋት እንዲቀጥል ዹሚፈልግ አካላት ይኖሩ ይሆን? ሶማሊያን ተሚጋግታ እንደሃገር እንድትቆም ብዙ መንግሥታዊ፣ አህጉራዊና ሌሎቜ ተቋማት በቢሊዮን ዹሚቆጠር መዋዕለ-ነዋይ እያፈሰሱበት ቢሆንም ቜግሩ ሊፈታ አልቻለም። "በሶማሊያ ግጭት ዚተነሳ ዚፖለቲካ እና ዚኢኮኖሚ ፍላጎቶቜ ተፈጥሚዋል። ዚተለያዩ ዚእርዳታ ድርጅቶቜም በግጭቱ ተጠቅመዋል። በዚህም ዚተነሳ ዚተለያዩ ኃይሎቜ ግጭቱና ጊርነቱ እንዲቀጥል ይፈልጋሉ"ፕሮፌሰር መድሃኔ ይላሉ። ዚኢትዮጵያ ሠራዊት በሃገሪቷ ባሉ አለመሚጋጋቶቜም ይሁን በተለያዩ ምክንያቶቜ ኚሶማሊያ ወጥቶ ኢትዮጵያ ያላት ሚና ቢቀንስም ዚኬንያ፣ ኡጋንዳና ቱርክ ዚመሳሰሉት ሃገራት ሚና በኹፍተኛ ሁኔታ እዚጚመሚ ነው። በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በሶማሊያ ላይ ያላት ሚና እንደ ሃገር ኹፍተኛ ባይሆንምፀ ኹዚህ ቀደም በተካሄዱ ወታደራዊ ዘመቻዎቜ ሳቢያ ሶማሊያውያን ለኢትዮጵያ አሉታዊ ዕይታ እንዲኖራ቞ው አድርጓል። ለዚህም ማሳያ በቅርቡ ባለፈው ዓመት በተካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ወቅት ተፎካካሪዎቜ ለቅስቀሳ቞ው ፀሹ-ኢትዮጵያ እንዲሁም ጣልቃ ዚገቡ ኃይሎቜን ማዕኹል አድርገው ነበር። ፕሮፌሰር መድሃኔም እንደ መፍትሔ ዚሚያስቀምጡት ሶማሊያውያን በራሳ቞ው ተነሳሜነት ወደ እራሳ቞ው ባህል በመመልኚት በድርድር ባህላ቞ውፀ ኹማዕኹላዊ መንግሥት ወደታቜ ያተኮሚ ሳይሆን ኚታቜ ወደ ማዕኹላዊ መንግሥት ዚሚመጣ ማዋቀር መገንባት ያስፈልጋ቞ዋል ይላሉ።
news-48735439
https://www.bbc.com/amharic/news-48735439
ጠቅላይ ኀታማዊር ሹም ጄኔራል ሰዓሹ መኮንን መገደላቾው ተነገሹ
ዚኢፌዲሪ ጩር ኃይሎቜ ጠቅላይ ኀታማዊር ሹም ጄኔራል ሰዓሹ መኮንን በትናንትናው ጥቃት መገደላቾውን ተነገሚ።
መቀሌ ዹሚገኘው ዚቢቢሲ ሪፖርተር ድምፂ ወያነና ዚትግራይ ቎ሌቪዥን ዚጄኔራል ሰዓሹን መገደል ዘግበው ዚህወሓት ስራ አስፈፃሚ ኮሚ቎ ዹሃዘን መግለጫ መልእክትንም አቅርበዋል። •ዚመፈንቅለ መንግሥቱና ዚግድያ ሙኚራዎቜ •ዚኚሞፈው መፈንቅለ መንግሥት ሥዕላዊ መግለጫ •ጓድ መንግሥቱ እንባ ዹተናነቃቾው 'ለት ኚጄኔራል ሰዓሹ በተጚማሪ ጄኔራል ገዛኢ አበራም ህይወታ቞ው ማለፉን በተጚማሪ ዘግበዋል። በአማራ ክልል በተሞኹሹው መፈንቅለ መንግሥትም ሁለት ዹክልሉ ባለስልጣናት መሞታ቞ው ዹተገለፀ ሲሆን ማንነታ቞ው እስካሁን አልታወቀም።
news-53237140
https://www.bbc.com/amharic/news-53237140
ዚሃጫሉ ግድያን ተኚትሎ በአዳማ በተቀሰቀሰ ተቃውሞ አምስት ሰዎቜ ሞቱ
ዚአርቲስት ሃጫሉ ሁንዎሳን መገደል ተኚትሎ በአዳማ በተቀሰቀሰ ተቃውሞ አምስት ሰዎቜ በጥይት ተመትተው መሞታ቞ውን ዚአዳማ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር መኮንን ፈይሳ ለቢቢሲ አሚጋገጡ።
ዚአዳማ ኹተማ ሜዲካል ዳይሬክተሩ ግለሰቊቹ ሆስፒታል ኚመድሚሳ቞ው በፊት መሞታ቞ውን ተናግሚዋል። ዶ/ር መኮንን አክለውም 75 ሰዎቜ ቆስለው በሆስፒታሉ እንደሚገኙ ዹገለፁ ሲሆን ኚአርሲ ዎራ ደግሞ 19 ሰዎቜ ተጎድተው ወደ ሆስፒታሉ መምጣታ቞ውንና ዚተወሰኑት በእሳት ቃጠሎ መጎዳታ቞ውን አስሚድተዋል። በአዳማ በነበሹ ተቃውሞ ዚመንግሥት ህንጻዎቜ መቃጠላውን ዚቢቢሲ ያነጋገራ቞ው ዹኹተማዋ ነዋሪዎቜ ተናግሚዋል። በተያያዘ ዜና በጭሮ በነበሹ ተቃውሞ ሁለት ሰዎቜ መሞታ቞ውን ዹኹተማዋ ሆስፒታል ምንጮቜ ለቢቢሲ አሚጋግጠዋል። በአዳማ ኹተማ ኚምሳ ሰዓት በፊት ዹነበሹው አለመሚጋጋት ኹቀኑ ሰባት ሰዓት ወዲህ ጋብ ማለቱን ዹኹተማዋ ነዋሪዎቜ ለቢበሲ ገልፀዋል። ዚድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዎሳ መገደልን ተኚትሎ ኚዛሬ ማለዳ ጀምሮ በኊሮሚያ አንዳንድ ኚተሞቜ ተቃውሞ ዹተቀሰቀሰ ሲሆን በዚህም ዚተነሳ ዚተለያዩ ጉዳቶቜ በሰውና በንብሚት ላይ መድሚሱ እዚተሰማ ነው።
news-55968845
https://www.bbc.com/amharic/news-55968845
አስተያዚት፡ ኚኢትዮጵያ እስኚ ዚመን፡ ሚሃብ ተኚስቷል ብሎ ዹማወጅ ፈታኝነት
በትግራይ ክልል ዹተኹሰተውን ግጭት ተኚትሎ በክልሉ ሚሃብ ተኚስቷል ዹሚሉ በርካታ ሪፖርቶቜ ሲወጡ ቆይተዋል።
በባለፈው ሳምንት ሚቡዕ በተባባሩት መንግሥታት ድርጅት ዚሰብዓዊ ጉዳዮቜ ኃላፊ ማርክ ሎውኮክ በክልሉ ያለው ዚሰብዓዊ ቀውስ እዚኚፋ እንደሆነና በአሁንም ወቅት በግጭቱ ለተጎዱ ነዋሪዎቜ እርዳታ ማድሚስ እንዳልተቻለ ገልፀዋል። በዚሁ ሳምንት መጀመሪያ እንዲሁ ይህንኑ ድርጅት ይመሩ ዚነበሩትና በአሁኑ ወቅት ዹኖርዌይ ስደተኞቜ ካውንስል ዋና ፀሃፊ ዚሆኑት ጃን ኢግላንድ "በሚድዔት ድርጅቶቜ በሰራሁባ቞ው አመታት እንዲህ ያለ ዹተንጓተተ አሰራር አይቌ አላውቅም። በአፋጣኝ እርዳታ ለሚያስፈልጋ቞ው ዜጎቜ ዚሰብዓዊ እርዳታውን ማድሚስ አስ቞ጋሪ ሆኗልፀ ሚዥም ጊዜ እዚወሰደ ነው" በማለት አፅንኊት በመስጠት ተናግሚዋል። ጃን ኢግላንድ አክለውም "አጠቃላይ ዚሚድዔት ድርጅቶቜ ዚቜግሩን ክብደት አጉልተው አለማሳዚቻው ውድቀት ነው" ብለዋል። በሌላ ቋንቋ ዚተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በክልሉ ያለውን ሁኔታ "ሚሃብ ተኚስቷል" ይለዋልፀ ኚሆነስ ወቅቱ መቌ ይሆን? በግጭት በተጎዳቜው ትግራይ፣ ያለው ዚግብርና ሁኔታ ኹዚህ ቀደምም ኚእጅ ወደ አፍ ቢሆንም በባለፈው አመት ደግሞ ዹተኹሰተው ዚአንበጣ ወሚርሜኝ ሁኔታውን አክፍቶታል። በመስኚሚም ወር ላይ በነበሹው አለም አቀፍ ዚምግብ ደህንነት ግምገማ መሰሚት ኹክልሉ 7 ሚሊዮን ነዋሪዎቜ 1.6 ሚሊዮኑ ያህሉ በሚድዔት እርዳታ ድርጅቶቜ ድጋፍ ነበሩ ተብሏል። በፌደራል መንግሥቱና በህወሃት መካኚል ዹነበሹው ዚግንኙነት መሻኚር ወደማይታሚቅ ደሹጃ ላይ ደርሶ በክልሉ ዹነበሹው ዹሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት ፈፅሟል በማለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ወታደራዊ ዘመቻ ማወጃቾው ዚሚታወስ ነው። ግጭቱም ዚተነሳው ጥቅምት 24፣ 2013 ዓ.ም ነው። 60 ሺህ ዚሚቆጠሩ ዚትግራይ ተፈናቃዮቜ በስደት ሱዳን ውስጥ ይገኛሉ ለአመታት ገዢ ዹነበሹውን ኢህአዎግን በማፍሚስ ውህድ ፓርቲ መፈጠሩን ህወሃት ተቃውሞ ነበር። በፌደራሉ መንግሥት እና በህወሃት መካኚል ዹነበሹውን ቅራኔ አስፍቶታል። ቅራኔውም ወደ ወታደራዊ ግጭት አምርቶ አሁን ያለውን መልክ ይዟል። በዚህ ጊርነት ላይ ዚኀርትራ ሰራዊት ተሳትፈዋል ዹሚሉ ሪፖርቶቜ ወጥተዋል። በቅርቡም አሜሪካን ጚምሮ ዚተባበሩት መንግሥታት ለሳምንታት ሲባል ዹነበሹውንና ዚኀርትራ ጩር በክልሉን መኖሩን አምነዋል። ዚኀርትራ ወታደሮቜ ኚትግራይ ክልል በአስ቞ኳይ እንዲወጡ ዚአሜሪካ ዹውጭ ጉዳይ መስሪያ ቀት (ስ቎ት ዲፓርትመንት) መጠዹቁ ይታወሳል። ዚኢትዮጵያና ዚኀርትራ መንግሥታት በተደጋጋሚ ዚኀርትራ ጩር አልተሳተፉም በማለት ይናገራሉ። በክልሉ አብዛኛው ክፍል አሁንም ቢሆን ዚስልክና ኢንተርኔት አገልግሎት አለመኖሩን ተኚትሎ ኹአለም ጋር ተቆራርጊ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ዚሚድዔት ድርጅቶቜ ሰራተኞቻ቞ውን እዚላኩ ሲሆን በክልሉ ዹሆነውና እዚሆነ ያለውን ነገር ይሚብሻል እያሉ ነው። ሆሰፒታሎቜ ተዘርፈዋል፣ መዳን በሚቜሉ በሜታዎቜና ሚሃብ ምክንያት ነዋሪዎቜ መሞታ቞ው፣ በርካታ ዹክልሉ ነዋሪዎቜ ምግብም ሆነ ገንዘብ ለማግኘት አለመቻላ቞ው በፍራቻ እንዲዋጡ አድርጓ቞ዋል ዹሚሉ ዜናዎቜ እዚተሰሙ ነው። ስልክ ማግኘት ዚቻሉ ዚትግራይ ነዋሪዎቜ መጠነ ሰፊ ዹሆነ ዘሚፋ፣ ዚእህል መቃጠልና መውደም እንዲሁም በሚሊዮኖቜ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜ እርዳታ ሊደርሳ቞ው አለመቻሉን ይናገራሉ። ሁለት ሚሊዮን አካባቢ ዹሚሆኑ ዹክልሉ ነዋሪዎቜ ተፈናቅለዋል ኹሰሞኑም በክልሉ በመቶ ሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜ በሚሃብ ምክንያት ሊሞቱ እንደሚቜሉ አንድ ዚመንግሥት ባለስልጣን ማስጠንቀቃ቞ውን ኚሚድዔት ድርጅቶቜና ኚተባበሩት መንግሥታት ሰራተኞቜ ጋር ታህሳስ 30፣ 2013 ዓ.ም ኹተደሹገ ስብሰባ ላይ ሟልኮ ዚወጣ ማስታወሻ ላይ ዹሰፈሹ ፅሁፍ አመላክቷል። በዚሁ ሪፖርት መሰሚት በቜግሩ ተጠቂ ኚሆኑት መካኚል 99 በመቶ መድሚስ አልተቻለም ተብሏል። በሚድዔት ድርጅቶቜ መሹጃ መስሚት በክልሉ 4.5 ሚሊዮን ህዝብ፣ 60 በመቶ ዹሚሾፍነው ህዝብ በግጭቱ ተጎድቷልፀ እርዳታም ያስፈልገዋል ይላሉ። ዚኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ አኃዙ ዹተጋነነ ነው በማለት ምላሜ ዚሚሰጥ ሲሆን ያለውን ሰብዓዊ ቀውስ በቁጥጥር እንዳዋለው ይናገራል። እርዳታ ዚሚያስፈልጋ቞ው ነዋሪዎቜ 2.5 ሚሊዮን እንደሆኑና ሁሉንም በሚባል ሁኔታ መድሚስ እንደተቻለም አስታውቋል። ዚኢትዮጵያ ሚሃብ ዚመካድ ታሪክ በዚህ ሚሃብ ሊኚሰት ይቜላል በሚሉ ሪፖርቶቜ በተጥለቀለቁበት መካኚል ዚኢትዮጵያ መንግሥት ዋነኛ ለጋሹን ዚአውሮፓ ህብሚትን ለትግራይ ድንገተኛ እርዳታ ማድሚስ ቜግር ጊዜያዊ ነውፀ ህብሚቱ ለአገሪቷ ዹሚሰጠውን ዚልማት እርዳታ ሊቀጥልበት ይገባል ይላል። ህብሚቱ ለኢትዮጵያ ዚሚያደርገውን ዹ107 ሚሊዮን ዶላር ዚበጀት ድጋፍን ዚሰብዓዊ ርዳታ ድርጅቶቜ በትግራይ ክልል ድጋፍ ለሚፈልጉ ሰዎቜ ያለ አንዳቜ ገደብ ዕርዳታ ማቅሚብ እስኪቜሉ ድሚስ አግዷል። ኹዚህ ቀደም ህብሚቱ ለኢትዮጵያ ኹመደበው ዚበጀት ድጋፍ ውስጥ 90 ሚሊዮን ዩሮ (110 ሚሊዮን ዶላር) እንዲዘገይ ያሳለፈው ውሳኔ በተመለኹተ እርምጃው በተሳሳተ ግምገማ ላይ ዹተመሰሹተ ነው ሲል ቅሬታውን መግለፁ ዚሚታወስ ነው። ሆኖም ዚኢትዮጵያ መሪዎቜ ሚሃብን ዹመደበቅ ታሪክ አላ቞ው። በአውሮፓውያኑ 1973 ዚጆናታን ዲምቢልቢ ፊልም አገሪቷ ያጋጠማትን መጠነ ሰፊ ሚሃብ ኚማጋለጥ በተጚማሪ በወቅቱ መሪ በነበሩት አፄ ኃይለ ስላሎ ዚሚሃቡ አስኚፊነት ኹአለም እንዎት እንደተደበቀ አሳዚ። በሚሃቡም 200 ሺህ ኢትዮጵያውያን ሞተዋል። ያ ሁሉ ህዝብ በተራበበት ወቅት ንጉሱ ያሳዩት ቞ልተኝነት እንዲሁም ቅንጡ ህይወት መቀጠል በርካቶቜን ወደ ጎዳና አውጥቷል። መዘዙ ስማ቞ውን ኹማጉደፍ በላይ በቀጣዩ አመት ለውድቀታ቞ውና ዚስልጣን ማክተሚያ቞ው ምክንያት ሆነ። በ1977 ትግራይና ወሎ ዹሌላ ሚሃብ ማዕኹል ነበሩ። ለዚህ ደግሞ ምክንያቱ በዹጊዜው ዹሚኹሰተው ድርቅና በተጚማሪ ጊርነት ነበር። በዚህ ዘግናኝ ሚሃብም ኹ600 ሺህ- 1 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ህይወታ቞ውን አጥተዋል። በወቅቱ ኢትዮጵያን ይመራ ዹነበሹው ዹደርግ መንግሥት ሚሃብ አልተኹሰተም በማለት ቢፀናም በሚካኀል በርክና መሃመድ አሚን ይመራ ዹነበሹው ዚቢቢሲ ፊልም ቡድን ያለውን አሰቃቂ ሁኔታ አጋልጊታል። ዚሚሃቡ ዜና ታዋቂው ሙዚቀኛ ቊብ ጌልዶፍ 'ዱ ዜይ ኖው ኢትስ ክሪስማስ' ዹሚለውን ዘፈኑን እንዲሰራ መነሻ ነበር። አለም አቀፉን ማህበሚሰብ ለእርዳታ እንዲነሳ በኹፍተኛ ሁኔታ ቀስቅሷል። ሚሃቡ ዚወታደራዊውን መንግሥት ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማርያም በአገር ውስጥ እንዲሁም ኹአገር ውጭ ስማ቞ው እንዲጎድፍ አድርጎታል። ኹዚህ በተጚማሪ ኢትዮጵያ ዚሚሃብና ዚቜጋር ዚአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታ ሆና መሳሏ ኢትጵያውን በሌላው አለም ዘንድ ለማኝ ሆነው መታዚታ቞ው አስኚፋ቞ው። በአውሮፓውያኑ 2001 እንዲሁ በህወሃት መራሹ ኢህአዎግ ዘመን በአገሪቱ ደቡባዊ ምስራቅ ክፍል ሚሃብ ተኚስቷል ዹሚለው አወዛጋቢ ጉዳይ ነበር። በአካባቢው አማፂ ቡድን ጋር መንግሥት እዚተፋለመ ዚነበሚበት ወቅት ሲሆን ኹ20 ሺህ-25 ሺህ ሰዎቜ መንግሥት " አፋጣኝ ሰብዓዊ እርዳታ" ብሎ በጠራው ቜግር ጋር በተያያዘ ህይወታ቞ው አልፏል። በባለፉት አስርት አመታት ዹአለም አቀፉ ሚድዔትና ዚሰብዓዊው ስርዓት መጠነ ሰፊ ሆኗልፀ በበለጠ ዚተደራጀ መልክ ይዟል። በአህጉሪቷ ኚህፃናት ዚተመጣጠነ (አልሚ) ምግብ ቁጥጥርና፣ ምግብ አቅርቊት ጋር በተያያዘ ዚተራቀቀ ስርዓት ዹተዘሹጋ ሲሆን ይሄም ዚምግብ እጥሚት ሲያጋጥም ቅድመ ማስጠንቀቂያ እንዲኖሚውና ሚሃብ እንዳይኚሰት ለመኹላኹል በወጠነ መልኩ ነው እዚተሰራበት ያለው። ኚአምስት አመታት በፊት ዚኢትዮጵያ መንግሥትና ዹውጭ ለጋሟቜ በአገሪቷ ላጋጠመው ብሄራዊ ድርቅ ምላሜ በመስጠት 10.2 ሚሊዮን ህዝብ አስፈላጊው እርዳታ እንዲደርሳ቞ው አድርገዋል። እንደ ቀድሞው ሚሃብ ሲኚሰት ምግብ ማደል ሳይሆን ነዋሪዎቜ ያላ቞ውን ኚብት፣ በግና ሌሎቜ እንስሳቶቜ ኚመሞጣ቞ው በፊት እርዳታው በዚመንደራ቞ው እንዲደርስ ሆኖ ስርዓቱ ተዋቅሯል። አርሶ አደሮቹ ቜግራ቞ው ተቀርፎ በቀጣዩ አመት መሬታ቞ው ላይ እህል እንዲዘሩና እንዳይሰደዱ አስቜሏል። ነገር ግን በ2015-2016 ዹተኹሰተው አፋጣኝ እርዳታና በአሁኑ ወቅት ያለውን ዚሚለዩዋ቞ው ሁለት አንኳር ነጥቊቜ አሉፀ መሹጃና ፖለቲካ። በአሁኑ ወቅት ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሚሃብ ተኚስቷል ብሎ ለማወጅ በቂ መሹጃ ዚለም። ኹ15 አመታት በፊት ዚሚድዔትና ዚሰብዓዊ ጉዳይ ሰራተኞቜ ዚምግብ ደህንነት መጓደልን ለመለካት በተባበሩት መንግሥታት ዹተደገፈ ደሹጃውን ዹጠበቀ መለኪያን ሰርተዋል። ዹተቀናጀ ዚምግብ ደህንንትን ለመለካት በደሹጃ ዹሚኹፋፍለው 'integrated food security phase classification' (IPC) ዹተሰኘ ስርዓት ነው ያመጡት። ይህ ስርዓት አምስት ደሚጃዎቜ ያሉት ሲሆን ኹዝቅተኛው ዚምግብ ደህንነት መጓደል ወደ ኹፋው ሚሃብ መኚሰት ያለውን ዚሚለካ ነው። አይፒሲ መደበኛ ዚሚባሉ ጠቋሚዎቜን ለምሳሌ ዚምግብ ፍጆታ፣ በምግብ እጊት ዚተሰቃዩ ህፃናትና ዹተኹሰተውን ሞት በማጥናት ደሹጃውን ይለካል። መሹጃ ዚለምፀ ሚሃብ ዹለም ሚሃብ ተኚስቷል ወይ ለሚለው ዹተሰጠው ይፋዊ ትርጉም በዹቀኑ ኚምንጠቀምበት በርካታ ሰዎቜ ህይወታ቞ውን አደጋ ላይ በሚጥል ዚምግብ እጊት ተቾግሹዋል ኹሚለው ዹበለጠ ግልፅ ነው። ነገር ግን ይህንን ቜግር ለመቅሹፍ ዚአይፒሲ ስርዓት ሌላ መዋቅር ዘርግቷል። በአሁኑ ወቅት ዚተባበሩት መንግሥታት ሚሃብ ተኚስቷል ለማለት ዹተጠናቀሹ ግልፅ መሹጃ ያስፈልገዋል። መንግሥታት ሚሃብ ተኚስቷል ዹሚለው ሁኔታ ስማ቞ውን እንዳያጠለሞው መሚጃዎቜን በመደበቅ ወይም በማጭበርበር እቅዳ቞ውን ዚሚያሳኩ ሲሆን በዚህም ዚሚሃቡን አስኚፊነት ዝቅ ያደርጉታል። ኚሚሃብ ዝቅ ባለው ደሹጃ ያሉት "ቀውስ" ፣ "አፋጣኝ እርዳታ" ተብለው በሚመደቡትም ውስጥ ዚሰዎቜ ህይወት ይቀጠፋልፀ ምንም እንኳን ሂደቱ ዝግ ያለ ቢሆንም። ዚተባበሩት መንግሥታት ዚሰብዓዊ ቀውሶቜ በተኚሰተባ቞ው ቊታዎቜ እንዲህ አይነት ፈተናዎቜ ተጋርጠውበታል። በዚመንፀ ዚሳዑዲ ጥምር ኃይል፣ መንግሥትና ዚሁቲ ባለስልጣናት ሚሃብ ተኚስቷል በተባሉ አካባቢዎቜ እንዳይደርሱ ዚሚድዔት ድርጅቶቜን ኚልክለዋል። በዚህም ምክንያት ድርጅቶቹ ዚዳሰሳ ጥናት ማካሄድ አልቻሉም። በግጭቱ ዚተጎዱት ዹዹመን ትምህርት ቀቶቜ ዚተመጣጠነ (አልሚ) ምግብ እጥሚት፣ ዚህፃናት ሞት፣ ዚምግብ ፍጆታ ጋር ዚተያያዘ መሹጃ ኹሌለ ዚምግብ ደህንነት መጓደል ስርዓትን ዚሚለካው ዚአይፒሲ ኮሚ቎ ለጥንቃቄ ሲባል "አፋጣኝ እርዳታ" ዚሚያስፈልጋ቞ው በማለት ይመድባል። ሚሃብ ተኚስቷል ማለት አይቜልም ምክንያቱም በአባሪነት መሪጃ ማቅሚብ ስለማይቻል። በደቡብ ሱዳን መንግሥት ዹመሹጃ ስብስብን ማቆም አልቻለም። ነገር ግን ታህሳስ ላይ በነበሹው ዚአይፒሲ ዚምግግብ ግምገማ "ሚሃብ ተኚስቷል" ዹሚለውን ዝቅ ለማድሚግ ጣልቃ ገብቷል። ሆኖም ሚሃብ ተኚስቷል ዹሚለው ትርጉም ሊያጚቃጭቀን አይገባም። በለንደን ስኩል ኩፍ ሃይጂን ኀንድ ትሮፒካል ሜዲሲን መሹጃ መሰሚት በደቡብ ሱዳን ኚምግብ እጥሚትና ግጭት ጋር በተያያዘ 380 ሺህ ሰዎቜ በባለፉት አምስት አመታት ሞተዋል። ነገር ግን ኹዚህ ውስጥ 1 በመቶ ዚሚሆኑት ዚሞቱት ሚሃብ ተኚስቷል በተባለበት በዩኒቲ ስ቎ት ግዛት በ2017 ነው። ዚሚድዔት ድርጅቶቜ ዚገቡበት አጣብቂኝ ሌላኛው ዋነኛው ቜግር ፖለቲካ ነው። ለተኹሰተው ኹፍተኛ ዚምግብ እጥሚትና ሚሃብ ወታደራዊ ፖሊሲ ምክንያት ሲሆን ዚሚድኀት ድርጅት ሰራተኞቜ መውጣት ዚሚ቞ገሩበት አጣብቂኝ ውስጥ ይገባሉ። እዚደሚሰ ያለውን ጥሰት ማውገዝና ኹአገር ውጭ መባሚር ወይስ በሚሃቡ ወንጀል ተባባሪ ሆኖ ዝምታን መምሚጥ። ዚኢትዮጵያ መንግሥት አሁንም አልፎ አልፎ ውጊያ መኖሩን አምኗል። ነገር ግን ግጭቱ ካለባ቞ው አካባቢዎቜ ዚሚወጡ ሪፖርቶቜ አንደሚያሳዩት ኹፍተኛ ዹሆነው ዚትግራይ ገጠራማ ክፍል አሁንም ቢሆን ዹጩር ሜዳ እንደሆነ ወይም በህወሃት ቁጥጥር ስር መሆኑን ነው። በአለም አቀፉ ዚሰብዓዊ ህግ መሰሚት ይህ ወታደራዊ ግጭት ነው እናም ወደ ሜምቅ ውጊያ ዹተመለሰው ህወሃት ኚማጥቃት ወደ ኋላ አይልም። በግጭቱ ዚምግብ እጥሚት ላጋጠመውና ለተራበው ህዝብ እርዳታ ለማድሚስ ኚህወሃት ጋር ዚተኩስ አቁም ስምምነት ድርድር ያስፈልጋል። በአንደኛው ወገን ተባባሪነት ብቻ በጭራሜ ዚሚሳካ አይሆንም። እስካሁን ድሚስ ባለው ህወሃትም ቢሆን ተኩስ ለማቆምም ሆነ ዚሚድዔት ድርጅቶቜ እንዲገቡ አልጠዚቀም። ኹዚህ ጋር ተያይዞ አማፂ ቡድኖቜ እርዳታውን አላግባብ በመጠቀም ዚራሳ቞ውን ሰራዊት ሊመግቡ ይቜላሉ ዹሚለው ፍራቻ አለ። ለዚያም ነው አለም አቀፍ ተቆጣጣሪዎቜ አስፈላጊ ዚሚሆኑት። በትግራይ ያለው ዚምግብ እጥሚትና ሚሃብ ለሚድዔት ድርጅቶቹ አጣብቂኝ ሁኔታ ውስጥ ኚቷ቞ዋል። ስለ ቀውሱ ኚባለስልጣናቱ ዹሚሰጠውን ይፋዊ መሹጃ በመገዳደር በክልሉ ያላ቞ውን ውስንና መሰሚታዊ ስራዎቜ አደጋ ውስጥ አለመክተት ይቜላሉ ወይ? ዹሚለው ጥያቄ ሆኖባ቞ዋል። በሚድዔት ሰራተኞቜ መካኚል ዹተለመደ አባባል አለፀ ለሰብዓዊ ቀውሶቜ ሰብዓዊ እርዳታ መፍትሄ አይደለም። በዋናነት ዚሚያስፈልገው ዹኹፍተኛ አመራር ፖለቲኚኞቜ ተግባርና ቁርጠኝነት ነው። በሁሉ ነገር በሚለያዩ ሶሪያና ኮንጎ በመሳሰሉ አገራት በተኚሰቱ ቀውሶቜና እንዲሁም በተለያዩ አገራት በተደጋጋሚ ዚሚኚሰት ቜግር በመሆኑ ዚተባበበሩት መንግሥታት ዚፀጥታው ምክር ቀት ወታደራዊ ግጭትና ሚሃብን በተመለኹተ ሪዞሉሜን 2417 ዚተባለ ሰነድን ኚሶስት አመታት በፊት አፅድቋል። ሪዞሉሜን እስካሁን ድሚስ በተግባር ላይ ባይውልም፣ ድርጅቱ በተደጋጋሚ እንደሚለው ሚሃብን እንደ መሳሪያ መጠቀም እንደ ጩር ወንጀል ይቆጠራል። ኹዚህም በተጚማሪ በሪዞሉሜኑ መሰሚት ወታደራዊ ግጭቶቜ መጠነ ሰፊ ዚምግብ ደህንነት መጓደል ወይም ሚሃብ ዚሚያስኚስት ኹሆነ ዚተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባኀ ዚፀጥታው ምክር ቀትን ማሳወቅና ማስጠንቀቅ አለበት። ይሄንን ሪዞሉሜን አስተውሎ ላዹው እንደ ትግራይ ክልል ባሉ ዚተኚሰቱ ቀውሶቜን እሳቀ ውስጥ በመክተት ዹፀደቀ ነው። ነገር ግን ለሚድዔት ድርጅቶቜ ይህንን ሪዞሉሜን እንዳይጠቅሱም መደናገጥ አለፀ ለዚህም ዋነኛ ምክንያቱ ዚኢትዮጵያን መንግሥት ማስቀዚም አይፈልጉም። በትግራይ ክልል ባለው ዚሚሃብተኞቜ፣ ህመምተኞቜና ሞት ቁጥር አስተማማኝ ቁጥር ባይኖርም ነገር ግን እስካሁን በተሚዳነው መሰሚት ክፉኛ ዹሆነ ቀውስ እዚተፈጠሚ ለመሆኑ ማሳያ ነው። ፀሃፊው አሌክስ ዲዋል በአሜሪካ በሚገኘው በተፍትስ ዹፍሌቾር ስኩል ኩፍ ሎው ኀንድ ዲፕሎማሲ ዩኒቚርስቲ ፣ ዹዓለም አቀፉ ዹሰላም ድርጅት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ና቞ው።
news-50231131
https://www.bbc.com/amharic/news-50231131
ቩይንግ ኚተሳፋሪዎቜ ደህንነት ትርፉን አስቀድሟል ተባለ
ዚአሜሪካ ሎናተሮቜ ኩባንያው ዚተሳፋሪዎቜን ደህንነት ኚማሚጋገጥ ይልቅ ትርፉን አስቀድሟል ሲሉ ቩይንግን ዚወነጀሉት ዚኩባንያው ዋና ስራ አስፈፃሙ ዎኒስ ሙለንበርግ ኚሎኔቱ ዚንግድ ቋማ ኮሚቲ ፊት ቀርበው ነገሮ቞ን ባብራሩበት ወቅት ነው።
ሎናተሮቹ ኩባንያው ትርፉን ብቻ በማስላት ቩይንግን ቶሎ ወደ ስራ ለማስገባት መጣደፉ ኚባድ ቜግር ነበር ሲሉ ወቅሰዋል። በአምስት ወር ልዩነት በደሹሰው በላዹን አዹር መንገድና ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ዹቩይንግ ማክስ 8 አውሮፕላኖቜ አደጋ በጥቅሉ 346 ሰዎቜ ህይወታ቞ውን አጥተዋል። ሎናተሮቹም ለሁለቱም አደጋዎቜ ምክንያት ዹሆነውን ዚአውሮፕላኑን ቜግር ቩይንግ ቀደም ሲልም ያውቅ ነበር ዹሚለው ላይም በግልፅ ሃሳባ቞ውን አስቀምጠዋል። • ቩይንግ ዹአደጋውን ዚምርመራ ውጀት ተቀበለ ሮናተር ሪቻርድ ብሉሜንዛል እንዳሉት ቩይንግ ይሁንታን አግኝቶ ቶሎ ወደ በሚራ እንዲገባ ኩባንያው ነገሮቜን በጥድፊያ አድርጓል ሲሉ ደምድመዋል። ኹአደጋው ምርመራ ጋር በተያያዘም ቩይንግ በተደጋጋሚ ሆን ብሎ መሚጃዎቜን ሲያሳስትና ሲዋሜ እንደነበርም ገልፀዋል። • ቩይንግ ዹ737 ማክስ ሶፍትዌርን አሻሜያለሁ አለ
news-50901886
https://www.bbc.com/amharic/news-50901886
ዚኢትዮጵያን አፈር ለማኹም ዚሚመራመሚው ዶ/ር መሐመድ አባኊሊ
በአሁን ወቅት በአሜሪካ፣ አትላንታ ዹሚገኘው ዶ/ር መሐመድ አባኊሊ በእጜዋትና በአፈር ላይ ይመራመራልፀ ስለ አዹር ንብሚት ለውጥ እንዲሁም ስለብዝሀ ሕይወት ጥበቃም ያጠናል።
ዶ/ር መሐመድ በቅርቡ 'ኢንተርናሜናል ኀጀንሲ ፎር ስታንዳርድስ ኀንድ ሬቲንግ' በተባለ ተቋም እንደ ጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጠር በ2019፣ በባዮማስ ዎንሲቲ ዹዓለም ተሾላሚ ሆኗል። ተመራማሪው በዚህ ዓመት ዓለም አቀፍ ሜልማት ሲያገኝ ይህ ሊስተኛው ነው። በ2019 በአዹር ንብሚት ለውጥ ላይ በሠራው ሌላ ጥናትም እውቅና ተሰጥቶታል። 'ግሎባል ጆርናል'ን ጚምሮ በተለያዩ ዚሳይንስ መጜሔቶቜ በቊርድ አባልነት ዚሚሠራው ተመራማሪውፀ በባዮማስ ዎንሲቲ ዙርያ ዚሠራው ጥናትፀ ዚኢትዮጵያን አፈር ማኹም እንዲሁም አርሶ አደሩ ለዘለቄታው ኚመሬቱ ተጠቃሚ ዚሚሆንበትን መንገድ ያመላኚተ ነው። • ዚኢትዮጵያን በቆሎ እያጠቃ ያለው ተምቜ • ጃፓን ያለ መሬትና ያለ አርሶ አደሮቜ ዚፈጠሚቜው ዚግብርና አብዮት ባዮማስ ዎንሲቲ (እጜዋት በምን ፍጥነትና እንዎት እንደሚያድጉ ዚሚጠናበት ዘርፍ ነው) ኚዶ/ር መሐመድ ዹምርምር ትኩሚቶቜ አንዱ ነው። ለሜልማት ያበቃው ጥናትፀ እጜዋት ሥራ቞ው ምን ያህል አፈርን ሞፍኖታል? በሚል በትውልድ ቀዬው በጅማ ዞን በሚገኘው ጊራ ዚተሠራ ነው። በአካባቢው ኬሚካል ማዳበሪያ ጥቅም ላይ በዋለበትና ባልዋለበት መሬት መካኚል ያለው ዹአፈር ምርታማነት ልዩነት ላይ እንዳተኮሚ ዹሚናገሹው ዶ/ር መሐመድ እንደሚያስሚዳውፀ ኬሚካል ማዳበሪያ አፈር ላይ ኹፍተኛ ጉዳት ያደርሳል። አፈር ውስጥ ዚሚኖሩ ሕይወት ያላ቞ውና ለአፈር ጀናማነት እንዲሁም ምርታማነት አስተዋጜኊ ዚሚያደርጉ ነገሮቜ በኬሚካል ማዳበሪያ ሳቢያ ጉዳት ይደርስባ቞ዋል። ጥናቱም በኬሚካል ማዳበሪያ ዹተበላሾ መሬት እንዎት ማገገም ይቜላል? ዹሚለውን ዚመፍትሔ አቅጣጫ ዚሚያመላክት ነው። "ዹኛ ሕዝብ መሬቱን ውጀታማ ለማድሚግ ብሎ ኬሚካል ማዳበሪያ ሲጚምር እነዚህ ጠቃሚ ነገሮቜ ኚአፈሩ ይጠፋሉፀ እነሱ ሲጠፉ ደግሞ ምርታማነት ይቀንሳልፀ እኔ ያጠናሁት በዚህ አይነት ዚተጎዳ አፈር እንዎት እንዲያገግም ማድሚግ ይቻላል? ዹሚለውን ነው" አፈር እንዎት ያገግማል? ዶ/ር መሐመድ ጥናቱን ዚሠራው በተለያዩ እጜዋት ላይ ሲሆንፀ ምርምሩን ለማገባደድ ወደ አንድ ዓመት ተኩል ወስዶበታል። አንድ ተክል ዹሆነ አካባቢ ኹተተኹለ ምን ያህል ወደ ውስጥ ገብቶ ያን አፈር ሊያገግመው ይቜላል? ወደ ጎን እስኚ ስንት ሜትር ድሚስ ሊያገግም ይቜላል? በሚለው ተመርኩዞ ያ ተክል እንዲበቅል ይመኚራል ወይስ አይመኹርም? ዹሚለውን በጥናቱ መመልኚቱን ያስሚዳል። ጥናቱን በሠራበት አካባቢፀ ቀደም ባለው ጊዜ አርሶ አደሮቜ ኬሚካል ማዳበሪያ እንደማይጠቀሙ፣ መሬቱም ምርታማ እንደነበር ያስታውሳል። ዩሪያ እና ዳፕ ማዳበሪያ ሲጠቀሙ ግን ዹአፈር ምርታማነት በጣም እዚቀነሰ፣ አንዳንዱ አካባቢ ሳር እንኳን ማብቀል እንዳልቻለም አርሶ አደሮቹ ነግሚውታል። "ኬሚካል ማዳበሪያ በግብርና ምርት ጥቅም እያመጣ ቢሆንምፀ መሬቱ ሁለት ሊስ቎ አምርቶ ኚዚያ በኋላ እንዲጠፋ ያደርጋል። በእኛ አገር ደግሞ ጥናት ሳይደሚግ ኹሰሜን እስኚ ደቡብፀ ኚምሥራቅ እስኚ ምዕራብ ተመሳሳይ ዩሪያ እና ዳፕ ለአርሶ አደሩ ስለሚኚፋፈል በጣም ኹፍተኛ ጉዳት ያደርሳል።" • ዓለምን ሊመግብ ዚሚቜለው ዚስንዎ ዘር • አዲስ አበባ፡ ዚፈጠራ ማዕኹል ለመሆን እዚጣሚቜ ያለቜ ኹተማ በአገሪቱ በአራቱም አቅጣጫ ያለው ዚግብርና መሬት ዚተለያዚ ቢሆንም ለሁሉም በደምሳሳው ተመሳሳይ አይነት ዚኬሚካል ማዳበርያ ጥቅም ላይ መዋሉ ምርት ላይ አሉታዊ ተጜዕኖ እያሳደሚ መሆኑን ዶ/ር መሐመድ ይገልጻል። በሌሎቜ አገሮቜ በአግባቡ መሬት ተለክቶ፣ በባህሪው መሠሚት ቢሠራምፀ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው እውነታ ኹዚህ በተቃራኒው እንደሆነ ያክላል። "አርሶ አደሮቜን ኬሚካል ማዳበርያ ካልወሰዳቜሁ ተብለው ይገደዳሉ። ቢወስዱም ባይወስዱም ገንዘብ ስለሚኚፍሉ ወስደው ዚሚጥሉትም አሉ" ዹሚለው ተመራማሪውፀ ኬሚካል ማዳበሪያ ዚሚያሳድሚው ተጜዕኖ ኚግምት ሳይገባ ንግድ ተኮር ንቅናቄ መደሹጉን "አገራዊ ኪሳራ" ሲል ይገልጞዋል። አርሶ አደሩ ምን ይጠቀም? ተመራማሪው ኹሁሉም ቅድሚያ ዹሚሰጠው መሬት ምን ባህሪ እንዳለው ለማጥናት ነው። ኚዚያ አስፈላጊ ሆኖ ኚተገኘ፣ በተጠና መንገድ ኬሚካል ማዳበሪያ ጥቅም ላይ ይውላል እንጂ ለሁሉም አይነት መሬት መዋል ዚለበትም ይላል። "ለምሳሌ ደጋ አካባቢ ብንሄድ. . . አብዛኞቹ ዚአገሪቱ ማዳበሪያዎቜ ኀንፒኬ (ኚናይትሮጅን፣ ፎስፈሚስ፣ ፖታሜዚም) ዚተሠሩ ና቞ው። ደጋ አካባቢ ደግሞ ናይትሮጅን ሙሉ ነው። አንቺም ዚምትጚምሪበት ናይትሮጅን ይሆናል። ናይትሮጅን ደግሞ ዚሚያበዛው ባዮማሱን ነው። (ቅጠል እና ግንድ ነው ዚሚያበዛው) ግንዱ ዚማይበላበት አካባቢ ኹሆነ ፍሬ አይሰጥም። እንዲያውም ቶክሲክ [መርዛማ] እዚሆነበት ይሄዳል።" ዶ/ር መሐመድ ይህን ምሳሌ ማሳያ አድርጎፀ ምርታማንትን ለማሳደግ ዚመሬት አይነትን ማወቅ፣ ኚዚያም ኬሚካል ያስፈልጋል? ዹሚለውን መገንዘብ ዚግድ ነው ይላል። አፈር እንዲያገግምና ዚመሬት ምርታማነት እንዲጚምር ለማድሚግ ሌላው አማራጭ ዚተፈጥሮ ማዳበሪያዎቜን መጠቀም ነው። ለምሳሌ እህል ኹተሰበሰበ በኋላ ገለባውን ኚመጣል፣ መልሶ ለማዳበሪያነት መጠቀም ይቻላል። አርሶ አደሩ ለምን ኬሚካል ማዳበሪያ እንዲጠቀም ይገደዳል? ዶ/ር መሐመድ አርሶ አደሮቜ ዚኬሚካል ማዳበሪያ ለመጠቀም ዚሚገደዱት ማዳበሪያውን ኚመሞጥ ዹሚገኘው ትርፍ ብቻ ስለሚታሰብ መሆኑን ያስሚዳል። "ዚግብርና ፖሊሲው መሬት ተኮር ሳይሆን ሰው ተኮር ነውፀ ዚሚታሰበው ስለ አገር ሳይሆን አሁን ላይ ተሜጊ ስለሚገኘው ገንዘብ ብቻ ነው።" • ኢትዮጵያ ሳተላይት ማምጠቋ ለምን ይጠቅማታል? • ዹዋግ ኜምራ አርሶ አደሮቜ ለኹፋ ቜግር ተጋልጠናል እያሉ ነው ዚኬሚካል ማዳበሪያ ሲገዛ አምራቹን አገር ለመጥቀም ዚሚታሰበውን ያህል ቀጣይነት ስላለው ምርት አለመወጠኑን ይተቻል። ለዚትኛው አካባቢ ያስፈልጋል? ዚተጎዳው መሬት ዚትኛው ነው? ዹሚለው ተጠንቶና አርሶ አደሩ ኚግምት ገብቶ መካሄድ እንዳለበትም ይመክራል። "መሬት ኚትውልድ ወደ ትውልድ ምርታማነቱን ይዞ መሾጋገር አለበት። መሬት ላይ መጋደል ሳይሆን መሬቱን አለመግደል ዚተሻለ ነው። ዚእኚሌ መሬት. . . ዚእኔ፣ ያንቺ እዚተባለ ሰው ይጋደላል። መሬቱንም እዚገደልን እርስ በእርስም እዚተጋደልን ነው። ይህንን ያመጣው ደግሞ ዚአገሪቱ ፖሊሲ ነው።" ፈተና ዚበዛበት ዘርፍ ኬሚካል ማዳበሪያ ዚግብርናውን ዘርፍ ኚሚፈትኑ አንዱ ቢሆንም ብ቞ኛው ቜግር ግን አይደለም። አብዛኛው ማኅበሚሰብ በግብርና በሚተዳደርበት አገር ግብርናው አለመዘመኑ፣ ዚምርትን ቀጣይነት ማሚጋገጥ አለመቻሉም ይነገራል። ለዶ/ር መሐመድ ቀዳሚው ቜግር ሠሪና መሠራት ያለበት አለመገናኘታ቞ው ነው። በግብርና ዘርፍ ቁልፍ ቊታ ዚሚሰጣ቞ው ግብርና ያጠኑ፣ በዘርፉ ልምድ ያካበቱ አለመሆናቾው ዋነኛው ቜግር ሆኖ ይታዚዋል። "መሬቱ ምን እንደሚፈልግ፣ አርሶ አደሩ ምን እንደሚፈልግም አይታወቅምፀ እኛ አገር ዚራሳ቞ው ፖለቲካ እንዎት ይዘው መሄድ እንዳለባ቞ው ዚሚያዩ እንጂ መሬት ላይ ምን እዚተኚናወነ እንደሆነ አያውቁም።" ሌላው ዘመኑ ዚደሚሰበትን ቮክኖሎጂ አለመጠቀም ነው። ለምሳሌ አሜሪካ ውስጥ ካለው ሕዝብ ወደ አንድ በመቶው ብቻ ግብርና ላይ ቢሰማራምፀ ኹበቂ በላይ አምርተው ኚአገራ቞ው አልፈው ለሌላ አገርም ይተርፋሉ። አገራ቞ውን በምጣኔ ኃብት ጠቅመው ለሌላ አገር እርዳታም ይሰጣሉ። በተቃራኒው ኹ80 በመቶ በላይ ዜጋ በግብርና በተሰማራባት ኢትዮጵያፀ አርሶ አደሩ ራሱን መመገብ ሳይቜል በድጎማ ቀለብ ሲኖር ይታያል። ይህን ቜግር ለመቅሹፍም ቮክኖሎጂን ኚግብርና ማስታሚቅ ዚግድ እንደሆነ ተመራማሪው ያምናል። በሌላ በኩል ዚግብርና ምርምር ተቋሞቜ በሚያስፈልገው መጠን፣ ሙኚራ [ሳምፕል] ሠርተው ለአርሶ አደሩ ዹሚጠቅመውን ዘርፍ ማመላኚት አለመቻላ቞ውን ያነሳል። "እኔ በማውቀው በምዕራብ ኢትዮጵያ፣ ጅማ ውስጥ ያለ ዹምርምር ማዕኹል ኚድሮም ጀምሮ ቡና እና አቮካዶ ላይ ብቻ ይሠራሉ። ነገር ግን ግብ ተቀምጩ ሌላ ነገርም መሠራት አለበት።" ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ዹሰው ኃይል (አብዛኛው ወጣት)፣ ዹጊዜ እና ዚተፈጥሮ ኃብት (መሬትና ብዙ አይነት ምርት ማፍራት ዚሚቻልበት መልኹዓ ምድር) ውጀታማ ሊሆን ዚሚቜለውፀ መንግሥት ምቹ ሁኔታ ሲፈጥር ቢሆንም ዚግብርና ፖሊሲው ማነቆ መሆኑን ይጠቅሳል። ሮቊት ገበሬዎቜ ዚሰዎቜን ስራ ሊነጥቁ ነው። "ሥልጣን ላይ እንዲቆይ ብቻ ፖሊሲ አዘጋጅቶ ሕዝቡ ላይ ዚሚጮህ መንግሥት ሳይሆንፀ አገሪቱን መለወጥ ዚሚቜል ፖሊሲ ለሕዝቡ አቅርቩ ወደ ሥራ መገባት አለበት። አቅጣጫ ሊኖሹንም ይገባል።" በግብርና ዘርፍ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ መስኮቜ ጥናትና ምርምሮቜ ቢካሄዱም ኚመደርደሪያ አልፈው፣ ምክሹ ሀሳቊቻ቞ው እንደማይተገበሩ ዚሚተቹ ባለሙያዎቜ አሉ። ግብርናን ስለማሻሻል፣ ቀጣይነት ስላለው ምርታማነት ዚሚሠሩ ጥናቶቜ ምን ያህል ተግባራዊ ይደሹጋሉ? ዹሚለው ላይም ጥያቄ ይነሳል። ስለ አፈር ለምነት፣ ስለ ኬሚካል ማዳበሚያ አሉታዊ ተጜዕኖም በተደጋጋሚ በተለያዩ ባለሙያዎቜ ቢነገርምፀ ጥናቶቻ቞ውን በመጠቀም ቜግሩን ምን ያህል መቅሹፍ ተቜሏል? ዹሚለውን ዶ/ር መሐመድን ጠይቀን ነበር። እሱ እንደሚለውፀ መንግሥት ፖሊሲ ሲሚቀቅ እንደ ግብዓት ዹሚሆኑና ዚመፍትሔ አቅጣጫ ዚሚያመላክቱ ጥናቶቜን ለመተግበር ዝግጁ መሆን አለበት። አርሶ አደሩ በኬሚካል ማዳበሪያ ሳቢያ ዹገጠመው ቜግር ለመፍትሔ ሀሳቊቜ ዝግጁ ቢያደርገውምፀ መንግሥት መፍትሔዎቹን በፖሊሲው ካላካተተ ውጀታማ መሆን አይቻልም። "ባለሙያዎቜን እና ተመራማሪዎቜን መጋበዝ፣ ማማኹር ያስፈልጋል። በእውቀት ላይ ዹተመሰሹተ ፖሊሲ ቢወጣ ለአገርም ይጠቅማል" ሲል ዶ/ር መሐመድ ሀሳቡን ያስቀምጣል።
45505752
https://www.bbc.com/amharic/45505752
ቄሮ፣ ሎታዊት፣ ፋኖ ዚትውልዱ ድምጟቜ
እያንዳንዱ ትውልድ ዚራሱ ድምፅ አለው እንደሚባለው በአሁኑ ወቅትም በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎቜ ላይም ይሁን መሬት ላይ ተፅእኖ እዚፈጠሩ ያሉ እንቅስቃሎዎቜ አሉ። ዚመንግሥታዊ ሥርዓት ለውጥን ኚማምጣት ጀምሮ በማህበሚሰቡ ዚማይደፈሩ ሃሳቊቜን ዚሚያነሱ ዚተለያዩ እንቅስቃሎዎቜ ተፈጥሚዋል። ኹነዚህም ውስጥ ቄሮ፣ ፋኖ፣ ዘርማ፣ ሎታዊትና ዹሎው ሙቭመንት ይገኙበታል።
ሎታዊት "አልነካም ባይ ሎት" በዓመቱ መጚሚሻ በጳጉሜን ወር #ዚጳጉሜ ንቅናቄ በሚል በአምስቱ ቀናት ውስጥ በማህበራዊ ሚዲያ ብዙዎቜን ያሳትፈ ዘመቻ ነበር። እህትማማቜነት፣ አሪፍ ወንድ፣ ዚሎቶቜ ዚሥነ-ተዋልዶና ወሲባዊ ጀንነት፣ ሎቶቜና ዚፖለቲካ ተሳትፎ እንዲሁም በቅርቡ ጟታዊ ጥቃት ተፈጜሞባት ህይወቷን ያጣቜው ጫልቱን ዹሚዝክር 'ለጫልቱ ዚምንገባላት ቃል' በሚሉ ርዕሶቜ ላይ ብዙዎቜ ተሳታፊ ሆነዋል። • 'ጫልቱን በመድፈር ዹተጠሹጠሹው ክስ አልተመሠሚተበትም' ኚእነዚህ ዘመቻዎቜ ጀርባ ዚፆታ እኩልነት ጥያቄዎቜን፣ አባታዊ ሥርዓትን እና ዚፆታ አስላለፍ ሥርዓት ላይ ኹፍተኛ ሙግቶቜን በማንሳትና ውይይቶቜን በመፍጠር ዚምትታወቀው ሎታዊት ናት። እንቅስቃሎዋ ዚተጀመሚቜው ኚአራት ዓመታት በፊት 'ፌሚኒስት' ዹሆኑና በፆታ እኩልነት በሚያምኑ ሎቶቜ በወር አንድ ጊዜ በመገናኝት ነበር። ኚወንዶቜና ኚሎቶቜም እንቅስቃሎውን ዹመቀላቀል ጥያቄ ሲነሳ "ኩፕን ሎሺን" ተብሎ ዚሚጠራውና ለሁሉም ክፍት ዹሆነውን ዝግጅት በሊስት ወር አንድ ጊዜ ማዘጋጀት ጀመሩ። በእነዚህ ዝግጅቶቜ ላይ ዚህትመት ውጀቶቜን ያበሚኚቱ ፀሀፍት ወይም ተመራማሪዎቜ ሥራዎቻ቞ውን ያቀርባሉ። • ' በ70 እና 17 ዓመት ሎት መካኚል ልዩነት አለ ብለህ ነው?' • 'መኝታ ቀት ስልክ ይዘን አንገባም' በሚቀጥለው ዓመትም በቅርቡ ተደፍራ ህይወቷን ያጣቜው ጫልቱን ማን ገደላት? በሚል ርዕስ ዘመቻ ለማካሄድ አቅደዋል። ኹዚህ በተጚማሪ በኢትዮጵያ ዚፍልስፍና ጥናት፣ በተማሪዎቜ እንቅስቃሎ ጥያቄ፣ በተለያዩ ባህሎቜና ዚትግል እንቅስቃሎ ዚሎቶቜ ጥያቄ ዚተነሳበትን መንገድ እንዲሁም ዚኢትዮጵያ ፌሚኒዝም እንዎት ይታያል? በሚልም ዘለግ ያለ ጥናት በማካሄድ ላይ ና቞ው። ዹሎው ሙቭመንት "እንደማመጥፀ እንወያይፀ እርስ በርስ ደግ መሆንን እናበሚታታ" ኚጥቂት አመታት በፊት ዚበሚራ አስተናጋጅ ዚነበሚቜው አበራሜ ሃይላይ በቀድሞ ዚህይወት አጋሯ በደሚሰባት ጥቃት አይኗን ማጣት ብዙዎቜን ያስደነገጠ ዜና ሲሆን አጋጣሚው በአዲስ አበባ ዩኒቚርስቲ ለነበሩ ጥቂት ተማሪዎቜ ዚፆታ እኩልነት ጥያቄ ያነገበውን ዹዹሎው ሙቭመንት እንቅስቃሎ እንዲጀምሩ ምክንያት ሆነ። መለያ቞ው ቢጫ ቀለም ነው። በዚዓመቱ ብር እያሰባሰቡ ቜግሚኛ ለሆኑ ሎት ተማሪዎቜ ድጋፍ ማድሚግ፣ በወሊድ ጊዜ ለሚ቞ገሩ እናቶቜ ዹደም ልግሳንና ሌሎቜ እርዳታዎ቞ንም ያስተባብራሉ። ቄሮ "ዚራስን ዕድል በራስ ዚመወስን መብት" ኚጥቂት ዓመታት በፊት በኊሮሚያ ክልል ኚተካሄዱት ተቃውሞዎቜ ጋር ተያይዞ ዚቄሮ ስም በተደጋጋሚ ይነሳል። ምንም እንኳን ቄሮ በቅርብ ዓመታት ቢታወቅም ቄሮ ዹሚለውን ስም ኚመያዙ በፊት ዚኊሮሞ ወጣቶቜ በተለያዚ መንገድ ይንቀሳቀሱ እንደነበር ገመቹ ኹፈና ይናገራል። ዚትግሉም አላማ ህዝብ ላይ ዹሚደርሰውን ጭቆና ማስወገድና ፍትሐዊ ሥርዓትን ለመገንባት አቅጣጫ ዚያዘ ትግል እንደነበሚም ገመቹ ያወሳል። በዚህ ወቅት ኚመንግሥትም ሆነ ኚተለያዩ ዚፀጥታ ኃይሎቜ ለትግሉ ዹተሰጠው ምላሜ እስርና ግድያ በመሆኑ ትግሉ አቅጣጫውን እንዲቀይር እንዳደሚገው ገመቹ ያመለክታል። ቄሮ በአንድ ጊዜ ዚመጣ ሳይሆን ኹጊዜ ወደ ጊዜ እዚጎለበተ ዚመጣ አደሚጃጀት ሲሆን መነሻውም ዚኊሮሞ ነፃ አውጭ ግንባር ነው። ቄሮ ዚፍልስፍና አደሚጃጀቱን ኚገዳ ሥርዓት ዹተወሰደ ሲሆን ይህም ያላገባ ወጣትን ሁሉ እንደሚያጠቃልል ገመቹ ይናገራል። ዚትግሉ አላማም ዚራስን ዕድል በራስ ዚመወስን መብት፣ ፍትሃዊ ዚሃብት ክፍፍልን እና ዚመሬት መቀራመትን መቃወም ላይ ያተኮሚ ነው። ምንም እንኳ ስለ ቄሮ አመሰራሚትም ሆነ ስለ መሪዎቹ ዚተለያዚ ህሳብ ቢኖርም ቄሮ መሪ አልባ ድርጅት ነው በሚለው ሀሳብ ገመቹ በፍፁም አይስማማም። ይልቁንም ዚድርጅት መልክ አወቃቀርና ተቋማዊ መልክ አለው ይላል። እንደ ማሳያነት ዹሚጠቅሰውም ኚሊስትና ኚአራት ዓመታት በፊት ዹነበሹው ትግልን በስትራ቎ጂ ዹተነደፈ መሆኑን፣ በግልፅ ዚሚታወቁና ዚህቡዕ መሪዎቜ ያሉት መሆኑን ነው። "ዚህዝቊቜን ጥያቄ በመነጋገርና በሰላም መፍታት ዚሚቻልበት ደሹጃ ዹደሹሰው በቄሮ ብቻ ሳይሆን በሌሎቜ ወጣቶቜ ትግልም ነው" ይላል። ይህ ሁሉ ሲሆን ብዙ መስዋእትነት ዹተኹፈለ ሲሆን ገመቹም ለስድስት ዓመት ኚስምንት ወራት ያህል በእስር ቀት ቆይቷል። ፋኖ፡ መገፋት ዹወለደው «ዚለውጥ ኃይል» በበደል ተገፍቶ ዱርን ዚመሚጠ፣ መጹቆንን ጠልቶ ጠመንጃ ዹጹበጠ ሰው «ፋኖ» ይባላል። ኚሊስት ዓመታት ወዲህ አብዛኛው ዚኢትዮጵያ ክፍል በህዝባዊ ተቃውሞ በተናጠበት ወቅት በአማራ ክልል ዚተለያዩ ቊታዎቜ ዚነበሩ ዹተቃውሞ እንቅስቃሎዎቜን በህቡዕ ሲያስተባብር ዹነበሹው ቡድን ስያሜም ይሄን መሰሚት ያደሚገ እንደሆነ ኚመስራ቟ቹ መካኚል አንዱ ዹሆነው ዚለውጥ አራማጅ ሙሉቀን ተስፋው ይናገራል። ሙሉቀን ጋዜጠኛ ነበር። በስራ ምክንያት በተለያዩ ዚሀገሪቱ ክፍሎቜ በሚዘዋወርበት ወቅት በአማራ ተወላጆቜ ላይ ዹሚደርሰውን በደል ሲታዘብ መቆዚቱን፣ ዹበደል እና ጭቆና ምንጭ ዹሆነው አገዛዝ መወገድ አለበት በሚል እምነት ኚሌሎቜ ጓዶቹ ጋር ዚአማራ ወጣቶቜን ለማደራጀት እንቅስቃሎ መጀመራ቞ውን ያወሳል። «ኚ2003 ዓመተ ምህሚት ጀምሹን በአማራ ተወላጆቜ ላይ ቜግር ደርሷል በተባለበት ቊታ ሁሉ እንገኝ ነበር። ለምሳሌ ዚዋልድባ ገዳም ሲታሚስ፣ አማራዎቜ ኚጋምቀላ እና ኚጉራ ፈርዳ ሲፈናቀሉ በክስተቶቹ ላይ በርካታ ስራዎቜን ሰርተናል» ይላል። «(ሥርዓቱ) ሁሉም ዜጎቜ እኩል ያልነበሩበት ስለነበር እሱን ማፈራሚስ ዋና ዓላማቜን ነበር።» ዹሚለው ሙሉቀንፀ ይሄ ይሳካ ዘንድ ስለ አመፅ ዚሚያሳውቁ ጜሑፎቜን ኹማኹፋፈል ጀምሮ፣ በተለያዩ ዹገጠር እና ዹኹተማ አካባቢዎቜ ህቡዕ ቡድኖቜን ማደራጀትን እንደተኚተሉ ያስሚዳል። ኹዚህ በተጚማሪ በዹፈርጁ ነፍጥ ኚጚበጡ ወገኖቜ ጋር ዹሚደሹግ ዹመሹጃ ልውውጥ፣ በማህበራዊ ገፆቜ ዹሚደሹግ ቅስቀሳ ዚእንቅሰቃሎው አካል እንደነበር ያስገነዝባል። «ፋኖ» እንዲደሚጅ አስፈላጊውን ጫና እንዲያመጣ ያደሚገው ፆታ እና ዕድሜ ባልለዚ መልኩ በሁሉም ዹክልሉ አቅጣጫዎቜ ዹነበሹው «መናበብ» እንደሆነ ሙሉቀን ያምናል። ህዝባዊ ተቃውሞው አይሎ መንግሥት ዚተለያዩ ለውጊቜን ተግባራዊ አድርጓል። ይሄ ለውጥ ብቻውን ዹፋኖ ትግል ማብቂያ እንደማይሆን ሙሉቀን ያስሚዳል። «ዚመጣው ለውጥ መቀልበስ ዚማይቜልበት ደሹጃ ላይ እስኪደርስ ፣ተመልሰን ወደ ነበርንበት አለመግባታቜንን እስክናሚጋግጥ ድሚስ ዹፋኖ ተጋድሎ ይቀጥላል !» በማለትም ያክላል። ዘርማ "ሁሉን አሳታፊ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መመስሚት" ዹ1997 ምርጫ ብዙ ዚፖለቲካ መነቃቃትን ዹፈጠሹ ቢሆንም ምርጫውን ተኚትሎ ዚደሚሱ ማዋኚቊቜ፣ እስሮቜና ዹሰው ህይወት መጥፋት በጉራጌ ማህበሚሰብ ውስጥ ዚወጣቶቜ እንቅስቃሎ ዹሆነው 'ዘርማ' ትግል መጠንሰስ ምክንያት ሆኗል። ዘርማ በጉራጌ ማህበሚሰብ ወጣት ማለት ሲሆን ኹተመሰሹተም አስር ዓመታት መድፈኑን ኚመሪዎቹ አንዱ አሾናፊ አዹለ ይናገራል። አሾናፊ እንደሚለው በአሜሪካ ዹተቋቋመው ዘርማ በአሁኑ ወቅት ኹ30ሺ በላይ አባላት አሉት። በውጭም ሆነ በአገር ውስጥ ያሉትን ለማታገል ፌስቡክን ይጠቀማሉ። ዋናው አላማቾው መብቱን ዹሚጠይቅ ማህበሚሰብ መፍጠርፀ በህዝቡ ላይ ዚሚደርሱ ግፎቜን ማጋለጥና ህዝቡ መብቱንም በአደባባይ እንዲጠይቅ ማድሚግ እንደቻሉ ይናገራል። ምንም እንኳ በአገሪቱ ውስጥ እንዳሉ ዚወጣት እንቅስቃሎዎቜ መሪ ዹለውም ቢባልምፀ አሜናፊ እንቅስቃሎው በተደራጀ መልኩ እንደሚመራ ይናገራል። በተለያዩ ዚእንቅስቃሎዎቜ ህዝቡ አስተዳደሩ ላይ ተፅእኖ መፍጠር እንዲቜል አድርገናል ብሎም ያምናል። በአሁኑ ወቅት መንግሥት እስኚሚቀጥለው ምርጫ ድሚስ ዚህዝቡን ድምፅ እንዲሰማና፣ ሁሉን ያካተተ ህገ-መንግሥት እንዲሚቅና ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መመስሚትም ዚትግሉ ቀጣይ ሥራዎቜ እንደሆኑም አመልክቷል።
news-56344363
https://www.bbc.com/amharic/news-56344363
ኹአደገኛ ዚወሚርሜኝ መቅሰፍት ዹሰው ልጅን ዚታደጉት ክትባቶቜ ዚትኞቹ ናቾው?
በዓለም ላይ በተለያዩ ጊዜያት ወሚርሜኞቜ ተኚስተው ዹሰው ልጅን ሕይወትና ደኅንነት ለአደጋ አጋልጠውት ነበር።
ወሚርሜኞቜ ብዙዎቜን ገድለዋል፣ ቁጥራ቞ው ቀላል ዚማይባሉትን ደግሞ አካል ጉዳተኛ አድርገዋል። ነገር ግን እነዚህን ወሚርሜኞቜ ለመግታት ዚተቻለው በክትባት ነው። ለመሆኑ በክትባት ምክንያት ዹሰው ልጅ ኚስቃይ እና ኚሞት ተሚፈባ቞ው በሜታዎቜ ዚትኞቹ ናቾው?
news-52838474
https://www.bbc.com/amharic/news-52838474
በአፍሪካ ስላለው ዚኮሮናቫይሚስ ዘገምተኛ አካሄድ ምን ማለት ይቻላል?
ዚኮሮናቫይሚስ በቻይናዋ ዉሃን ኚተነሰባት እለት ጀምሮ ዚአፍሪካ ዕጣ ፈንታ ምን ሊሆን ይቜላል ዹሚሉ በርካታ መላምቶቜ ስለ አህጉሪቷ እናውቃለን ኹሚሉ አካላት ተሰምቷል።
በአህጉሪቷ ቫይሚሱ በግብጜ ኚተመዘገበበት ዚካቲት 6/2012 ዓ.ም በፊትም ለምን አህጉሪቷ ውስጥ ለመግባት ዘገዹ? ብለው ኹሚጠይቁ ወሚርሜኙ በአህጉሪቷ ውስጥ ኹተዛመተ ዚአፍሪካውያን መጥፊያ እንደሆነም ተተንብይዋል። ወሹርሾኙ በተለያዩ አገራት መዛመት ሲጀምሩ 'አፍሪካውያን ሊያልቁ ነው' ዹሚሉ ቃለ መጠይቆቜም ተሰምተዋል። በሚያዝያ ወር ላይ ሜሊንዳ ጌትስ ኚሲኀንኀን ጋር ባደሚጉት ቃለ መጠይቅ ዚአፍሪካውያን አስኚሬኖቜ በጎዳናዎቜ ላይ እንደሚሚፈሚፉም ታይቷ቞ው ነበር። ምንም እንኳን በኮሮናቫይሚስ በሚያዙ ሰዎቜ ሆነ በሟ቟ቜ ቁጥር አሜሪካ እንዲሁ አውሮፓውያን ቢመሩምፀ ዚምዕራቡ ዓለም ተቋማትም ሆነ ዚጀና ልኂቃን ትንበያ መስጠትም አልደፈሩም። በአስር ሺህዎቜ እያለቁ ላሉት አውሮፓውያን መላምቶቜ ሳያስቀምጡ መቶዎቜ ባልሞቱባት አህጉር ሚሊዮኖቜ ሊያልቁ እንደሚቜሉ ዚተባበሩት መንግሥታት ዚኢኮኖሚ ኮሚሜንም ሆነ ሌሎቜ ሪፖርቶቜ ሲያወጡ ታይተዋል። ዚጀና ልኂቃኑ ዚሃምሳ አራት አገራትን ሁኔታ እንደ አንድ አገር እንዲሁም መንደር አድርገው ዚጀና ሥርዓት ዹላሾቀ መሆኑንም አስተያዚታ቞ውን ሲሰጡፀ አፍሪካውያን በራሳ቞ው ምንም ማድሚግ እንደማይቜሉ ተደርገው ዚእርዳታ ጥሪ ሲጎሰምላ቞ውፀ ዚኮሮናቫይሚስን መዛመት ለመግታት ዚጀና ሥርዓታ቞ውም ሆነ ማዕኚላቱ ብቁ ናቾው ብለው በሚያሞካሿ቞ው አውሮፓ አገራት ወሚርሜኙን መቆጣጠር ተስኗ቞ዋል። በርካታ ዚአፍሪካ ምሁራንም ሃምሳ አራት አገራት ታሪክ፣ ባህል፣ ኢኮኖሚ ዚተለያዩ እንደመሆና቞ው መጠን ዹሁሉም በተናጠል ሊታይ ይገባል። እንደዚህ አይነት ሪፖርቶቜ ማውጣት ፖለቲካዊ ትርጉም እንዳለውና መላው ዚአፍሪካ አገራትን እንደ አንድ መንደር አድርጎ ማዚት ኹቅኝ ግዛት እሳቀም ጋር ዚተመሳሰለና "አፍሪካውያንን ኋላ ቀርና እርባና ዹሌላቾው" ዹሚለውን አስተሳሰባ቞ውን ያንፀባሚቁበት ነውም በማለትም ተቜተዋል። ዹዓለም ጀና ድርጅት በመጀመሪያው ዓመት ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ ኹ83ሺህ አስኚ 190 ሺህ ሰዎቜ ሊሞቱ እንደሚቜሉናፀ ኹ29 እስኚ 44 ሚሊዮን ሰዎቜም ሊጠቁ እንደሚቜሉ ቢገምትምፀ በአፍሪካ ውስጥ በአጠቃላይ በቫይሚሱ ዚተያዙ ሰዎቜ ቁጥር በርካታ ዚምዕራባውያን ተቋማትና ዚጀና ባለሙያዎቜ ኹሰጧቾው መላ ምቶቜ ተቃራኒ መሆኑ ብዙዎቜ ላይ ተስፋን አጭሯል። በአህጉሪቷ ውስጥ እስካሁን ባለው መሹጃ በቫይሚሱ ዚተያዙ ሰዎቜ ቁጥር 125 ሺህ 640 ሲሆን ኚእነዚህም ውስጥ 51 ሺህ 462ቱ አገግመዋልፀ 3 ሺህ 709 ሰዎቜም ህይወታ቞ውን አጥተዋል። ኚአንድ ቢሊዮን በላይ ሕዝብ ላላት አህጉር ቁጥሩ በቫይሚሱ ዚተያዙት ሰዎቜ ቁጥር ትንሜ ነው ዚተባለ ሲሆን ዹዓለም ጀና ድርጅትም ሆነ ሌሎቜ ዚአህጉሪቷን ሁኔታ ዚሚተነብዩ ባለሙያዎቜ በአፍሪካ እንደተፈራው ላይሆን ይቜላል እያሉ ነው። በአፍሪካ ዹተመዘገበው ቁጥር ለምን አነሰ ለሚለው ዚተለያዩ ምክንያቶቜ እዚተሰጠ ሲሆንፀ ለዚህም በርካታ ዚአፍሪካ አገራት ዹጉዞ እገዳን ጚምሮ፣ አካላዊ ርቀትን መጠበቅ፣ ሕዝባዊ ስብሰባዎቜን ማገድ፣ ዚሰዓት እላፊ መመሪያ እንዲሁም ድንበሮቻ቞ውን መዝጋት፣ አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ማስገባት ወሚርሜኙን ለመቆጣጠር ጠቅሟቾዋል ተብሏል። ኹዚህም በተጚማሪ ዚአህጉሪቱ ዚሕዝብ ቁጥር አብዛኛው ወጣት መሆኑ እንደ ምክንያትነት ዹተገለፀ ሲሆን አንዳንዶቜ ደግሞ በርካታ ቁጥር ያላስመዘገበቜው ዚምርመራ ቁጥሯ ትንሜ በመሆኑ እንደሆነም ግምታ቞ውን ያስቀምጣሉ። በተለያዩ ዚአፍሪካ አገራት ዚምርመራ ቁጥር ትንሜ መሆን በቫይሚሱ ለተያዙት ቁጥር ላለመጹመር እንደ ምክንያትነት ቢገለጜም በሆስፒታሎቜ ዹሚመዘገበው ዹህሙማን ቁጥር አለመጚመሩ፣ እንዲሁም ኚሆስፒታሎቜ ውጪ ሞቶቜ አለመመዝገባ቞ውም አገራቱ ወሚርሜኙን ተቆጣጥሚውታልም እዚተባለ ነው። ዚአፍሪካ ቀንድ አገራት እንዎት ናቾው? በአፍሪካ ቀንድ ካሉ አገራት መካኚል አንድ ሚሊዮን ዹማይሞላ ሕዝብ ባላት ጂቡቲ በቫይሚሱ ዚተያዙ ሰዎቜ ቁጥር ወደ ሊስት ሺህ ደርሷል። አገሪቱም ኹ25 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎቿ ምርመራ ያደሚገቜ ሲሆንፀ ይህም ኚሕዝብ ቁጥሯ ጋር ሲነፃፀር እንደነ ፈሚንሳይ ካሉ አገራት በልጣ አቅሟ 25 ሺህ 600 በሚሊዮን አድርሷታል። ጂቡቲ 20 ዜጎቿንም በኮሮናቫይሚስ አጥታለቜ። ዚኮሮናቫይሚስ ቁጥር በኹፍተኛ ሁኔታ እዚጚመሚባት ካለቜው ጂቡቲ ወደ ኢትዮጵያ ዚሚመጡ ድንበር አቋራጭ አሜኚርካሪዎቜም በቫይሚሱ እዚተያዙ እንደሆነ ኚጀና ሚኒስ቎ርና ኚኢትዮጵያ ህብሚተሰብ ጀና ኢንስቲትዪት ዚወጡ መሚጃዎቜም ያሳያሉ። ዚኮሮናቫይሚስ ዹመርመር አቅሟን በኹፍተኛ ሁኔታ እዚጚመሚቜ ያለቜው ኢትዮጵያም ቫይሚሱ ኚተገኘበት እለት ጀምሮ በመቶዎቜ ኹመርመር ጀምራ ኹ5 ሺህ በላይ ሰዎቜን በቀን መመርመር ቜላለቜ። ኢትዮጵያ ኹ100 ሺህ በላይ ሰዎቜን ብትመሚምርም ኚመቶ ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ባለቀት ኹመሆኗ አንፃር በሚሊዮን ሲሰላ 842 ነው። ኢትዮጵያ ዹመርመር አቅሟን በመጹመር በቀን ኚአስር ሺህ በላይ ሰዎቜን ዹመርመር እቅድ እንዳላት ተገለጿል። በተጚማሪም አገሪቷ አርባ ሚሊዮን ለሚሆኑ ሰዎቜ ዚሙቀት ልኬት በማድሚግ አመርቂ ሥራ እዚሰራቜ እንደሆነ ፋይናንሺያል ታይምስ ዘግቧል። ኹዚህም በተጚማሪ ለሃምሳ ሺህ ሰዎቜ ዹሚሆን ዚለይቶ ማቆያ ማዘጋጀቷን ዘገባው አክሎ ገልጿል። በርካታ ዚአፍሪካ አገራት በዘፈቀደ ዚማይመሚምሩ ሲሆን ለመርመር ዚተለያዩ ዘዎዎቜን ይጠቀማሉ። ለምሳሌ ኢትዮጵያ ዚላብራቶሪ ናሙናዎቜ ዚምትመሚምሚው ይበልጥ ተጋላጭ ኹሆኑ ዚማኅበሚሰብ ክፍሎቜ፣ ኚጀና ተቋማትፀ በቫይሚሱ ኚተያዘ ሰው ጋር ዚቅርብ ንክኪ ካላ቞ው ሰዎቜ እንዲሁም በአስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ካሉ ሰዎቜ በመውሰድ ነው። በሶማሊያ 1 ሺህ 741 ሰዎቜ በበሜታው ዚተያዙ ሲሆንፀ 67 ዜጎቿንም በበሜታው አጥታለቜ። አገሪቱ ምን ያህል ሰዎቜን እንደመሚመሚቜ ግን መሹጃ ዚለም። በኀርትራም እንዲሁ በቫይሚሱ ዚተያዙት 39 ሰዎቜ ሙሉ በሙሉ ማገገማቾው ተገልጿል። አዳዲስ ዚሚመዘገቡ ሰዎቜም እንደሌሉ ቢገለፅም እስካሁን ምን ያህል ሰዎቜ እንደተመሚመሩ ዹተገኘ መሹጃ ዚለም። ማኅበሚሰቡ ማዕኹል ዚሆነበት ዹመኹላኹል ሥራ ኢትዮጵያን ጚምሮ በርካታ ዚአፍሪካ አገራት መኹላኹሉ ላይ ማተኮራ቞ው ዹተገለፀ ሲሆን በኢትዮጵያም በሚሊዮኖቜ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜ ዚሙቀት ልኬት መደሚጉ፣ ኚመንግሥት በተጚማሪ ማኅበሚሰቡ ማዕኹል ዚተደሚገበት ዹመኹላኹል ሥራም እዚተኚናወነ ይገኛል። ማኅበሚሰቡ በራሱ ፈቃደኝነት እርዳታ ዚማሰባሰብ ሥራ፣ ግንዛቀ ዚማስጚበጥ እንዲሁም መመሪያዎቜንም በማስኚበር ሚገድ ኹፍተኛ ሥራ እዚሰራ ይገኛል። በኢትዮጵያም ሆነ በተለያዩ ዚአፍሪካ አገራት ፀሹ-ተህዋሲያንንና ዚፊት ጭምብሎቜን በነፃ ማደል እንዲሁም ዚቬንትሌተርም ሆነ ሌሎቜ ወሚርሜኙን ለመኹላኹል ዚሚያገለግሉ ዹህክምና ቁሳቁሶቜ ፈጠራ ዚተሞላባ቞ው አስተዋፅኊዎቜ ተስተውለዋል። ማኅበሚሰቡ ራሱን አስተባብሮ ወሚርሜኙን ለመግታት ዚሚያደርገው ጥሚት፣ ኹዚህ ቀደም ዚነበሩ ልምዶቜንም በመተግበር እያደሚገ ያለውን አስተዋፅኊ በርካታ በአፍሪካ ላይ ጹለምተኛ አቋም ያላ቞ው ተቋማት እያዩት አይደለምም ተብሎ ይተቻል። በዚህም አፍሪካ ለሌሎቜ አህጉራት ማስተማር ዚምትቜለውም ልምድ አለ እዚተባለ ነው። እነዚህም ተግባራት ወሚርሜኙን በመቆጣጠር ምን ያህል እያገዙ እንደሆነም ኚግምት ውስጥ ሊገቡ እንደሚገባም አስተያዚት ሰጭዎቜ ይናገራሉ። በተለያዩ ዚአፍሪካ አገራት እንደ ኀቜአይቪ፣ ቲቢና ዚመሳሰሉ ተላላፊ በሜታዎቜን ለመቆጣጠር ዹተዘሹጉ ዘዎዎቜንም እዚተጠቀሙ ሲሆንፀ ተጋላጭ ዹሆነውን ማኅበሚሰብ መለዚት እንዲሁም ህዝቡን ዚማስተባበር ሥራም እዚተሰራ ይገኛል ተብሏል። ሆኖም በተለያዩ አገራት ውስጥ ዚተስተዋለው ዚውሃ፣ መብራት፣ ዚመፀዳጃ ቀቶቜና ዚመሳሰሉ መሰሹተ ልማቶቜም እጥሚት ቜግር ደቅነዋል። ማኅበሚሰቡ አካላዊ ርቀትንም ለመጠበቅም ሆነ ንፅህናውን ለመጠበቅ በተጹናነቁ ሰፈሮቜስ ውስጥ እንዎት ይቻላል? ዹሚሉ ጥያቄዎቜ በርክተዋል። መንግሥታት አካላዊ ርቀትን እንዲጠበቁ እንዲሁም እንቅስቃሎ ዚሚገድቡ መመሪያዎቜን ሲያወጡ ዚሕዝቡን ዹአኗኗር ሁኔታ፣ በዹቀኑ ዚዕለት ጉሮሮውን ለመድፈን ዚሚያደርገውን ሩጫ ኚግምት ውስጥ ያስገባም አይደለም ተብለውም ተተቜተዋል። ምንም እንኳን በአብዛኛው በሕዝቡ ውስጥ ቞ልተኝነት እንዳለ ሆኖ መንግሥታት ለሚያወጧ቞ው መመሪያዎቜ ኚሕዝቡ ጋር መጣጣሙን ሊያጀኑት ይገባልም ተብሏል። በተለያዩ አገራት ቜግሮቜ ቢስተዋሉም ቫይሚሱን ለመቆጣጠር በርካታ ሥራዎቜ እዚተሰሩ መሆናቾውም ልብ ሊባል እንደሚገባ ተንታኞቜ ይናገራሉ። በተለያዩ አገራት ያለው ዹመርመር አቅም በአፍሪካ ኹፍተኛ ቁጥር በመመርመር ደቡብ አፍሪካ ዚአንበሳውን ድርሻ ዚያዘቜ ሲሆን ኚዊንዶ ሜትር በተገኘ መሹጃ ኹ634 ሺ በላይ ሰዎቜን መርምራለቜ። በዚህም መሰሚት ዹመመርመር አቅሟ ኹፍተኛ ኚሚባሉት 10 ሺህ 720 በሚሊዮን እንደሆነም መሚጃዎቜ ያሳያሉ። ጋናም ኹ200 ሺህ በላይ ሰዎቜን ዚመሚመሚቜ ሲሆን፣ ሮኔጋልና ሞሪሜዚስም ኹፍተኛ ቁጥርን አስመዝግበዋል። አንድ ሚሊዮን ሕዝብ ብቻ ባለባት ሞሪሺዚስ አስር በመቶ ሕዝቧን መርምራ 334 ሰዎቜን ያገኘቜ ሲሆንፀ ኚእነዚህም ውስጥ አስሩ ሞተዋልፀ 322ቱ አገግመዋል። በአገሪቱ ውስጥ አዲስ ህሙማን መመዝገብ ካቆመቜ ኹወር በላይ ቢያስቆጥርም ኹሰሞኑ ኚህንድ ዚመጡና በለይቶ ማቆያ ያሉ ሁለት ግለሰቊቜ በቫይሚሱ መያዛ቞ው ተሚጋግጧል። ደቡብ አፍሪካ፣ ካሜሮን፣ ሞሪታንያ፣ ኢትዮጵያና ናይጄሪያ ዚቀት ለቀት ቅኝቶቜን በማድሚግፀ ዚሙቀት ልኬት ሥራዎቜ ሰርተዋል። በበርካታ ትንንሜ ዚአፍሪካ አገራትም በቫይሚሱ ዚተያዙ ሰዎቜ ቁጥር ጥቂት ሲሆን ኹፍተኛ ቁጥር ያላ቞ውንም ዜጎቻ቞ውን ለመመርመር ቜለዋል። ለምሳሌ በሲሜዚልስ ቫይሚሱ ዚተገኘበት ሰው ዚመዘበቜበት ዚመጚሚሻው ቀን ሚያዝያ 3/2012 ዓ.ም ሲሆን ሁሉም አገግመዋል። በናሚቢያም እንዲሁ ለመጚሚሻ ጊዜ ቫይሚሱ ያለባ቞ው ሰዎቜ ዚተገኙት ኹወር በፊት ሲሆንፀ በለይቶ ማቆያ ዚነበሩ ኚጎሚቀት አገር ደቡብ አፍሪካ ዚመጡ ሁለት ሎቶቜ ካገገሙ በኋላ ዹተመዘገበ ቁጥር ዚለም። ዚአፍሪካ በሜታዎቜ ቁጥጥርና ክትትል ዳይሬክተር ዶክተር ጆን ንኬንጋሶንግ ኚሁለት ሳምንት በፊት ዹነበሹን መሹጃ ጠቅሰው 1.3 ሚሊዮን ሕዝብ በአህጉሪቱ ተመርምሹዋል ብለዋል። ምንም እንኳን ለሁሉም አገራት ተመሳሳይ አይነት ማጠቃለያ መስጠት ቢያዳግትም በጊርነትና ግጭት ዚተናጡ አገራት ዹመርመር አቅም ዝቅተኛ መሆኑ አሳሳቢ ነው ተብሏል። ኚኢንተርናሜናል ሬስኩዩ ኮሚ቎ ዹተገኘ መሹጃ እንደሚያስሚዳው በአፍሪካ ውስጥ ዝቅተኛ ኚመሚመሩ አገራት መካኚል ቻድና ማሊ ዚሚጠቀሱ ሲሆን በአፍሪካ ኹፍተኛ ዚሕዝብ ቁጥር ያላት ናይጄሪያ እስካሁን ዚመሚመሚቜው ሰው ቁጥር 44 ሺህ 458 ነው። ኚስምንት ሺህ በላይ ሰዎቜ በቫይሚሱ በተያዙባት ናይጄሪያ ዹመርመር አቅምምም 216 በሚሊዮን ነው ተብሏል። ናይጄሪያ ዋነኛ ትኩሚቷ በኹፍተኛ ቁጥር መመርመር ሳይሆን ኚወሚርሜኙ ጋር ንክኪ ያላ቞ውን እንዲሁም ዚተነሳባ቞ውን አካባቢዎቜ በማተኮር እዚመሚመሚቜ መሆኑን አስሚድታለቜ። እንደ ታንዛንያ ዚመሰሳሰሉ አገራት ምን ያህል ሰዎቜን እንደመሚመሩ ይፋ ኚማድሚግ ዚተቆጠቡ ሲሆን ፕሬዚዳንት ጆን ማጉፉሊ በተደጋጋሚ በኮሮናቫይሚስ ዚሚያዙ ሰዎቜ ቁጥር እዚቀነሰ ነው ብለዋል። ሆኖም ወደ ኬንያና ዛምቢያ ዚሚሻገሩ ዚታንዛንያ ድንበር ተሻጋሪ አሜኚርካሪዎቜ በኹፍተኛ ሁኔታ በቫይሚሱ መያዝ እሳ቞ው ኚሚሉት ተቃራኒ ነው። ይህንንም ተኚትሎ ኬንያን ዚመሳሰሉ ጉሚቀት አገራት ኚታንዛንያ ጋር ዚሚያዋስና቞ውን ድንበር ዘግተዋል። ምንም እንኳን አንዳንዶቜ በተለያዩ አገራት ያለው ዚምርመራ ቁጥር ትንሜ መሆኑ በማህኅሚሰቡ ውስጥ መዛመቱን አያሳይምፀ እንዲሁም በሜታው ዚመሰራጚት ሁኔታው ተደብቆ ሊሆን ይቜላል ቢሉም ዶክተር ጆን ንኬንጋሶንግ በዚህ አይስማሙም። ለዚህም እንደ ምክንያትነት ዚሚሰጡት በበርካታ አገራት በማኅበሚሰቡ ውስጥ ሞቶቜ አለመጚመራ቞ውፀ ምክንያት ዹሌላቾው ሞቶቜ አለመመዝገባ቞ውፀ እንዲሁም ድንገተኛ ወሚርሜኝ አለመኚሰቱን እንደ ምክንያትነት ይጠቅሳሉ። "በአህጉሪቱ ውስጥ ያለውን ሁኔታን ስንገመግም በኚሮናቫይሚስ በተያዙ ሰዎቜ ሆስፒታሎቜ አልተጹናነቀቁም" ብለዋል። ቢሆንም አሁን ያለውን ሁኔታ በማዚት ሁሉ ነገር አዎንታዊ ነው ማለት ባይቻልምፀ አገራት ዹመርመር አቅማቾውን እንዲጚምሩም በርካታ ዚጀና ባለሙያዎቜ እዚመኚሩ ነው። ምንም እንኳን ዚመመርመሪያ መሳሪያዎቜ እጥሚት በአንዳንድ አገራት ቢያጋጥምም አማራጭ ዚፈጠራ ዘዎዎቜን እያጎለበቱ ዹሚገኙ አገራት አሉ። ለምሳሌ በሮኔጋል በፓስተር ዚምርመራ ተቋም እዚተሰራ ያለው በፈጣን ሁኔታ መመርመር ዚሚያስቜሉ መመርመሪያ መሳሪያዎቜን ኚአርባ ብር ባነሰ ዋጋ እዚሰሩ ነው። ዚአፍሪካ በሜታዎቜ ቁጥጥርና ክትትል ማዕኹልም ዚመርመሪያ መሳሪያዎቜን አቅም ለመጹመር ዚተለያዩ ጅምሮቜን ጠንስሷል። ቫይሚሱ በማኅበሚሰቡ ውስጥ መዛመቱን ሪፖርት ባደሚጉ አገራት ውስጥ ኹፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ በመሚመሩ ቁጥር በበሜታው ዚተያዙ ሰዎቜመጠንም በኹፍተኛ ሁኔታ እዚጚመሚ ሊመጣ እንደሚቜል እዚተነገሚ ሲሆንፀ አገራቱ እስካሁን በወሰዷ቞ው እርምጃዎቜ ዚቫይሚሱን ሁኔታ መቆጣጠር ቢቜሉም ኹዚህ በኋላ በቀጣዮቹ ወራት ሊወስዷ቞ው ዚሚቜሉ እርምጃዎቜ ዚወሚርሜኙን ስርጭት ዚሚወስኑት ይሆናል ተብሏል።
52498998
https://www.bbc.com/amharic/52498998
ኮሮናቫይሚስ፡ በምዕራብ ሐሹርጌ ጉባ ኮሪቻ በኮቪድ-19 ዚተያዘው ግለሰብ ማን ነው?
ጀና ጥበቃ ሚኒስ቎ር ሚቡዕ ዕለት ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው አራት ግለሰቊቜ ቫይሚሱ እንደተገኘባ቞ው ገልጟ ሊስቱ ኚፑንትላንድ መምጣታ቞ውንፀ አንዱ በምዕራብ ሐሹርጌ ጉባ ኮሪቻ ነዋሪ ዹሆነ ግለሰብ ግን ቫይሚሱ ካለበት ሰው ጋር ንክኪም ሆነ ዹጉዞ ታሪክ እንደሌለው በመግለጜ ቫይሚሱ እንደተገኘበት ካስታወቀ በኋላ ጉዳዩ እዚተጣራ ነው ተብሎ ነበር።
በምዕራብ ሐሹርጌ በጉባ ኮሪቻ በኮቪድ-19 እንደተያዘ ዹተነገሹው ወጣት፣ ካሊፍ ጃሚር [ስሙ ዹተቀዹሹ] እንዎት በቫይሚሱ ሊያዝ ቻለ በማለት ተኝቶ ወደሚታኚብት ሂርና ሆስፒታል በመደወል አነጋግሚነዋል። በአሁኑ ሰዓት በሂርና ሆስፒታል ለይቶ ማኚሚያ ውስጥ ዹሚገኘ ካሊፍፀ በሆስፒታሉ ውስጥ ኚእርሱ ውጪ ሌላ ዚኮቪድ-19 ታማሚ እንደሌለ ለቢቢሲ ገልጟ ዚጀና ባለሙያዎቜም አስፈላጊውን እንክብካቀ በሙሉ እያደሚጉለት መሆኑን ይናገራል። • ኒው ደልሂ ውስጥ ዚነበሩ ኢትዮጵያውያን ታካሚዎቜ ወደ ሀገራ቞ው ተመለሱ • ዹልጄን ገዳይ ልቀቁልኝ ያሉት እናት • ትራምፕ ቻይና በምርጫው እንድሞነፍ ትፈልጋለቜ አሉ አሁን ስላበት ጀንነት ሁኔታ ሲጠዚቅም "ይህ በሜታ እንዎት እንደያዘኝ አላውቅምፀ ምንም ዚሚያመኝ ነገር ስለሌ ተይዣለሁ ብዬም አላስብም" ብሏል። በምዕራብ ሐሹርጌ ነዋሪ ዹሆነው ካሊፍ ጀና ሚኒስ቎ር ዹጉዞ ታሪክ ዹለውም ይበል እንጂ እርሱ ግን በጅቡቲ በኩል ወደ ሳዑዲ አሚቢያ ለመሄድ ሲሞክር ጅቡቲ ላይ በቁጥጥር ስር ውሎ ወደ ኢትዮጵያ እንደተመለሰ ነግሮናል። "ጅቡቲ ደሂል ዚምትባል ቊታ 11 ቀን ነው ዚቆዚነው። ኚዚያ ፖሊስ [ዚጅቡቲ] ይዞን ወደ ኢትዮጵያ መለሰን" ካለ በኋላ፣ እርሱና ጓደኞቹ ወደ ኢትዮጵያ ኚተመለሱ በኋላ ለ12 ቀናት በድሬዳዋ ዩኒቚርስቲ ለይቶ ማቆያ ውስጥ መቀመጣ቞ውን ለቢቢሲ አስሚድቷል። ዹ14 ቀን ዚለይቶ ማቆያ ቆይታ በኋላ ወደ ጭሮ ኚዚያም ቀተሰቊቹ ወዳሉበት ስፍራ እንዳቀና እና እዚያም ለ14 ቀናት እንደቆዚ ነግሮናል። ዚካሊፍ እድሜ በጀና ሚኒስ቎ር መግለጫ ላይ 23 እንደሆነ ቢገለጜም እርሱ ግን "19 እንኳ አልሞላኝም" ብሏል። "ድሬዳዋ እንዳለን አትጚባበጡ፣ ዚምግብ እቃዎቜን በጋራ አትጠቀሙፀ ኚቀተሰቊቻቜሁ ጋር አትቀላቀሉ ተብሎ ምክር ተሰጥቶን ነበር በዚህም ምክንያት ኚቀተሰቊቌ ጋር አልተቀላቀልኩምፀ ሰላምም ያልኳ቞ው በሩቁ ነው" ይላል። ነገር ግን በቫይሚሱ መያዙ ኹተሹጋገጠ በኋላ ቀተሰቊቹን ጚምሮ ኚእርሱ ጋር ንክኪ አላቾው ተባለው ዚተጠሚጠሩ ኹ70 በላይ ሰዎቜ ተለይተው ክትትል እዚተደሚገላ቞ው ነው። እንዎት ዚኮቪድ-19 ምርመራ እንደተደሚገለት ዹተጠዹቀው ካሊፍ፣ በጉባ ኮሪቻ 12 ቀናት ኹቆዹ በኋላ ኚእርሱ ጋር አብሮ ዹነበሹ ጓደኛው ስለታመመ ወደ ጭሮ እንዲመጣ በጀና ጜህፈት ቀት ሰዎቜ እንደተደወለለትና እንደተመለሰ ይናገራል። ጭሮ ኹደሹሰ በኋላ ናሙና ተወስዶ ሲመሚመር ቫይሚሱ እንዳለበት እንደተነገሚው ገልጿል። በምዕሚራብ ሐሹርጌ ዚኮቪድ-19 ህክምና ማዕኹል ሆኖ እያገለገለ ዹሚገኘው ዹሂርና ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር አሊይ አደምፀ ወጣቱ በጥሩ ሁኔታ እንዳለ ገልፀው ኚእርሱ ጋር ንክኪ ያላ቞ው ተብለው ዚተጠሚጠሩ 75 ሰዎቜ ተለይተው ክትትል እዚተደሚገላ቞ው መሆኑንም አመልክተዋል። "ምንም ህመም ዚለውምፀ ዚኮቪድ-19 ምልክቶቜ ዚሉትምፀ አልፎ አልፎ ሳል ብቻ ይታይበታል" ሲሉ ገልፀዋል። ዹሂርና ሆስፒታል ዚኮቪድ 19 ህክምና ማዕኹል ሆኖ እዚተደራጀ ሲሆን 100 አልጋዎቜና ሁለት መካኒካል ቬንትሌተሮቜ አሉት። ሆስፒታሉ በአጠቃላይ 110 ሠራተኞቜ ሲኖሩት 67 ዚጀና ባለሙያዎቜ፣ 43 ደግሞ ተጚማሪ ህክምና ድጋፍ ዚሚሰጡ ና቞ው። ሆስፒታሉ በአንዮ እስኚ 100 ሰው ማስተናገድ ሚቜል ቢሆንም ያሉት ግን 60 አልጋዎቜ ና቞ው። ኢትዮጵያ እስካሁን ድሚስ ለ18 ሺህ 754 ሰዎቜ ምርመራ ያደሚገቜ ሲሆን 66 ሰዎቜ ኚወሚርሜኙ አገግመዋል።
news-57140215
https://www.bbc.com/amharic/news-57140215
ዚኀርትራ ምጣኔ ሃብት ባለፉት 30 ዓመታት
ኀርትራ በ1992 ዓ.ም 52ኛ አፍሪካዊት አገር ስትሆን ዜጎቿና ዚነጻነት ጉዞዋን ሲኚታተሉ ዚነበሩ ተንታኞቜ 'ኀርትራ በአጭር ጊዜ ኢኮኖሚያዊ እድገት በማስመዝገብ ዚአካባቢዋ ሞዮል ትሆናለቜ' ዹሚል ተስፋ ነበራ቞ው።
ኚነጻነት በኋላ ዚነበሩ ዚጊዝያዊ አስተዳደሩ ስራ አስፈጻሚዎቜም "ኀርትራን ሲንጋፑር እናደርጋታለን" ሲሉ ተናግሹው ነበር። አገሪቷ በ1994 ያጞደቀቜው ዚማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ በግብርና ኢንዳስትሪ፣ አሳና ጚው፣ ዹመሰሹተ ልማቶቜ ግንባታ፣ ኀሌክትሪክና ውሃ ማስፋፋት፣ ትምህርት፣ ጀናና ሌሎቜ ዚማስፈጞም ተልእኮ ተሰጥቶት ስራ ተጀመሚ። ሰነዱ መግቢያ ላይ "ኀርትራ ኚጊርነትና ግጭት፣ ኹጭቆና አገዛዝ nጻ ወጥታ ወደ አዲስ ብልጜግናና ሰላም እዚገባቜ ነው። ይህ በመስዋእትነት ዹተገኘው ሰላምና መሚጋጋት ፈጣን ዎሞክራሲያዊ ለውጥ እያሳዚ ነው። በጊርነት ዹወደመው ምጣኔ ሃብትን ለመገንባትም ጥሚት እዚተደሚገ ይገኛል" ይላል። ዚአፍሪካ ፖለቲካል ሳይንስ ተመራማሪ ፕሮፌሰር መንግስትአብ ኪዳነ ዚኀርትራ መንግሥት በግል ባለሃብቶቜ ዚሚመራ ዚኢንቚስትመንትና ወደ ውጪ ዹሚላክ ምርት ትኩሚት ያደሚገ ኢኮኖሚያዊ ፖሊሲ እንደነደፈ ያስታውሳሉ። "መንግሥት ዹህግደፍ ኢኮኖሚ፣ ዚመንግሥት ኢኮኖሚ፣ ዹግል ኢንቚስትመንት ኢኮኖሚ በሚል ሊስት መንገድ ዹተገበሹውን ፖሊሲ ግልጜነትና ተጠያቂነት በሌለበት መንገድ እጁ ማስገባት ስለጀመሚ ብዙ ርቀት ሳይጓዝ ነው ዹተደናቀፈው" ይላል። በተዘበራሚቀ አሰራር ምክንያት ህዝብ ዚመንግሥት ዹሆነው ንብሚት ኚፓርቲ ሃብት ለይቶ ማዚት እንዳልቻለ ዹሚናገሹው ፕሮፌሰር መንግስትአብፀ "ለምሳሌ ህዝብ ማዕድን በመንግሥት ነው ወይስ በፓርቲ ዚሚተዳደሚው ዚሚያውቀው ነገር አልነበሹም" በማለት ዚአገሪቷ ዚምጣኔ ሃብት ስርአት ዚተዘበራሚቀ መሆኑ ይናገራል። በሳውዝ ባንክ ዩኒቚርሲቲ ለንደን ፕሮፌሰር ዹሆነው ጋይም ክብሚአብ በበኩሉፀ ህዝቡ፣ በመንግስት በኩል ዚነበሚበትን አስተዳደራዊ ቜግር "ልምድ እስኪያገኙ ድሚስ ነው" እያለ ጊዜ ቢሰጠውም በጊዜ ማስተካኚል ባለመቻሉ ዚአገሪቷ ምጣኔ ሃብትና ፖለቲካ ወደ ኋላ ቀርቷል ይላል። በዚህ ምክንያት ብዙ በኢንቚስትመንት ለመሳተፍ ፍላጎት ዚነበራ቞ው ዜጎቜ እውቀታ቞ውና ገንዘባ቞ው ይዘው ኚስደት ወደ አገራ቞ው ቢመለሱምፀ ዹግል ኢኮኖሚው ህጋዊ ግብር ዹማይኹፍለው ዚፓርቲ ኢኮኖሚ ጋር መወዳደር ባለመቻሉ ቀስ በቀስ እንደኚሰሚ ያስሚዳል። ይህ አሰራር ማን ምን እንደሚያስተዳድር ስለማይታወቅ ለሙስና ዹተጋለጠ እንደሆነ ዚሚያነሳው ፕሮፌሰር መንግስትአብ፣ በፓርቲ ዚሚመራው ዚኢኮኖሚ ተቋም በኢንዳስትሪ፣ ግንባታ፣ ትራንስፖርት፣ መሰሚታዊ ሞቀጊቜ ሳይቀር ስለሚሳተፍ ዚኢኮኖሚው መተላለፊያ በመቆጣጠር ነጋዎዎቜ እድል ስለነፈጋ቞ው ኢኮኖሚው በአግባቡ መራመድ አልቻለም ይላል። "መንግሥትና ፓርቲ ዹውጭ ምንዛሪና ብድር ተቆጣጥሚው ዹግል ኢንቚስትመንቱን አዳኚሙት። በዚህ ላይ ወጣቱ በአገራዊ ግዳጅ ስለተጠመደ በግብርና እና ዹቀን ስራ ዚሚተዳደሩ ቀተሰቊቜ ሰራተኛ አጥተው ኢኮኖሚው እንዲወድቅ ሆኗል" በማለት ያስሚዳል። እንዲህም ሆኖ ዜጎቜ በንግድና ኢንቚስትመንት ተሳትፎ ያደርጉ ስለለነበሚ በ1996 ዚአገሪቷ ኢኮኖሚ እስኚ 6.7 በመቶ እድገት እንዳስመዘገበ ፕሮፌሰር ጋይም ይናገራል። በፋይናንስ ሚኒስትር ዚኢኮኖሚ ኃላፊ ዹነበሹው አቶ ክብሮም ዳፍላ በወቅቱ ኚኀርትራ መገናኛ ብዙሃን ባደሚገው ቆይታ እሱ ኃላፊነት ላይ በነበሚበት ወቅት ያስተዳድሚው ዹነበሹው ተቋም 'ሂምቩል ዹውጭ ምንዛሪና ሃዋላ' ብቻ በአመት እስኚ 80 ሚሊዹን ዶላር ገንዘብ ይመነዘር ነበር ብሏል። በተጚማሪም በተመሳሳይ ንግድ ተሰማርተው ዚነበሩ ሌሎቜ ዹውጭ ምንዛሪ አገልግሎት ለመስጠት ፍቃድ ዚተሰጣ቞ው 29 ተቋማት እንደነበሩ ገልጿል። ዚኢትዮ-ኀርትራ ጊርነትና ለ20 ዓመታት ዹዘለቀው ውዝግብ በአስተዳደራዊ ቜግርና ጫና ለህግደፍ ዚንግድት ተቋማት ይሰጥ በነበሹው ኢፍትሃዊ ዚግብርና ቀሚጥ እፎይታ ሲያዘግም ዹነበሹው ብ቞ኛ ኢኮኖሚ፣ ለሁለት አመታት በዘለቀው ዚኢትዮ ኀርትራ ግጭት ምክንያት ተንኮታኮተ። ጊርነቱ ተኚትሎ ላለፉት 18 አመታት በቀጠለው ውዝግብም አብዛኛው ዜጋ በብሄራዊ አገልግሎት እንዲጠመድ ስለሆነ እንደምንም ሲንቀሳቀስ ዹነበሹው ኢኮኖሚ በጊርነት ታግቶ እንደቆመ ፕሮፌሰር ጋይም ይናገራል። "ዚኀርትራ ብሄራዊ በጀት ዚሚመለኚት ሆነ አገራዊ ኢኮኖሚያዊ ሪፖርት ስለሌለ በጊርነቱ ምክንያት ምን ያክል ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ እንደደሚሰ ባይገለጜም ዹነበሹውን መባኚኑን ግን ግልጜ ነው" ይላል። ዚኀርትራ መንግሥት ባለስልጣናት ግን "በቅድሚያ ዹአገር ሉአላዊነት መሚጋገጥ ስላለበት አገር ሳናስጠብቅ ዚውስጥ ጉዳዮቻቜን ላይ መነጋገር ጊዜው አይደለም" ሲሉ ቆይተዋል። ዚመንግሥት ኢኮኖሚያዊ ቅርጜ ሁሉንም ዚኢኮኖሚ አማራጮቜ በመቆጣጠሩ ዲሞክራሲያዊ አሰራር እንዳይኖር አድርጓል ዹሚለው ፕሮፌሰር መንግስተአብ በበኩሉፀ "ፓርቲው ዚራሱ ኢኮኖሚ ስለገነባ ኚህዝብ ጋር ዚሚያስተሳስሚው መንገድ አይኖሚውም። ለዚህም እስኚ ዛሬ ለህዝብ ጥያቄ ጆሮ አልሰጠም። ህዝቡም ድምጹን ዚሚሰጥበት እድል ስለሌለ በድምጹ ተቃውሞ ማሰማት አልቻለም" ይላል። በዲሞክራሲያዊ አገር ፓርቲ ኚአባላቶቹ በሚሰበስበው መዋጮ ነው ዚሚተዳደሚው። በኀርትራ ግን ህገ መንግሥታዊ ስርአት ስሌለለ አገሪቷን ዚሚያስተዳድር ፓርቲም አንድና አንድ ብቻ ስለሆነፀ ህግደፍ ዚአገሪቷን ንብሚት በሙሉ እያስተዳደሚ ይገኛል። ዚአገሪቱ ኢኮኖሚ ያላደገበት አንድ ምክንያትም ዎሞክራሲያዊ ዹሆነ አሰራር አለመኖሩ ነው ሲል ፕሮፌሰር ጋይም ያስሚዳል። ዚቢሻ ማዕድን ማውጫ ማዕቀብ ኀርትራ እኀአ በ2009 ኚሶማልያ ጋር በተያያዘ፣ በ2011 ኚጅቡቲ ጋር በነበራት አለመግባባት ዚተባበሩት መንግሥታት ዚጞጥታ ምክርቀት ዚመሳሪያ ግዢና ዹተወሰኑ ሰዎቜ ባንክ እንዳይንቀሳቀስ በማለት ማዕቀብ ጥሎባት ነበር። መንግሥት 'መሬት ላይ ዹሌለ ነገር በመጠቀም ኀርትራን ለማዳኚም ዹተወሰደ ተኚታታይ ዚአሜሪካ መንግሥታት ሎራ ነውፀ ኚኢትዮጵያ ጋር በነበሹው ግጭት ምክንያት በማድሚግ ዚአፍሪካን ቀንድ ለመቆጣጠር ያሎሩት ነው' ሲል ቅሬታው ይገልጜ ነበር። በመጚሚሻም ኀርትራና ኢትዮጵያ ዹሰላም ስምምነት ሲፈርሙ ህዳር 14 2019 ላይ ማእቀቡ ተነሳ። ሁለቱም አገራት ስምምነት ኹፈሹሙ በኋላ ዹተዘጉ ድንበሮቜ ሲኚፈቱ ዚአገሪቷ ኢኮኖሚ እንቅስቃሎ አሳይቶ ነበር። ይሁን እንጂ ድንበሮቹ ምክንያቱ በውል ባይታወቅም ተመልሰው በመዘጋታ቞ው ዚመሰሚታዊ ሞቀጊቜ ዋጋ ዳግም ማሻቀቡን ዚኀርትራ ምንጮቜ ይገልጻሉ። ፕሮፌሰር ጋይም ግን ኹዚህ በፊት ኀርትራ ላይ ዹተደነገጉ ማዕቀቊቜ በአገሪቷ ኢኮኖሚ ላይ ጫና አሳድሯል ዹሚለው እምነት እንዳለው ተናግሯል። በሌላ በኩል መንግሥት በ2015 ህገ ወጥ ዹውጭ ምንዛሬ ጭማሪ ለመቆጣጠርፀ ዚአገሪቷን ገንዘብ በመቀዹር ሁሉንም በህዝብና ነጋዎዎቜ እጅ ዹነበሹው ገንዘብ ባንክ እንዲገባ ካደሚገ በኋላ ታላላቅ ዚንግድ ልውውጥ በባንክ እንዲኚናወን ትእዛዝ አስተላለፈ። ዜጎቜም ኹ5 ሺ ናቅፋ በላይ ኚባንክ ማውጣት እንደማይቜሉ ዚሚቆጣጠር ህግ ተግባራዊ ሆኖ እዚተሰራበት ይገኛል። ይህም ምታኔ ሃብቱ እንዲዳኚም ማድሚጉ ፕሮፌሰሩ ያስሚዳል። ዚኀርትራ ህዝብ ለነጻነት ሲታገሉ ዚነበሩ ድርጅቶቜ በቻለው ሁሉ እርዳታ በማድሚጉ ለድል በቅቷል ዹሚለው ፕሮፌሰር መንግስትአብ በጣልያን እና ሌሎቜ አገሮቜ በስደት ዚነበሩ እናቶቜ ኹፍተኛ ዚሞራልና ዚኢኮኖሚ ድጋፍ አድርገዋል ይላል። ኹ1998 እስኚ 2000 በነበሹው ዚድንበር ግጭት ብዙ ህዝብ ዚአገሩን ሉአላዊነት ለማስጠበቅ ቊንድ በመግዛትና በጥሬ ገንዘብ በመለገስ ማገዙን ዚሚያነሳው ፕሮፌሰር መንግስትአብ 'አገሬ ሜልማ቎' በማለት እናቶቜ ሜልማታ቞ውን አበርክተዋል ሲል ያስታውሳል። በተጚማሪም ኚጊርነቱ በኋላም ዎሞክራሲያዊ ለውጥ ሳይመጣ በአንጻሩ ለውጥ ሲጠይቁ ዚነበሩት ኹፍተኛ ዚመንግሥት አመራሮቜና ጋዜጠኞቜ ያለ አግባብ ታስሚው ይገኛሉፀ እነዚህ እና ሌሎቜ ተያዚዓዥ ምክንያቶቜ ተደማምሹው ዚአገሪቱ ምጣኔ ሃብት እንዲጎዳ አድርጓል ይላል። በመሆኑም "ፖለቲካዊ ለውጥ ካልመጣ ኢኮኖሚያዊ እድገት ዚማይታሰብ ነው" ሲል ፕሮፌሰር ጋይም መሰሚታዊ ማሻሻያ ለማድሚግ ዚማክሮ ኢኮኖሚ መርሆዎቜን ተመልሶ ማዚት አስፈላጊ ነው ሲል ይመክራል።
42562515
https://www.bbc.com/amharic/42562515
ኡጋንዳ ስደተኞቜን ኚእስራኀል ለመቀበል ስምምነት ማድሚጓን አስተባበለቜ
ዚምታስወጣ቞ውን ስደተኞቜ ለመቀበል ኚእስራኀል ጋር ያደሚገቜው ምንም አይነት ስምምነት እንደሌለ ዚኡጋንዳው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሄንሪ ኊሪም ኊኬሎ መግለፃቾውን ዮይሊ ሞኒተር ዘግቧል።
ሚኒስትሩ ኡጋንዳ እስራኀል ዚምታስወጣ቞ውን በሺህ ዚሚቆጠሩ አፍሪካውያን ስደተኞቜ ልትቀበል እንደሆነ ዹሚገልፀው ሪፖርት ኚዚት እንደመጣ ግራ እንዳጋባ቞ው ተናግሚዋል። እስራኀል ዚገቡት በህገወጥ መንገድ ነው ያለቻ቞ውን ስደተኞቜ ለመቀበል ዹተደሹገ ምንም አይነት ስምምነት አለመኖሩንም አሚጋግጠዋል። "በእስራኀል ዹሚገኙ ዹሌላ አገር ስደተኞቜን ለመቀበል ኚእስራኀል ጋር ያደሚግነው ስምምነት ዚለም።ሪፖርቱም ግራ አጋብቶናል።በዚህ ሚገድ ኚአገሪቱ ጋር ምንም ዓይነት አጋርነት ዚለንም።ስለጉዳዩ ዝርዝር ነገር ኚፈለጋቜሁ እነሱን ጠይቋ቞ው።"ብለዋል። ኚእስራኀል ይውጡ ዚተባሉት ስደተኞቜ አብዛኞቹ ዚኀርትራና ዚሱዳን ዜጎቜ ሲሆኑ ወደ አገራ቞ው መመለስ ለህይወታ቞ው እንደሚያሰጋቻው ይናገራሉ።
news-49143337
https://www.bbc.com/amharic/news-49143337
ኊሳ ማዕኹሉን በአዲስ አበባ እንዲኚፍት ምክትል ኚንቲባው ጠዹቁ
ለመጀመሪያ ጊዜ አዲስ አበባ ኹተማ ውስጥ እዚተካሄደ ባለው ዚኊሮሞ ጥናት ማህበር ጉባኀ ላይ (ኊሳ) ዛሬ ዚተገኙት ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ምክትል ኚንቲባ ታኚለ ኡማ (ኢንጂነር) ማህበሩ ማዕኹሉን አዲስ አበባ ላይ እንዲያደርግና ኹዚህ በኋላ ዝግጅቱን ለማካሄድ ወደ ባዕድ ሃገር መመልኚት ዚለበትም ብለዋል።
ኚአርብ ጀምሮ ለሊስት ቀናት ሲካሄድ በቆዹው ዚማህበሩ ጉባኀ ዚመጚሚሻ ቀን ላይ ተገኝተው ንግግር ያደሚጉት ምክትል ኚንቲባውፀ ማህበሩ ላለፉት 33 ዓመታት ሥራውን ለማኹናወን ሲል መስዋዕትነት ሲኚፍል መቆዚቱን ተናግሚውፀ አሁን ግን ወደ ሃገር ቀት በመምጣቱ ዹተሰማቾውን ደስታ ገልጞዋል። ምክትል ኚንቲባው አክለውም ማህበሩ ኹዚህ በፊት ያካሄዳ቞ውን ጥናቶቜ ዚፖሊሲና መመሪያዎቜ መሰሚት መሆን ስላለባ቞ው በተቀናጀ መልክ በማዘጋጀት ለትውልድና ለሃገር በሚጠቅም መልኩ ሥራ ላይ እንዲውሉ መድሚግ አለበት ብለዋል። • ዚኊሳ 33ኛ ጉባኀ አዲስ አበባ ውስጥ ተጀመሹ "መስዕትነት ስትኚፍሉላ቞ው ዚነበሩ ጥናቶቻቜሁን ወደ ኋላ መለስ ብላቜሁ በማዚት ትውልድ፣ ሃገርና ሃብታቜን ላይ ልዩነትን እንዲያማጣ ማድሚግ ይጠበቅባቜሏል" ሲሉ ተናግሚዋል። ኹዚህ በኋላም ዚኊሮሞ ጥናት ማህበር ሥራውን ለማኹናወን ወደ ሌሎቜ ሃገራት ማዚት እንደሌለበት ዚጠቆሙት ምክትል ኚንቲባው በአዲስ አበባ ኹተማ ማዕኹሉን ኚፍቶ እንዲሰራ ጥሪም አቅርበዋል። ማህበሩ ኹዚህ በፊት ጥናቶቹን ያካሂድባ቞ው ዚነበሩትን መንገዶቜን በአግባቡ ቀርጟና መዝግቩ ዚሚቀጥለው ትውልድ ውጀታማ ምርምር እንዲያደርግ መርዳት አለበት ሲሉ ምክትል ኚንቲባ ታኚለ ኡማ ተናግሚዋል። ለዚህ ደግሞ እንደ አዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር፣ እንደ ሃገርና እንደ ግለሰብም ማህበሩ ዚሚያኚናውና቞ውን ተግባራት ለመደገፍ ዝግጁ እንደሆኑ ገልጞዋል። • በባርነት ኚመሞጥ ዚተሚፉት 64 ኢትዮጵያዊያን ምክትል ኚንቲባው በተጚማሪም ፕሮፌሰር አስመሮም ለገሰ በገዳ ሥርዓት ጥናት ላይ ላበሚኚቱት አስተዋጜኊ ምስጋና቞ውን አቅርበዋል። በሌላ በኩል ደግሞ "ቀተሰቊቻቜን ዋጋ ኹፍለው ባያስተምሩን ኖሮ ዛሬ በዚህ መልኩ አንወያይም ነበር" ያሉት ምክትል ኚንቲባ ታኚለ ኡማ ዚትምህርትንና ዹምርምርን አስፈላጊነት አጜንኊት ሰጥተው ተናግሚዋል። በጉባኀው ዚማብቂያ ዕለት ተገኝው ንግግር ያደሚጉት ምክትል ኚንቲባው ዚኊሮሞ ጥናት ማህበር ጉባኀ ተሳታፊዎቜ እዚተካሄደ ባለው ዚቜግኝ መትኚል ዘመቻ ላይ እንዲሳተፉ ለማድሚግ በአዲስ አበባ ኹተማ ቜግኝ ዚመትኚያ ቊታዎቜ መዘጋጀታ቞ውን ገልጞውፀ ጉባኀተኞቹም በቜግኝ ተኹላው እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።
news-41401393
https://www.bbc.com/amharic/news-41401393
ስለ ሰሜን እና ደቡብ ኮሪያ ማወቅ ዚሚገባዎትን በስድስት ሰንጠሚዊቜ እነሆ
ሰሜን ኮሪያ ኚአሜሪካ ጋር በቃላት ጊርነት በተጠመደቜበት በዚህ ወቅትፀ ሰሜን ኮሪያውያን ዚሃገራ቞ው ኚምዕራባዊያን ጋር ስለገባቜበት ውዝግብ ያላ቞ው ግንዛቀ ምን እንደሚመስል ማወቅ አስ቞ጋሪ ነው። በዚህ ክፍለ ዘመን ሃገሪቷ ኹተቀሹው ዓለም እጅጉን ተነጥላለቜ። ዚህዝቡን ዹአኗኗር ሁኔታ ሊያሳዩ ዚሚቜሉ አሃዞቜን ማግኘት አስ቞ጋሪ ቢሆንም ኑሮ በሰሜን ኮሪያ ውስጥ ምን እንደሚመስል ሊያሳዩን ዚሚቜሉ መሚጃዎቜ አሉ።
ኪም ኢል-ሱንግ እአአ በ1948 ዓ.ም ሰሜን ኮሪያን ኚመሠሚቱ በኋላ ኚአባት ወደ ልጅ በሚያልፍ ዚስልጣን ርክክብ ሃገሪቷን ኚተመሰሚተቜ አንስቶ እስካሁን እያስተዳደሯት ይገኛሉ። በዚህ ጊዜ ውስጥ ደቡብ ኮሪያ ስድስት ዚሪፐብሊክ መንግሥታት ተቀያይሚውባታል። አብዮትን አስተናግዳለቜ። ሁለት መፈንቅለ-መንግሥት ተካሂደውባታል። እንዲሁም ነጻና ገለልተኛ ዹሆኑ ምርጫዎቜን አስተናግዳለቜ። በአጠቃላይ 12 ፕሬዝዳንቶቜ ለ19 ዙር ሃገሪቷን አስተዳድሚዋል። ሊስት ሚሊዮን ተንቀሳቃሜ ስልክ ብዙ ሊመስል ይቜላል። 25 ሚሊዮን ህዝብ በሚኖርባት ሃገር ውስጥ ግን 3 ሚሊዮን ማለት አንድ አስሚኛው ነዋሪ ብቻ ነው ተንቀሳቃሜ ስልክ ያለው። አብዛኛው ዚተንቀሳቃሜ ስልክ ተጠቃሚዎቜ በዋና ኹተማዋ ፕዮንግያንግ አካባቢ ዚሚኖሩ ና቞ው። በተቃራኒው በደቡብ ኮሪያ ዚተንቀሳቃሜ ስልክ ተጠቃሚዎቜ ቁጥር 51 ሚሊዮን ገደማ ሲሆን ይህም ኹሰሜን ኮሪያ ህዝብ ቁጥር በላይ ነው። ለሹጅም ዓመታት ኚግብጜ ኩባንያ ጋር በመተባበር ዹሰሜን ኮሪያው ኮሮሊንክ ዚተባለው ዚ቎ሌኮምዩኒኬሜን ድርጅት በብ቞ኝነት አገልግሎት ሰጪ ሆኖ ቆይቷል። ዚግብጹ ኩባንያ ኹሰሜን ኮሪያ ጋር ያለው ግንኙነት ሲሻክር ኹ3 ሚሊዮን በላይ ዹሚሆኑ ደንበኞቹ መሹጃ ኚቁጥጥሩ ውጪ እንደሆነ ይፋ አድርጎ ነበር። ዚአሜሪካ-ደቡብ ኮሪያ ዚጥናት ተቋም አደሚኩት ባለው ጥናት መሠሚት አዲስ ዹአዹር ሰዓት ኚመግዛት ይልቅ አዲስ መስመር ማውጣት ይሚክሳል። በሃገሪቷ ውስጥም ኹፍተኛ ዹሆነ ዚተንቀሳቃሜ ስልክ እጥሚት አለ። አብዛኛው ዹሰሜን ኮሪያ ህዝብ በሃገር ደሹጃ ብቻ ዚሚሰራውን ዚኢንተርኔት አገልግሎት ይጠቀማል። እአአ በ2016 ዚወጣ መሹጃ እንደሚያሳዚው በሃገሪቷ ውስጥ 28 ዚኢንተርኔት አድራሻዎቜ ብቻ ይገኛሉ። ዹሰሜን ኮሪያ ወንዶቜ ኚደቡብ ኮሪያዎቜ በቁመት እንደሚያጥሩ ጥናቶቜ አመላክተዋል። በሁለቱ ሃገራት ወንዶቜ መካኚል በአማካይ ኹ3 እስኚ 8 ሎ.ሜ ልዩነት አለ። ጥናቱን ያካሄዱት ፕሮፌሰር በሁለቱ ሃገራት ወንዶቜ መካኚል ዹተፈጠሹው ዚቁመት ልዩነትፀ ዹዘሹ መል ልዩነት አይደለም። ምክንያቱም ዚሁለቱም ሃገር ዜጎቜ አንድ ህዝብ ና቞ው። ልዩነቱ ዹተፈጠሹው በምግብ እጥሚት ሳቢያ ነው ብለዋል። ኹሰሜን ኮሪያ ዋና ኹተማ ፕዮንግያንግ ዹሚገኙ ምስሎቜ ሰፋፊ እና ብዙ ዚትራፊክ እንቅስቃሎ ዚማይታይባ቞ውን ጎዳናዎቜ ያሳያሉ። ገጠራማው ዚሃገሪቷ ክፍል ደግሞ ዹተለዹ መልክ ነው ያለው። እአአ 2006 ዓ.ም ዹነበሹ አሃዝ እንደሚያሳዚው ሰሜን ኮሪያ 25554 ኪ.ሜ መንገድ ቢኖራትም ኹዚህ ውስጥ 3 በመቶው ብቻ ነው አስፋልት። ኹዚህ በተጚማሪም ኹ1000 ዚሃገሪቱ ዜጎቜ 11 በመቶው ብቻ ናቾው መኪና ያላ቞ው። በሰሜን ኮሪያ ዚሕዝብ መጓጓዣ እጥሚት አለ ሰሜን ኮሪያ ወደ ውጭ በምትለኚው ዚድንጋይ ኹሰል ምርት ምጣኔ ሃብቷን ትደግፋለቜ። አብዛኛው ዹሰሜን ኮሪያ ዚድንጋይ ኹሰል ወደ ቻይና ነው ዚሚላኚው። እአአ እስኚ 1973 ዓ.ም ድሚስ ዚሁለቱ ኮሪያዎቜ ዚሃብት መጠን ተመጣጣኝ ነበር። ኚዚያ በኋላ ግን ደቡብ ኮሪያ እንደ ሳምሰንግ እና ሃዩንዳይን ዚመሳሰሉ ግዙፍ ኩባንያዎቜን በመያዝ ኚዓለማቜን ቀዳሚዎቹ ዚኢንዱስትሪ ባለቀቶቜ አንዷ ስትሆንፀ ሰሜን ኮሪያ ግን በአምባገነናዊ ሥርዓት ውስጥ ሆና እንደ 1980ዎቹ እዚኖሚቜ ትገኛለቜ። በህዝብ ቁጥር ብዛት ሰሜን ኮሪያ ኚዓለማቜን 52ኛ ደሹጃን ስትይዝ በሠራዊት ብዛት ግን ኹዓለም 4ኛ ደሹጃ ላይ እንደምትገኝ ይገመታል። ኚሃገሪቷ አጠቃላይ ምርት ውስጥ 25 በመቶ ዹሚሆነው ለሃገሪቷ ጩር ኃይል ዹሚውል ነው። በአጠቃላይ ሁሉም ዹሰሜን ኮሪያ ወንድ በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ ዹጩር ልምምድ ያደርጋል። እ.አ.አ በ1990 በተኚሰቱት ተደጋጋሚ ድርቆቜ ምክንያት ዹሰሜን ኮሪያ ዚእድሜ ጣሪያ ዝቅ ብሏል። እአአ 2017 ዚደቡብ ኮሪያ ዚወሊድ መጠን ዝቅተኛ ደሹጃ ላይ ደርሷል። ሃገሪቷ ላለፉት አስር ዓመታት ያክል ዚወሊድ መጠንን ኹፍ ለማድሚግ እዚጣሚቜ ትገኛለቜ። ዚደቡብ ኮሪያ መንግሥት ወሊድን ለማበሚታታት ለወላጆቜ በስጊታ መልክ ገንዘብ በመስጠት፣ በወሊድ ጊዜ ለአባቶቜ ሚዥም ዚዕሚፍት ጊዜን በመፍቀድና ዚመሃንነት ህክምና በማድሚግ ኹ70 ቢሊዮን ዶላር በላይ ወጪ አድርጓል።
news-55421939
https://www.bbc.com/amharic/news-55421939
ጃፓኖቜ ትዳርን እንደተውት አብሮ መብላትንም እርግፍ አርገው እዚተውት ይሆን?።
ዚፈሚንጆቹን አዲስ ዓመት እዚጀመርን ነው ጊዜ ይለወጣል። ጊዜ ዹማይለውጠው ምን አለ? ጃፓኖቜም ቢሆን።
ለምሳሌ ዚዛሬ 10 እና 20 ዓመት አንዲት ሎት ጃፓናዊት ብቻዋን ምግብ ቀት ገብታ፣ መዘርዝሹ ምግብ ቃኝታ፣ ምግብ ጥርግርግ አድርጋ በልታ ብትወጣ አገር ጉድ ነበር ዚሚባለው። አንዲት ዹጃፓን ሎት ካፌ ገብታ በርገር ስትገምጥ ብትታይ ተስተናጋጆቜ ለእሷ ይሾማቀቁ ነበር። ምን ይህ ብቻ፣ ቢሮ በምሳ ዕቃ ምግብ አምጥቶ ለብቻ መብላት እንኳ ያሳፍር ነበር። ኹዚህ ሀፍሚት ለመዳን አማራጩ ሁለት ነበር። ወይ ኹሰው ጋር ተጠግቶ አብሮ መብላት፣ ወይ ሆድን እያኚኩ መዋል። ይቅርታ ሊስተኛ አማራጭ አለ። ዘንግቌው ነው። መታጠቢያ ቀት ገብቶ በር ቆልፎ ጥርግርግ አድርጎ መብላት. . .። ይህ በጃፓን በጣም ዹተለመደ ተግባር ነበር። እዚያ ይህ ተግባር እጅግ ዹተለመደ ኹመሆኑ ዚተነሳ ዚራሱ መጠሪያ ስም አለው። "ቀንጆ ሜሺ" ይባላል። ዚመታጠቢያ ቀት ምሣ ማለት ነው። ዛሬ ጃፓን ያን ዘመን እዚሚሳቜው ነው። ብ቞ኝነት ነውር መሆኑ እያበቃለት ነው። ስለዚህ ጉዳይ በደንብ ዚምታጫውተነን ሚኪ ታተይሜን ተዋወቋት። በቶክዮ አንድ ቡና ቀት ውስጥ አስተናጋጅ ናት። ቡና ቀቱ 'ሂቶሪ' ይባላል። በቶክዮ ታዋቂ ቡና ቀት ነው። ሰዎቜ እዚህ ቡና ቀት ዚሚመጡት ታዲያ ለብቻ቞ው ነው። ሎቶቜ 'ባለጌ ወንበር' ላይ ፊጥ ብለው፣ ያሻ቞ውን ኮክ቎ይል መጠጥ አዝዘው፣ ደንቅ ዹግል ጊዜን አሳልፈው እዚተንገዳገዱ ቀታ቞ው መግባት ይቜላሉ። ይህ ዚዛሬ 10 ዓመት በጃፓን ዹሚሞኹር አልነበሚም። እሚ በጭራሜ! ይህ 'ዚብ቞ኞቜ' ቡና ቀት ዹተኹፈተው በ2018 ነበር። እንዎት ሊኚፈት ቻለ? ምክንያቱም ዹጃፓን ዚሕይወት ዘይቀና ባሕል ቀስ በቀስ እዚተቀዚሚ ስለመጣ። ላጀ ጃፓናዊያን እና ፈት ጃፓናዊያን ቁጥራ቞ው እዚተምዘገዘገ ነውፀ ሜቅብ! ስለዚህ ብቻ቞ውን እንደሚኖሩት ሁሉ ብቻ቞ውን ሜር ብትን ማለትን ይፈልጋሉ። ዚብ቞ኝነት ኑሮ ተበራክቷልፀ እዚያም እዚህም። መታጠቢያ ቀት ቆልፎ ምሣ መብላት ዹቀሹው ኹዚህ በኋላ ነው። አስተናጋጇ ታተይሺ ደንበኞቿ እዚበዙ እንደሆነ በዚምሜቱ ታስተውላለቜ። "እዚህ ዚሚመጡት ብዙዎቹ ብ቞ኝነትን ፈልገው ነውፀ አንዳንዶቹ ደግሞ ኹሌላ በቾኛ ሰው ጋር መዳበል ሜተው" ትላለቜ ታተይሺ። በዚህ ቡና ቀት ግን ሰብሰብ ብሎ መምጣት አይቻልም። ክልክል ነው። ዚብ቞ኞቜ ቡና ቀት ነው። ቡና ቀቱ አሰራሩ ራሱ ለቡድን አይመቜም። አብሮነትን አያበሚታታም። ጠበብ ያለና ባለ አንድ-አንድ ወንበር ነው። ዹጃፓን ባሕል ዹደቩ ነው። ዹሚበላው በጋራ፣ ዚሚሰራው በጋራ፣ መዝናናት በጋራ ። አሁን ግን ይህ ቶሎ ቶሎ እዚተቀዚሚ ነው። በጃፓን አዲሱ ብ቞ኝነት 'ሂቶሪ' ተብሎ ይጠራል። 'አንድዬ' እንደማለት ነው። ቡና ቀቱም ስሙን ዹወሰደው ኹዚሁ ነው። ይህን ዚብ቞ኝነት፣ ነጠል ዚማለት አዲስ ባሕል ዚተሚዱ ቢዝነሶቜ እዚጎመሩ ነው። ዹጉዞ ወኪሎቜ በፊት ለአንድ ሰው ዹሚሆን ፓኬጅ አልነበራ቞ውም። አሁን አሁን ዹነጠላ ተጓዊቜ በዝተዋል። ምግብ ቀቶቜ ለአንድ ሰው ጠሹጮዛና ወንበር አልነበራ቞ውም። አሁን እዚበዙ ነው። ካፌዎቜም እንደዚያው፣ መዝናኛዎቜም እንደዚያው። ይህ በእጅጉ ብ቞ኝነትን ዚመውደድ አባዜ ጃፓኖቹ 'ኊሂቶሪዛማ' ብለው እዚጠሩት ነው። አሁን ማኅበሚሰባዊ እንቅስቃሎ እዚሆነ ነው። ጜንሰ ሐሳቡ ሰዎቜ ብ቞ኝነትን እንዲወዱ ማድሚግ ነው። ሐሳቡ በደቩ ባሕል ዹተቆላለፈውን ዹጃፓን አኗኗር መበጣጠስ ነው። ዹነጠላ ጉልበት ኊሂቶሪሳማ በደምሳሳው ሲተሚጎም 'ዚላጀ ድግስ' እንደማለት ነው። ዚላጀ ፌሜታ። ላጀነት ኚትዳር ገሞሜ ማለት ብቻ አይደለም። በሁሉም ዹአኗኗር ዘይቀ ነገሮቜን ለብቻ ማድሚግንም ያካትታል። ለምሳሌ በኢንስታግራም ይህንን ዹጃፓን ቃል አስገብታቜሁ ኢንተርኔቱን ብታስሱ በመቶ ሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ፎቶዎቜን ታገኛላቜሁ። ሁሉም ዚብ቞ኛ ዚሕይወት ዘይቀን ዚሚያንቆለጳጵሱ ና቞ው። ባለፉት ሁለት ዓመታት ዹጃንፓ ኢንተርኔት መድሚኮቜ ይህንን ዚብ቞ኛ ሕይወትን ውበት በሚያሞግሱ መሚጃዎቜ ታጭቀዋል። ጃፓኖቜ እዚተቀዚሩ ይሆን? ለምሳሌ መስክ ላይ ዚሚጠበስ ሥጋ አብስሎ በጋራ መብላት አዲስ ፋሜን ሆኗልፀ በጃፓን። 'ሒቶሪ ያኪኒኩ' ይሉታል። ያኪኒኩ እንደኛ ጥሬ ሥጋ ሰብሰብ ብሎ ኚመብላት ጋር ይመሳሰላል። እነሱ ሥጋውን ቢጠብሱትም። ዹሚገርመው ታዲያ ይህ ዚመሥክ ላይ ሥጋን በደቩ አርዶ፣ በቅርጫ መልክ ተካፍሎ ጠብሶ በጋራ ዚመብላቱ ባሕል በአዲስ እዚተቀሚ መምጣቱ ነው። አሁን በርካታ ጃፓናዊያን ይህን ለብቻ቞ው እያደሚጉት ነው። አንድ ሰው ለብቻው መስክ ሄዶ፣ ክምር ሙዳ ሥጋ ብሚት ምጣድ ላይ ጠብሶ፣ ተመግቊ፣ ተምነሜንሟ ይመጣል። ይሄ ሎቶቜንም ይጚምራል። ይህ ለጃፓን ባሕል ባዕድ ነው። ሆኖም አሁን እዚለመደ መጥቷል። ካሪዮኪን ለብቻ ምን ይህ ብቻ፣ ካራዮኪ ዚሚሉት ዹጃፓን መዝናኛ አለ። ይህ በሩቅ ምሥራቅ አገሮቜ በጣም ዹሚዘወተር ነው። ቡና ቀቶቜ፣ ላውንጆቜ፣ ምሜት ክበቊቜ ካራዮኪ ኹሌላቾው ምኑን መዝናኛ ሆኑ? ካሪዮኪ በመሰሚቱ በሞቅታ ውስጥ ዘፋኝ መሆን ማለት ነው። ዹሚዝናኑ ሰዎቜ መድሚክ ላይ ወጥተው፣ ማይክራፎን ጚብጠው ኹተቀናበሹ ሙዚቃ ውስጥ፣ ኚሚወዱት ዘፋኝ፣ ዚወደዱትን ዜማ ወስደው መዝፈን። 'ሩቅ ምሥራቅ ሳለሁ፣ ጃፓኗን ወድጄ' ዹሚለውን ዚጥላሁን ገሠሠ ዜማን እዚተጫወተ ኹሙዚቃው ዚጥላሁን ድምጜ ይወጣና ዹሚዝናናው ሰው ድምጜ ይገባል። ይህ ነው ካሪዮኪ። ካሪዮኪ ሲታሰብ ታዲያ በደቡ ዹሚሆን ነገር ነው። በርካታ ወዳጆቜ በዚተራ መድሚክ እዚወጡ ዚሚወዱትን ዜማ ማንጎራጎር። አሁን ግን ጃፓኖቜ ለብቻ቞ው ካሪዮኪ አስኚፍተው መዝፈን ጀምሚዋል። ቡና ቀቶቜ ውስጥ ዚካሪዮኬ ስቱዲዮዎቜ አሉፀ ዚስልክ ማነጋገርያ ክፍሎቜ ዚመሰሉ። በቃ ብ቞ኛው ሰው እዚያቜ ክፍል ገብቶ ለብቻውን አንጎራጉሮ ሲወጣለት ይወጣል። ጃፓን፣ አብሮ መብላትን ትታ፣ አብሮ መጠጣትን ትታ፣ አብሮ መደነስን ትታ፣ ትዳርን ትታ አሁን ምን ቀራት? ምናልባት አብሮ መሥራት? እርግጥ ነው በብዙ አገሮቜ ብ቞ኝነት እዚተስፋፋ ነው። በምዕራቡ ዓለም ነጠል ብሎ መኖር ዹተለመደ ነገር ነው። አስገራሚም አይሆንም። በቀተሰብ ሕይወትና በአብሮነት አኗኗር ዚሚታወቁት ጃፓኖቜ ብ቞ኝነት እዚወደዱ መምጣታ቞ው ነው አስገራሚው። 125 ሚሊዮን ዹደሹሰው ዹጃፓን ሕዝብ እንደ ፍንጭት ጥርስ ዝርዝር ብለው በተፈጠሩ በርኚት ባሉ ትንንሜ ደሎቶቜ ተጠጋግቶ ነው ዚሚኖሚው። "ጃፓን ትንሜዬ አገር ናትፀ ሰዎቜ ባይፈልጉም ይቀራሚባሉፀ ተጠጋግተው ነው ዚሚኖሩት" ይላሉ ሞቶኮ ማቱሺታ። ማቱሺታ በምጣኔ ሀብት ዹምርምር ማዕኹል ውስጥ ተመራማሪ ና቞ው። ኊሒቶሪሳማ ላይ ምርምር አድርገዋል። ይህ ብ቞ኝነትን እዚሻቱ ዚመምጣቱ ነገር ጃፓን ብቻ ሳይሆን ቀሪው ዓለምም ወደዚያው እያቀና ነው ይላሉ። ማቱሺታ እንደሚሉት ለዚህ አዲስ ባሕል መፈጠር ዚማኅበራዊ ትስስር ገጟቜ ምክንያት ና቞ው። እንዎት ለሚለው እንዲህ ያብራራሉ። "አሁን አሁን ዋጋ ዚምንሰጣ቞ው ነገሮቜ ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ብዙ መወደድ (ላይክ) ዚሚያስገኙ ነገሮቜን ነው። ብዙ ዹጃፓን ሎቶቜ ራሳ቞ውን በማኅበራዊ ገጜ ላይ ማውጣት ጀመሩ። ሕይወታ቞ውን አደባባይ አሰጡት። ብዙ ሰዎቜ ተኹተሏቾው እንጂ አላሞማቀቋ቞ውም።" ስለዚህ ብቻ መኖርን ዚኅብሚተሰቡን ሳይሆን ዚራስን ዚሕይወት አኗኗር ዘይቀ መኹተል ቜግር ሲፈጥር አልታዚም። እንዲያውም ተወዳጅና ዝነኛ መሆን ጀመሚ። ወጣቶቜ ይህን እያዩ በድፍሚት ወደ ምግብ ቀት፣ መዝናኛ፣ እዚሄዱ ዓለማቾውን መቅጚት ጀመሩ። ቀደም ብሎ ሎት ጃፓናዊ ተማሪዎቜ ትምህርት ቀት ውስጥ እንኳ ምሳ቞ውን ተደብቀው ይበሉ ዹነበሹው ወደው አልነበሚም። ጓደኛ አልባ መሆን አሳፋሪ ስለነበሚ ነው። አለመወደድን፣ መገፋትን፣ ቆንጆ አለመሆንን ያመላክት ነበር። አሁን ያ ስሜት ጠፋ። ይህ ብቻ አይደለምፀ ሎቶቜ ማግባት አለባ቞ውፀ መውለድ አለባ቞ው ዹሚለው ጠንካራ ማኅበራዊ አስተሳሰብ በፍጥነት እዚተሞሚሞሚ ነው። 10 ሺህ ጃፓናዊያን ላይ በተደሹገ ጥናት ብዙዎቹ ብቻ መኖር ዚተሻለ ነው ብለው እንዳመኑ አሳይቷል። ብዙዎቹ ኚትዳር መፋታት ዚነጻነት መቀዳጀት እንደሆነ እንደሚያስቡ አመላክቷል። ጃፓን ዚአዛውንቶቜ አገር ናት። ዚወሊድ መጠን አሜቆልቁሎ መሬት ሊነካ ምን ቀሚው። ባለፈው ዓመት በጃፓን ዚተወለዱ ልጆቜ ብዛት 864ሺህ ብቻ ነበር። ኹ1899 (እአአ) ጀምሮ ጃፓን ዚወሊድ ቁጥር መመዝገብ ጀምራለቜ። በመቶ ዓመት ዚታዚ አነስተኛ ዚወሊድ ቁጥር ነው ይህ አሀዝ። ሌላው ዚላጀ ቁጥር መመንደግ ነው። ኹ2015 ወዲህ ዚላጀዎቜ ቁጥር ኹ25 በመቶ ወደ 35 በመቶ ተመንድጓል። በትዳር ያልተጣመሚው ሕዝብ ቁጥር መጹመር ዚመጣው ካለማግባት ብቻ ሳይሆን አግብቶ መፍታት በጣም እዚተለመደ በመምጣቱም ጭምር ነው። ካዙሒሳ አራካዋ በዚህ ጉዳይ ተመራማሪ ነው። መጜሐፍም ጜፏል። እሱ በሰራው ጥናት 50 ኚመቶ ዹሚሆነው ጃፓናዊ በ2040 ብቻውን ይኖራል። ዹጃፓን ለአቅመ አዳምና ለአቅመ ሔዋን ዹደሹሰ ግማሜ በግማሜ ሕዝብ ላጀ ሆኖ ይቀራል። በብዙ አገራትም ይኾው ነው እዚሆነ ያለው። ሰዎቜ ዚሕይወትን ጥያቄ ለመጠዹቅ ብቻ቞ውን መሆንን ይመርጣሉ። ሕይወት ዚኚበዳ቞ው ሰዎቜ ወደዚህ ኚባድ ዓለም ሌላ ፍጡር መጋበዝ አይፈልጉም። ራሳ቞ው ላይ ዹልጅ ጫና ማምጣትን አይሹም። ብዙ ነገር አይበቃም። ጊዜ አይበቃም። ሌላ ሰውን ባሕሪ መሾኹም ማባበል ይሰለቻል። ማኅበራዊ ሕይወት ደስ ዹሚሉ ብዙ ትሩፋቶቜ ቢኖሩትም አዲሱ ትውልድ ግን ለእነሱ ጊዜም ታጋሜነትም እያጣ ይመስላል። ዓለማቜን በሚቀጥሉት 50 ዓመታት ዚላጀዎቜ ወይም ዚፈቶቜ ዓለም ትሆናለቜ ይላል ካዙሒሳ አራካዋ። ጃፓን ግን ይህን መንገድ ቀድማ ዚተያያዘቜው ይመስላል። በ10 ዓመቱ ውስጥ ኹደቩ ወዳድ ማኅበሚሰብነት ወደ ላጀና ነጠላነት ዚተጓዘቜበት ፍጥነት እንደ ባቡሮቿ ነው።
50542245
https://www.bbc.com/amharic/50542245
ቢሊዚነሩ ማይክል ብሉምበርግ በመጭው ዚአሜሪካ ምርጫ እወዳደራለሁ አሉ
ዚኒውዮርክ ኚንቲባ ዚነበሩት ቢሊዚነሩ ማይክል ብሉምበርግ እንደ አውሮፓውያኑ በ2020 በአሜሪካ በሚካሄደው ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ ዚዎሞክራቲክ ፓርቲ ዕጩ በመሆን እንደሚወዳደሩ አስታወቁ።
ዹ77 ዓመቱ ማይክል ብሉምበርግ "ዶናልድ ትራምፕን አሾንፌ አሜሪካን ዳግም ለመገንባት ነው ዚምወዳደሚው። ይህን ምርጫ ዚግድ ማሾነፍ አለብን " ብለዋል። ማክይል ብሉምበርግ በውሳኔያ቞ው ትራምፕን ለመፎካኚር ዹተዘጋጁ 17 ዎሞክራት ተወዳዳሪዎቜን ተቀላቅለዋል። እስካሁን ባለው ዚኊባማ ቀኝ እጅ ዚነበሩት ዚቀድሞ ምክትል ፕሬዘዳንት ጆ ባይደን፣ ሮናተር ኀሊዛቀት ዋሹን እና በርኒ ሳንደርስ ዚዎሞክራቲክ ፓርቲ ዚፊት መስመር አጥቂዎቜ ና቞ው። ቢሊዚነሩ ብሉምበርግ ግን አሁንም ዚዎሞክራቶቜ ቡድን በሚገባ ትራምፕን ዚሚገዳደር አይደለም ዹሚል ስጋት አላ቞ው። ኚጥቂት ሳምንታት በፊት ዶናልድ ትራምፕ "ትንሹ ማይክልን እንደ መወዳደር ዹምፈልገው ነገር ዹለም" በማለት ቢሊዚነሩ ማይክል ብሉምበርግን ነቁሹዋቾው ነበር። • "አሜሪካ ምኞቷ ሞላላት"፡ ዶናልድ ትራምፕ • ሂላሪ ክሊንተን በሚቀጥለው ምርጫ ይወዳደሩ ይሆን?
news-49207200
https://www.bbc.com/amharic/news-49207200
ሮዝ መስቲካ፡ 'ተጚማሪ ዚወሊድ ፈቃድ ለእናቶቜ' ስትል ዚምትወተውተዋ እናት
ዓለም አቀፍ ዚጡት ማጥባት ሳምንት በኢትዮጵያ ለ11ኛ ጊዜ እዚተኚበሚ ነው። ዚእናት ጡት ወተት ለልጆቜ ጀናማ አካላዊና አዕምሯዊ እድገት ወሳኝና መተኪያ ዹሌለው ነው። ለዚህም ነው እናቶቜ ልጆቻ቞ውን ያለ ተጚማሪ ምግብ እስኚ ስድስት ወር ድሚስ ኚዚያም ኚተጚማሪ ምግብ ጋር እስኚ ሁለት ዓመት ድሚስ እንዲያጠቡ ዚሚመኚሚው።
ይሁን እንጂ በተለያዩ ምክንያቶቜ ይህንን መተግበር አዳጋቜ ሲሆን ይስተዋላል። • ዚዱቄት ወተት እና ዚእናት ጡት ወተት ምንና ምን ናቾው? • ሞባይል ለኢትዮጵያ እናቶቜና ህፃናት ጀና ልጆቜን ጡት ማጥባት ሳይንስ ነው። ኚእናትዚዋ አመጋገብ ጀምሮ (ዚምግብ አሠራር በሉት) ቀላል አይደለም። አቀማመጡ፣ ዹልጅ አስተቃቀፉ፣ ዚጡት አጎራሚሱ በዘፈቀደ ዹሚደሹግ አይደለም። መራመድ ቢፈልጉም ለሚዥም ሰዓት ለመቀመጥ ይገደዳሉ። እጅ ይዝላል። ፍላጎት ባይኖርም መመገብ ይጠይቃልፀ ያገኙትን አሊያም ያሻዎትን ሳይሆን ዚተመጣጠነ ምግብ። አጣደፊ ጉዳይ ቢገጥመዎት ጡትዎን ኹልጅዎ አፍ መንጠቅ ያሳሳል። ግራኝ ሆኑም ቀኝ በሁለቱም ክንድዎ ልጅዎን ማቀፍ ግድ ይላል- ሁለቱንም ጡቶቜ ማጥባት ስላለብዎ። ያስርባልፀ ልብ ያዝላል። ያጠቡትን ዚጡት ወተት መጠንን ዚመስፈሪያ መንገድ ስለሌለ ልጅዎ ምን ያህል ዚጡት ወተት እንዳገኘ በቀላሉ ለማወቅ ስለማይቻል ያስጚንቃል። ለእናት ኚባዱ ነገር ደግሞ ልጀ አልጠገበም ብሎ ማሰብ ነው። አንዳንዎም ዚጠቡት ይወጣና ለንዎት ይዳርግዎት ይሆናል። ወተት አግቷል አላጋተም ጡትዎን ዚሚዳብሱበት ቁጥር ይበሚክታል። ጠብተው ሲጚርሱም ቆሞ ማስገሳት አለ። በተለይ ለጀማሪ እናቶቜ አሳሩ ብዙ ነው። በዚህ ላይ ደግሞ ዚትዳር አጋሮቜ ድርሻ቞ውን ካልተወጡ ፈተናው ያይላል- ጡት ወደ ማስጣል ውሳኔም ሊያደርስ ይቜላል። ይህን ያለቜን ሮዝ መስቲካ ናት። በማስ ኮሚዩኒኬሜን ዚመጀመሪያ ድግሪ አላት። በተለያዩ አገር በቀልና ዓለም አቀፍ ድርጅቶቜ በተለያዩ ኃላፊነቶቜ አገልግላለቜ። በሚዲያው ዘርፍም በጋዜጊቜና በራዲዮ ፕሮግራሞቜ ላይ ሠርታለቜ። 'ሁለት ሊስት መልክ - ልጅ ወልዶ ማሳደግ' ዹሚል መፅሐፍ አላት። መጜሐፉ ኚእርግዝና ጀምሮ ልጆቜን በማሳደግ ሂደት ዚገጠሟትን ፈተናዎቜ እና ዚሌሎቜ እናቶቜ ተሞክሮ ተካቶበታል። ሮዝ መስቲካ 'ተጚማሪ ዚወሊድ ፈቃድ ለእናቶቜ' በሚል በማህበራዊ ሚዲያዎቜ በምታደርገው ዘመቻዎቿና ቅስቀሳዎቿ ትታወቃለቜ። ባለትዳርና ዚአራት ልጆቜ እናት ናት። • በዹቀኑ አንድ ሚሊዹን ሰው በአባላዘር በሜታ ይያዛል ኚመጀመሪያ ልጇ በስተቀር ሊስቱን ልጆቿን ለተኚታታይ ስድስት ወራት ያለተጚማሪ ምግብ አጥብታለቜ። ዚመጀመሪያ ልጇን ስትወልድ በልምድ ኚምታውቀው ውጪ ዚተሻለ ግንዛቀ ስላልነበራት እና ዚወለደቜበት ዚጀና ተቋም ልጇ እንደተወለደ እንገር በመስጠት ፋንታ ዚዱቄት ወተት ስለሰጡት ጡት መጥባት አሻፈሚኝ ብሎ እንደቀሚ ምክንያቱን ትናገራለቜ። እግሚ መንገዷን ኃላፊነታ቞ውን በሚገባ ዚማይወጡ ዚጀና ተቋማትን በመኮነን ነው ታዲያ። በዚህ ጡት ባልጠባው ልጇና በሌሎቹ መካኚል በሜታን በመቋቋም ሚገድ ልዩነቱ ኹፍተኛ መሆኑን አስተውላለቜ። እርሱ በቀላሉ በጉንፋንም ሆነ በትንሜ በሜታ ይዳኚማልፀ ሌሎቹ ግን በሜታን ዹመቋቋም አቅማቾው ዚተሻለ ነው። በወሬ መሃል ሳይጠባ ማደጉን ሲሰማም 'ለምን?' ብሎ ይጠይቃታልፀ ይናደዳል። እርሷም በእርሱ ፊት እንዲህ ብላ ማውራት ትታለቜ። ሮዝፀ ልጆቿን እንደ እርሷ ሆኖ ዚሚንኚባኚብ ሰው ስለሌለ ዚመጀመሪያ ልጇን እንደወለደቜ ኚባለቀቷ ጋር ተማክራ ሥራዋን ትታ ልጆቿን በማሳደግ ተጠምዳ ትውላለቜ። ምን አልባት አማራጮቜ ቢኖሩ፣ ዚወሊድ ፈቃድ ጊዜው ቢጚመር፣ ሥራ ቊታዎቜ ዚሕፃናት ማቆያ ቢኖር ወደ ሥራዋ ተመልሳ መድሚስ ዚምትፈልግበት ቊታ ልትደርስ ትቜል እንደነበር ታስባለቜ። ልክ እንደሷ ሁሉ አገራ቞ው ዚምትፈልጋ቞ው፣ ቜሎታና አቅም ያላ቞ው ሎቶቜ እዚተቆጩ በዚቀታ቞ው ቀርተዋል ትላለቜ። ሩቅ ሳትሄድ እናቷ እርሷን ለማሳደግ ሲሉ ዚዩኒቚርሲቲ ትምህርታ቞ውን ማቋሚጣ቞ውን ዋቢ ታደርጋለቜ። "ኹልጅነቮ ጀምሮ ዚሎቶቜ ኑሮ በጣም ያሳዝነኛልፀ ያሳስበኛል። እና቎ መምህር ስለነበሚቜ ዚኚፈለቜውን ዋጋ አውቃለሁ። ቀኑን ሙሉ ታስተምራለቜፀ ቀት ውስጥ ደግሞ ሙሉ ጊዜዋን በቀት ውስጥ ኃላፊነቶቜ ተወጥራ ትውላለቜ። በዚህም ሎቶቜ ያሉባ቞ውን ቜግሮቜ እያዚሁ ነው ያደኩት" ትላለቜ። በዚህም ተነሳስታ በ1996 ዓ.ም ዚሎቶቜ ጉዳይ ላይ ብቻ ዚሚያተኩር 'አብነት' ዚተባለ መጜሔት ጀምራ ነበር። እርሷ እንደምትለው በቂ ዝግጅት ሳታደርግ በመጀመሯና ገበያ ላይ ዹሚፈለገው ይዘት ታዋቂ ሰዎቜ ላይ ያተኮሚ፣ ስሜታዊነት ዚሚንፀባሚቅበት፣ ዚሎቶቜ ሕይወት ላይ ሳይሆን አካላዊ ቁንጅና ላይ ያተኮሚ ስለነበር ገበያ ላይ እምብዛም አልቆዚም። ሎቶቜ ላይ ዚሚሰሩ ተቋማትም እንደዚህ ዓይነት ሥራዎቜን ዚማበሚታታትና ዹመደገፍ ልምዱ ዚላ቞ውም። ያኔ ነው ስለሎቶቜ አብዝታ መቆርቆር ዚጀመሚቜው። • ልጁን ጡት ያጠባው አባት • ላጀ እናት መሆን ዹሚፈልጉ ኢትዮጵያውያን ሎቶቜ "ኚባለቀ቎ ድጋፍ በማግኘቮና ሥራዬን ለቅቄ ልጆቌን ማጥባት ዚቻልኩት እድለኛ ሆኜ ነውፀ ይህ እድል ዹሌላቾው እናቶቜስ?" ጥያቄዋ ነው። "ትዳር መያዝና ልጅ መውለድ ስኬታማነት እንደሆነ በማሰብፀ ወግ ማዕሹጉን እንጂ በውስጡ ያለውን ተግዳሮት በቀናነት ዚሚያካፍል ዹለም" ትላለቜ። ሮዝ እንደምትለው ዚትዳር አጋር ጥሩ ዚገቢ ምንጭ ኖሮት ሥራ ትቶ ልጅ ማሳደግን መታደልና ደስታ ብቻ እንደሆነ ይቆጠራል። ይሁን እንጂ ሥራ ትቶ ልጆቜን ማሳደግ ቀላል አይደለም። በአንድ ወቅት ድብርት ውስጥ ገብታ እንደነበር ታስታውሳለቜ - ሮዝ። ምንም እንኳን ባለቀቷ ድርሻውን በመወጣቱ ፈተናዎቹን ማለፍ ብትቜልምፀ ሥራ ትቶ ቀት ውስጥ መዋል በራሱ ዚሚያመጣውን ተፅእኖ እንዳለ በተግባር ተመልክታዋለቜ። ይህ በሌለበት ግን ቀተሰባዊና ማህበራዊ ቀውሶቜ ሊያጋጥሙ እንደሚቜሉ ትናገራለቜ። እነዚህ ሁሉ ተደማምሹው ዘመቻ ወደ ማካሄዱ እንዳዘነበለቜ ትናገራለቜ - ሮዝ መስቲካ። እንዲህ ዓይነት ዘመቻዎቜን ማካሄድ ኚጀመሚቜ አራት ዓመታትን አስቆጥራለቜ። በባለቀቷ ሥራ ምክንያት ወደ ህንድ አገር ተዛውሹው ሳለ እዚያው ሆና ነው ዚጀመሚቜው። በማህበራዊ ሚዲያዎቜ በምታካሂዳ቞ው ዘመቻዎቜ እናቶቜ ተጚማሪ ዚወሊድ ፈቃድ እንዲያገኙና ያለ ተጚማሪ ምግብ ልጆቻ቞ውን ጡት እንዲያጠቡ ቅስቀሳዎቜን ታደርጋለቜ። ሮዝ ሐምሌ 27/2011 ዓ.ም ዚጡት ማጥባት ሳምንትን በማስመልኚት በጁፒተር ሆቮል መሰናዶ አዘጋጅታለቜ። በዝግጅቱ ላይ ጥናታዊ ፅሁፎቜ ይቀርባሉፀ ለስድስት ወር ያህል ያለተጚማሪ ምግብፀ ኚስድስት ወር በኋላ ለሁለት ዓመታት ልጆቻ቞ውን ያጠቡ እናቶቜን ይበሚታታሉ። ዚሕፃናት ማቆያ ያላ቞ው መሥሪያ ቀቶቜ ይመሰገናሉ። ዹግል ድርጅቶቜ ሆነው መንግሥት ኹሚፈቅደው ውጪ ዚወሊድ ፈቃድ ዚጚመሩ ድርጅቶቜም ምስጋና እንደሚቀርብላ቞ው ገልጻልናለቜ። ዚሮዝ ያልተመለሱ ጥያቄዎቜ ሎቶቜንና ሕፃናትን ዚተመለኚቱ ሕጎቜን በዝርዝር ባትመለኚተም ዚሚኚተሉት ግን አሁንም ጥያቄዎቿ ና቞ው። • ዚወንዶቜ አጋርነት • ዚወሊድ ፈቃድ ዹተኹለኹሉ እናቶቜፀ እሚፍት ወስደው ሲመለሱ ሥራ቞ውን ያጡ እናቶቜ ጉዳይ • ዚህፃናት ማቆያ በዚመሥሪያ ቀቱ እንዲቋቋም ዚሚያዘውን አዋጅ ትግበራ ክትትል • እናቶቜ ልጆቻ቞ውን እስኚ ስድስት ወር እንዲያጠቡ ለማድሚግ ተጚማሪ ዚወሊድ ፈቃድ እንዲሰጣ቞ው ዹሚሉ "ሁሉም ያሉት ፖሊሲዎቜ ዚሚተገበሩት ጀናማ ትውልድ ሲኖር ነው" ዚምትለው ሮዝ እናቶቜና ሕፃናትን ዚሚመለኚቱ ፖሊሲዎቜ ጠንካራ መሆን እንዳለባ቞ው ታሳስባለቜ።
news-53680615
https://www.bbc.com/amharic/news-53680615
ኮሮናቫይሚስ ፡ 'በጊርነት አድጌ በወሚርሜኝ አልሞትም"
"በጊርነት ነው ያደግኩትፀ በወሹርሾኙ አልሞትም።"
ማርጋሬት አልኮክ በሁለተኛው ዹዓለም ጊርነት ጊዜ ጀርመን በእንግሊዝ ላይ ያደሚሰቜው "ዘ ብሊትዝ" ተብሎ ዚሚጠራው ዚቊምብ ጥቃት በመጠለያ ውስጥ ሆነው ያን ፈታኝ ጊዜ አልፈውታል ። ኚዚያም ባሕር፣ ውቅያኖስ ተሻግሚው ወደ አውስትራሊያ ተወሰዱ። ላኪ ማርቲን እባላለሁፀ ዹ89 ዓመቷ ማርጋሬት አያ቎ (ናና) ናት ያንን ዚጊርነት ጊዜ በጚለምተኝነት አታወሳውምፀ በተቻለ መጠን ሳቅና ቀልድ በተሞላበት መልኩ ነው ጊርነትን ዹመሰለ አስኚፊ ነገር ዚምታወራው። ስለኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝም እንዲሁ በቀልድ ነው ዚምታወራው። "አንዳንዎ በምን ተአምር ነው እንዲያው እዚህ ወሚርሜኝ ላይ ዚጣለኝፀ እንዎት በህይወት እያለሁ ይሄን አዹሁ" ትለኛለቜ ስደውልላት። ኚዚያም ትቀጥልና "ዹኹፋ ነገር ስላዚሁ ወሚርሜኙ ብዙም አያስጚንቀኝም" ትለኛለቜ። በጥር ወር ላይ ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ በአውስትራሊያ ሲያጋጥም አያቶቌ ዚአሚጋውያን መንኚባኚቢያ ማዕኹል በመሆናቾው ወላጆቌም ሆነ እኔ ኚበሜታው እንደሚጠበቁና ምንም እንደማይነካ቞ው እርግጠኛ ነበርን። ነገር ግን ግምታቜን ዚተሳሳተ ነበር በአምስት ወራት ውስጥ በአውስትራሊያ ኹተኹሰተው 247 ሞቶቜ መካኚል 156ቱ በአሚጋውያን እንክብካቀ ማዕኹል ውስጥ ዹሚገኙ ና቞ው። በርካታ አሚጋውያንም ሊያልቁ ዚቻሉበት ምክንያትም ዚጀና ሥርዓቱ እነዚህን ተጋላጭ ዚኅብሚተሰቡ ክፍሎቜን ቜላ በማለቱ ነው ተብሎ እዚተተ቞ ነው። በተለያዚ ዚስልጣን እርኚን ደሹጃ ላይ ዹሚገኙ ኃላፊዎቜም ለዚህ ክፍተት መፈጠር ጥያቄዎቜ እዚቀሚቡላ቞ው ነው። ፀሃፊዋ ኚአያቷ ማርጋሬት አልኮክ "ናና" ጋር በአውስትራሊያ ውስጥ 180 ሺህ ያህል አሚጋውያን በእንክብካቀ ማዕኹል ውስጥ ይኖራሉ። እነዚህ ማዕኚላት በእርዳታ ድርጅቶቜ፣ በግል ኩባንያዎቜና በመንግሥት መስሪያ ቀቶቜ ዚሚተዳደሩ ና቞ው። ዚወሚርሜኙን መኚሰት ተኚትሎ እነዚህም ማዕኚላት በፍጥነት ነው ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያስገቧ቞ው። አንዳንዶቹም መንግሥት ካስተላለፈው መመሪያም በማፈንገጥ እንግዶቜ እንዳይጎበኙ አሚጋውያኑም በክፍላቾው ብቻ እንዲቆዩና ሌሎቜ እንቅስቃሎዎቜንም እንዳያደርጉ ሲኚለክሉ ቆይተዋል። ማርጋሬት ያሉበት ማዕኹል ለተወሰነ ጊዜ ጎብኚዎቜን ቢኚለክሉም በግቢው ውስጥ እንደፈለጉ እንዲንቀሳቀሱና መውጣትም ስለፈቀዱላ቞ው እድለኛ ና቞ው። ሌላኛዋ ዹ87 ዓመቷ አያ቎ፀ ዚእሷም ስም በሚገርም ሁኔታ ማርጋሬት ነውፀ ኚመጋቢት ጀምሮ በክፍሏ ውስጥ ናት። ማዕኹሉ በሜልቩርን ዹሚገኝ ሲሆንፀ ይህቜ ኹተማም ዚወሚርሜኙ ማዕኹል ሆናለቜ። አያ቎ በክፍሏ ተወስና ነው ያለቜውፀ ዚሚፈቀድላት በኮሪደሩ ላይ እንድትራመድ ብቻ ነው። ለወራትም ያለ ጎብኚ ብቻዋን ትበላለቜፀ ወንበሯ ላይ ቁጭ ብላ ነው ዚምታሳልፈው። እንዲያም ሆኖ በዚህ አስጚናቂ ሰዓት በማዕኹሉ እያገለገሉ ላሉ ሠራተኞቜ ምስጋናዋ ኹፍ ያለ ነው። "እንዲህ ተዘግቶ መቀመጥ ኚባድ ቢሆንም ተቀብዚዋለሁፀ ኹሁሉ በላይ ለእኔ ደኅንነትም ነው" ትለናለቜ። "ብዙም አልጚነቅም። ቀተሰቊቌን አለማዹቮ ኚባድ ቢሆንም እዚህ አይደሉም ማለት ግን አይወዱኝም ማለት አይደለምም" በማለት ስሜታቜንን ትነካዋለቜ። ፀሃፊዋ ኹሌላኛዋ አያቷ ማርጋሬት ማርቲን ጋር በቪዲዮ ሲያወሩ እሷ ያለቜበትን ማዕኹል ዚሚያስተዳድሚው ኩባንያ በሁሉም ነገር ዝግጁ እንደሆነ አሳውቆናል። ጥብቅ ዹሆነ ዚጜዳት ቁጥጥርን ጚምሮ፣ ወሚርሜኙን ለመኹላኹል ዚሚያስፈልጉ ቁሳቁሶቜን በኹፍተኛ መጠን አኚማቜቷል። ነገር ግን በተለያዩ ሁለት ግዛቶቜ ዹሚገኙ ማዕኚላት ዚቫይሚሱን መዛመት መቆጣጠር አቅቷ቞ው በርካታ አሚጋውያን ሚግፈዋልፀ ይህም ሁኔታ ለቀተሰቊቻ቞ው ልብ ሰባሪ ሆኗል። እነዚህ አሚጋውያን በቫይሚሱ በቀላሉ እንደሚጠቁና፣ ተጋላጭም እንደሆኑ ማወቅ ዚሮኬት ሳይንስ አይደለም። በርካታዎቹ አሚጋውያን ሌላ ተደራራቢ ህመሞቜ ያሉባ቞ው ሲሆኑ በማዕኚላቱም ውስጥ ያለው ዹህክምና አገልግሎት ዹተወሰነ ነው። ኹዚህም በተጚማሪ ዹማዕኹሉ ሠራተኞቜም በተለያዩ ቊታዎቜ ኚመስራታ቞ውም አንፃር ቫይሚሱን በቀላሉ ያዛምታሉ። በዚካቲት ወር ላይ በአውሮፓ በሚገኙ ማዕኚላት ውስጥ ያሉ አሚጋውያን በሚያሰቅቅ ሁኔታ እንደ ቅጠል እዚሚገፉ እንደሆነ ታሪኮቜ መውጣት ጀመሩ። ይህም ሁኔታ በአውስትራሊያ ሊያጋጥም እንደሚቜል አገሪቷ ማወቅ ነበሚባት ዚሚሉት በሞናሜ ዩኒቚርስቲ ዚጀና ሕግ ክፍል ኃላፊ ጆ ኢብራሂም ና቞ው። "ዚአውስትራሊያ ምላሜ በቂ አልነበሚም። ለሚመጣው ነገር በሙሉ ዝግጁ አልነበሚቜም እናም አሁን ዹተፈጠሹው ክስተት ሊያስደንቀን አይገባም" ይላሉ ። "ብዙ ሰዎቜ ይህ መሆኑ አይቀሬ ነበር ሲሉ ይሰማል። ይሄ ግን ትክክለኛ አይደለምፀ ምክንያቱም ምንም ማድሚግ አንቜልም ነበር ዹሚለውን ትርጉም ስለሚሰጥ ነው። ዚኮሮናቫይሚስ በአሚጋውያን ላይ ምን ያህል አደጋ እንደደቀነ ኚግምት ውስጥም አላስገባነውም። በሌሎቜ አገሮቜ ላይ እያለቁ ዚነበሩትንም አሚጋውያን መሚጃዎቜ አላጀንነውም" ይላሉ። በመጋቢት ወር ላይ በሲድኒ ዹሚገኝ ዶሮቲ ሄንደርሰን ሎጅ ዚተባለ ዚአሚጋውያን ማዕኹል ሠራተኛ በኮሮናቫይሚስ መያዟ ተሚጋገጠፀ በግንቊት ወርም 21 በማዕኹሉ ዚሚኖሩ አሚጋውያንና ሠራተኞቜም ተያዙ። ኚእነዚህም ውስጥ ስድስቱ ሞቱ። ሌላ እንዲሁ በሲድኒ ውስጥ ዹሚገኝ ኒውማርቜ ዚተባለ ማዕኹልም በኮሮናቫይሚስ ዚተያዙ ህሙማንን ወደ ጀና ማዕኹል ኹመላክ ይልቅ ክፍላቾው ውስጥ እንዲዘጉ አደሚገ። ማዕኹሉ ዚሠራተኞቜ ዕጥሚት እንዲሁም ዚኮሮናቫይሚስ መኚላኚያ ቁሳቁሶቜም በበቂ ሁኔታ አልነበሩትም። ይህንንም ተኚትሎ 19 አሚጋውያን ሲሞቱ በርካቶቜም በቫይሚሱ ተያዙ። በኒውማርቜ አሚጋውያን እንክብካቀ ማዕኹል ቀተሰቊቻ቞ው ዚሞቱባ቞ው ተቃውሟቾውን ሲያሰሙ ዚአሚጋውያኑ መሞት በርካታ ጥያቄዎቜን ቢያጭርም ይህ ለምን እንደተኚሰተ አጥጋቢ ምላሜ ዚሚሰጥ አካል አልተገኘም። አሁንም ኚክስተቱ ያልተማሚቜው አውስትራሊያ አሚጋውያኗን በኮሮናቫይሚስ እያጣቜ ነው። ዚቪክቶሪያ ግዛት እንደ አዲስ ወሚርሜኙ እያገሚሞባት ሲሆን ኚማህበሚሰቡ ስርጭት በተጚማሪ ዚአሚጋውያኑ ዚእንክብካቀ ማዕኚላት በኹፍተኛ ሁኔታ እዚተጠቁ ነው። በአሁኑ ወቅትም 1 ሺህ 200 ዹሚሆኑ አሚጋውያን በ97 ማዕኚላት ውስጥ መያዛ቞ው ተሚጋግጧል። ፕሮፌሰር ኢብራሂም እንደሚሉት ዚእንቅስቃሎ ገደቊቜ ብቻ቞ውን ቫይሚሱን መግታት አይቜሉም። "በሜታው ቢያጋጥም ምን ማድሚግ አለብን ዹሚለው ላይ ዹተቀመጠ ግልጜ ያለ ፖሊሲም ሆነ ይህንንም መቆጣጠር ዚሚቜል መዋቅር አልተዘሹጋም" ይላሉ። ዚአሚጋውያኑን ዚእንክብካቀ ማዕኚላት በቀጥታ ዹሚመለኹተው ዚፌደራል መንግሥቱን ቢሆንም ወሚርሜኙን ደግሞ በዚግዛቱ ያሉ ዚኅብሚተሰብ ጀና ኃላፊዎቜ በበላይነት ይቆጣጠሩታል። "በዚህም ምክንያቱ ኃላፊነቱ ዹማን ነው በሚል መወዛገብ ተፈጠሚ። ይሄ ብቻ አይደለም ዚኮሮናቫይሚስ ህሙማን ህክምናው መሰጠት ያለበት ሆስፒታል ወይስ ቀታ቞ው ውስጥ ዹሚለውም ላይ ውሳኔ ሳያገኝ እንዲሁ እያወዛገበ ነበርም" በማለት ያስሚዳሉ። ዹተቃዋሚ ፓርቲ መሪ አንቶኒ አልባኔዝ በዚህ ሳምንት ሰፋ ያለ ምርመራና ኃላፊነት ሊወስዱ ዚሚባ቞ውም አካላት እንዲጠዚቁ ተናግሚዋል። "በኒውማርቜ እንክብካቀ ማዕኹል ካጋጠመን ክስተት ለምን አልተማርንም? ይህ ዹተኹሰተው ኚወራት በፊት ነበር" በማለትም ይጠይቃሉ። በሜልቩርን ዚግዛቲቷና ዚፌደራል ኀጀንሲዎቜ ተጣምሚውም በቪክቶሪያ ዹተኹሰተውን ዚወሚርሜኝ ቀውስ ለመቆጣጠር ጥሚት እያደሚጉ ነው። ለፕሮፌሰር ኢብራሂም ግን ዋናው ነገር ብሔራዊ ግብሚ ኃይል ተቋቁሞ በአውስትራሊያ ዹሚገኙ ዚእንክብካቀ ማዕኚላት ሁኔታ ሊገመገም እንዲሁም ቁጥጥር ሊደሚግበት ይገባል ይላሉ። "በዚህም መንገድ ነው ዚትኞቹ ማዕኚላት አደጋ ውስጥ እንዳሉ ዚምንሚዳው" ዚሚሉት ፕሮፌሰሩ አክለውም "ኚዚያ በመቀጠልም ያለምንም ማንገራገር ፈጣንና ዚማያዳግም እርምጃ ሊወሰድ ይገባል" በማለትም ምክራ቞ውን ለግሰዋል። በእንክብካቀ ማዕኚላቱ ዹተፈጠሹውንም ሁኔታ ዚሚያጣራ ዚመንግሥት ቡድንም ተቋቁሟል። ኚተለያዩ ቊታዎቜ ዹተገኙ መሚጃዎቜ እንደሚያስሚዱትም ለእነዚህ አሚጋውያን መሞት ዋነኛ ምክንያቶቜ በማዕኚላቱ ዹሚገኙ ሠራተኞቜ እጥሚት እና በቂ ስልጠና አለማግኘት ዚሚጠቀሱ ና቞ው። ኹዚህም በተጚማሪ ዚኮሮናቫይሚስ ዚመኚላኚያ ቁሳቁሶቜ እጥሚትና ዚጀና ኃላፊዎቜ ምላሜ መዘግዚት ይገኙበታል። ዚአውስትራሊያ ህክምና ማኅበር በበኩሉ መንግሥትን ተጠያቂ አድርጓልፀ ጥብቅ ምርመራም ያስፈልጋል እያለ ነው። በቪክቶሪያ ዹሚገኘው ቅርንጫፉ ፕሬዚዳንት ጁሊያን ራይት ለናይን ጋዜጣ እንደተናገሩት ቀውሱ "ዹተገመተውን አሳዛኝ ክስተት ጥሎ አልፏል" እንዳሉ አስነብቧል። በቪክቶሪያ ዹሚገኙ በርካታ አሚጋውያን በኮሮናቫይሚስ መሞታ቞ው አይቀሬ እንደሆነ ዚአውስትራሊያ ጀና ቢሮ ፀሐፊ ብሬንዳን መርፊ ኹሰሞኑ ተናግሚዋል። ውድ አያቶቌ በእነዚህ ማዕኚላት አለመገኘታ቞ው እድለኛ ነኝ። አሁንም ዚሚገኙባ቞ው ዚእንክብካቀ ማዕኚላት ኚኮሮናቫይሚስ ነፃ ና቞ው። አንደኛዋ አያ቎ ማርጋሬት ጎብኚም አያያትምፀ ሌላኛዋ አያ቎ ማርጋሬትን ግን በሳምንት አንዮ እንድናያት ተፈቅዶልናልፀ እና቎ም ቅዳሜ እለት ሄዳ ነበር። ለሚዥም ጊዜያት ሳቁ፣ ተቃቀፉ፣ ቀልድም ጣል እያደሚጉ ኮሮናቫይሚስ እንዳለ ዘነጉት። አያ቎ ናና ቫይሚሱ ኚያዛት መሞቻዬ ነው ብትልም እንዲህ በቀላሉ እጅ አልሰጥም ትላለቜ። "ህፃን እያለሁ ዳክዬዎቜ አባሚሩኝ ግን አልደሚሱብኝምፀ አሁንም ኮሮናቫይሚስ ይይዘኛል ዹሚል ግምት ዹለኝም" ብላ አስቃናለቜ።
news-43174899
https://www.bbc.com/amharic/news-43174899
ፍቅርና ጋብቻ በቀይ ሜብር ዘመን
ፍቅር ተስፋ በሌለባ቞ው ቊታዎቜም ያብባል
ለአይናለምና ለገነትም ይህ ነበር ዚሆነው። እ.አ.አ በ1978 በኢትዯጵያ ታሪክ ኚባድ ዹቀይ ሜበር ወቅት ተጋቡ። ዹደም መፋሰሱ ኚጋብቻ቞ው ኚዓመት በፊተ ዹጀመሹ ሲሆንፀ እሱም መንግሥቱ ኃይለማሪያም ሥልጣን ይዞ ጠላቶቹን ለማጥፋት ቆርጩ ዚተነሳበት ጊዜ ነበር። . ሥልጣን በተቆጣጠሚበትም ጊዜ በሺህ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜ ሞቱ ደግሞም በሺህ ዚሚቆጠሩ ለመፈናቀል ተገደው ነበር። ይህ ግን አይናለምንና ገነትን ኚአዲስ አበባ ወጣ ብላ በምትገኘው በሰንዳፋ ዚጋብቻ ቃላቾውን ኚመቀያዚር አላገዳ቞ውም ነበር። ለዚህ ታስበው ዚተወሰዱት ፎቶግራፎቜ ኹ Vintage Addis Ababa ሲሆን በልዩ ሁኔታዎቜ ላይ ሰዎቜ እንዎት እንደሚኖሩ ማሳያ እንዲሆን ታስቊ በቀተ-መዛግብት ዚተቀመጡ ነበሩ። ሚዥሙ ዚመጠናናት ጊዜ እ.አ.አ በ1973 ነበርፀ ወጣቶቹ ዚተዋወቁት በአንድ ሰፈር ይኖሩ ስለነበር ነው። በዓመቱ ደርግ መንግሥት ወደ ሥልጣን ሲመጣ ለመንግሥቱ ኃይለማሪያም ዚሥልጣን ጥርጊያ መንገድ አመቻ቞። እ.አ.አ በ2008 በሌለበት መነግሥቱ ኃይለማሪያም ሞት ተፈርዶበታል። እሱ በዚምባብዌ ነው ዚሚኖሚው። ይህን ተኚትሎ ዹተኹሰተው ግርግር ሳያስቡት ሕይወታ቞ውን አንጠልጥሎ አስቀሚው። አይናለም ገነትን ዹሁለተኛ ደሹጃ ትምህርት እንደጚሚሰቜ ለማግባት አቅዶ ነበር። ሆኖም ግን እ.አ.አ በ1978 ዹተቃውሞ ሰልፍ ላይ ተይዛ ለሊስት ወራት ታሰሚቜ። "በደርግ ስር መኖር ቀላል አልነበሹም" ትላለቜ ገነት። በመቀጠልም "ያለው ፍራቻ ሙሉ ሰው ኹመሆን ያደናቅፈን ነበር" ብላለቜ። ዹደርግ ሥርዓት ዚታሰሚን ሰው ቀተሰብ እንዲጠይቅ ባይፈቅድምፀ አይናለም ግን በዹተወሰነ ቀናት ገነትን ያያት ነበር። ዚአብዮቱ ጠባቂ ስለነበር ሌሎቜ ተቃዋሚዎቜ ስለግንኙነታ቞ው ቢያውቁ ለሕይወቷ ያሰጋ ስለበር በጣም ይጠነቀቅ ነበር። "ሰላም መባባልም ሆነ መነጋገር አንቜልም ነበር። ጥበቃዎቹ እንደምንተዋወቅ ሊያውቁብን ይቜሉ ነበር። ሆኖም ግን ግቢው ውስጥ ባዚሁት ቁጥር ደስ ይለኝ ነበር" ትላለቜ። ገነት ታስራ ዹነበሹ ቢሆንም ዚጋብቻ቞ው ፎቶግራፎቜ ግን ዚጉስቁልና አንዳቜ ምልክት ዚላ቞ውም። ጉልበት ተሳመ ዹሠርጋቾውን ዕለት በኢትዮጵያ ባህል መሠሚት ጀመሩት። አይናለም ገነትን ኚቀተሰቊቿ ቀት ወደ እራሱ ቀት ለመውሰድ ኚመሄዱ በፊት ዚእናቱን ጉልበት ስሞ ነበር ኚቀቱ ዚወጣው። በቀቱ ደጃፍ ላይም ጎሚቀትና ጓደኞቹ ሊሞኙት ተሰብስበው ነበር። ጥቁር ሱፍ አንገትን በሚሾፍን ነጭ ሹራብ ዹለበሰው አይናለም ገነትን ለማምጣት ወደ ተዘጋጀቜው ቌቭሮሌት አቀና ። ቀለበቶቻ቞ውን ፒያሳ ኹሚገኘው አፍሪካ ወርቅ ቀት ዚገዙት ሙሜሮቜ ኚሰዓት በኋላ በገነት አባት ቀት ቄስ ፊት ቃል ገቡ። ኚተጋበዙት 300 ሰዎቜም ራቅ ብለው ሙሜሮቹ ፎቶግራፍም ለመነሳት ቜለው ነበር። ለገነት በሚያሳዝን ሁኔታ ግን አይናለም እ.አ.አ በ2008 ኹዚህ ዓለም በሞት ተለዚ። እሷ ግን አብሚው ያሳለፉትን ጊዜያት በጣም እንደምትወድና እንደምትናፍቅ ትናገራለቜ። "ያፈቀርኩትን ሰው ነበር ያገባሁት፣ ያሳደግሁትም ኚልቀ ዚምወዳ቞ውን ልጆቜ ነው" ትላለቜ። ዚፎቶግራፎቹ መብት ሙሉ በሙሉ ዹVintage Addis Ababa ነው።
news-54478773
https://www.bbc.com/amharic/news-54478773
ተፈጥሮ ፡ እውቅና ሳያገኝ ለአደጋ ዹተጋለጠው ዹሃላይ ደጌ አሰቊት ጥብቅ ደን
ዹሃላይደጌ አሰቊት "ብሔራዊ እጩ ፓርክ" በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ደሹጃ ብርቅዬ ዹሆኑ እንስሳትን በውስጡ ዚያዘ ነው። ኹ1960ዎቹ ጀምሮ በጥብቅ ደንነት ዹኖሹው ፓርኩ፣ በብሔራዊ ፓርክ ደሹጃ አለማደጉ ግን በበጀትና በአስተዳደር ዹተደሹጃ እንዳይሆንና ለሕገ ወጥ ድርጊት ተጋላጭ አድርጎታል።
በአፋርና በኊሮሚያ ክልል ውስጥ ዹሚገኘው ሃላይደጌ አሰቊት ፓርክ፣ 1 ሺህ 90 ካሬ ኪሎ ሜትር ስፋት እንደሚሞፍንና በርካታ እንስሳትንና ዚእጜዋት ዝርያዎቜን ያቀፈ መሆኑን ዚፓርኩ ኃላፊ አቶ መቆያ ማሞ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። እንደሃላፊው ገለጻ በፓርኩ ውስጥ 42 አጥቢ ዚዱር እንስሳት፣ ኹ240 በላይ አዕዋፋት እና ኹ260 በላይ ደግሞ ዚዕጞዋት ዝርያዎቜ ይገኙበታል። አብዛኞቹ እንስሳት ጎብኚዎቜ ሊያይዋ቞ው ዹሚፈልገጹውና ምናልባትም በአፍሪካ ደሹጃ በብዛት በዚሁ ፓርክ ዹሚገኙ መሆናቾውን አቶ መቆያ ይገልጻሉ። ፓርኩ ኚአዲስ አበባ ወደ ሐሚር በሚወስደው መንገድ 280 ኪሎ ሜትር ላይ ዚሚገኝ፣ ኚአዋሜ ብሔራዊ ፓርክ ብዙም ያልራቀ ምቹ ዚጉብኝት አካባቢ መሆኑን ኃላፊው ያብራራሉ። ፓርኩ በብሔራዊ ፓርክ ደሹጃ ተመዝግቩ አስፈላጊው ዚአስተዳደርና ዚጥበቃ ሁኔታ እንዲሟላላት ጥያቄ ማቅሚብ ዹተጀመሹው ኚስድስት ዓመታት በፊት በ2006 ዓ.ም ነበር። ነገር ግን እስካሁን ጥያቄው ምላሜ አላገኘም። በወቅቱ ሁሉንም መስፈርቶቜ በማሟላት ዚአካባቢውን ማኅበሚሰብ ይሁንታን በማግኘት እውቅናውን ለማሰጠት ሂደቱ መጀመሩን አቶ መቆያ ያስታውሳሉ። ኹሃላይደጌ አሰቊት ጋር ሰባት ፓርኮቜ ወደ ብሔራዊ ፓርክነት ለማደግ ጥያቄ ቢያቀርቡም እነሱ ግን እስካሁን እውቅና አላገኙም። "ሰነድ በማዘጋጀት ሚገድ ዚሚጠበቅብንን ሁሉ አጠናቀናል" ዚሚሉት አቶ መቆያ፣ "ሰነዱ በጠቅላይ ዐቃቀ ሕግ አስፈላጊው ምርመራና ማሻሻያ ተደርጎበት አስተያዚት እንድንሰጥ ተመልሶልናል" ይላሉ። ዚያንጉድራሳ ብሔራዊ ፓርክ ኹሃላይ ደጌ አሰቊት ፓርክ በቅርብ ርቀት ስለሚገኝ፣ ዹሃይላደጌ አሰቊት ፓርክን በሞግዚትነት ያስተዳድሚው ነበር። ዚያንጉድራሳ ብሔራዊ ፓርክ ቀደም ሲል በፌደራል መንግሥት ሥር ይተዳደር ዹነበሹ ቢሆንም፣ አሁን ግን ዹአፋር ክልል በራሱ ሊያስተዳደሚው ሂደቶቜ እዚተጠናቀቁ ነው። ይህ ሲሆን ደግሞ ዹሃላይ ደጌ አሰቊት ብሔራዊ ፓርክ ብቻውን ያለ ጠባቂ ይቀራል ዹሚል ስጋትን ፈጥሯል። በዚህ ምክንያትም ጥበቃው ያልተጠናኚሚ ኹመሆኑ አንጻር ዚዱር እንስሳቱ ለሕገ ወጥ አደን ይጋለጣሉ፣ ሌሎቜ ሕገ ወጥ ተግባራትም ሊስፋፉ ይቜላሉ ዹሚለው ስጋትም አለ። አብዛኞቹ ዚአካባቢው ዚዱር እንስሳት አነስተኛ ዝርያ ያላ቞ውና በመጥፋት ላይ ያሉ በመሆናቾው እነዚህ ብርቅዬ ዚዱር እንስሳት ኚነጭራሹ ዚመጥፋት አደጋ ሊገጥማ቞ው ይቜላል ዹሚለውም ሌላኛው ስጋት ነው። በአፋር በኩል ዚዱር እንስሳትን ዹመጠበቅ ጥሩ ልምድ መኖሩ ለፓርኩ ሕልውና አንዱ እድል ቢሆንምፀ በሌላ በኩል ግን እነዚህን እንስሳት አንዳንድ ሰዎቜ ለመድኃኒትነትና ለሌሎቜ ጉዳዮቜ ስለሚፈልጓ቞ው በሕገ ወጥ አደን ሊያጠፏ቞ው ይቜላሉ ይላሉ አቶ መቆያ። በፓርኩ ላይ ዹተጋሹጠው አደጋ ፈጣን ምላሜ ዚሚያስፈልገው መሆኑን ዚኢትዮጵያ ዚዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ኩመራ ዋቅጂራ ይናገራሉ። ፓርኩን ወደ ብሔራዊ ፓርክነት ዚማሳደጉ ሂደት በተለያዩ ምክንያቶቜ ኚሚገባው በላይ መጓተቱን ዚሚያምኑት አቶ ኩመራፀ በአሁኑ ወቅት ግን ተስፋ ሰጭ ደሹጃ ላይ ነው ያለው ይላሉ። ፓርኩ በሁለት ክልሎቜ ውስጥ ዹሚገኝ በመሆኑ በዹደሹጃው ዹሚገኝ መዋቅርን ማሳተፍ እንደሚጠይቅ ጠቅሰውፀ እስካሁን ሂደቱ በሚፈለገው መጠን ባይፈጥንም ነገር ግን በሚንስትሮቜ ምክር ቀት እንዲጞድቅ አስፈላጊው መሹጃ ተሰባስቊ በዝግጅት ላይ መሆኑን ይገልጻሉ። በርካታ አደሚጃጀቶቜና ዚለውጥ ሥራዎቜ ስለሚሰሩ ኚእነሱ ጋር ማጣጣሙ ጊዜ እንደወሰደ ተናግሚዋል። ፓርኩ ለሹጅም ጊዜ 'ጥብቅ ክልል' ተብሎ ነበር ዚሚታወቀው። በዚህ ምክንያትም ፓርኩ ተገቢው ጥበቃና አስተዳደር ሳያገኝ ቆይቷል። ኹ2002 ዓ.ም ጀምሮ ግን ፓርኩ ያለውን ጥቅም በመገንዘብ በያንጉድራሳ ፓርክ ጥላ ስር ሆኖ ሲተዳደር ነበር። ፓርኩ ለቱሪዝም ዘርፍ እምቅ ሃብት ያለው ሲሆንፀ ሳላ ዚሚባለው እንስሳ በአፍሪካ ደሹጃ በብዛት ዚሚገኝበትም ነው። ይህ እንስሳ በብዛት ዹሚገኘው ኬንያ፣ ኡጋንዳ እና ኢትዮጵያ ውስጥ ሲሆን ኚኢትዮጵያ ደግሞ በብዛት ዹሚገኘው ሃላይ ደጌ አሰቊት መሆኑን አቶ ኩመራ ተናግሚዋል። ሌላኛው ለጥፋት ዹተጋለጠው ዚሜዳ አህያ ዝርያም በዚሁ ፓርክ ውስጥ ይገኛል። ዹዚህ ዝርያ ትልቁ መንጋ ዹሚገኘው እዚሁ ፓርክ ውስጥ መሆኑን አቶ ኩመራ ዋቅጂራ ይገልጻሉ። በመሆኑም እነዚህ እንስሳትን በዘላቂነት በፓርኩ ውስጥ ህልውናቾውን ለማስጠበቅና ፓርኩ ዹሚሰጠውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማሳደግ ጥሚቶቜ ቀደም ብለው ቢጀመሩም እስካሁን መቋጫ እንዳላገኙ ይገልጻሉ። ኹ40 ዓመታት በላይ በጥብቅ ደንነት ብቻ በመቆዚቱ በ2002 ዓ.ም ጥብቅ ደኑ ያሉት ጞጋዎቜ ተለይተው በያንጉድራሳ ፓርክ ጥላ ሥር ሆኖ ጥበቃ እንዲደሚግለት መደሹጉም ተነግሯል። ኚአራት ዓመታት በኋላ ደግሞ ዚባለሙያ ቡድን ተዋቅሮ በ2006 ዓ.ም ወደ እጩ ብሔራዊ ፓርክነት እንዲያድግ ሥራዎቜ ተሰርተው መነሻ ሐሳቡ ለሚመለኹተው አካል ጥያቄው ቀርቧል። በአፋር እና በኊሮሚያ ክልሎቜ ምክክር ተደርጎ ስምምነት ላይም ተደርሶ እንደነበር አቶ ኩመራ ያስታውሳሉ። በወቅቱ ቀሪው ሂደት ዹነበሹው ዚብሔራዊ ፓርክነት እውቅና እንዲያገኝ ሹቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ ለሚንስትሮቜ ምክር ቀት እንዲቀርብ ማድሚግ ነበር። ነገር ግን እዚህ ደሹጃ ኹተደሹሰ በኋላ በተለይ በኊሮሚያ ክልል በኩል ዹተወሰኑ ቢሮዎቜ ጉዳዩን እንደማያውቁትና አካሄዱም ትክክል አለመሆኑን መግለጜ በመጀመራ቞ው ሂደቱን ማስቀጠል አለመቻሉን አቶ ኩመራ ይገልጻሉ። ፓርኩ አሰቊት ገዳምንም ዚሚያካትት ስለነበሚ 'ሃላይደጌ አሰቊት' ዹሚል ስም በመያዙ ኚስያሜ ጋር ዚተያያዘ ቅሬታ አጋጥሞ ነበር። በዚህ መካኚል ደግሞ አመራሮቜ በፍጥነት ስለሚቀያዚሩ መጀመሪያ ጉዳዩን ያንቀሳቀሱት አካላት በመቀዚራ቞ው ጉዳዩ እንደገና ተመልሶ ወደ ኋላ ተጎተተ ይላሉ አቶ ኩመራ። በዚህ ምክንያት ፓርኩን ወደ ብሔራዊ ፓርክነት ዚማሳደጉ ሂደት ተስተጓጎለ። ዚሚንስትሮቜ ምክር ቀት ደግሞ ሁሉም በዹደሹጃው ዹሚገኙ ዚሚመለኚታ቞ው አካላት ዚተስማሙበትን ሰነድ ካሚጋገጠ በኋላ ነው እውቅና ዚሚሰጠው። በሁለቱ ክልሎቜ በኩል በተነሱ ቅሬታዎቜ ምክንያትም እነዚህ ሂደቶቜ እንዲሟሉ ወደ ኋላ ተመልሶ ዚሁለቱንም ክልል ዹዹደሹጃው አመራሮቜና ነዋሪዎቜን ማወያዚት ማስፈለጉም ተነግሯል። ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ኩመራ እንደሚሉትም እነዚህን ጉዳዮቜ ታሳቢ በማድሚግ በአሁኑ ወቅት አንድ ግብሚ ኃይል ተቋቁሞ፣ ዝርዝር እቅድ ተዘጋጅቶለት፣ ለእውቅና ሚያበቁት ሂደቶቜና ዚክልሎቜ ይሁንታ ተጠናቆ ዚእውቅና ጥያቄው እስኚመቌ መቅሚብ እንዳለበት በእቅድ መቀመጡን ጠቅሰዋል። በዚሁ መሰሚትም በስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ቀሪ ሥራዎቜ ተጠናቀው ለሚንስትሮቜ ምክር ቀት ዚእውቅና ጥያቄ ለማቅሚብ እዚተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።
news-56924983
https://www.bbc.com/amharic/news-56924983
ምርጫ 2013፡ "በራሱ መሬት ላይ እንግዳ ዹሆነ ሕዝብ ቢኖር ዹአፋር ሕዝብ ነው"
በአሞባሪነት ተፈርጇል። እንደ ግንቊት 7 እና ኊብነግ ነፍጥ አንስቶ በኀርትራ በሹሃ ኳትኗል። ዹጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አስተዳደር ሥልጣን ኚያዘ በኋላ ወደ አገር ቀት ገብቷል።
አሁን በአፋር ኹፍተኛ ተሰሚነት ካላ቞ው ፓርቲዎቜ አንዱ ነው። "ዹአፋር ሕዝብ ፓርቲ" ወይም በእንግሊዝኛ ምሕጻሩ ኀፒፒ (APP) ተብሎ ይጠራል። ኚፓርቲው ሊቀ መንበር አቶ ሙሳ አደም ጋር በቁልፍ ዹአፋር ሕዝብ ጉዳዮቜ ዙርያ ዘለግ ያለ ቆይታ አድርገናል። ፓርቲ ስለበዛ እስኪ ዚእርስዎን ፓርቲ በአጭሩ ያስተዋውቁን? በፈሚንጆቜ 2010 ላይ ነው ዚተመሠሚትነው። ኚዚያ በኋላ ግን ሕጋዊነት አልነበሚውም። እዚህ ዹነበሹው ነገር ፈሹሰና ኚዚያ ፓርቲው በአሞባሪነት ተፈሚጀ። አባላቱ ተበተኑ። ህቡዕ ገባን። ተሰደድን። ምን ያህል ወታደሮቜ ነበሯቜሁ? ወደ 3ሺህ ታጣቂ ወታደሮቜ ነበሩን። ኀርትራ ነው ዚነበሩት። ወታደሮቻቜሁ አሁን ዚት ነው ያሉት? ኚለውጡ በኋላ በምዕራፍ፣ በምዕራፍ አስገብተና቞ዋል። አጠቃላይ ወታደሮቻቜን መልሰው ተቋቁመዋል። ዚወታደራዊ ክንፋቜን ዜሮ ፐርሰንት ነውፀ በዚህ ሰዓት። ምን ያህል አባላት አሏቜሁ? በቋሚነት ወርሃዊ ክፍያ ዹሚኹፍሉ አባላት 250ሺህ ሰዎቜ ይሆናሉ። ለምንድነው "ዹአፋር ግንቊት 7" ዚሚሏቜሁ? ዛሬም አንድ ጋዜጠኛ ይህንኑ ሲጠይቀኝ ነበር። 'ኚግንቊት 7 ጋር ግንኘነት አላቜሁ ይባላል' አለኝ። 'ግንቊት 7 አለ እንዎ?' አልኩት። ምናልባት መንፈሱን ኢዜማ ወርሶት ኹሆነ ብለን በዚያ እንያዘውና ጥያቄውን እንቀጥል። ለምን ይህ ቅጜል መጣ? ዚግንቊት 7 ተላላኪዎቜም' ዚሚሏቜሁ አሉ። ዹአፋር ሕዝብ ፓርቲ ሲፈጠርም አግላይ አስተሳሰብ ዚለውም። ጜንፈኛም አይደለም። አማካይ (Moderate) ዚፖለቲካ አካሄድን ነው ዚሚመርጠው። ግንቊት 7 በትግል ወቅት አብሚን ዚተባሚርን ዚትግል አጋር ፓርቲ ነበር። ኀርትራም ሳለን ሰፊ ግንኙነት ነበሚን፣ ውጭ እያለንም 'ኢትዮጵያን ናሜናል ሞቭመንት' ዚሚባል እንቅስቃሎ ነበሚን። እዚያ ውስጥ እነ ሌንጮ ባቲ ዚነበሩበት ድርጅት፣ ዚሲዳማ አርነት ንቅናቄና እኛም፣ ግንቊት 7ም ነበሚ። አሁን ግንቊት 7ም ፈርሶ እኛም እንደ አዲስ ተደራጅተን ነው ያለነው። አሁን ኢዜማ አለ። ኢዜማና ፓርቲያቜን ጥሩ ግንኙነት ነው ያለን። ይሄ ምንም ዹሚሾፋፈን ነገር ዚለውም። በፖለቲካ አስተሳሰብ ደሹጃ ግን አንድ ነን ማለት አይደለም። መሠሚታዊው ልዩነታቜሁ ምንድነው? ለምሳሌ በመንግሥት አወቃቀር ላይ እኛ አሁን ያለው ዚፌዎራል አወቃቀር መቀጠል አለበት፣ ቜግር ዚለበትም ነው ዚምንለው። ቋንቋ ላይ መሠሚት ያደሚግ ዘውጌ ዚፌዎራል አወቃቀር ትክክለኛ ነው ብላቜሁ ነው ዚምታምኑት? አዎ! ፌዎራል አወቃቀር ቜግር አለበት ብለን አናምንም። ዚፌዎራሊዝሙ አፈጻጞም፣ ዚተተገበሚበት መንገድና 'ማኒፑሌት' ዚተደሚገበት መንገድ (ዚተጠመዘዘበት ሁኔታ) ግን መርዘኛ ነው ብለን እናምናለን። መርዘኛ ብቻ ሳይሆን ሕዝቊቜ ማንነታ቞ውን ይዘው አብሚው እንዳይኖሩ ዚሚያደርግ መጥፎ አተገባበር ነበሹ ብለን ነው ዚምናስበው። ኢዜማ ደግሞ መልኚአምድራዊ (Geographic) ፌዎራሊዝም ነው መኖር ያለበት ይላል። ኚእኛ ጋር በጣም ይራራቃል። ዹአፋር ሕዝብ መንፈሳዊ አባት ኚነበሩት ሡልጣን ሐንፍሬይ አሊሚራህ ጋር ዹናንተ ፓርቲ ዹተለዹ ግንኙነት ነበሹው ልበል? ስትገቡም አብራቜሁ ነው ዚገባቜሁት። ሡልጣን አሊሚራህ በጣም ቅርብ ወዳጃቜንም መካሪቜንም ነበሩ። በወንድማ቞ው ዚሚመራ ዹአፋር ነጻ አውጪ ፓርቲ አለ። እኩል ነበር ዚሚያዩን። በተለይ ኚእኛ ፓርቲ መሪ ዶ/ር ኮን቎ ሙሳ ጋር ልባዊ ግንኙነት ነበራ቞ው። ዚተሰደዱ ጊዜ ኹፍተኛ አቀባበል አድርገንላ቞ዋል። በብዙ ነገር ይደግፉን ነበር። ኚሚጠበቅባ቞ው አባታዊ ድጋፍም በላይ መካሪያቜን ነበሩ። ይሄን ጥያቄ ያለምክንያት አላነሳሁም፣ አቶ ሙሳ። ሡልጣኑ ኚእናንነተ ጋር መወገን ዚጚዋታውን ሕግ ስለሚቀይር ነው። እርሳ቞ው በአፋር ክልል "አያቶላህ" ማለት ና቞ው። በፖለቲካ ባሚኳቜሁ (Endorse ) ማለት ትልቅ ዚፖለቲካ ድል ነው። ዚድጋፍ መሠሚታቜሁንም ያደላድላል። ልክ ነህ። ይሄ እንግዲህ እንደ ሰው ዕይታ ነው ዚሚወሰነው። እኛ በፕሮግራም ደሹጃ ለአገር ሜማግሌዎቜ፣ ለነባር ታጋዮቜ እና ለመንፈሳዊ አባቶቜ ፕሮግራም ቀርጾን ነው ዚምንቀሳቀሰው። ለአገር ሜማግሌዎቜ ዹተለዹ ስፍራ አለን። ራሱን ዚቻለ ፓርላማ (ቌምበር) አዘጋጅተናል...። እሱን ወደኋላ እንመለስበታለን። ሌላ ጥያቄ ላንሳ። ፓርቲያቜሁ ስለሎቶቜ ግድ ይለዋል? ለምሳሌ ስንት አባላት በአመራር ደሹጃ አሏቜሁ? እኛ ዚሎቶቜን ተሳትፎ በዋዛ አንመለኚተውም። ሎቶቜ ያለገደብ ዚፖለቲካ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ነው ዚምንታገለው። ዹአፋር ሎት እንደሌሎቜ አካባቢዎቜ ሁኔታዎቜ ዚተመቻቹላት ሎት አይደለቜም። ዹአፋር ሎቶቜን ወደ ፖለቲካ ሜዳ ማምጣት በራሱ ቀላል ሥራ አይምሰልህ። ያም ሆኖ በጣም ብዙ ሎት አባልና ደጋፊዎቜ አሉን። ወጣት ሎቶቜ በስፋት ገብተው ፖለቲካ እንዲሠሩ እናደርጋለን። በአሐዝ አስደግፈው ይገሩኝፀ ስንት አባላት በሥራ አስፈጻሚ ደሹጃ አሉ? ኚአሥራ አንድ ሥራ አስፈጻሚ መሀል አራቱ ሎቶቜ ና቞ው። ቁልፍ ኃላፊነቶቜን ዚያዙም ና቞ው። በማዕኹላዊ ኮሚ቎ ደሹጃ 45 አባላት አሉ። 15ቱ ሎቶቜ ና቞ው። ትንሜ ቁጥር ነውፀ እናውቃለን። ግን በስፋት እዚሠራንበት ነው። በነገርህ ላይ፣ ኚኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎቜ ኚብዙዎቹ እኛ በሎቶቜ አሳታፊነት ዹላቅን ነን። ምርጫ ቊርድ በዚህ ሚገድ ያወጣው ጥናት አለ። እኛ ጋ በአባላት ደሹጃ 34 ኚመቶ ሎቶቜ ና቞ው። ይሄ ትንሜ ቁጥር ቢመስልም በአገር ደሹጃ ትልቁ 38 ኚመቶ ነው። እውነት ለመናገር እኛ ሎቶቜን ወደፊት ለማምጣት ቁርጠኛ ነንፀ ግን ሥራው ቀላል አይደለም። ዹአፋር ሎት ሌሊት ወጥታ ማታ ነው ዚምትገባው። እንጚት ለቅማ፥ እሚኝነቱፀ ውሃ መቅዳት በሎቷ ጫንቃ ላይ ነው ያለው። ዹአፋር ሎት ፖለቲካን ለመሥራት ምን ዚተመቻ቞ላት ነገር አለ? ይቺ አሐዝ ላይ ዚደሚስነውም በኹፍተኛ ትኩሚት ስለሠራንበት ነው። ኚተመሚጣቜሁ ዹአፋር ፓርላማን ባለ ሁለት ቌምበር ለማድሚግ አስባቜኋል። ዚባሕላዊ ሜማግሌዎቜ ዚሚወኚሉበት ሾንጎ ይኖሚዋል። ይሄ ለምን አስፈለገ? ኚጀርባው ያለው ፖለቲካዊ አመክንዮ ምንድነው? ጥሩ! በክልልም በአገርም ደሹጃ እያወዛገበን ያለ ነገር አለ። ወይ ዘመናዊ አልሆንም ወይም በራሳቜን ባሕል ውስጥ ዘመናዊ ፖለቲካን አልፈጠርንም። በመሀል እዚዋለለን ያለን ሕዝቊቜ ነን። ተጭበርብሚናል። አመክንዮው ወደራስ መመለስ ነው። እኛ በምክር ቀት ደሹጃ ሁለቱ ምክር ቀቶቜ (ቌምበርስ) ይኖሩናል። ሊስተኛ ደግሞ አማካሪ ምክር ቀት ይባላል። ዚመጀመርያው ምክር ቀት በሕዝብ በሚመሚጡ እንደራሎዎቜ ዹሚሞላ ነው። ሁለተኛው ኚተለያዩ ባሕላዊ ተቋማት በተለይም ሃይማኖታዊና ባሕላዊ አባቶቜ፣ ነባር ታጋዮቜ ዚሚወኚሉበት ነው። ዹአፋር ሜማግሌዎቜ በማንኛውም ዚፖለቲካ ድርጅት ውስጥ ታግለው ይምጡ፣ ለሕዝባቜን ለአገራቜን ዋጋ ኚፍለዋል፣ ወድቀው ተነስተዋልፀ ብዙ አይተዋል። እነዚህ ሜማግሌዎቜ ወደድንም ጠላንም ዚካበተና ዹደሹጀ ዕውቀት አላ቞ው። ለዚህ ተገቢውን ቊታ መስጠት አለብን። መንግሥት "ፈንክሜን" ሲያደርግ ባሕላዊውንም ዘመናዊውምን አስተዳደር አጣምሮና አስታርቆ መሄድ አለበት ብለን እናምናለን። ሁለቱ ቌምበር ያስፈለገው ለዚህ ነው። በመሀል ዚአማካሪ ምክር ቀት አለ። አማካሪ ምክር ቀቱ ደግሞ በዚትኛውም ዓለም ዹሚገኙ ዹአፋር ተወላጆቜ ዹሆኑ ምሁራንን ያቀፈ ነው ዚሚሆነው። ይህ አማካሪ ምክር ቀት ዚባሕላዊ ሾንጎውንና ዹላይኛውን ዹክልል ምክር ቀት እንደ ድልድይ ያገናኛል። ዹአፋር ሕዝብ በማይናወጜ ብሔራዊ ስሜቱ ይነሳል። መንፈሳዊ መሪው "እንኳን እኛ ግመሎቻቜን ባንዲራውን ያውቋታል" ብለዋል ይባላል። በታሪክም ውስጥ በግዛት አንድነት ጉዳይ ላይ ኚቱርክ፣ ኚግብጜ፣ ኚፖርቹጋል ዚመጡ ወራሪዎቜን በመመኚት ይነሳል። ዹአፋር ሕዝብ ለዚህ ተግባሩ በኢትዮጵያ ታሪክ ተገቢው ቊታ ተሰጥቶታል ብለው ያምናሉ? ወይስ ተገድፏል? ዹአፋር ሕዝብ በኢትዮጵያ ታሪክ በተለይ ሉዓላዊነትና አገራዊ አንድነት ላይ ሰፊ ገድል ዹፈጾመ ሕዝብ ነው። እንደ አገር ያልተዋጋና቞ው፣ እንደ ሕዝብ ብቻ ዚመለስና቞ው ትልልቅ ውጊያዎቜ አሉ። አፋር ብትመጣ ዕውቅ ዚጊርነት አውድማዎቜ አሉ። ዹተቀሹው ዚኢትዮጵያ ሕዝብ ሳይዘምት አፋሮቜ ብቻ ዚመኚቷ቞ው ብዙ ጊርነቶቜ አሉ። አልተጻፉም እንጂ። ዚተለያዩ ወራሪዎቜ ኢትዮጵያን ለማፍሚስ በመጡበት ጊዜ ትላልቅ ውጊያ አፋሮቜ አድርገው ውጊያ በተጀመሚበት መሬት እንዲያልቅ አድርገዋል። በታሪክ ደሹጃ አፋር ተወርቶለታል ወይ ላልኹኝ ዚሚያውቀው ያውቀዋል። ነገር ግን ሌላው እንደሚንቆለጳጰሰው አልተንቆለጳጰሰም። ሕዝቡም ያን ዹሚፈልግ አይደለም። በአገሩ ጉዳይ ኹማንም ምስጋና እንዲ቞ሚው አይፈልግም። በነገርህ ላይ ጣሊያንን ዹወጉ አርበኛ አባቶቜ ዛሬም አፋር አሉ። ሜዳሊያ ያጠለቀላ቞ው ግን ዚለም። ባንዲራ ያለበሳ቞ው ዚለም። ታሪካቜሁን እንጻፍ ያላ቞ው ግን ዚለም። ዚፖለቲካ ታሪክ (Political History)ን ዚሚጜፉ ሰዎቜ አፋር ቢመጡ ቱባ ታሪክ ያገኛሉ። አፋሮቜ ሌላውን "ይሄ ክልልህ አይደለም፣ ውጣ" ሲሉ አይሰማም። በሌላ አካባቢ ይህ ነገር ትልቅ ቀውስ ፈጥሯል። ምንድነው እናንተ ጋር ያለው ነገር? ዹኛ ዚባሕላዊ ፍልስፍና መነሻ አንድነት ነው። አንድ ብለህ ነው ሁለት ዚምትለው። ሁለት ኚአንድ በኋላ ነው ዚሚመጣው። ይቺን አገር አንድ ሆና ስትቆይ ትኚበራለቜ። ደግሞም ተኚብሚን ቆይተናል። በአንድነታቜን ተኚብሚንበታል። ዹተኹፋፈሉ ሕዝቊቜ በቅኝ ግዢ ወድቀው ነው ዚሚገኙት። ዹተኹፋፈሉ ሕዝቊቜ ዚባሪያ ቀንበርን ተሾክመው ዛሬም ድሚስ ኚዚያ ዳፋ አልተላቀቁም። ባሕላ቞ውም ማንነታ቞ውን እምነታ቞ውን አጥተዋል። አንድነታቜን ነው ኹዚህ ያዳነን። ማንነታቜን እንዳናጣ ያደሚገን እሱ ነው።አፋር ይህን አሳምሮ ስለሚያውቅ ይመስለኛል። ዚመገፋቱ፣ ዹመገለሉ ነገር እንዳለ ነግሚውኛል። ያም ሆኖ ነው ስለ አገር አንድነት ዹጾና አቋም አለን ዹሚሉኝ? ይሄ እኛን ዚመግፋቱ፣ ዹማግለሉ ነገር አስተዳደራዊ ጉዳይ ነው። ወደፊት ታግለህ ዚምታስቀይራ቞ው ነገሮቜ ና቞ው። በአገርህ ዚሚያደራድሩህ ነገሮቜ አይደሉም። በፌዎራል ደሹጃ አፋር ያለውን ውክልና እንዎት ይገመግሙታል? በፌዎራል ደሹጃ ያለን ውክልና ዜሮ ሊባል ዚሚቜል ነው። አንዲት ሚኒስትር ናት ያለቜው። ኚዚያ ባለፈ ሃያ ዚሚኒስ቎ር ኀጀንሲና ተቋማት ውስጥ በዳይሬክተርነት ደሹጃ እንኳን አፋሮቜ ዚሉም። ለምን ይመስልዎታል? ድሮ ዹተማሹ ዹሰው ኃይል ዚላቜሁም ይሉን ነበር። ካልተማርክ ዚመንግሥት ሥራ አስፈጻሚ ልትሆን አትቜልምፀ ልክ ነበሩ። አሁንስ? አሁን በጀና፣ በምህንድስና፣ በሳይንስ፣ በአስተዳደር ዹአፋር ሕዝብ በዚህ ሰዓት ኹማንም አያንስም። ነገሩ መዋቅራዊ ግፉእነት (Structural marginalization) ነው በአፋር ሕዝብ ላይ ላለፉት 50 ዓመታት ዚተደሚገው። ዹኃይለ ሥላሎ ሕገ መንግሥት "ዘላን ርስት ዹለውም" ይለን ነበር። ደርግም ኚመጣ በኋላ፣ ወያኔም በአፋር ሕዝብ ብዝበዛና ጭፍጹፋ ነው ያካሄዱት። ዹአፋር ሕዝብ በአገሩ አስተዋጜኊ እንዲያደርግ ሥርዓቶቹ ዕድል ሰጥተውት አያውቁም። "ገዢ መደቊቜ ዚተፈጥሮ ሃብቱን እንጂ ዹአፋርን ሕዝብን አይፈልጉትምፀ ጉዳያ቞ው ኟኖም አያውቅም" ትላላቜሁ በማኒፌስቷቜሁ ላይ። ምን ማለታቜሁ ነው? ይሄኮ በተጚባጭ ያዚነው ነው። ዹኖርነው ነው። ሩቅ ሳንሄድ ወያኔ ምንድነው ያደሚገው። ሰፊውን ዹጹው መሬት ሙሉ በሙሉ በሚባል ሁኔታ በእጁ አስገባ። አንድ በል። አፋሮቜን ያኔ ምን ያሠራ቞ው እንደነበር ታውቃለህ? መጥሚቢያ ይዘውፀ ጹው መቅሚጜ (እንደ ብሎኬት ቅርጜ ማውጣት) ነበር ዚሚሠሩት። አፋሮቜ "ዹቀን ጆርናታ" ነበር ዚሚኚፈላ቞ው። በዚያ በሚሃ፣ ቁምጣ ለብሰው ዹጹው ቅርጜ ማውጣት ነበር ሥራ቞ው። ዚመሬት ባለቀትነት መብት ዚላ቞ውምፀ ዚአምራቜነት መብት ዚላ቞ውም። ዚነበራ቞ው ተሳትፎ ዚጉልበት ሠራተኝነት ብቻ ነው። በዚያ በበሚሃ። አፍዎራ ብትሄድ ይህን ታያለህ። እንቀጥልፀ አብአላ ሂድ። ኹፍተኛ ዹወርቅ ክምቜት አለ። ብሔራዊ ባንክ ቅርንጫፍ ኚኚፈተባ቞ው ቊታዎቜ አንዱ እዚያ ነው። ፖታሜ አለ። ኹፍተኛ ምዝበራ ነበር ዚሚደሚገው። አፋር ግን ተጠቃሚ ሆኖ አያውቅም። በራሱ መሬት ላይ እንግዳ ዹሆነ ሕዝብ ቢኖር ዹአፋር ሕዝብ ነው። በተጠቃሚነት ደሹጃ ተገለን ቆይተናል ነው ዹሚሉኝ? ግን'ኮ ያው ሁሉም ክልል ይህንን ነው ዹሚለው ... ምን መሰለህ! እኛ ቅድሚያ ዹምንሰጠው ዚኢትዮጵያ አንድነትና ሉዓላዊነትን ነው። በኢትዮጵያ አንድነት ጉዳይ ላይ አንደራደርምፀ በፍጹም። ይሁንና እንደ አፋር በትልቋ ኢትዮጵያ ውስጥ መኚበርንም፣ መክበርም እንፈልጋለን። ሀብት ማፍራት ማደግ እንፈልጋለን። መልማት እንፈልጋለን። ዹኛ ሎቶቜ ምጥ ሲመጣባ቞ው ሌላ ክልል እንዲሄዱ አንፈልግም። ሌላው "እኔ አውቅልሃለው" እንዲለን አንፈልግም። ራሳቜንን ቜለን መቆም እንፈልጋለን። ኀርታሌ ቱሪስት ዚሚያስደነግጥ ቊታ ነው። አፋር ዚቱሪስት ገነት ሆና ለምንድነው "ቱሪስት አንድ ቀን ዚማያድርባት ኹተማ ዚተባለቜው? ብትመሚጡ በዚህ ሚገድ ምን አስባቜኋል? ዳሎል ዚዓለማቜን ዝቅተኛ ቊታ ነው። ኀርታሌ ዚዓለማቜን ሞቃታማው ቊታ ነው። ሉሲ አዳኣር ላይ ነው ዚተገኘቜው። ኚፌዎራል መንግሥት ጋር በመነጋገር ሉሲ ዚተገኘቜበት ቊታ ላይ ትልቅ ሙዝዹም በመገንባት እዚህ አፋር እንድትመጣና እንድትጎበኝ እንፈልጋለን። ዹአገር ውስጥ ቱሪስቱም ዹውጭ ቱሪስቱም እኛ ጋር መጥቶ እንዲጎበኛት ነው ፍላጎታቜን። ዚደኅንነት ዚም቟ት ዚትራንሰፖርትና ዹሆቮል አገልግሎቶቜን ማዘመን አስበናል። ቱሪስቶቜ ተመቜቷ቞ው ሄደው ስለኛ መልካም ትዝታ቞ውን እንዲያጋሩ ማድሚግ አለብን። ዚአርብቶ አደር ዚግጊሜ መሬት ባለቀትነቱ እንዲሚጋገጥ እንሠራለን ትላላቜሁ። አልተሹጋገጠም እንዎ? አልተሚጋገጠም። ዚግጭቶቜ መነሻም ኹዚህ ዚተነሳ ነው። አሁን ትላልቅ ፋብሪካዎቜ ይኚፈታሉ። ተንዳሆ፣ ዹኹሰም ስኳር ፋብሪካ እርሻ ልማቶቜም አሉ። ማኀበሚሱ በአንድ ቊታ ሚግቶ ዚማይኖር፣ ተንቀሳቃሜ ስለሆነ ብቻ ባዶ መሬት ሲያዩ ተንሰፍስፈው ይወስዱታል። ይሄ መሬት ባለቀት እንዳለው ይሚሳሉ። አርብቶ አደሩ ተንቀሳቃሜ ነው ማለት ዚመሬት ይዞታው አይሚጋገጥለት ማለት አይደለም። ዚአርብቶ አደሩን ጉዳይ እንመለስበታለን። በአፋር ኚተሞቜ ውስጥ ነጋዎዎቜ በሙሰኛ ባለሥልጣናት ፍዳ቞ውን ነው ዚሚበሉት ይባላል። ዹአፋር ሕዝብ ጉዳት ተናግሚናልፀ በክልላቜን ያሉ ዹሌላ ቋንቋ ተናጋሪ ወንድሞቻቜን ጉዳትም መናገር አለብን። በትውልድ አፋር ያልሆኑ ሰዎቜ ዚሚሠሯዋ቞ው ሥራዎቜ አሉ። በብዛት ነጋዎዎቜ ና቞ው። ነጻ ሆነው እንዳይሠሩ ሥርዓት ዚለም። በግብር ያሠቃይዋ቞ዋል። ማንኛውም ዹክልሉ ባለሥልጣን ብር ባስፈለገው ሰዓት ብር አምጣ ይልሃል። ሟፌሩን ነው ዚሚልክብህ። ዹሚገርም ነገር ልንገርህፀ በአፋር ሟፌሮቜ ዕቁብ አላ቞ው። ዕቁብ ዚገቡት በዚሳምንቱ ለደንብና ሥርዓት አስኚባሪዎቜ ለመስጠት ነው። ዚሚያሳዝን ነው። በብዛት አፋር ተወልደው አፋር ያደጉ ነጋዎዎቜን ነው ዚሚያሰቃዩት። ዚመለወጥ መብታ቞ውን ነው ዚነፈጉት። ወንድሞቻቜን እዛ መኖራ቞ው አልቀሚ፣ ለፍቶ ማደራ቞ው አልቀሚ፣ በዚያ በሹሃ ላባ቞ውን ጠብ አድርገው መኖራ቞ው አልቀሚ። አንድ ባለሥልጣን መጥቶ ሀብትህን ይቀማዋል። ዚዜጎቜን እኩል ተጠቃሚነት ዚሚጻሚር ነው። ዱብቲን ብታያት ዚምትገርም ኹተማ ናት። ትልቅ ዚገበያ ቊታ ናት። ኹፍተኛ ዚገንዘብ ልውውጥ ያለባት ኹተማ ናት። አንድ ደህና ቀት ዚለም። ገብተህ ምግብ በልተህ ሹክተህ አትወጣም። እንዳሉ ዚቆርቆሮ ቀቶቜ ና቞ው። ዹጩር ካምፕ ነው ዚሚመስሉት። እዛ ውስጥ እዚሠሩ ያሉት ለምንድን ነው ዘመናዊ ሱቅ ዚማይኚፍቱት ስትል ያለተተመነና መጠኑ ዚማይታወቅ ግብር ይዘውብን ይመጣሉ ይሉሃል። ይሄ ያሳፍራል። ባለሥልጣኖቹ ሟፌራ቞ውን እዚላኩ ነጋዮን "ብር ላክ" እያሉ ማሰቃዚት ማቆም ይኖርባ቞ዋል። በክልላቜሁ ኚለውጡ በኋላ ለውጥ አለ? እውነት ለመናገር በክልል ደሹጃ ያለው አመራር በጣም ዹሚደነቅ ነው። ትልቅ አክብሮትም አለንፀ ለሰዎቹ። በደፈናው መጹፍለቅ አካሄዳቜን አይደለም። ዹክልሉ ፕሬዝዳንትም ሌሎቹም ኚፓርቲያቜን ጋር መልካም ግንኙነት ነው ያላ቞ው። በብዙ ነገሮቜ ላይ አብሮ መሥራቱ አለ። ሌሎቜ ክልሎቜ ጋር ባልተለመደ ሁኔታ አብሮ ዚመሥራቱ ነገር እኛ ጋር አለ። ነገሩ ዹሚበላሾው ወደታቜ ሲወርድ ነው። ለጠቅላይ ሚኒስትሩም ይህንኑ ነግርያ቞ዋለሁ። ኚአዲስ አበባ ወጥተህ ክልል ስትሄድና ወደታቜ ስትወርድ ዚብልጜግና ለውጥ እዚጠፋ ይሄዳል። ዚታቜኛው መዋቅር ለውጡን አያውቀውም ብያ቞ዋለሁ። ለምሳሌ ዕጩዎቻቜንን ኚሥራ ያባርሩብናል። አንዳንድ ቊታዎቜ ላይ ዘመቻ ስናደርግ ሕዝቡ ግልብጥ ብሎ ሲወጣ ወሚዳ ላይ ያሉ ካድሬዎቜ ይደነግጣሉ። በኛ ክልል እንዲህ ዓይነት ቅስቀሳ ኖሮ አያውቅም። ያስደነግጣ቞ዋል። በቃ እነዚህ ሰዎቜ ሊያጠፉን ነው ብለው ስለሚሰጉ ወኚባ ይፈጥሩብናል። አንዳንድ ቊታ ደግሞ አዳራሜ መጥተው መክፈቻ ንግግር አድርገው አይዟቜሁ፣ አገራቜሁ ነው ብለው አበሚታተውን ዚሚሄዱ ካድሬዎቜ አሉን። "ይህን ትግል እናንተ ናቜሁ ያመጣቜሁት። በምርጫና በምርጫ ብቻ እንሞናነፋለንፀ አብሜሩ" ብለው ዚሚያሰናብቱንም አሉ። ነገሮቜ ዚማይስተካኚሉ ኹሆነ ኚምርጫው እንዳንወጣ ስጋት አለን። አርብቶ አደር ዹምንወክል ፓርቲ ነን ትላላቜሁ። አርብቶ አደሩ ማኅበራዊ ፍትሕን ይናፍቃል። ዚአርብቶ አደሩን አጀንዳ ብሔራዊ አጀንዳ ዚምታደርጉት እንዎት ነው? በኢትዮጵያ ደሹጃ ዚሚወጡ ማናቾውም ፖሊሲዎቜ አርብቶ አደሩን ማዕኹል ያደሚጉ እንዲሆኑ ታግለናል። ትግላቜን ይቀጥላል። ለምሳሌ ዚምርጫ ሕጉ ሲወጣ ፓርላማ ላይ 6 አንቀጟቜ እንዲስተካኚሉ ያደሚግነው እኛው ነን። ዚምርጫ ሕጉ አንድ ሰው መራጭ ለመሆን ሁለት ዓመት መኖር አለበት ዹሚል ነበር። ይሄ ዚአርብቶ አደሩን ዹአኗኗር ዘይቀ ያላገናዘበ ነው በሚል አንስተን ተስተካክሏል። ሌሎቜም ብዙ አሉ። ዚቀት ቁጥር ዚግድ ነው ይላል መራጭ ለመሆን። ዹኛ ሕዝብ ዚቀት ቁጥር ዚለውም። ተንቀሳቃሜ ነው። ይህን አስተካክለናል። ዚአርብቶ አደር ፖሊስ እንዲቀሚጜ ኹፍተኛ ጫና ያደሚገው ዹአፋር ሕዝብ ፓርቲ ነው። አሁን በሚኒስተሮቜ ምክር ቀት ፖሊሲው ጞድቆ ወደ ትግበራ ሊገባ ደርሷል። እንግዲህ አስበውፀ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዚእንሰሳት ሃብት ደሹጃ በአንደኝነት ተቀምጣ እስኚዛሬ ድሚስ ዚአርብቶ አደር ፖሊሲ ዚሚባል ነገር አልነበራትም። አርብቶ አደሩ ኚሕዝቡ በመቶኛ ምን ያህል ነው? በቁጥር ደሹጃ ኹ12 እስኚ 15 ሚሊዮን ሕዝብ ይሆናል። በመሬት ስፋት ዚአገሪቱን 62 ኚመቶ ይሞፍናል። በውጭ ምንዛሬ ሚገድ ኚቡና ቀጥሎ በ2ኛ ደሹጃ ነው ዚሚጠቀሰውፀ ዚእንሰሳት ተዋጜኊ። ዚእርሻ ጠቅላላ አገራዊ ጥቅል ምርት (GDP) አርብቶ አደሩ 43 በመቶ አስተዋጜኊ ያደርጋል። ይህ ዘርፍ በፖሊሲ ካልተደገፈ እንዎት ነው አገር ወደፊት ዚምትሄደው? እኛ በፖሊሲ ደሹጃ ነው ዚምንታገለው። በእስክሪብቶ ነው ዚምንዋጋውፀ በፌዎራል ደሹጃ ጀምሹናል ለውጡን እናስቀጥላለን። በአፋርና በሶማሌ አዋሳኝ ቊታዎቜ በቅርቡ ግጭት ነበር። አቶ ሙስጠፌና አቶ አወል ተገናኝተው እንፈተዋለን ሲሉ ነበር። በእርግጥ እንፈተዋለን ስላሉ ዚሚፈታ ነው? ዹአፋርና ዚኢሳ ግጭት ድሮም ዹነበሹ ነው። ለምን አልተፈታም? በአጭሩ ልመልስልህ። ዚመንግሥት ክፍተት ነው ዚቜግሩ ምንጭ። ምን ማለቮ መሰለህ? አቶ ሙስጠፌና አቶ አወል ተገናኝተው፣ ኹጠቅላይ ሚኒስትሩም ጋር ተወያይተው ውሎ ሳያድር በነገታው በመቶዎቜ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜ ተፋጅተዋል። ስለዚህ በወሬ ቜግሩ አይፈታም። ትክክለኛ ዚመፍትሄ ፍላጎትና ፍለጋ አልነበሚም። ዚሊስቱ ቀበሌዎቜ ጉዳይ ብዙም ውስብስብ አይደለም። ዹአፋር ክልል አስፈላጊውን ሁሉ ለእነዚህ ቀበሌ ነዋሪዎቜ በማድሚግ ዚሚፈታ ነው። አፋር ክልል ትምህርት ጀና መሰሹተ ልማት ሊያቀርብላ቞ው ግዎታ አለበት። ነዋሪዎቹ ሶማሌዎቜ ናቾው አይደልፀ በሊስቱ አወዛጋቢ ቀበሌዎቜ? እና ሶማሌ ቢሆኑስ መሠሚት ልማት መነፈግ አለባ቞ው? እንደዛ ማለቮ ሳይሆን ጥያቄያ቞ው ዚቊታ ይገባኛል ሳይሆን ዚልማት ነው ወይ ማለቮ ነው? አዎ በአፋር ክልል ዹሚገኙ ልዩ ቀበሌዎቜ ና቞ው። ሶማሌዎቜ ናቾው ዚሚኖሩበት። በዚያ በኩል ደግሞ ይሄን እንወስዳለን ይህን እንመልሳለን ማለት ሳይሆንፀ ሕግና ሥርዓትን መኹተል አለበት። በመንግሥት ደሹጃ ድንበር ማካለል መሠራት አለበት። "ያ ዹኔ ነውፀ ይሄ ዹኔ ነው" መባባል ሳይሆን እንደ ዘመናዊ ሰው ተነጋግሮ መፍታት ያስፈልጋል። ወሰን ማበጀት ያስፈልጋል። ሁለቱ ሕዝቊቜ ኚሚያለያያ቞ው ይልቅ ዚሚያቀራርባ቞ው ነገር ይበዛል። እንዎት ነው ወደ ግጭት ዚሚገቡት? ሁለቱ ሕዝቊቜ ተፈጥሮ ያጎራበተቻ቞ው አንድ ዓይነት ዚጉስቁልና ሕይወት ዚሚመሩ ወንድማማቜ ሕዝቊቜ ና቞ው። በተመሳሳይ ኚኢትዮጵያ ፖለቲካ ገሞሜ ዹተደሹጉ ግፉኣን ና቞ው። በዚህ ቜግር ላይ ነዳጅ ማርኹፍኹፍ አያስፈልግም። እኛ መንግሥት ስንሆን ቅድሚያ ዹምንሰጠው ጉዳይ ይህ ነው። አፋር ዚኢትዮጵያ ጉሮሮ ነው ዚምትባለው። አፋር ሰላም ኹሌለ ዹመሐል አገር ሰው ጋር በነገታው ነው ሕመሙ ዚሚደርሰው። ይህ በቅርቡ በነዳጅም እጥሚትም ታይቷል። ዚክልላቜሁን በአስተማማኝ ሰላም ለማስጠበቅ ዚትኛውን መንገድ ትኚተላላቜሁ? ዚልዩ ኃይል ማደራጀትን ታምኑበታላቜሁ? ልዩ ኃይልን በተመለኹተ አንድ ወጥ አገራዊ አቅጣጫ መቀመጥ አለበት ብለን ነው ዚምናምነው። መደበኛ ፖሊስ አለ፣ ፌዎራል ፖሊስ አለ፣ መኚላኚያ አለ። ወደ ታቜ ስትወርድ ሚሊሻ አለ። እነዚህ በቂ ናቾው ብለን እናምናለን። ዘመናዊ ዓላማ ያለው ዹሰለጠነ ዚፖሊስ ኃይል መገንባት ያስፈልጋል። ምን እያደሚጉ እንደሆኑ ዚሚያውቁ። ለዜጎቜ ኹለላ መስጠት እንጂ ደኅንነት መንሳት ሥራ቞ው እንዳልሆነ ዚሚያወቁ ዚጞጥታ ኃይሎቜ ያስፈልጋሉ። ዚክልሎቜ ዚልዩ ኃይል ፉክክር ያሳስበናል። ኚሁለቱ አንዱ መሆን አለበት። ወይ በአገር ደሹጃ ወደ ተለያዩ ዚጞጥታ መዋቅሮቜ መበተን አለባ቞ው። ወይ ደግሞ ሥርዓት ያለው ፊትና ኋላው ዚሚታወቅ ዹተለዹ ተልእኮ ያለው ኃይል መገንባት አለበት። ምን ማለቮ ነው? ለምሳሌ በፊት ፊናንስ ዚሚባሉ ነበሩ። ኚኮንትሮባንድ ጋር ዚተያያዙ ቁጥጥሮቜን ዚሚኚታተሉ። ዹጾሹ ሜብር ግብሚ ኃይል አለ። ተልዕኮው ተለይቶ ዚተቀመጠለት። እንደዚህ ለተለዹ ተልዕኮ ጞጥታ መዋቅር ሊያስፈልግ ይቜላል እንጂ ልዩ ኃይል መልካም ነገር ይዞ ይመጣል ብለን አናስብም። ይሄ ዚመንግሥት ትልቅ ዚቀት ሥራ ነው ዚሚሆነው። ኚጂቡቲ ጋር በተያያዘ ስለ ጂቡቲ ኹአፋር ዚተሻለ ሊናገር ዚሚቜል ዚለም። ቀተሰብ ሕዝብ ነው። አንድ ዚመጚሚሻ ጥያቄ ላንሳ...። እንደው በሚዥም ዘመን ጂቡቲ ኚኢትዮጵያ ጋር ኅብሚት ፈጥራ ሉአላዊነቷ እንደተጠበቀም ቢኟን ለኢትዮጵያ ነጻ ዚንግድና እንቅስቃሎ ቀጠና ሆና በአንድ አገራዊ ስሜት ኚኢትዮጵያ ጋር ዚምትቀርብ ይመስልዎታል? በቅድሚያ ዚእነርሱን ሉዓላዊነት መንካት አልፈልግም። ኹጠዹቅኹኝ አይቀር አንድ ነገር ልንገርህ። ዚጂቡቲ ጉዳይ ዹኛ ጥንካሬ ላይ ዚሚመሠሚት ጉዳይ ነው፡፡ ጂቡቲና ኢትዮጵያ ፈቅደው አንድ ለመሆን ዚሚ቞ገሩ አገሮቜ አይደሉም። ዚሩቅ ነገርም አይደለም። ይገባኛል! እንዎት ፖለቲኚኛ እንዲህ ይላል ልትለኝ ትቜላለህ። በአጭሩ ላስሚዳህ። ጂቡቲ ላይ ያሉት ኢሳና አፋሮቜ ና቞ው። ዚነሱ ትልቁ ዚቀተሰብ ግንድ ያለው እዚህ አፋር ኢትዮጵያ ነው። ኹዚህ ጂቡቲ ዹሄደ እንጂ ኚጂቡቲ እዚህ ዹሰፈሹ ሕዝብ ዚለም። አፋር እኮ እዚያ አጎትፀ እዚህ አክስት አለው። አባት እዛ ነው ልጅ እዚህ ነው። እናት እዛ ልጂቱ እዚህ። በቃ ምን ልበልህ ቀተሰብ ነው። ኢሳውም በተመሳሳይ ማለቮ ነው። ስለዚህ እኛ ኹጠነኹርን በተለይ አንድ ዚኢኮኖሚ አገር ኚጂቡቲ ጋር ለመፍጠር ዚሩቅ ዕቅድ ኟኖም አይደለም ዚሚታዚን። ለምሳሌ ሱዳንን በቀኒሻንጉል እንጎራበታለን። ወደ አንድ ዚኢኮኖሚ ማኅበሚሰብ ለመምጣት ግን አስ቞ጋሪ ነው። ትልቅ አገር ነው። ብዙ ብሔር ያለበት አገር ነውፀ ሱዳን። ጂቡቲ ግን ኢሳና አፋር ነው። ዹኔ ወንድምና እህቶቜ ና቞ው። ቀተሰብ ነን። ስለዚህ እንደ ቀተሰብ ልንይዛቾው ነው ዚሚገባው። ውሃ ማቅሚብ። ኀሌክትሪክ ማቅሚብ፣ መሠሹተ ልማት ማቅሚብፀ ንግዱን ማሰባጠር ነው። ቀስ በቀስ በምጣኔ ሀብት "ኢንተግሬትድ" መሆን ቀላል ነው። ይህ በተለይም በሶማሌ ክልልና በአፋር ክልል በኩል መሆን ዚሚቜል ነገር ነው። ይህ በኢትዮጵያ መሚጋጋት፣ አንድነትና ጥንካሬ መሳካት ዚሚቜል ነገር ነው። ጂቡቲን ወደ ኢትዮጵያ ማምጣትና አንድ ዚኢኮኖሚ ማኅበሚሰብ መፍጠር ለእኛ ለአፋሮቜ ኚባድ ሥራ አይደለም። በአፋር በኩል መሳለጥ ዚሚቜል ነገር ነው። እኔ አሁንም ቢሆን ዚጂቡቲን ሉአላዊነት ጥያቄ ውስጥ ለማስገባት አይደለም። በመፈቃቀድ ግን አንድ ዚኢኮኖሚ ማኅበሚሰብ መገንባት ዚሩቅ ነገር ተደርጎ መታሰብ ዚለበትም። ጎጠኝነትን እዚተውን ኚመጣን ይህን ተግባራዊ ለማድሚግ ኚባድ አይደለም። ኢስማኀል ኡማር ጊሌ ባለፈው አዋሜ ወንዝን መጠቀማቜንን እናሚጋግጣለን ዹሚል ይዘት ያለው ትዊት አድርገው ነበር። አይተኾዋል? አዎ አይቌዋለሁ። እሳ቞ው ራሱ ዹኛ ስለሆኑ ነው አዋሜን 'ዹኛ ነው' ዚሚሉት ብለን ነው ዚወሰድነው። ለዚያ ነው ያልተገሚምነው። ያልተናደድነው።
48159695
https://www.bbc.com/amharic/48159695
ቩይንግ 737 ተንሞራቶ ወንዝ ውስጥ ገባ
አሜሪካ ቎ክሳስ ውስጥ አንድ ዹቩይንግ አውሮፕላን ካሚፈ በኋላ ተንሞራቶ ወንዝ ውስጥ ገብቷል። አውሮፕላኑ ያሚፈው መብሚቅ ዹቀላቀለ ዝናብ እዚዘነበ ሳለ ነበር።
በቩይንግ 737 ተሳፍሚው ዚነበሩት 143 ሰዎቜ ዹኹፋ ጉዳት አልደሚሰባ቞ውም። ሆኖም ኚተሳፋሪዎቹ መካኚል ወደ 20 ዚሚሆኑት ቀላል ጉዳት ደርሶባ቞ው ወደ ህክምና መስጫ ተወስደዋል። • ቩይንግ ትርፋማነ቎ ቀንሷል አለ በሚያሚ ኀር ኢንተርናሜናል ስር ዚሚተዳደሚው አውሮፕላኑ ጉዞውን ዹጀመሹው ኚኩባ ጓንታናሞ ቀይ ነበር። ተሳፋሪዎቹ እንዳሉት በዝናብ ወቅት ያሚፈው አውሮፕላኑ ሎንት ጆን ዚተባለ ወንዝ ውስጥ ተንሞራቶ ገብቷል። ኚተሳፋሪዎቹ አንዱ ቌሪል ቩርማን ለሲኀንኀን "አውሮፕላኑ መሬቱን ነክቶ ነጠሚ። አብራሪው መቆጣጠር እንዳቃተው ያስታውቅ ነበር" ብለዋል። • ቩይንግ ዹአደጋውን ዚምርመራ ውጀት ተቀበለ ተሳፋሪዋ እንደገለጹትፀ አውሮፕላኑ ዚገባው ወንዝ ውስጥ ይሁን ባህር ውስጥ አላወቁም ነበርፀ "ሁኔታው አስፈሪ ነበር" ብለዋል።
news-48715607
https://www.bbc.com/amharic/news-48715607
"እንዎት ለሎት ልጅ ዚወንዶቜ ክለብ ይሰጣል?' ተብሎ ነበር" ኢንስትራክተር መሠሚት ማኒ
ውልደቷ ድሬዳዋ ነውፀ ልዩ ስሙ አንደኛ መንገድ ኚሚባል ሥፍራፀ ደቻቱ ግድም ማለት ነው። ይህ ሠፈር ደግሞ ለአሾዋው ቅርብ ነው። ኳስ እያንቀሚቀቡ ለማደግ ዹሰጠ ነው።
አንደኛ ደሹጃ ትምህርቷን በለገሃሬፀ ሁለተኛውን ደግሞ በድሬዳዋ አጠቃላይ ትምህርት ቀት ተስተምራለቜ። ፊፋ በ1983 ዹዓለም ዚሎቶቜ እግር ኳስ ዋንጫን በይፋ ኚማካሄዱ በፊት ሎቶቹ በይፋ እግር ኳስ እንዲጫወቱ አይፈቀድም [አይፈለግምም] ነበር። ነገር ግን ይህ ኳስ ኚመጫወት አላገዳትም [በፕሮፌሜናል ደሹጃ ባይሆንም]። ማንም ኚተጫዋቜነት ወደ አሠልጣኝነት ወደ መምጣት ዚኚለኚላት አልነበሚምፀ በኢትዮጵያ [በአፍሪካም] ታሪክ ዚመጀመሪያዋ ሎት ዚወንዶቜ እግር ኳስ ቡድን አሠልጣኝ ኹመሆን ሊመልሳት ዚቻለም አልተገኘም. . . እርሷም ማንም ወደኋላ እንዲጎትታት አልፈቀደቜም. . . መሠሚት ማኒ። • «ዚኔ ትውልድ ታሪክ እንደሚሠራ እምነት አለኝ» ሎዛ አበራ ዚአሠልጣኝነት ሕይወት «አሠልጣኝነትን ዚጀመርኩት ገና በልጅነቮ ነው ። ልጅ እያለሁ ራሱ 'ዚሊደርሺፕ' ተሰጥዖ ነበሚኝ። ኚዚያ ጓደኞቌን ሰብስቀ 'ድል በትግል' ዚሚባል ቡድን መሠሚትኩ። ኚዚያ ዹሕንፃ ቡድንፀ ቀጥሎ ዚመድህን ድርጅት ዹተወሰነ ድጋፍ እያደሚገልኝ ማሠልጠን ጀምርኩ። ኚዚያ ዹ'ሮቭ ዘ ቺልድሚን' ዚሎቶቜ እና ወንዶቜ ቡድንን መሥርቌ ማሠልጠን ያዝኩ።» መሠሚት ዚምታሠለጥነው ዚእግር ኳስ ቡድኖቜን ብቻ አልነበሚም። ዚ቎ኒስ እና መሚብ ኳስ ቡድኖቜንም ታሠለጥን ነበር። 'ማ቎ሪያል' ስለነበር ፍላጎቱ ያላ቞ው ዚድሬዳዋ ልጆቜ እንዲሠለጥኑ አደርግ ነበር። 1970 ዎቹ ላይ እነ ማክዳ፣ ታጠቅ፣ አዹር ኃይል እና መሰል ዚሎት እግር ኳስ ቡድኖቜፀ ዚሎቶቜ እግር ኳስ ሲቋሚጥ በዚያ ኚሰሙ። ኚዚያ 1986 ላይ ዚመጀመሪያውን ዚሎቶቜ እግር ኳስ ቡድን በማቋቋም በታሪክ መዝገብ ስሟን አሰፈሚቜ። 2004 ላይ ዚኢትዮጵያ ሎቶቜ ፕሪሚዬር ሊግ ሲጀመር መሠሚት ዹኹተማዋን ሎቶቜ ቡድን ይዛ ተቀላቀለቜ። መሠሚት ማኒ ታሠለጥነው ዹነበሹው ዚድሬዳዋ ኹነማ መሚብ ኳስ ቡድን [1977] ድሬዳዋ ኹነማ 2007 ላይ ድሬዳዋ ኹነማ ዚፕሪሚዬር ሊጉ ታናሜ በሆነው ዹሊግ ውድድር ላይ ተሳታፊ ነበር። ይሄኔ ነው መሠሚት ማኒ ዚወንዶቹን ቡድን ተሚክባ ለፕሪሚዬር ሊግ ለማሰለፍ ቃል በመግባት ሥራ ዚጀመሚቜው። «እርግጥ በጣም 'ቻሌንጂንግ' ነበር። ቢሆንም ለእኔ ብዙ ያልኚበደኝፀ ኹልጅነቮም ጀምሮ ወንዶቜን እያሠለጠንኩ ማደጌ ነው። ትላልቆቹም ሳሰለጥና቞ው ዚሚሠጡኝ አክብሮትና ፍቅር እንዲሁም ኃላፊነታ቞ውን ዚሚወጡበት መንገድ አቅም ሆኖኝ ነበር። በፆታ መለካ቎ ግን አልቀሚም። 'እንዎት ለሎት ልጅ ዚወንዶቜ ክለብ ይሰጣል? ቀልድ ነው እንዎ ዚያዙት?' ያሉ አልጠፉም ነበር። አንዳንዶቹም እንደውም ይሄ ለፖለቲካ 'ኮንሳምፕሜን' ነው ብለው ኚንቲባው [ዚድሬዳዋ] ድሚስ ይሄዱ ነበር። ነገር ግን ለኔ ዹበለጠ አቅም ነበር ዚሆነኝ። ምክንያቱም ይህንን መቀዹር አለብኝ አልኩኝፀ በምን? በውጀት።» ኹውጭ ብዙ ፈተና ዚገጠማት መሠሚት ኚውስጥም መንገዱ አልጋ 'ባልጋ አልሆነላትም። በዚያ ላይ ዚመጀመሪያው ዙር ለመሠሚት ቀላል ዚሚባል አልነበሚምፀ ሊስት ነጥብ ማግኘት። «ተጚዋ቟ቌን ማሳመን አንዱ ፈተና ነበር። በሎት ሠልጥነው አያውቁምፀ ትልልቅ ተጚዋ቟ቜ ና቞ው። 'እንዎት ነው አሁን እሷ እኛን ዚምትመራን?' ዹሚል ጥያቄ ነበራ቞ው። አንዳንዶቹ ዚመሥራት ፍላጎታ቞ው ውርድ ያለም ነበር። ነገር ግን ልጆቌን በሥራ ማሳመን ቻልኩኝ። በተለይ ሁለተኛው ዙር ላይ በውጀት በጣም አሪፍ ነበርን። እንደውም ኹ12 ጚዋታ 11 አሾንፈን በአንዱ ብቻ ነው አቻ ዚተለያዚነው።» ጉዞ ወደፕሪሚዬር ሊግ ድሬዳዋ ኹነማ በአሠልጣኝ መሠሚት ማኒ እዚተመራ ፕሪሚዬር ሊግ ገባ። ሁሉም 'ሎት ዚወንዶቜ አሠልጣኝ?' ሲል መጠዹቅ ጀመሚ። አድኖቆት ጎሚፈላት። ተጫዋ቟ቜ፣ ኢትዮጵያውያን፣ በተለይ ደግሞ ድሬዎቜ ቆመው አጚበጚቡላት። ፕሪሚዬር ሊግ ኚብሔራዊ ሊግ ሲነፃፀር ኚበድ [በጥራት] ያለ ቢሆንም መሠሚትን ዚሚያቆም ግን አልተገኘም። ክለቧ ትልቁ ዓላማው ዹነበሹው ኚፕሪሚዬር ሊጉ ተመልሶ አለመውሚድ ነበር። መሠሚት ግን አለመውሚድ አላስጚነቃትምፀ ውጀቱ ዹበለጠ እንዲያምር ጣሚቜ። «ስንጀምሚው አራት ጚዋታ ማሾነፍ አልቻልንም ነበር። ኚአምስተኛው ጚዋታ በኋላ ግን ሁሉንም እያስተካኚልን መጣን። እንደውም በአንደኛው ዙር አምስተኛ ሆነን ጚሚስንፀ ይሄ ደግሞ ትልቅ ድል ነው። በተለይ ኚብሔራዊ ሊግ ለመጣ ቡድን ሊያውም በሎት አሠልጣኝ ለሚሠለጥን።» ፍቺ ኚድሬዳዋ ጋር ቢሆንም ሁለተኛው ዙር ዚድሬዳዋ ውጀት ዕለት ተ'ለት ያሜቆለቁል ያዘ። በመጀመሪያዎቹ አምስት ጚዋታዎቜ ጥሩ ውጀታ ማምጣት ዚቻለው ድሬዳዋ ኹነማ ሊስት ነጥብ ብርቁ ሆነ። ምን ተፈጠሹ? «እኔ እስኚዛሬም ድሚስ ሳስበው ግራ ይገባኛል። ምንድን ነው ነገሩ ብዬ ልጆቌን ጠዚቅኩፀ ግን አጥጋቢ ምላሜ አላገኘሁም። አንድ ዹማላውቀው እና ውጀታቜንን እንዲያሜቆለቁል ያደሚገ ነገር እንዳለ አሁንም ድሚስ ይሰማኛል። አሁን ራሱ አንዳድንድ ተጚዋ቟ቜን ሳገኝ እጠይቃለሁፀ ግን ብዙም አይነግሩኝም። ዹሆነ ነገር እንዳለ ግን ይሰማኛልፀ ኹውጭም ኚውስጥም። ወደፊትም መጠዹቄን አላቆምም።» • ሎት እግር ኳሰኞቜ ስንት ይኹፈላቾው ይሆን? ኚዚያ «በዚህ መንገድ መቀጠል አልቻልኩም ትላለቜ» መሠሚት። «ገንዘብ ፈልጌ አይደለም ዚመጣሁት እኔ። እኔ መሥራት ነው ዚምፈልገው። በዚህ መንገድ መቀጠል ደግሞ አልፈልግም። ጫናዎቜ በዝተዋል። እግር ኳስ ደግሞ ነፃነት ይፈልጋል። እኔ በቃኝ '቎ንኪው' ብዬፀ ልጆቌን እና 'ስታፉን' ተሰናብቌ ቡደኑን ለቅቄ ወጣሁ።» ይህ ዹሆነው እንግዲህ 2008 ላይ ነው። መሠሚት 2002 ላይ ሉሲዎቜን ተሚክባ ታሪክ ፅፋለቜፀ ታሪኩ ምንድን ነው? ብሎ ለሚጠይቅ 'ቡድኑ ለመጀመሪያ ጊዜ በሎት አሠልጣኝ ዚተመራበት ወቅት በመሆኑ [ዚተሰጣት ኮንትራት ዹ3 ወራት ብቻ ቢሆንም]' መልሷ ነው። መሠሚት ኚዚያ በኋላ በሰሜን አሜሪካ ዚኢትዮጵያውያን ስፖርት ፌዎሬሜን በቀሚበላት ግብዣ ወደ አሜሪካ አቀናቜ። ለሁለተኛ ጊዜ ደግሞ ኚአሜሪካ ኀምባሲ በቀሚባለት ግብዣ አሜሪካ ደርሳ ተመልሳለቜ። ወደ አሜሪካ ኚማቅናቷ በፊት ሉሲዎቜን እንደገና ተሚክባ ነበር [2009]። ስትመለስ ግን ዚአሠልጣኝነት ቊታው በሌላ ሰው ተይዞ ጠበቃት። እንደገና ሉሲዎቜን ተሚክባ ወደ ኡጋንዳ አቀናቜፀ በሎካፋ ዋንጫ ላይ ለመሳተፍ። ኳስ ይዞ በማጥቃት ዚአጚዋወት ስልት ዚምትታወቀው መሠሚት ውድድሩን ሊስተኛ ሆና በማጠናቀቅ ዚነሃስ ሜዳሊያ ይዛ ተመለሰቜ [ዚራሳቜን ድክመት ነው እንጂ ዋንጫ ማምጣት ይገባን ነበር ትላለቜ]። ቢሆንም ኮንትራቷ ኹመጠናቀቁ በፊት ሉሲዎቜ ሌላ አሠልጣኝ ተሟመላ቞ው። መሠሚት አዲሱን መፅሐፏን ለማስመሚቅ ጉድ ጉድ በማለት ላይ ትገኛለቜ። 'ዚስኬት ተምሳሌት' ዹተሰኘ ርዕስ ሰጥታዋለቜ። ያለፈቜበትን ውጣ ውሚድ ዚሚያትት 198 ገፆቜ ያሉት መፅሐፍ ነው። «ይሄኔ ነው ጀምሬው ዹነበሹውን መፅሐፍ ልጚርስ ብዬ ትኩሚ቎ን ወደዚያ ያደርግኩት» ብላናለቜ። ክፍያ መሠሚት ድሬዳዋ ኹነማ እያለሜ ምን ያህል ነበር ዚሚኚፈልሜ? እንደው ፈቃደኛ ኚሆንሜ ብትነግሪን? «ኧሚ በደንብ ነው ምነግርህ [ፈገግታ]. . . እንግዲህ እኔ ፕሪሚዬር ሊግ እያለሁ 14 ክለቊቜ ነበሩ። በወቅቱ ዝቅተኛው ዚአሠልጣኝ ክፍያ ዹኔ ነበር። ተቆራርጊ እጄ ላይ 'ሚደርሰኝ 13ሺህ 500 ብር ነበር። ያኔ ዚወሚዱት ዳሞንና ዚሆሳዕና ቡድን አሠልጣኞቜ ኹኔ ዚተሻለ ክፍያ ያገኙ እንደነበር አውቃለሁ። ምክንያቱም እኔ ብዙ ጊዜ በፆታዬ ነው 'ምለካው። እንጂ ባለኝ አቅም አልነበሚም። ይሄን ሳስብ ያመኛል ግን በቃ ፍቅር ነውፀ ኳሱን እወደዋለሁፀ እሠራዋለሁ። ስፖርታዊ ጚዋነት አሠልጣኞቜ እና ተጚዋ቟ቜ በድህሚ-ጚዋታ መጚባበጥና ማልያ መቀያዚር ዹተለመደ ነው። እርግጥ አሁን አሁን በሰላም ጚዋታን መጚሚስ በራሱ ትልቅ ድል እዚሆነ ቢመጣም። እንደው በመሠሚት እንዎት እንሞነፋለን ያሉ አሠልጣኞቜ እና ተጫዋ቟ቜ እጅ ነስተዋት ያውቁ ይሆን? «ዚነፈጉኝን እንኳ ብዙም አላስታውስምፀ ግን እኔ አንድ ጊዜ በደስታ ውስጥ ሆኜ ሳልጚባበጥ በመቅሹቮ ተኚስሻለሁ። እዚሁ ድሬዳዋ ላይ ነው። ኹሙገር ሲሚንቶ ጋር እዚተጫወትን ነበር። ደርቢ በመሆናቜን ጚዋታው ደመቅ ያለ ነበር። 0-0 ነበርንና ባለቀ ሰዓት አገባንና አሞነፍን። በቃ በጣም ደስተኛ ስለነበርኩ ዹሙገር አሠልጣኝን ሳልጚብጠው ቀሚሁ። ኚዚያ እስኚ ክስ ደሹጃ ደርሶ ነበር።» እንዎት ይሚሣል? ሰዎቜ አሠልጣኝ መሠሚትን ሲያስቡ ቀድሞ ትዝ ዹሚለቾው ኚድሬዳዋ ኹነማ ጋር ዚተጎናፀፈቜው ስኬት ነው። እርሷም ኚማትሚሳ቞ው ድሎቜ መካኚል አንዱ እርሱ ነው። ግን ኚዚያም በላይ ዚማልሚሳው ትላለቜ መሠሚት. . . «ዚማልሚሳ቞ው ሁለት ቀናት አሉ። አንደኛው ኚአዲስ አበባ ኹነማ ጋር አራት ውስጥ ለመግባት ዚተጫወትነው ነው። 1 ለ 0 እዚመራን ነበርፀ ኚዚያ አቻ ሆንን። አንድ ጹምሹን መምራት ያዝንፀ ግን መልሶ ተቆጠሚብን። በስመዓብ አሁን በቃ 2 ለ 2 ሆነን ወደ ፍፁም ቅጣት ምት ልንሄድ ነው። ኚምክትሌ ጋር ተነጋገርኩና 'ቀንቹ' በሹኛ 'ፔናሊቲ' ጎበዝ ስለሆነ ብለን አስገባነው። በሚኛቜን ሊስት ጎል አዳነልንና አሞነፍን።» «ሁለተኛው ቅዱስ ጊዮርጊስን ዚሚታንበትን ነው። እንግዲህ ጊዮርጊስ በጣም ትልቅ ቡድን ነው። እኔ ደግሞ ፕሪሚዬር ሊጉ አዲሎ ነው። እና በሜዳዬ ሊያውም በጚዋታ ብልጫ ማሾነፌ ፍፁም አልሚሳውም። በጣም ልዩ ነበር። 2012. . .? መሠሚት አሁን ላይ ዚአዲስ አበባ ሎቶቜ እግር ኳስ ቡድንን በማሠልጠን ላይ ትገኛለቜ። አንደኛ ዲቪዚዮን ላይ እዚተጫወተ ዹሚገኘው አ.አ. ስድስተኛ ደሹጃን ይዞ ዚውድድር ዘመኑን አጠናቋል። መሠሚት ስለወደፊቱ ዕቅዷ እጅጉን እያሰበቜበት እንደሆነ አልደበቀቜንም። «ብዙ ዕቅዶቜ አሉኝ። ዚሕፃናት አካዳሚም አለኝ [120 ሕፃናት ያሉት]። እሱን ኹፍ ማድሚግም ሕልሜ ነው። ዚአሠልጣኝነት ጥያቄዎቜም ይመጣሉ። እውነት ለመናገር ብዙ 'ፍራስትሬት' ዚሚያደርጉ አጋጣሚዎቜ ገጥመውኛል። ሙያውን ለመተው ሁላ አስቀ አውቃለሁፀ ግን ደግሞ ብዙ ሰዎቜ ይህን ውሳኔዬን ሲቃወሙ አያለሁ። በተለይ ያሠለጠንኳ቞ው ልጆቜ 'ኖ መቀጠል አለብሜ' ዹሚል አስተያዚት ይሰጡኛል። ስለዚህ ቁጭ ብዬ ማሰብ አለብኝ ብያለሁ።» ኢንስትራክተር መሠሚት ማኒ ሉሲዎቜን በተደጋጋሚ አሠልጥናለቜ ምክር ለተተኪዎቜ በኢትዮጵያም ሆነ በአህጉሹ አፍሪካ ኚመሠሚት ሌላ ሎት ዚወንዶቜ እግር ኳስ ክለብ አሠልጣኝ እንዳለቜ አልሰማንምፀ አላዚንም። ይህንን ክብር መጎናፀፍ ምን ዓይነት ስሜት ይሰጥ ይሆን? «በጣም ነው ደስ ዚሚለኝ። ሌላ ሎት አለመኖሯ ሳይሆንፀ ስኬታማ መሆን መቻሌ ደስ ያሰኘኛል። ሎት ልጅ ይህንን ማድሚግ እንደምትቜል ደግሞ ማሳዚት መቻሌ እጅግ ያኮራኛል። እንጂ ብ቞ኛ ስለሆንኩኝ አይደለምፀ በቃ ይቻላል ዹሚለውን መንፈስ ማንገስ መቻሌ ነው። ሁሌም ዹምለው ሎቶቜ በፆታ቞ው ሳይሆን በአቅማቾው ቢለኩ ነው።» «አንዲት ሎት አናጢም መሆን ትፈልግ፣ ኢንጅነር ወይም ኀሌክትሪሺያን ለዚያ ሙያ ዹሚሆን ዕውቀት ያስፈልጋታል። ይህ ደግሞ እንዲሁ አይገኝምፀ ልፋት ይጠይቃልፀ ጥሚት ያስፈልጋልፀ ድካም ያስፈልጋልፀ በቀላሉ ዹሚገኝ ነገር ዚለም። እኔ ሎት ስለሆንኩ እንደው እንደ ገፀ-በሚኚት እንዲሰጠኝ አልፈልግም። በራሎ ልክፀ ባለኝ አቅም እንጂ። ዚማይቻል ምንም ነገር ዚለም። ሕልም ይኑሚን።» እኛም ምክር ያፅና ብለናልፀ ለመሠሚትም መልካም ዕድል! • "ዚናንዬ ሕይወት" ዚአይዳ ዕደማርያም ምስል ኚሳቜ መፀሐፍ
news-54018572
https://www.bbc.com/amharic/news-54018572
2012፡ ዚታላቁ ዚኢትዮጵያ ህዳሎ ግድብ ኚጅማሬ እስኚ ውሃ ሙሌት
በ2012 ዓ.ም ኹፍተኛ ትኩሚትን ኚሳቡ ክስተቶቜ መካኚል አንዱ ዹሆነው ዚታላቁ ዚህዳሎ ግድብ ዚመጀመሪያ ምዕራፍ ዹውሃ ሙሌት በአጭር ጊዜ ውስጥ መኹናወኑ በበርካታ ኢትኊጵያውኣን ዘንድ ደስታንና ተስፋን ፈጥሯል።
አስር ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ በግንባታ ላይ ዹቆዹው ውሃ መያዝ መጀመሩ ሱዳንና ግብጜን ቅር አሰኝቷል። ዚግድቡ ግንባታ ተጠናቆ ዹውሃ ሙሌቱ ደሹጃ በደሹጃ ተካሂዶ ኃይል ማመንጚት ሲጀምር በአፍሪካ ግዙፉ ይሆናል። ግብጜ አሁንም ቢሆን ዚአባይን ውሃ በጋራ መጠቀም በሚለው ጉዳይ ላይ ኚኢትዮጵያ ጋር ሙሉ በሙሉ መስማማት ያቃታት ሲሆን ሁሉን አቀፍ ስምምነት መደሹግ አለበት በማለት ስትኚራኚር ቆይታለቜ። በ2003 ዓ.ም ላይ ኢትዮጵያ ዚታላቁ ህዳሎ ግድብን መገንባት ኚጀመሚቜበት ጊዜ አንስቶ በተለይ ግብጜ ተቃውሞዋንና ስጋቷን በተለያዩ መንገዶቜ ስትገልጜ እስኚ ዛሬ ደርሳለቜ። በዚህ ጊዜው ግብጜና ኢትዮጵያ ሱዳንን ጚምሮ ላለፉት አስር ዓመታት ያህል በአባይ ወንዝ ጉዳይ ላይ ኚስምምነት ለመድሚስ ሲደራደሩ ዹነበሹ ቢሆንም እስካሁን ሊስቱንም አገራት ዚሚያስማማ ሁሉን አቀፍ መግባባት ላይ መድሚስ አልተቻለም። ዚታላቁ ዚኢትዮጵያ ህዳሎ ግድብ ወሳኝ ክስተቶቜ ዹጊዜ ሰሌዳ 2003 መጋቢት፡ ዚኢትዮጵያ መንግሥት በአባይ ወንዝ ላይ በቢሊዚኖቜ ዹሚቆጠር ዶላሮቜ በማውጣት ሊገነባው ያሰበውንና በአፍሪካ ትልቁ እንደሚሆን ዚተነገሚለትን ዹውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ይፋ አደሚገ። ሚያዝያ ላይ ዚግድቡ ግንባታ ተጀመሚ። ግንቊት ወር ላይ ግብጜ ሱዳንና ኢትዮጵያ በግድቡ ግንባታ ዙሪያ ዹቮክኒክ ኮሚ቎ አዋቅሹው ጥናት ማካሄድ ጀመሩ። መስኚሚም ላይ ደግሞ ዚኢትዮጵያ መንግሥት ግድቡ ዚግብጜን ዹውሃ ድርሻ ዚሚጎዳ አይደለም አለ። ዚኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር በግብጜ ጉብኝት ለማድሚግ ካይሮ በገቡበት ወቅት ደግሞ ዚግብጜ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግድቡ ሁለቱንም አገራት ሊጠቅም እንደሚቜል ተናገሩ። 2004 ግንቊት፡ ኚሊስቱ አገራት ዚተወጣጣ ዚኮሚ቎ አባላትን ጚምሮ ሌሎቜ አራት ዹውጭ አካላትን ያካተተው ዓለም አቀፍ ዚባለሙያዎቜ ቡድን ዚግድቡን ተጜእኖ ማጥናት ጀመሚ። በጥቅምት 2005 ላይ ቡድኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ግድቡ ዚሚገነባበትን ቊታ ሄዶ ጎበኘ። ኹዚህ በኋላም ስፍራውን አራት ጊዜ ሄደው ጎብኝተዋል። 2005 ግንቊት፡ ኢትዮጵያ ዚአባይን ወንዝ አቅጣጫን ቀዚሚቜ። ሰኔ ላይ ደግሞ ዚባለሙያዎቹ ቡድን ዚመጚሚሻ ሪፖርቱን አቀሚበ። ኢትዮጵያና ግብጜም በሪፖርቱ አተሹጓጎም ላይ መስማማት አልቻሉም። ዚግብጹ ፕሬዝዳንት ሞሀመድ ሙርሲ በግድቡ ዙሪያ ጠንኹር ያሉ ሀሳቊቜን ማራመድ ጀመሩ። በተለያዩ አጋጣሚዎቜም በ቎ሌቪዥን በሚያደርጓ቞ው ንግግሮቜና ውይይቶቜ ላይ ኃይል መጠቀም ዹሚለውን ሀሳብ በተደጋጋሚ ያነሱ ነበር። ግብጜ በተደጋጋሚ ጉዳዩን ወደ ዓለም አቀፍ ፍርድ ቀት እንደምትወስደው ብትናገርም ብዙም ሳይቀይ አገራቱ ዚባለሙያዎቹ ቡድን ያቀሚበውን ሀሳብ ተግባራዊ ለማድሚግ ፖለቲካዊና ቎ክኒካዊ ስምምነት ላይ ለመድሚስ ተስማሙ። በ2006 መስኚሚም ወር ላይ ዚተባበሩት መንግሥታት አጠቃላይ ስብሰባ በኒውዮርክ ሲካሄድ ሁለቱ አገራት ባደሚጉት ዚጎንዮሜ ስብሰባ በታላቁ ህዳሎ ግድብ ዙሪያ ድርድሩን ለማስቀጠል ተስማሙ። በኅዳር እና በታህሳስ ወር ላይ ዚኢትዮጵያ፣ ግብጜና ሱዳን ዹውሃ ሚኒስትሮቜ ካርቱም ላይ ተሰባስበው ዚባለሙያዎቹ ያቀሚቡት ሀሳቊቜን ተግባራዊ ለማድሚግ ውይይት አካሄዱ። ነገር ግን ስብሰባው ያለምንም ስምምነት ተጠናቀቀ። 2006 ጥር፡ ዚኢትዮጵያ፣ ዚግብጜና ሱዳን ዹውሃ ሚኒስትሮቜ ለሊስተኛ ጊዜ በካርቱም ተሰበሰቡ። በስብሰባውም በቀሪ ጉዳዮቜ ላይ መስማማት ስላልቻሉ ኹዚህ በኋላ ስብሰባ ላለማድሚግ ተስማሙ። ዚካቲት ወር ላይ ደግሞ ዚኢትዮጵያና ዚግብጜ ዹውሃ ሚኒስትሮቜ ብቻ በአዲስ አበባ ቢሰበሰቡም ምንም አይነት ስምምነት ላይ መድሚስ ሳይቜሉ ቀርተዋል። መጋቢት ወር ላይ ዚግብጜ ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስ቎ር መስሪያ ቀት በታላቁ ዚሕዳሎ ግድብ ዙሪያ ዚግብጜን አቋም ለዓለማቀፉ ማህበሚሰብ ለማሳወቅና በጎኑ ለማሰለፍ ጠንክሮ እዚሰራ መሆኑን አስታወቀ። ሚያዝያ ወር ላይ ደግሞ ኢትዮጵያ ግብጜ በታላቁ ህዳሎ ግድብ ዙሪያ ዹጀመሹቾውን ዘመቻ እንድታቆምና ወደ ሊስትዮሹ ድርድር እንድትመለስ ጥያቄዋን አቀሚበቜ። ሰኔ ወር ላይ ዚግብጹ ጠቅላይ ሚኒስትርና ዚኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር በኢኳቶሪያል ጊኒ በተካሄደው ዚአፍሪካ ሕብሚት ስብሰባ ላይ በተጓዳኝ ውይይት በማድሚግ ዚሊስትዮሜ ኮሚ቎ው በድጋሚ ሥራውን እንዲጀምር ተስማሙ። በነሐሮ ወር ላይ ደግሞ ዚሊስቱ አገራት ዹውሃ ሚኒስትሮቜ በካርቱም ድርድራ቞ውን በድጋሚ ጀመሩ። በዚያውም በባለሙያዎቹ ቡድን ምክሹ ሀሳብ መሰሚት አገራቱ በገልተኛ ዓለም አቀፍ ድርጅት ዚሚመራና ኚሊስቱ አገራት ዚተወጣጡ አባላት ያሉት ኮሚ቎ ለማቋቋም ተስማሙ። 2007 መስኚሚም ፡ ዚግብጜና ዚሱዳን ውሃ ሚኒስትሮቜ ዚግድቡን ዚግንባታ ሂደት ኹጎበኙ በኋላ ዚሊስትዮሜ ኮሚ቎ው አባላት በአዲስ አበባ ውይይት አደሚጉ። ጥቅምት ወር ላይ ደግሞ ዚግድቡን አጠቃላይ ጥናት ዚሚያካሂድ ገለልተኛ ዓለም አቀፍ አማካሪ ድርጅትን ለመምሚጥ በካይሮ ስብሰባ አደሚጉ። 2007 ጥር፡ ግብጜ ዚግድቡን 74 ቢሊዚን ኪዪቢክ ሜትር ውሃ ዚመያዝ አቅምና ዚግድቡን ኚፍታ አልቀበለውም አለቜ። መጋቢት ላይ ደግሞ ሊስተኛው ዙር ዚሊስትዮሜ ኮሚ቎ ስብሰባ በሱዳኗ መዲና ካርቱም ተካሄደ። በዚያውም ሊስቱ አገራት በመርህ ደሹጃ በሚያስማሟ቞ው ጉዳዮቜ ላይ ተፈራሚሙ። በተመሳሳይ ወርም ዚግብጹ ፕሬዝደንት በኢትዮጵያ ዚሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት በመገኘት ንግግር አደሚጉ። 2007 ሚያዝያ፡ ዚሊስትዮሜ ኮሚ቎ው በአዲስ አበባ በመገናኘት ዚግድቡን አጠቃላይ ጥናት ዚሚያኚናውኑ ሁለት ዚአውሮፓ አማካሪዎቜን መሚጡ። ሐምሌ ወር ላይ ደግሞ ዚኮሚ቎ው አባላት በካይሮ ባደሚጉት ስብሰባ ዚሁለቱ አማካሪዎቜ ዚመጀመሪያ ዙር ምክሹ ሀሳብን ገመገሙ። 2008 ኅዳር፡ ዚሊስትዮሜ ኮሚ቎ው በካይሮ ተሰበሰበ። በዚህ ስብሰባ ላይም ሁለቱ ዚአውሮፓ አማካሪ ቢሮዎቜ መካኚል አለመግባባት መፈጠሩ ተገለጞ። ታህሳስ ወር ደግሞ ኮሚ቎ው ካርቱም ላይ ተሰብስቊ ዚካርቱሙን ስምምነት ተፈራሚመ። በስምምነቱ መሰሚትም ዚግድቡን አጠቃላይ ዚጥናት ሥራ በአንድ ዓመት ውስጥ ለማጠናቀቅና ኚማማመኚሩ እራሱን ባገለለው ድርጅት ፈንታ አዲስ አማካሪ ለመምሚጥ ተግባቡ። 2008 ጥር፡ ዚግብጜ ፕሬዝዳንትና ዚኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አዲስ አበባ ውስጥ በመገናኘት ዚካርቱሙን ስምምነት ለማክበርና ኚመግባባት ላይ ለመድሚስ ተስማሙ። ዚካቲት ወር ላይ ደግሞ ዚሊስትዮሜ ኮሚ቎ው በካርቱም በመሰብሰብ ግድቡ በግብጜና በሱዳን ላይ ስለሚኖሚው ተጜእኖ በፈሚንሳይ አማካሪ ድርጅት በተሰራው ጥናት ላይ በመወያዚት ግምገማ አካሄደ። 2009 መስኚሚም፡ ሊስቱም አገራት በዓለም አቀፉ ዚባለሙያዎቜ ቡድን ዹቀሹበውን ምክሹ ሀሳብ ለማስፈጞም 'ቢአርኀልአይ' ኚተባለው ዚፈሚንሳይ ድርጅት ጋር ስምምነት ተፈራሚሙ። 2009 ዚካቲት፡ ሁለቱ ዚፈሚንሳይ አማካሪ ድርጅቶቜ ዚመጀመሪያ ዙር ሪፖርታ቞ውን በግድቡ ዙሪያ አቀሚቡ። ሪፖርቱን ግብጜ ስትቀበለው ኢትዮጵያና ሱዳን ግን ውድቅ አደሚጉት። ሚያዝያ ወር ላይ ደግሞ ዚግብጜ ፕሬዝዳንትና ኢትዮጵያ ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካይሮ ውስጥ ተገናኙ። በዚያውም ዚግብጹ ፕሬዝዳንት ካርቱም ላይ ዹተፈሹመውን ስምምነት ተግባራዊ በማድሚግ ዚግድቡ ሙሌት ላይ ኚስምምነት መድሚስ እንደሚገባ ገለጹ። 2010 ጥቅምት፡ ዚሊስትዮሜ ኮሚ቎ው ካይሮ ውስጥ በመሰብሰብ በሁለቱ ዚፈሚንሳይ አማካሪ ድርጅቶቜ በቀሹበው ምክሹ ሀሳብ ላይ በተፈጠሩ አለመግባባቶቜ ዙሪያ ምክክር አደሚገ። ሕዳር ወር ላይ ደግሞ በድጋሚ ኮሚ቎ው በካይሮ ቢሰበሰብም ምንም ስምምነት ላይ መድሚስ ሳይቻል ቀሚ። በዚያው ወር ላይ ደግሞ ዚኢትዮጵያ ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስ቎ር ግብጜ ቜግር እዚፈጠሚቜ ነው በማለት ኚሰሰ። 2010 ጥር፡ ዚግብጹ ፕሬዝደንት ድርድሩ ተስፋ ሰጪ ነገር እዚታዚበት አለመሆኑ እንዳሳባ቞ው በመግለጜ ዹዓለም ባንክን በጉዳዩ ለማስገባት ሀሳባ቞ውን አቀሚቡ። ነገር ግን ኢትዮጵያ ዚግብጜን ሀሳብ ሙሉ በሙሉ ውድቅ አደሚገቜው። በዚያው ወር ላይ ኢትዮጵያ፣ ግብጜና ሱዳን ዓመታዊ ዚሊስትዮሜ ስብሰባ ለማካሄድና በአንድ ወር ውስጥ ኚግድቡ ጋር በተያያዘ ዚመሰሚት ልማት ፈንድ በማቋቋም ዚሊስቱንም አገራት ዹውጭ ጉዳይ መስሪያ ቀቶቜን ያካተተ ኮሚ቎ ለማቋቋም ተስማሙ። ሚያዝያ ወር ላይ ደግሞ ዚሊስቱ አገራት ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቜ፣ ዹውሃ ሚኒስትሮቜና ዚደኅንንት ኃላፊዎቜ በካርቱም ተሰበሰቡ። ነገር ግን ስብሰባው ፍሬያማ ስምምነት ላይ መድሚስ ሳይቜል ተበተነ። ግንቊት ወር ላይ ዚኢትዮጵያ፣ ግብጜና ሱዳን ዹውጭ ጉዳይ፣ ዚደህንንትና ዹውሃ ሚኒስትሮቜ በድጋሚ ስብሰባ቞ውን በአዲስ አበባ ላይ አደሚጉ። ግብጜም ስብሰባው ስኬታማ እንደነበሚ ገለጞቜ። ሰኔ ወር ላይ ዚኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ለመጀመሪያ ጊዜ ግብጜን ሲጎበኙ በአባይ ወንዝ ላይ ዚሚገነባው ግድብ ዚግብጜን ዹውሃ ድርሻ እንደማይጎዳ ተናገሩ። 2011 መስኚሚም ፡ ኚግድቡ ሙሌት ጋር በተያያዘ ግብጜ ስምምነቱን አልፈርምም አለቜ። 2011 ጥር፡ በሱዳን እዚተካሄደ በነበሹው ኹፍተኛ ሕዝባዊ ዹተቃውሞ እንቅስቃሎ ምክንያት ዚግድቡ ድርድር መቋሚጡን ግብጜ አስታወቀቜ። ሐምሌ ወር ላይ ዚግብጹ ፕሬዝዳንት እና ዚኢትዮጵያ ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካይሮ ውስጥ ተገናኙ። በዚያውም ዚሊስትዮሜ ድርድሩን ለማስቀጠል ተስማሙ። 2012 መስኚሚም ፡ ዚግብጜ ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስ቎ር ዚድርድሩ መጓተት እንዳላስደሰተው አስታወቀ። ኢትዮጵያ ደግሞ ግብጜ ኚግድቡ አሞላል ጋር በተያያዘ ያቀሚበቜውን ሀሳብ በድጋሚ ውድቅ አደሚገቜው። ግብጜ በበኩሏ ኢትዮጵያ ግድቡን ወደ ሥራ እንዳታስገባ አስጠነቀቀቜ። ጥቅምት ወር ላይ ደግሞ ዋይት ሐውስ ለመጀመሪያ ጊዜ በታላቁ ዚህዳሎ ግድብ ላይ መግለጫ አወጣ። ግብጜም በግድቡ ድርድር ላይ አሜሪካ እጇን እንድታስገባ ጥያቄዋን አቀሚበቜ። ኢትዮጵያ ደግሞ ዚግብጜን ጥሪ ተቃወመቜ። ዚኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ለፓርላማ ባደሚጉት ንግግር ማንኛውም አይነት ኃይል ኢትዮጵያን ግድቡን ኚመገንባት እንደማያስቆማት ተናገሩ። ግብጜ ደግሞ ዹጠቅላይ ሚኒስትሩን ንግግር በመተ቞ት በአሜሪካ ዋሜንግተን ለመነጋገር ዹቀሹበውን ሀሳብ እንደምትቀበለው ተናገሚቜ። ሁለቱ አገራት በሶቺ በተካሄደው ዚሩሲያ አፍሪካ ጉባኀ ላይ በመገናኘት ዚሊስትዮሜ ድርድሩን ለማስቀጠል ተስማሙ። ኅዳር ላይ ደግሞ በአሜሪካ አደራዳሪነት አዲስ ውይይት ተጀመሚ። ዚሊስቱ አገራት ዹውሃ እና ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቜም በበዋሜንግተን ድርድራ቞ውን ካደሚጉ በኋላ በአሜሪካና በዓለም ባንክ ታዛቢነት ሁለተኛ ድርድራ቞ውን በአዲስ አበባ አካሄዱ። ታህሳስ ወር ላይ ዚሊስትዮሜ ኮሚ቎ው በካይሮ፣ ዋሜንግተን እና ካርቱም በአሜሪካና በዓለም ባንክ ታዛቢነት ሊስት ስብሰባዎቜን አካሄደ። ዚኢትዮጵያ ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስ቎ርም ስብሰባው ውጀታማ እንደነበሚና ግብጜም ኚግድቡ ሙሌት ጋር በተያያዘ ያቀሚበቜውን ሀሳብ እንደተወቜው አስታወቀ። ነገር ግን ግብጜ አልተውኩትም በማለት አስተባበለቜ። 2012 ጥር፡ ዚአገራቱ ዹውጭ ጉዳይና ዹውሃ ሚኒስትሮቜ ዋሜንግተን ሁለት ጊዜ ሲገናኙ ዹውሃ ሚኒስትሮቜ ብቻ ደግሞ አዲስ አበባ ውስጥ ደግሞ አንድ ጊዜ ብቻ ተገናኝተዋል። ሕጋዊና ቎ክኒካዊ ጉዳዮቜ ላይ ዚሚሰራው ቡድን ደግሞ ካርቱም ውስጥ ተገናኘ። በዚህ ወቅት ኚተደሚሱ ስምምነቶቜ ዙሪያ ግብጜና ኢትዮጵያ እርስ በርሳ቞ው ዚሚጣሚሱ መግለጫዎቜን አወጡ። ሕጋዊና ቎ክኒካዊ ቡድኑ እንዲሁም ዹውሃና ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ በአሜሪካ ዋሜንግተን በተደጋጋሚ ተወያዩ። ነገር ግን ዚመጚሚሻዎቹን ሁለት ስብሰባዎቜ ኢትዮጵያ አልተካፈለቜም። ግብጜ ደግሞ ኚግድቡ ሙሌት ጋር በተያያዘ በአሜሪካ አሞማጋይነት ዹቀሹበውን ሀሳብ ተቀብላ ስምምነቱን ፈሚመቜ። መጋቢት ወር ላይ ደግሞ ዚኢትዮጵያ መኚላኚያ ኃላፊዎቜ በግድቡ ላይ ዹሚፈጾም ማንኛውም አይነት ጥቃትን ለመመኚት ዝግጁ መሆናቾው አስታወቁ። ዚኢትዮጵያ ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስ቎ርም አሜሪካ በድርድሩ ላይ ወደ አንድ ቡድን ያጋደለ አቋም እንዳሚመደቜ በመግለጜ ቅሬታውን አቀሚበ። ግብጜ በበኩሏ ወደ አሚብ አገራት በመሄድ አቋሟን እንዲሚዱና እንዲደግፏት ዘመቻ አደሚገቜ። ኢትዮጵያም በአሚብ ሊግ ዹቀሹበውን ሀሳብ አልቀበለውም አለቜ። ግንቊት ላይ ደግሞ ዚግድቡን ሙሌት ዹተመለኹተውን በኢትዮጵያ ዹቀሹበውን ሀሳብ ግብጜ አልቀበለውም እንደማትቀበለው አሳወቀቜ። ኢትዮጵያ ደግሞ ዚግድቡን ግንባታ ለማጠናቀቅና ዹውሃ ሙሌት ሥራውን በተገቢው መንገድ ለማኹናወን ዚግብጜን ይሁንታ እንደማትፈል በመግለጜ ለተባበሩት መንግሥታት ዚጞጥታው ምክር ቀት ደብዳቀ ጻፈቜ። ግብጜ ደግሞ ቀደም ብላ ሁለቱ አገራት ስምምነት ላይ ሳይደርሱ ኢትዮጵያ ግድቡን ዚመሙላት ሥራውን እንዳትጀምር ለጞጥታ ጥበቃው ምክር ቀት ደብዳቀ አስገብታ ነበር። ዚተባበሩት መንግሥታት በበኩሉ ሁለቱ አገራት አለመግባባታ቞ውን በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱት ሀሳቡን አቅርቧል። ሰኔ ወር ላይ ሱዳን ለተባበሩት መንግሥታት ዚጞጥታ ጥበቃ ምክር ቀት በጻፈቜው ደብዳቀ ሁለቱ አገራት ውይይት ሳይካሄድ ምንም አይነት ውሳኔ እንዳያስተላልፉ ስትል ጠዚቀቜ። በጉዳዩ ላይ ዹማሾማገል ሥራ ለመስራት ሩሲያ ሀሳብ አቅርባ ነበር። ዚኢትዮጵያ፣ ግብጜና ሱዳን አምስት ተኚታታይ ድርድሮቜን አካሄዱ። ግብጜ ድርድሩ ተስፋ ሰጪ አይደለም ስትል ኢትዮጵያ በበኩሏ ድርድሩ ውጀታማ ዹማይሆነው በግብጜ ምክንያት ነው ስትል ኚሳለቜ። ሰኔ 26 ላይ ደግሞ ዚደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንትና ዚወቅቱ ዚአፍሪካ ሕብሚት ሰብሳቢ ሲሪል ራማፎሳ ኚሊስቱ አገራት መሪዎቜ ጋር በቚዲዮ ኮንፈሚንስ ተገናኘተው ተወያዩ። በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታትም ስምምነት ላይ ለመድሚስ ዚተስማሙ ሲሆንፀ ኢትዮጵያ ግን ዚግድቡ ዚመጀመሪያ ዙር ሙሌት በተኚታይነት በነበሩት ሳምንታት እንደምትጀምር በመግለጜ ዚግድቡን ሥራ ለማኹናወን አገራትን መለመን እንደበቃት አስታወቀቜ። ሐምሌ ላይ ዚግብጜ ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኚታላቁ ዚሕዳሎ ግድብ ጋር በተያያዘ ወታደራዊ አማራጭ እንደማኚተሉ ገለጞ። በአፍሪካ ሕብሚት አስተባባሪነት ሊስቱንም አገራት በማሳተፍ ዚተካሄደውም ድርድር ያለምንም ስምምነት ተጠናቀቀ። ተኚትሎም ዚኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሀን ዚታላቁ ህዳሎ ግድብ ሙሌት መጀመሩን ይፋ ማድሚግ ጀመሩ። ዚአሚብ አገራት ሚዲያዎቜም ዜናውን ተቀባበሉት። ግብጜ በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጣት ዚኢትዮጵያን መንግሥት ጠዚቀቜ። ኚጥቂት ሰዓታት በኋላ መሹጃውን ቀድሞ ይፋ ያደሚገው ዚአገሪቱ ዚ቎ሌቪዥን ጣቢያ ዜናውን ኚገጹ ላይ አነሳ። ሱዳን በበኩሏ ዚሙሌት ስራው ተጀመሹ ኚተባለ በኋላ ዹ90 ኪዩቢክ ሜትር ቅናሜ ማዚቷን አስታወቀቜ።
news-52604645
https://www.bbc.com/amharic/news-52604645
"በፋና ኚትግራይ ዚሚወጡ መሚጃዎቜ ተለቅመው እንዲለዩ ይደሹጋል" ዹመቀለ ፋና ኀፍ ኀም ሥራ አስኪያጅ
መቀለ በሚገኘው ዹፋና ኀፍ ኀም ቅርንጫፍ ሬዲዮ ጣቢያ ዚሚሰሩ ጋዜጠኞቜና አመራር አዲስ አበባ ዹሚገኘው ዚድርጅቱ ዋና መሥሪያ ቀት በሥራቜን ላይ ጫና እዚደሚሰብን ነው አሉ።
ዹመቀለ ፋና ኀፍኀም 94.8 ሥራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ መሰሚት ታደሰ "ፋና ሁለት ዓይነት ፋና ሆኗል" ሲል በመቀለው ቅርንጫፍና በአዲስ አበባው ዋና መሥሪያ ቀት መካኚል ስለተፈጠሚው መለያዚት ያስሚዳል። "በመቀለና አዲስ አበባ ያሉ አጀንዳዎቜ ተለያይተዋል። በሁለቱም ዚሚሰራጩ ዜናዎቜና ዝግጅቶቜም ዹማይገናኙ ሆነዋል" ዹሚለው ሥራ አስኚያጁፀ በክልሉ ስላሉ ጉዳዮቜ ሳይሆን ኹመሃል አገር ለሚመጡ አጀንዳዎቜ ዚቅድሚያ ትኩሚትን መስጠት አለባቜሁ በሚል ጫና እንደተደሚገባ቞ው መሆኑን ይገልጻል። ይህንን በመቃወም በተደጋጋሚ ለማስሚዳት ቢሞክሩም ኹዋናው መሥሪያ ቀቱ በኩል ሰሚ እንዳጡና ዚድርጅቱን ኀዲቶሪያል ፖሊሲ በማይጥስ መልኩ ለክልላዊና አገራዊ ጉዳዮቜ ሜፋን መስጠት እንደቀጠሉ ሥራ አስኪያጁ ተናግሯል። "ድርጅቱ ኀዲቶሪያል ፖሊሲፀ እንዲሁም ሌሎቜ ማንዋሎቜና ዚኢትዮጵያ ብሮድካስት አዋጅ እንደሚለው ኹሆነ ሚድያው 60 ኚመቶ ለአገራዊ ጉዳዮቜ ወይም መሚጃዎቜ ሜፋን መስጠት አለበት። ፋና ግን ላለፉት ሁለት ዓመታት አገራዊ አጀንዳዎቜን ወደጎን ትቷል" ሲል ይገልጻል- ጋዜጠኛ መሰሚት። ምክንያቱን ሲያስሚዳም "ተቋሙ በአዲስ አበባና በኹተማዋ ለሚገኘው ዚፌደራል መንግሥትን ዚሚመለኚቱ አጀንዳዎቜ ሜፋን በመስጠት ክልላዊ ጉዳዮቜን ሚስቷልፀ ይህም ዚመንግሥት ቃል-አቀባይ ሆኖ እንደማገልገል እንቆጥሚዋለን" ብሏል። "በደብዳቀ አሳውቀናል. . . " ቜግሩ ማስተካኚያ እንዲደሚግበት ኹዋናው መሥሪያ ቀት አመራሮቜ ጋር እንደተነጋገሩና ኚአመራሩ ዚያገኙት መልስ ግን "ኹዚህ ለሚሰጣቜሁ አጀንዳ ትኩሚት ሰጥታቜሁ መሥራት አለባቜሁ" ዹሚል እንዶነ አስታውሷል። ዚቅርንጫፉ ሥራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ መሰሚት እንደሚለውፀ በዹክልሉ ዚተኚፈቱት ዹፋና ኀፍኀሞቜ በዚአካባቢያ቞ው ላሉ ጉዳዮቜ ሜፋን መስጠት ብቻ ሳይሆን አዲስ አበባ ለሚገኘው ዋናው ማሰራጫም ክልላዊ በዜናም ይሁን በፕሮግራም በመልክ እንዲያቀርቡ በኀዲቶሪያል ፖሊሲውም እንዲሆንም በማንዋሎቹ ሰፍሮ ይገኛል። "ይሁን እንጂ" ይላል ጋዜጠኛ መሰሚት "በመቀለም ይሁን በትግራይ ክልል ዚሚኖሩ ሁነቶቜ በዜናና በፕሮግራም መልክ ስንልክላ቞ው አብዛኞቹ እንዲታገዱ፣ ሌሎቹ በተዛባ መልኩ እንዲቀርቡ፣ አልፎ አልፎም እኛ ዚዘገብነውን ትተው ሌላ ምንጭ ዹመጠቀም ሁኔታ አለ" ሲል ስለሁኔታው ይገልፃል። ይህ ክስተት እዚተደጋገመ በመሄዱም በህዳር ወር 2012 ላይ ወደ ዋናው መሥሪያ ቀት ደብዳቀ በመጻፍ "እኛ ዚምንልካ቞ው መሚጃዎቜ ሲታገዱና በተዛባ መልኩ ሲቀርቡ እዚህ ካሉት አድማጮቻቜን ጋር ስለሚያራርቁን መሻሻል አለበት። 'ይህ መሆን ካልቻለ ግን ኹዚህ ወዲህ ዚምንልክላቜሁ ዘገባ አይኖርም' ዹሚል መልዕክት አስተላልፈናል" በማለት ይናገራል። ይሁን እንጂ በህዳር ወር ላይ ለተጻፈ ደብዳቀ እስኚ ዛሬ ምላሜ እንዳልተሰጣ቞ው ዹሚናገሹው ሥራ አስኪያጁፀ በእነርሱ በኩልም ወደ ዋናው ማሰራጫ ዚተላኩ ዘገባዎቜ እንዳልነበሩ አስታውሷል። ይህ ዋናው መስሪያ ቀትና በቅርንጫፍ ጣቢያው መካኚል ያለው አለመግባባትም ኚሁለት ዓመት በፊት እንደጀመሚ ሥራ አስኪያጁ ይገልጻል። "ዚመንግሥት ለውጥ ኹተደሹገ ወዲህ ፋና በአካባቢያቜን ዹነበሹው ተቀባይነትና ተደማጭነት እዚቀነሰ መጥቷል። በዚህ ሁኔታ ውስጥም ሆነን ግን ለአካባቢያቜን ይመጥናል ዹምንላቾውን ይዘቶቜና አጀንዳዎቜን ማቅሚብ ስንጀምር ጉዳዩ እዚኚሚሚ ሄደ" መሄዱን ጋዜጠኛ መሰሚትአመለክቷል። ጚምሮም ዹመቀለው ቅርንጫፍ ኚአዲስ አበባ ለሚሰራጩ ፕሮግራሞቜ በተመደበው ዹአዹር ጊዜ አንዳቜም መሞራሚፍ ሳያደርግ ሙሉ ሜፋን መስጠቱን አስሚድቷል። እሱ እንደሚለውፀ ይህ በሚሆንበት ጊዜ ግን በዋናው ማሰራጫ ትግራይን ለሚመለኚቱ ዘገባዎቜ ዹሚሰጠው ሜፋን ሙሉ በሙሉ እንዲቆም ሆኗል። ዚታገዱ ይዘቶቜ ምን ምን ናቾው? መቀለ ፋና ኀፍ ኀም ኚአዲስ አበባ ዹሚተላለፉ ፕሮግራሞቜ በሊንክ እዚተቀበለ በመቀለና አካባቢዋ ለሚገኙ አድማጮቜ ዚሚያደርስ ሆኖ በቀን ካለው ዚሥርጭት ሰዓትም ስምንቱን በራሱ ጋዜጠኞቜ ለሚያዘጋጃ቞ው ፕሮግራሞቜ ያውላል። ክልሉን ዚሚመለኚቱ ጉዳዮቜም በነዚህ ሰዓታት ሜፋን ያገኛሉ። አለመግባባቱ ዹተፈጠሹውም በእነዚ ሰዓታት ላይ በሚቀርቡት ክልላዊ ጉዳዮቜ ላይ ቁጥጥር መደሹግ በመጀመሩ እንደሆነ ዚቅርንጫፉ ሥራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ መሰሚት ይናገራል። "እንዳንሰራ቞ው ወይም ሜፋን እንዳንሰጣ቞ው ዹተኹለኹልነው ጉዳዮቜ በርካታ ና቞ው። ኚትግራይ ዚሚወጡ መሚጃዎቜ ተለቅመው እንዲለዩ ይደሚጋል። አብዛኞቹም እንዳይተላለፉ ይደሹጋል" ይላል። በማስኚተልም "ለምሳሌ ዹክልሉ ምክር ቀት ውሳኔዎቜ፣ ዹክልሉ ፓርቲዎቜ በተለይም ዚህወሓት መግለጫዎቜ፣ ዹክልሉ ሥራ አስፈጻሚዎቜ ዹሚሰጧቾው መግለጫዎቜ፣ ዚምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ መግለጫዎቜና ቃለ-መጠይቆቜን በተደጋጋሚ ልኹን እንዳይተላለፉ ታግደዋል" ሲል በዝርዘር ያስቀምጣል። ሌላው ቀርቶ በክልሉ ዚተካሄዱ ታላላቅ ሕዝባዊ ሰልፎቜም በቀጥታና ኚተካሄዱ በኋላ ዹአዹር ሜፋን እንዳይሰጣ቞ው መደሹጉንም ገልጿል። "ሜፋን ዚተሰጣ቞ውም ካሉ በተሞራሚፈና ባልተባለ መልኩ ሲቀርቡ ታዝበናል። እዚያ ያሉ ጋዜጠኞቜም 'ዚፌደራል መንግሥት በሚመለኚት ዚሚሰጡ አስተያዚቶቜ እንዳትልኩልን' ይሉናል" በማለትም ይናገራል። ማስጠንቀቂያው! ጋዜጠኛ መሰሚት እንደሚለው ጉዳዩ እዚጠነኚሚ በመምጣቱ በሚያዝያ 30/2012 ዓ.ም ኹዋና መሥሪያ ቀቱ ዚተጻፈ ማስጠንቀቂያ ደብዳቀ በግንቊት 1/2012 ደርሷ቞ዋል። ደብዳቀው ግን በግልጜ ያሰፈሚው መልዕክት እንደሌለ ይናገራል። "ደብዳቀው ዚሚድያ ተቋሙ 'ኀዲቶሪያል ፖሊሲና መመሪያዎቜን አለማክበርና እንዲኚበሩ አለማድሚግ' ይላል። በዝርዝር ያሰፈሚው ነገር ዚለምፀ ጥቅል ነው። ዚተጣሰው ነገር ምንድነው? ያልተኚበሚውስ? ዚሥራ ዲሲፕሊን ጥሰትም ይላልፀ በማንና መቌ ነው ዚተጣሰው? ዚሚሉት በግልጜ አልሰፈሩም" ብሏል። ደብዳቀው ተፈጜመዋል ዚተባሉት ጥሰቶቜ በአስ቞ኳይ እንዲስተካኚሉ ስለሚጠይቅ መታሚም ያለባ቞ው ነገሮቜ ምን ምን እንደሆኑ በግልጜ ባለመቀመጣ቞ው "ግልጜ ያልሆነ ደብዳቀ" ሲል ገልጟታል። ዚተነሱት ጉዳዮቜ በግልጜና በዝርዝር እንዲቀመጡም ወደ ዋናው መሥሪያ ቀት ደብዳቀ መላካ቞ውንም አስታውሷል። ኀፍቢሲስ ምን ይላል? ደብዳቀው ኹፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አክሲዮን ማህበር ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ በቀለ ሙለታ ቶላ እንደተጻፈ በስም፣ ፊርማና ማህተም መሚዳት ቜለናል። ቢሆንም በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡን በስልክ ጥያቄ ያቀሚብንላ቞ው ዋና ሥራ አስኪያጁ "ጉዳዩን በደንብ ስለማላውቀው መልስ መስጠት አልቜልም" ብለውናል። በማስኚተልም "ጉዳዩም ዚውስጥ ጉዳይ ስለሆነ በውስጥ ነው ዚምንፈታው እንጂ አሁን መናገር አልቜልም" በማለት ለተጚማሪ ጥያቄዎቜ ምላሜ ለመስጠት ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል። ዹመቀለ ፋና ኀፍ ኀም ሥራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ መሰሚት ታደሰ እንደሚለው ኹሆነ "ዚድርጅቱ ስም እዚተበላሞ በመምጣቱ ምክንያት ብዙ ጋዜጠኞቜ ሥራ቞ውን ለቀዋል። ዚተቀሩት ደግሞ እነዚህን ፈተናዎቜ በመቋቋም አሁንም ኀዲቶርያል ፖሊሲውን በመጠበቅና 'ለወራት ስናካሂደው ዹነበሹውን ትግል እናስቀጥላለን' በማለት ሥራ቞ውን እንደቀጠሉ" ገልጿል። "አሁን እዚመጣ ስላለው ቁጣና ማስጠንቀቂያ ቀድሞውንም እናውቀው ነበርፀ ሙያዊ አቅማቜንን በመጠቀምም ትግራይንና ዚትግራይን ሕዝብ እናገለግላለን። ምናልባት ቅጣት ኚመጣም ተዘጋጅተናታል" ብሏል ሥራ አስኪያጁ። በአገሪቱ ኹሚገኙ ጥቂት ግዙፍ ዹመገናኛ ብዙሃን ተቋማት አንዱ ዹሆነው ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በተለያዩ ስፍራዎቜ ካሉት ዚኀፍኀም ጣቢያዎቜ አንዱ ዹሆነው መቀለው ቅርንጫፍ ጣቢያ ኹተኹፈተ 10 ዓመት እንደሆነው ለማወቅ ተቜሏል።
news-49619074
https://www.bbc.com/amharic/news-49619074
ህንዳዊቷ በ73 ዓመታ቞ው መንታ ተገላገሉ
በሕንድ ደቡባዊ ግዛት አንድህራ ፕራደሜ ዹ73 ዓመቷ አዛውንት ዚመንታ ሎት ልጆቜ እናት ሆነዋል። አዛውንቷ ባሳለፍነው ሐሙስ በሐኪሞቜ እገዛ ዚሎትን እንቁላልና ዚወንድ ዘር ፈሳሜ (ስፐርም) በቀተ ሙኚራ በማዋሃድ [IVF treatment] መንትዮቜ ጾንሰው ዐይናቾውን በዐይናቾው ማዚት ቜለዋል።
ዹ73 ዓመቷ ማንጋያማ ያራማቲ • በሕይወት ኚሌለቜ እናት ዚተወለደቜው ሕፃን • መንታ ጠብቃ አምስት ዚተገላገለቜው እናት ዹ73 ዓመቷ ማንጋያማያ ማርቲ እንዳሉትፀ እሳ቞ውና ዹ82 ዓመቱ ባለቀታ቞ው ልጅ መውለድ ቢፈልጉም እስካሁን ድሚስ ሳይሳካላ቞ው ቆይቶ ነበር። ማንጋያማያ ሁለቱን መንታ ሎት ልጆቜ ዚወለዷ቞ው በቀዶ ሕክምና ነው። ሀኪማ቞ው ዚነበሩት ዶ/ር ኡማ ሳንካራምፀ እኝህ እናት ኚነልጆቻ቞ው በጥሩ ጀንነት ላይ እንደሚገኙ አሚጋግጠዋል። ልጆቹ ኚተወለዱ ኚሰዓታት በኋላ ቢቢሲ ያነጋገራ቞ው አባት ሲታራማ ራጃሮ በበኩላ቞ው " በጣም ተደስተናል" ብለዋል። ይሁን እንጂ ይህንን በተናገሩ ማግስት ድንገተኛ ስትሮክ ስላጋጠማ቞ው በሆስፒታል ውስጥ ዹሕክምና ክትትል እያደሚጉ ይገኛሉ። • አደጋው ስፍራ በዹቀኑ እዚሄዱ ዚሚያለቅሱት እናት ማን ናቾው? እድሜያ቞ው በመግፋቱ ምክንያት በባለቀታ቞ውና በእሳ቞ው ላይ አንድ ነገር ቢፈጠር ልጆቹን ማን ሊያሳድጋ቞ው ይቜላል? ተብለው ዚተጠዚቁት ዹ82 ዓመቱ አዛውንት ሮጀርፀ "በእጃቜን ላይ ምንም ነገር ዚለምፀ መሆን ያለበት ይሆናልፀ ሁሉም ነገር በፈጣሪ እጅ ነው ያለው" ሲሉ ምላሜ ሰጥተዋል። በመንደራ቞ው ልጅ ባለመውለዳ቞ው መገለል ይደርስባ቞ው እንደነበር ዚሚናገሩት ጥንዶቹፀ ልጆቜ መውለድ ለነሱ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ያስሚዳሉ። እናት ማንጋያማያፀ "ልጅ አልባዋ ሎት እያሉ ይጠሩኝ ነበር" ሲሉ ይደርስባ቞ው ዹነበሹውን ዚሥነ ልቩና ጫና ያስታውሳሉ። "ብዙ ጊዜ ሞክሚናልፀ በርካታ ዹሕክምና ተቋማትንም ጎብኝተናል" በማለት አሁን ግን በሕይወት ዘመናቾው ደስታን ዚተጎናፀፉበት ጊዜ እንደሆነ ይገልፃሉ። ኚሊስት ዓመታት በፊትም እዚያው ሕንድ ውስጥ በ70ዎቹ ዚዕድሜ ክልል ዹሚገኙ ዳለጂንደር ካዩር ዚተባሉ አዛውንት ወንድ ልጅ መውለዳ቞ው ይታወሳል።
news-49354761
https://www.bbc.com/amharic/news-49354761
"በክልል ደሹጃ ቅሬታ ሲቀርብ ዚመጀመሪያው ነው" ዹምዘናና ዚፈተናዎቜ ኀጀንሲ
ዹሃገር አቀፉ ዹኹፍተኛ ትምህርት መግቢያ ዹ12ኛ ክፍል ፈተና ውጀት ይፋ ኹተደሹገ አንስቶ ዚተለያዩ ቅሬታዎቜ እዚተሰሙ ነው። ቅሬታው ዹጀመሹው በፈተናው ኹፍተኛ ውጀት ያስመዘገቡ ተማሪዎቜ ሳይቀሩ ስኮላስቲክ አፕቲቱዩድ በሚባል ዹፈተና ዓይነት ዝቅተኛ ውጀት በማስመዝገባ቞ው ነው።
ይህንንም ተኚትሎ ዚትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ ዹፈተናው ውጀት ላይ ቅሬታ እንዳለው አስታውቋል። ዚኊሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮም በፈተናው ውጀት ላይ ቅሬታ እንዳለው ለቢቢሲ ገልጿል። ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ ኀጀንሲ በበኩሉ ዚአፕቲቲዩድ ፈተና ውጀትን ዚሚያጣራ ኮሚ቎ ማዋቀሩን ተናግሯል። • ዚትግራይ ክልል ዹ12ኛ ክፍል ፈተና ውጀት ላይ ቅሬታ አቀሹበ • ዚስኮላስቲክ አፕቲቲዩድ ፈተና ውጀትን ዚሚያጣራ ኮሚ቎ ተዋቀሹ ያነጋገርና቞ው በአገር አቀፍ ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ ኀጀንሲ ዚኮሚዩኒኬሜን ዳይሬክተር አቶ ሚዲ ሺፋ ዛሬ እንደገለፁልን "በክልል ደሹጃ ቅሬታዎቜ ሲሰሙ ይህ ዚመጀመሪያው ነው" ብለዋል። አቶ ሚዲ ሺፋ እንደሚሉት ዹፈተና ማሚሚያ ሶፍትዌሩና ዚማሚሚያ ማሜኑ ኚእንግሊዝ አገር ዚመጣ ሲሆን አገልግሎት መስጠት ኹጀመሹም ዓመታት እንደተቆጠሩ ያስሚዳሉ። ይህ ማሜን ሥራ ላይ ኹመዋሉ አስቀድሞ 'ኮብል' ዚሚባል ሶፍትዌር ለፈተና ማሹም አገልግሎት ይውል እንደነበር ያስታውሳሉ። ኀጀንሲው ዹሚዘጋጀው ዹ10ኛ ክፍልን አገር አቀፍ ፈተና እንደሆነ ዚሚገልፁት አቶ ሚዲፀ ዹ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዚዩኒቚርሲቲ መግቢያ ስለሆነ ዹሚዘጋጀው በአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ነው። በአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ዹምርምር ተቋም ውስጥ ባሉ ባለሙያዎቜም ዚእያንዳንዱ ዚትምህርት ዓይነት ፈተና ይዘጋጃል። ይሁን እንጂ ኀጀንሲው ፈተናውን ዚመሚኚብ፣ ዚማሰራጚት፣ ዹማሹም እና ውጀት ዹመግለፅ በአጠቃላይ ዚማስተዳደር ኃላፊነት አለው። እርሳ቞ው እንደገለፁልን ዹ12ኛ ክፍል ዹፈተና ዚመልስ ቁልፍም ዚሚመጣው ኚአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ነው። ለመሆኑ ኹፈተና ዝግጅት እስኚ ውጀት ዹሚኹናወኑ ተግባራት ምንድን ናቾው? 1.ቅድመ ጥንቃቄ ዹፈተና ዝግጅቱ ቅድመ ጥንቃቄና ሚስጢራዊነቱ ዹሚጀምሹው እያንዳንዱ ዚትምህርት ዓይነት ማን እንደሚያዘጋጀው ባለማሳወቅና ሚስጢራዊነቱን በመጠበቅ ነው ይላሉ- አቶ ሚዲ። ፈተናው በሚዘጋጅባ቞ው ጊዜያትም አገልግሎት ላይ ኚሚውሉት ኮምፒዩተሮቜ መሹጃ አፈትልኮ እንዳይወጣ ታስቊ ኔትወርክ አልባ ተደርገው ዹተዘጋጁ ና቞ው። ፈተናው ኹተዘጋጀ በኋላም ዚሚቀመጥባ቞ው ዹፈተና ካዝናዎቜ አሉ። በሕትመት ወቅትም ዚሚታተምበት ተቋም በደህንነት ካሜራ 24 ሰዓት ጥበቃ ይደሚግለታል። በመማተሚያ ቀቱ ሥራውን ዚሚያኚናውኑት ባለሙያዎቜ በሥነ ምግባራ቞ውና በሥራ ብቃታ቞ው ለፈተና ሥራ ብቻ ዚተመሚጡ ና቞ው። እያንዳንዱ እንቅስቃሎ ዹሚደሹገው ኚኀጀንሲው ዚተመሚጡ ባለሙያዎቜና ዚፌደራል ፖሊሶቜ ባሉበት ነው። • ''ውጀቱ ለእኔ ደመወዜ ነው" ኹፍተኛ ውጀት ያስመዘገበው ብሩክ እናት ፈተናው ወደ 'ሚታተምበት ክፍል ምንም ዓይነት ነገር ይዞ መግባት ዚማይፈቀድ ኹመሆኑም በላይ ኹፍተኛ ፍተሻና ቁጥጥር ይደሚጋል። ኹዚህም ባሻገር ፈተና ወደ ተለያዩ አካባቢዎቜ በሚጓጓዝበት ወቅት በምርጫ ቊርድ ቁልፍ ታሜገው ነው። ተሚካቢው አካልም ቃለ ጉባኀ ተፈራርሞፀ ወደ ክልል ሲሄድም በፌደራል ፖሊስ ጥበቃ ተደርጎ ነው። ፈተናው በወጣው መሚሃ ግብር መሰሚት ለተማሪዎቜ እስኚሚሰጥ ድሚስም እንዲቆይ ዹሚደሹገው ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ ነው። 2.ግንዛቀ ማስጚበጫ (Orientation) ኹፈተናው ቀደም ብሎና በፈተናው ወቅት ተማሪዎቜ አስፈላጊ መሚጃዎቜንና ዚመልስ ምርጫ቞ውን በጥንቃቄ እንዲሞሉ ግንዛቀ እንዲኖራ቞ው ማብራሪያ ይሰጣ቞ዋል። ይሁን እንጂ በልጅነት ምክንያት ትኩሚት ባለመስጠትም ሆነ በመደናገጥ ስህተት ሲሰሩ ግን ያጋጥማል። ፈተናው ሲሰጥም ጥብቅ ቁጥጥር ይደሚጋል። 3.ኹዹፈተና ጣቢያው ዚመልስ ወሚቀቶቜን መሰብሰብ በዚህ ሂደት ዹፈተና ወሚቀቶቹ ተሰብስበው በዚትምህርት ዓይነቱ፣ በዹክልሉና ዞኑ ይደራጃሉ። ኚተደራጁ በኋላ ኚእርማት በፊት በወሚቀት (Hard copy) ዚተሰበሰቡት ዚመልስ ወሚቀቶቜ ስካን ተደርገው ወደ ሶፍት ኮፒ (Soft copy) ይለወጣሉ። ኚዚያም በተቋሙ ዳታ ቀዝ (ዹመሹጃ ቋት) ውስጥ እንዲገቡ ይደሚጋል። 4.ቁልፍ ማስተካኚያ (Key correction) ተፈታኞቜ ስም ሲፅፉ ወይም በራሳ቞ው በተማሪዎቹ መሞላት ዚሚገባ቞ው ኮዶቜን ሲፅፉ ዚሚሳሳቱ ካሉ ቁልፍ ማስተካኚያ ይደሚጋል። በዚህ ሂደት ነው ዹፈተና ወሚቀቶቹ ኚአራሚዎቹ እጅ ጋር ዚሚነካኩት። ይህ ስህተት ኹዹመፈተኛ ጣቢያዎቹ ዚሚመጣ ዚተፈታኞቜ ስም ዝርዝር (Master List) ጋር ተመሳክሮ ይስተካኚላል። "እንደዚህ ዓይነት ስህተት ዚሚፈጥሩ ተማሪዎቜ በርካታ ናቾው" ዚሚሉት ዳይሬክተሩ "ዚራሳ቞ው ጉዳይ ብለሜ ብትተያ቞ው ዜጎቜ ናቾው" ሲሉ በዚህ ምክንያት ማስተካኚያ እንደሚደሚግ ገልፀውልናል። ለተቋሙ ጊዜ ዚሚወስድበትም ይህን ዚማስተካኚል ሥራ ነው። መልሱን ለማስተካኚል ግን ዚሶፍት ዌሩም ስሪት አይፈቅድም። ለማስተካኚል ቢታሰብ እንኳን ዚሚቻል አይደለም። 5.ዚእያንዳንዱ ፈተና ዚመልስ ቁልፍ ዚመልስ ቁልፉ ሶፍት ዌሩ ውስጥ ኚገባ በኋላ እያንዳንዱን ፈተና ዹማሹም ሥራ ይጀመራል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ኹሆነ ዹፈተና ማሚሚያ ማሜኑ ፈተናውን ለማሹም ዚሚወስድበት ጊዜ ብዙ አይደለም። ሂደቱ በፍጥነት ነው ዚሚኚናወነው። ይህንን ዹፈተና ማሚሚያ ማሜን ያቀሚበው ድርጅት ማሜኑ ያለዕክል ዚሚጠበቅበትን ተግባር እንዲያኚናውን በዹጊዜው ፍተሻ ያደርግለታል። አገልግሎት ዚማይሰጡና ያሚጁ ማሜኖቜ እዚተወገዱ በአዳዲስ ይተካሉ። በዚወቅቱም በባለሙያዎቜ ክትትል ይደሚግለታል። ስለዚህ "ዚሚያሰጋ ነገር ዹለም" ብለዋል- ዳይሬክተሩ። ቅሬታዎቜ ... በዘንድሮው ሀገር አቀፍ ፈተና ውጀት ዚስኮላስቲክ አፕቲቲዩድ ፈተና በሌሎቜ ዚትምህርት ዓይነቶቜ ኹፍተኛ ውጀት ያስመዘገቡ ተማሪዎቜ ሳይቀሩ በርካታ ተማሪዎቜ ዝቅተኛ ውጀት በማስመዝገባ቞ው ቅሬታዎቜ ቀርበዋል። በዚህ ዚትምህርት ዓይነት ላይ ኹዚህ ቀደም ቅሬታ ቀርቩ እንደማያውቅ ዚሚናገሩት ባለሙያው በ2007 ዓ.ም ግን [ጊዜውን እርግጠኛ አይደሉም] በአስሚኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በታሪክ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ቅሬታ ተነስቶ እንደነበር ያስታውሳሉ። በወቅቱም ቅሬታዎቜ ቀርበው በባለሙያዎቜ ሲፈተሜ ዚመልስ ቁልፉ ወደ ማሚሚያ ማሜኑ ሲገባ ስህተት መፈጠሩ ታውቆፀ ኚዚያ በኋላ ትክክለኛው ዚመልስ ቁልፍ ገብቶ እንዲታሚም መደሹጉንና ውጀቱ በድጋሚ እንደተገለፀ ይናገራሉ። • 28 ዹ10ኛ ክፍል ተማሪዎቜ በፈተና ወቅት ወለዱ ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ ዹሀገር አቀፍ ፈተናዎቜ ሟልኮ መውጣት እንዲሁም ውጀት ላይ ቅሬታ መሰማታ቞ው ዹተለመደ ሆኗል። በዚህም ምክንያት በፈተና ወቅት በመላ ሃገሪቱ ኢንተርኔት እስኚ ማዘጋትም ደርሷል። ፈተና በድጋሚ ዚተሰጠበት አጋጣሚም ዚቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። ይህንኑ ያነሳንላ቞ው ዳይሬክተሩ "ያኔ በአገሪቱ ውስጥ ፖለቲካዊ አለመሚጋጋት ነበርፀ ፈተናው እያንዳንዱ ዚአገሪቱ ጫፍ እስኚሚደርስ ድሚስ ዚተለያዩ ዚፀጥታ ቜግሮቜ ነበሩ" ይላሉ። ነገር ግን በትክክል በወቅቱ ተኚስቶ ዹነበሹው ጉዳይ በሕግ ዚተያዘ ስለሆነ እርሱ ላይ ዝርዝር መሹጃ ኚመስጠት ተቆጥበዋል። ታዲያ አሁን ያለው ሁኔታ እንዲህ ዓይነት ቜግር እንዲፈጠር ዚሚያደርግ አይደለም ነው ዹሚሉን? ስንል ለዳይሬክተሩ ጥያቄያቜንን አስኚተልን። "ኹቀደመው ጋር ሲነፃፀር ሰላማዊ ነው ማለት ይቻላልፀ ይሁን እንጂ ቜግሮቜ ዹሉም ማለት አይደለም" ሲሉ መልሰዋል። በፈተና ውጀት ዙሪያ በክልሎቜ ደሹጃ ቅሬታ ሲቀርብ ይህ ዚመጀመሪያው ሲሆን እንደ ግለሰብ ግን በዚዓመቱ ቅሬታዎቜ እንደሚቀርቡና እንደሚታይላ቞ው ዳይሬክተሩ ገልፀዋል። ቢቢሲ ሚቡዕ እለት ያነጋገራ቞ው ዹሃገር አቀፍ ዚትምህርት ምዘናና ፈተናዎቜ ኀጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ አርዓያ ገ/እግዚአብሄር በበኩላ቞ውፀ በውጀቱ ላይ ለሚነሱ ቅሬታዎቜ በሙሉ አስፈላጊው ማጣራት ኚተካሄደ በኋላ ምላሜ ይሰጠዋል ብለዋል።
news-52586475
https://www.bbc.com/amharic/news-52586475
ያልተነገሚላ቞ው ዹሁለተኛው ዹዓለም ጊርነት ጀግና ሎቶቜ
እስቲ ለአፍታ ዚጊርነት ጀግኖቜን ያስቡ። በጀግንነት ሲፋለሙ ያሰቧ቞ው ወንዶቜ ናቾው ሎቶቜ? በብዙዎቜ አእምሮ ጀብድ ዹፈጾሙ ሎቶቜ አይታወሱም። አርብ ዕለት ዹሁለተኛው ዹዓለም ጊርነት በአውሮፓ ያበቃበት 75ኛ ዓመት ዕለት ነበር። እኛም በሁለተኛው ዓለም ጊርነት ጀብድ ዹፈጾሙ 8 ሎቶቜን ልናስተዋውቃቜሁ ፈቅደናል።
ቌንግ ቀንሁ፡ ሞትን በፈገግታ ዚተቀበለቜው ቌንግ ቀንሁ ቻይናዊ ጀግና ነበሚቜ። ጃፓን እ.አ.አ. 1937 ላይ አገሯን ስትወር ቌንግ ኚሌሎቜ ጋር ሆና ወራሪውን ጠላት ኚአገሯ ለማባሚር ታግላለቜ። ቌንግ በስለት ተወግታ ኹመገደሏ ጥቂት ደቂቃዎቜ በፊት ዚተነሳቜው ፎቶግራፍ ሰዎቜ ያለፍርሃት ዚትጥቅ ትግል እንዲያደርጉ መነሳሳትን ዹፈጠሹ ነበር። ፎቶግራፉን ያነሳው ጃፓናዊ ፎቶግራፍ አንሺ ዚቌንግን ዚመጚሚሻ ሰዓታት መዝግቩ አስቀምጧል። • ዚኮሮናቫይሚስ ተመራማሪው ዶ/ር ቢንግ ሊው ለምን ተገደሉ? በጃፓን ጩር በቁጥጥር ሥር ኚዋለቜ በኋላ ድብደባ ተፈጜሞባታልፀ በበርካቶቜ በተመሳሳይ ጊዜ ተገዳ ተደፍራለቜፀ ለጠላቶቿ ግን አልተንበሚኚኚቜም። ምንም እንኳ ዚቌንግ ሕይወት ቢያልፍም ኚመሞቷ በፊት በተነሳቜው ፎቶ ላይ በፈገግታ ተሞልታ እና እጆቿን ደሚቷ ላይ አጣምራ አይኖቿ ካሜራውን እያዩ ነበር። ቌንግን ለመዘኹሹም በጃፓን ወታደሮቜ ኹ300 ሺህ በላይ ቻይናውያን በተገደሉበት ናንጂንግ ኹተማ 5 ሜትር ዹሚሹዝም ሃውልት ቆሞላታል። ቌንግ በ24 ዓመቷ ነበር እ.አ.አ. በ1938 ዚተገደለቜው። ኖራ ኢናያት ካሃን፡ ሰላይዋ ልዕልት ኖራ ኢናያት ካሃን ዚህንድ ልዕልት እና ዚብሪታኒያ ሰላይ ነበሚቜ። ኖራ በ18ኛው ክፍለ ዘመን ዚሕንዷን ማይሱሩ ኹተማ ሲያስተዳድር ኹነበሹው ቲፑ ሱልታን ዹዘር ግንድ ትመዘዛለቜ። ኚሕንዳዊ ዚእስልምና እምነት አስተማሪ እና ኚአሜሪካዊቷ ተዋናይት ዚተወለደቜው ኖራፀ ትውልድ እና እድገቷ ሩሲያ፣ ሞስኮ እንዲሁም ትምህርቷን ዚተኚታተለቜው ደግሞ ፈሚንሳይ፣ፓሪስ ነው። ዹቋንቋ ቜሎታዋ ዚብሪታኒያ ዚደህንነት ኃላፊዎቜን ቀልብ ገዛ። ኖራ ኚብሪታኒያ ተነስታ በናዚ ጀርመን ቁጥጥር ሥር ወደሚገኘው ፈሚንሳይ በፓራሹት አማካኝነት ገብታ ዹናዚ ጀመርን ወታደሮቜን እንቅስቃሎ በተመለኹተ ለእንግሊዝ መሹጃ አቀብላለቜ፣ አጋር ዚነበሩትን ፈሚንሳይ እና እንግሊዝ መካኚል ግንኙነት እንዲፈጠር ሚድታለቜ። ኖራ አደገኛ ዚሚባለውን ዚሬዲዮ ኊፕሬተርነት ኃላፊነትን በብቃት ተወጥታለቜ። በጠላት ክልል ውስጥ ላለመያዝ በተደጋጋሚ መቀመጫዋን ትቀያይር ነበር። በመጚሚሻ ግን በናዚ ጀርመን ደህንነት ኃይል ተያዘቜ። ኖራ ለእስር በተዳሚገቜበት ወቅት በተደጋጋሚ ኚእስር ለማምለጥ ሙኚራ አድርጋለቜ። • "ስለምንወዳቜሁ ሠርጋቜን ላይ አትምጡ" ዚአዲስ አበባዎቹ ሙሜሮቜ ለማምለጥ በሞኚሚቜ ቁጥር ዚሚደርስባት ስቃይ እና እስር በኹፋ ሁኔታ ይባባስ ነበር። ናዚ ጀርመኖቜ ዚተለያዩ ስልቶቜን በመጠቀም ኖራ መሚጃዎቜን እንድታወጣ በርካታ ጥሚቶቜን ቢያደርጉም ሳይሳካላ቞ው ቀርቷል። ጀርመኖቜ 'ሜድላይን' ኚሚባለው ዚሚስጥር ስሟ ውጪ ሕንዳዊ ስለመሆኗ እንኳ ማወቅ አልቻሉም። እ.አ.አ. መስኚሚም 1944 ላይ ኖራን ጚምሮ ሌሎቜ ሶስት ሎቶቜ፣ ጀርመን ወደሚገኝ ማሰቃያ ካምፕ ኚተወሰዱ ኚቀናት በኋላ ተሚሜነዋል። ኖራ ለጀብዱ ስራዎቿ ዚፈሚንሳይ እና ብሪታኒያ መንግሥታት ሜልማት አበርክተውላታል። እርሷን ዹሚዘክር ሃውልትም በለንደን ኹተማ ቆሟል። ሊዩድሚል ፓቚሊቌንኮ፡ ዚሞት ሎት ሊዩድሚል ፓቚሊቌንኮ ባሪክ እጅግ ውጀታማ ኚነበሩ አልሞ ተኳሟቜ መካኚል አንዷ ነበሚቜ። ናዚ ጀርመን እ.አ.አ. 1941 ዚተባበሩት ሶቬት ህብሚትን በወሚሚበት ወቅት 306 ጠላቶቿን ኚርቀት መትታ ጥላለቜ። ኚእነዚህም መካኚል ቀላል ዚማይባሉት እንደ እርሷ አልሞ ተኳሟቜ ነበሩ። ኹአልሞ ተኳሟቜ ጋር ዚነበራት ግብግብ 'ሌዲ ዮዝ' ዚሞት ሎት፣ ዹሚል ስም አሰጥቷታል። ዹናዚ አልሞ ተኳሟቜ ሊያገኟት አልቻሉምፀ ይሁን እንጂ በሞርታር ጥይት ተመትታ በደሚሰባት ጉዳት አልሞ ተኳሜ ሆና መቀጠል አልቻለቜም። ይህ ግን አገሯ ኚጠላት ጋር ዚምታደርገውን ፍልሚያ ኹማገዝ አልገደባትም። • ኚኮሮናቫይሚስ ለማገገም ምን ያክል ጊዜ ይወስዳል? ዚተለያዩ ተልዕኮቜን በመውሰድ በመላው ዓለም ዚተጓዘቜው ሊዩድሚል በሥራዋ አማካኝነት ኚወቅቱ ፕሬዝደንት ፍራንክሊን ሩዝቬልት ጋር ተገናኝታለቜ። ሊዩድሚል ለጀብድ ሥራዋ ዹወርቅ ኮኚብ ተሾላሚ ብትሆንም ሕይወቷ ካለፈ በኋላ ኚሩሲያ ዚታሪክ መዝገብ ላይ ስሟ እንዲሰሚዝ ተደርጓል። "ዹሁለተኛው ዹዓለም ጊርነት በሶቬት ታሪክ ውስጥ ጀግና ተብለው በታሪክ መዝገብ ላይ ዚሰፈሩት ወንዶቜ ብቻ ና቞ው። ሎቶቜ ዹዛኔ ዚታሪክ አካል አይደሉም" ስትል ዚጟታ እኩልነት ተሟጋቿ ኢራይና ስላቪስካ ለቢቢሲ ተናግራለቜ። ናንሲ ዌክ፡ ነጯ አይጥ ዚተወለደቜው ኒው ዚላንድ ያደገቜው ደግሞ አውስትራሊያ ነው። ናንሲ አደገኛ ተዋጊ እና አማላይ፣ ጠጪ እና ለጠላቷ ናዚ ዚራስ ምታት ነበሚቜ። ናንሲ ገና ዹ16 ዓመት ታዳጊ ሳለቜ ኚትውልድ አገሯ በመጥፋት ወደ ፈሚንሳይ አቀናቜ። በዚያም ዚጥንታዊ ግብጜ ቋንቋ እቜላለሁ ብላ በመዋሞት በአንድ ዚፈሚንሳይ ጋዜጣ ላይ ጋዜጠኛ ሆና ተቀጠሚቜ። ኚአንድ ፈሚንሳይ ዜጋ ጋር በፍቅር ዚወደቀቜው ናንሲ በፍቅር ተጣምራ ትዳር ለመመስሚት ብዙ ጊዜ አልወሰደባትም። በማርሮ ኹተማ ሳለቜ ጀርመኖቜ ፈሚንሳይን እ.አ.አ. 1939 ላይ ወሚሩ። ናንሲ ዚፈሚንሳይ አርበኞቜን ተቀላቀለቜ። በተለያዚ አጋጣሚ በጀርመን ጩር ተኹበው ዚነበሩ ፈሚንሳውያን ታጋዮቜን እያስመለጠቜ ወደ ስፔን አሜሜታለቜ። • በኮሮናቫይሚስ ኹተቀጠፉ ኢትዮጵያውያን መካኚል ጥቂቶቹ ኚብሪታኒያ በመነሳት በፓራሹት ኚአውሮፕላን እዘዚለለቜ በፈሚንሳይ በርካታ ተልዕኮቜን በድል ተወጥታለቜ። ኚአንድ ዹጀርመን ካምፕ ጠባቂ ጋር በጚበጣ ውጊያ ድል ነስተዋለቜ። እስኚ 500 ኪ.ሜትር ድሚስ ወደ ጠላት ድንበር ዘልቃ በመግባት በማይታመኑ አጫጭር ጊዜያት ውስጥ ዚተለያዩ ተልዕኮቜን በስኬት ተወጥታለቜ። ድምጜ ሳታሰማ ጠላት መንደር ገብታ በመውጣት ክህሎቷ ዚተነሳ "ነጯ አይጥ" ዹሚል ስያሜን በጀርመን ጩር አሰጥቷታል። በ98 ዓመቷ እ.አ.አ. 2011 ኹዚህ ዓለም በሞት ዚተለዚቜው ናንሲፀ ለጀብድ ሥራዋ ዚተለያዩ ሜልማቶቜን ተቀብላለቜ። ጄን ቫያል፡ ዘጋቢ፣ ሰላይ፣ ፖለቲኚኛ ጄን ቫያል ትውልዷ በአፍሪካዊቷ ኮንጎ ሪፐብሊክ ቢሆንም በልጅነቷ ወደ ፈሚንሳይ አቅንታለቜ። ጋዜጠኛ ሆና እዚሰራቜ ሳለቜ ነበር ሁለተኛው ዹዓለም ጊርነት ዚተቀሰቀሰው። መኖሪያዋ ዚነበሚቜው ፓሪስን ጥላ በመሰደድ በደቡባዊ ፈሚንሳይ ተደራጅተው ዚነበሩትን ዚፈሚንሳይ ነጻነት ታጋዮቜን ተቀላቀለቜ። ጄን ዚምትልካ቞ው መልዕክቶቜ በኮድ ዹተቆለፉ ስለነበሩ ጠላት እጅ ሲደርሱ ኚተራ አህዝ እና ዚቃላት ድርዳራ ውጪ ትርጉም ዚሚሰጡ አልነበሩም። ጄን ዹናዚ ወታደሮቜን እንቅስቃሎ እዚሰለለቜ ለአጋር አገሮቜ እና ለነጻነት ታጋዮቹ ትልክ ነበር። እ.አ.አ. 1943 ላይ በጠላቶቿ እጅ ወደቀቜ። ኚዚያም ዹአገር ክህደት ዹሚል ክስ ተመሰሚተባት። በናዚ ጀመርን ኚተያዘቜ በኋላ ወደ ማርሮ ዚሎቶቜ እስር ቀት ተልካ ዚጉልበት ሥራ ስትሰራ ነበር። ኚእስር ቀት አምልጣ ይሆን በምህሚት ተለቃ ግልፅ ባይሆንም ጄን ሁለተኛው ዓለም ጊርነት ህይወቷን አልነጠቃትም። እ.አ.አ. 1947 ላይ ዚፈሚንሳይ ሎኔት አባል ሆና ተመርጣ ነበር። ሄዲ ላማር : ዚሆሊውዷ በውበቷ ገዳይ ትውልደ ኊስትሪያዋ ሄዲይ ላማር በትወና ስራዋ ዝናዋ ዹናኘ መልኹ መልካም ሎት ነበሚቜ። ዚሆሊውዷ እንቁ 6 ባሎቜ ነበሯት። ሄዲ ዚመጀመሪያ ትዳሯ ባይጥማት ኚቬይና ተነስታ ወደ ፓሪስ ኹዛም ወደ ለንደን አቀናቜ። በለንደንም ዝነኛ ዹነበሹውን ዚጥበብ ሰው ሉዊስ ሜይር ጋር ተዋወቀቜ። በሆሊውድ መስራት እንድትቜል ዚሚያስቜላትን ኮንትራትም አስፈሚማት። "ዚዓለማቜን ውቧ ሎት" በማለት ያስተዋውቃት ጀመር። ዚተሳተፈቜባ቞ው 30 ፊልሞቜ ዝነኛ አድርጓታል። ዹሁለተኛው ዹዓለም ጊርነት ጀግና ያስባላት ግን ዹፊልም ስራዎቿ አልነበሩም። ዚፈጠራ ሥራዋ እንጂ። • ዚኮሮናቫይሚስ ክትባትን በማግኘት ህንድ ዹዓለምን ሕዝብ ትታደግ ይሆን? ዚፈጠራ ሥራዋ አሜሪካ፣ ፈሚንሳይ እና ብሪታኒያ ዚጠላቶቻ቞ውን መርኚቊቜ ለማጥቃት ጥቅም ላይ ዚሚያውሏ቞ው ተተኳሟቜ (ቶርፒዶ) ፍሪክዌንሲዎቜ በጠላት እንዳይጠለፉ ዚሚያስቜል ስርዓት ነበር። ቶርፒዶዎቹ ፍሪኩዌንሲያ቞ውን በመቀያዚር በጠላት እንዳይታፈኑ ወይም እንዳይጠለፉ አስቜላለቜ። ምንም እንኳ ለፈጠራ ስራዋ እውቅና ባይ቞ራትምፀ ዚፈጠራዋ ግብዓት ዹሆኑ ሃሳቊቜ በብሉቱዝ እና ዋይፋይ ቎ክኖሎጂዎቜ ላይ ተንጞባርቀዋል። ማይ ዪ: በጎራዎ እና መርዝ ዹማይ ዪ ትግል ዹጀመሹው ጃፓኖቜ በሁለተኛው ዓለም ጊርነት ወቅት በርማን ኚመውሚራ቞ው በፊት ነበር። ለአገሯ በርማ ነጻነት ድምጿን ኹፍ አድርጋ ትናገር ነበር። ዚእንግሊዝን ቅኝ ገዢነት ተቃውማለቜ። በሁለተኛው ዹዓለም ጊርነት ወቅትም በእግሯ በጠላት ዚተያዙ ስፍራዎቜን እያቆራሚጠቜ ጎራዎ እና መርዝ በበልቃጥ ይዛ ትጓዝ ነበር። በሕንድ ጃፓኖቜ ምን ያህል በበዛ ጭካኔ ሕዝቡን እያሰቃዩ እንደሆነ ዹሚገልፅ በራሪ ወሚቀቶቜን በርማዎቜ በሚገኙበት ስፍራ ትበትን ነበር። በፓራሹት መውሚድ ስልጠና ዚወሰደቜው ዩ ምንም እንኳ ዚመጀመሪያ ልጇን ኚወለደቜ በኋላ ኚትዳር አጋሯ ጋር ወደ በርማ ለመመለስ ብታቅድም፣ ዚመጣላትን እድል ለሌላ ተዋጊ አሳልፋ በመስጠት ጊርነቱ ካለቀ በኋላ እ.አ.አ. በጥቅምት 1945 ተመልሳለቜ። ኹሁለተኛው ዹዓለም ጊርነት በኋላ ቢሆን ለነፃነት እና ኚዚያም በኋላ ወታደራዊ መንግሥትን ታግላለቜ። ራሱና ሰይድ፡ ሎቷ አንበሳ ኢንዶኔዢያዊቷ ራሱና ሰይድ በዚህ ዝርዝር ውስጥ ካሉት ጀግኖቜ ለዚት ያለቜ ነበሚቜ። በኢንዶኔዢያ ዚነጻነት ትግል ውስጥ ትልቅ ቊታ እንደነበራት ይነገርላታል። ለእሷ ዋነኛ ጠላቷ ወራሪው ዹጃፓን ኃይል ሳይሆን ዚደቜ ቀኝ ገዢዎቜ ነበሩ። ገና በወጣትነቷ ነበር ወደ ፖለቲካ በመግባት ዚራሷን ፓርቲ ዚመሰሚተቜው። ፓርቲውም ዚኢንዶኔዢያ ሙስሊም ማህበር ዚሚባል ሲሆን ኃይማኖትና ህብሚ ብሄራዊነትን ዚሚሰብክ ነበር። • አቅመ ደካሞቜን እያማለለ ዹሚገኘው ዚማፊያዎቜ ገንዘብ በአንድ ወቅት ዹቅኝ ገዢው ዚደቜ ባለስልጣናትና ወታደራዊ ኃላፊዎቜን ዹሚወርፍ ንግግር በማድሚጓ ደግሞ ብዙዎቜ አይሚሷትም። በዚህም ሎቷ አንበሳ ዹሚል ስያሜ ማግኘት ትቜላለቜ። ይህንን ንግግር ባደሚገቜበት ወቅት ወዲያው በቁጥጥር ስር ዚዋለቜ ሲሆን ለ 14 ወራትም ታስራ ነበር። ጃፓኖቜ በጊርነቱ ተሾንፈው ኚኢንዶኔዢያ ኚወጡ በኋላም አገሪቱ ነጻነቷን ማግኘት አልቻለቜም። ዚደቜ ቅን ገዢዎቜ ተመልሰው መጥተው ነበር። በዚህም ምክንያት ለአራት ዓመታት ዹዘለቅና ብዙ ደም ያፈሰሰ ጊርነት ተደርጓል። ታዲያ ራሱና ሰይድ በዚህ ጊርነት ላይ ቁልፍ ሚና እንደነበራት ይነገራል። በዋና ኹተማዋ ጃካርታም አንድ መንገድ በእሷ ስም ተሰይሟል።
54769255
https://www.bbc.com/amharic/54769255
ዚአማራ ክልል መንግሥት በድንበር አካባቢ ስላለው ግጭት ምን አለ?
ዚአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ትናንት ምሜት 4፡30 ጀምሮ በአጠቃላይ በሰሜን እዝ ዚመኚላኚያ ሠራዊት ካምፖቜ፣ ዎፖዎቜ፣ እና ዚተለያዩ መሰሹተ ልማት ባሉባ቞ው አካባቢዎቜ ላይ ዚትግራይ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ፣ ዹተቀናጀ ጥቃት ማድሚስ መጀመሩን በዛሬው ዕለት ለአማራ መገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።
ዚትግራይ ክልል ልዩ ኃይል በክልሉ ዹሚገኘው ዚመኚላኚያ ኃይል አዛዊቜ እንዳይንቀሳቀስ ኚማድሚግ ጀምሮ አሁን ደግሞ ወደጥቃት መሞጋገሩን ተናግሚዋል። ሠራዊቱ ያለውን ትጥቅ ወደ መቀማት ሄዶ እንደነበርም አቶ ተመስገን አስታውቀዋል። አቶ ተመስገን አክለውም በአማራ ክልልም ሶሮቃ እና ቅራቅር በሚባሉ አካባቢዎቜ ዚጥቃት ሙኚራ ማድሚጉንና በክልሉ ልዩ ኃይል መመኚቱን ተናግሚዋል። እንደ አቶ ተመስገን ገለጻ ኹሆነ በሌሎቜ ዹክልሉ አካባቢዎቜም ሊገመት ዚሚቜል ጥቃት ያለ ሲሆን፣ ዹክልሉ ልዩ ኃይል አንዳንድ በትግራይ ልዩ ኃይልና ሚኒሻ አባላት ኚበባ ውስጥ ዚነበሩ ዚመኚላኚያ አባላትንም ማዳንና ማውጣት ቜሏል ብለዋል። ልዩ ኃይሉ ኹዚህ በተጚማሪ አንዳንድ ዚኚባድ መሳሪያዎቜንም ኚስፍራው በማውጣት ተመልሰው ለውጊያ እንዲዘጋጁ ማድሚጋ቞ውን ተናግሚዋል። ዚኮማንድ ፖስቱን ኚመኚላኚያ ጋር በመሆን በቅንጅት እዚመሩና እዚሰሩ መሆኑን ዚተናገሩት አቶ ተመስገን "ዚአማራ ሕዝብ ስትራ቎ጂካዊ ጠላቱን እስካላጠፋ ድሚስ በዹጊዜው ዚሞሚሪት ድር ስናፀዳ አንኖርም" ብለዋል። በአገሪቱ ዚተለያዩ አካባቢዎቜ ዚሚኚሰቱ ግጭቶቜ በሕወሓት ዚገንዘብ፣ ዚቁሳቁስ እና ዚሥልጠና ድጋፍ ዚሚደሚግለት ነው በማለትም በአልመዳ ጹርቃጹርቅ ፋብሪካ ውስጥ ዚኀርትራ ወታደርን አይነት ልብሶቜን በመስፋትና ዚትግራይን ልዩ ሀይል በማልበስ ለትግራይ ህዝብ ኀርትራ ወሚሚቜህ በማለት ህዝቡን ሊያደናግር ነው በማለት ገልፀዋል። ለአንዮና ለመጚሚሻ ጊዜ ይህንን ኃይል ሥርዓት ዚማስያዝ ስራ ኚፌደራል መንግሥቱ ጋር በመሆን ዹክልሉ መንግሥት እንደሚሰራም ተናግሚዋል። ሁሉም ዚፀጥታ ኃይል ዹሚሰጠውን ትዕዛዝ ተቀብሎ ዚሚመጣውን ጥቃት ለመኹላኹል ዝግጁ እንዲሆን ተናግሚዋል። ዹተቃዋሚ ፓርቲ አመራር ኹክልሉ መንግሥት እና ኚፌደራል መንግሥቱ ጎን እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል። ኚሰራዊቱ በተለያዩ ምክንያት ወጥተው ዚነበሩ አባላትም ዹክልሉ መንግሥት ጥሪ ማቅሚቡን ተናግሚዋል።
news-55438474
https://www.bbc.com/amharic/news-55438474
"ባለቀ቎ን እና ዘጠኝ ልጆቌን አጠገቀ ገደሏቾው" ኚበኩጂ ነዋሪዎቜ አንዱ
ታኅሣሥ 14 ቀን 2013 ዓ. ም. በቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ መተኹል ዞን፣ ቡለን ወሚዳ፣ በኩጂ ቀበሌ ኚለሊቱ 10፡00 ሰዓት አካባቢ ታጣቂዎቜ ባደሚሱት ጥቃት ኹ100 በላይ ሰዎቜ በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቾው ይፋ ተደርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይም ይህንን ጥቃት "ጭፍጹፋ" መሆኑን ገልጾው "በወገኖቻቜን ላይ በተፈጾመው ኢሰብአዊ ተግባር በእጅጉ አዝኛለሁ" በማለት ሐዘናቾውን ገልጞዋል። ዚቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዚሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ መለሰ በዹነ በጥቃቱ እጃ቞ው አለበት ዚተባሉ ዹክልልና ዚፌደራልም አመራሮቜ በቁጥጥር ስር እንደዋሉፀ 42 ዚታጠቁ ሜፍቶቜ እ እደተደመሰሱፀ ስለትን ጚምሮ ዚተለያዩ ዹጩር መሣሪያ በቁጥጥር ስር እንደዋለ ተናግሚዋል። ባለቀታ቞ውንና 9 ልጆቻ቞ውን ያጡት አርሶ አደር ዹ41 ዓመቱ አርሶ አደር አቶ በላይ ዋቅጅራ ነዋሪነታ቞ው ታጣቂዎቜ በድንገት ጥቃት ፈጜመው ኹ120 በላይ ሰዎቜ በተገደሉባት ዚበኩጂ ቀበሌ ውስጥ ነው። በጥቃቱ በሰዓታት ውስጥ ባለቀታ቞ውና 9 ልጆቻ቞ው ተገድለዋል። አቶ በላይ "ባለቀ቎፣ 5 ሎት ልጆቌ እና 4 ወንድ ልጆቌ ናቾው ዚተገደሉት" ይላሉ በሐዘን በተሰበሹ ድምጜ። ቀተሰቡ በእንቅልፍ ላይ እንዳለ ቀታ቞ው ላይ በተኹፈተው ተኩስ መላው ቀተሰባ቞ውን ያጡት አቶ በላይ ወገባ቞ው ላይ በጥይት ተመትተው አሁን ቡለን ሆስፒታል ውስጥ ይገኛሉ። "ሚቡዕ ሌሊት 12 ሰዓት አካባቢ መጥተው ኚበቡን። ኚዚያም በር ሰብሚው ገቡና ተኩስ ኚፈቱብን። አስሩንም ዚቀተሰቀን አባላት አጠገቀ ነው ዹገደሏቾው" ይላሉ። ለ27 ዓመት በትዳር አብሚው በመኖር አስር ልጆቜ ያፈሩት ዚባለቀታ቞ው ስም ኊብሎ ፉፋ እንደሆነ ዚሚናገሩት አቶ በላይ ጥቃት ፈጻሚዎቹ "ኚገደሏት በኋላ አንገቷ ላይ ዹነበሹውን ወርቅ ወስደው ሄዱ" በማለት ገልጞዋል። አርሶ አደሩ አቶ በላይ ሐዘናቾው ኚባድ ነው። በግፍ ዚተጚፈጚፉትን ዚልጆቻ቞ውን ስም ደጋግመው ይጠራሉ። ቢቢሲ ሲያናግራ቞ውም "ኚትልቋ ጀምሬ ዚልጆቌን ስም ልዘርዝርህ. . . ሹመ቎ በላይ ዚጀመሪያ ሎት ልጄ ናት። ኚዚያ በኋላ ደራርቱ በላይ፣ ቀጥላ ሲዲቄ በላይ፣ ቀጥላ ጞሃይነሜ በላይ . . ." እያሉ ሳግ ቢተናነቃ቞ውም አላቋሚጡም። ኚእንባ቞ው ጋር እታገሉ "ዚወንዶቹ ታላቅ መገርሳ ይባላል። ቀጥሎ አያና በላይ እና ደሹጄ በላይ። ኀሊያስ ዚመጚሚሻው ልጄ ነው" እያሉ እንባ቞ው ገነፈለ። ብቻ቞ውን ዚቀሩት አባት ቆስለው ሆስፒታል ና቞ው። በጭካኔ ዚተገደሉት ባለቀታ቞ውና ልጆቻ቞ውን ማን እንደሚቀብራ቞ው ያሳስባ቞ዋል። "ሰው ሁሉ ኚአካባቢው ሞሜቶ ወጥቷል። ማን ይቅርበራ቞ው? በሞራ ተጠቅልለው ነው ያሉት" ብለዋል። ዚአስር ልጆቜ አባት ዚነበሩት አቶ በላይ አንዲት ልጃቾው ተርፋለቜ "እንደ አጋጣሚ አጎቷ ጋር ወንበራ ኹተማ ሄዳ ነው ዚዳነቜው። ኚቀተሰቡ እሷ ብቻ ናት ዚተሚፈቜው።" ሚቡዕ ጎህ ኚመቅደዱ በፊት ዚተኩስ ድምጜ በአካባቢያ቞ው መስማታ቞ውን ዚሚገልጹት አርሶ አደሩ "ባለቀ቎ን በጥይት ሲመቱ እሷን እኚላኚላለሁ ብዬ ስሄድ እኔንም መቱኝ። ኚዚያ ሮጥኩ። እኔን ፍለጋ ሲመጡ ዝም ብዬ ተኛሁ። ሳያገኙ አለፉ" ይላሉ ኚጥቃቱ እንዎት እንደተሚፉ ሲያስሚዱ። ጥቃት አድራሟቹ ኚሁኔታ቞ው ወታደር እንደሚመስሉና ጥይት በሻንጣ መያዛ቞ውን ዚሚናገሩት አቶ በላይ "በዓይን ዹምናቃቾው ሰዎቜ አሉበት። አንዳንዶቹን መልካ቞ውንም አይተን አናውቅም" ይላሉ። ኚጥቃቱ ለማምለጥ ዚሮጡ ሰዎቜን በጥይት ተኩሰው እንደገደሏ቞ውና ኚጎሚቀታ቞ው ኹሚገኝ አንድ ቀት በርካታ ሰዎቜ መገደላቾውን "ኚጎሚቀ቎ አንድ ጎጃሜ ቀት 13 ሰው ታርዷል" ብለዋል። "ይሄ ይኚሰታል ብለን አልጠበቅንም። መንግሥት አካባቢያቜን 'ሰላም ነው'፣ 'ዚልማትና ዚእድገት ቊታ ነው'፣ 'እናንተን ዚሚነካ ዚለምፀ ሥራቜሁን ሥሩ' ብለው አታለው ጚሚሱን።" በጥቃቱ ኚአቶ በላይ ቀተሰብ በተጚማሪ በርካታ ሰው ተገድሏል። ቀቶቜ ተቃትለዋል። እሳ቞ው እንደሚሉት "መኚላኚያ ገባ እንጂ አንድም ሰው አይርፍም ነበር"። "እኔ አካባቢ 80 አስክሬን ተቆጥሯል። ሜዳ ውስጥ ገና ያልተቆጠሚ አስክሬንም አለ። እንዲህ አይነት ነገር አይተን አናውቅም። እኔ እንኳን ዹጩር መሳሪያ ጩር ዚለኝም። መንግሥት ሰላም ነው እያለ አታለለን። እኛ ምንም ዹምናወቀው ነገር ዹለም" ሲሉ በምሬት ለቢቢሲ ተናግሚዋል። ባለቀታ቞ውንና ዘጠኝ ልጆቻ቞ውን በግፍ ዚተነጠቁት አቶ በላይ ተስፋ ዚቆሚጡ ይመስላሉ። "ኹዚህ በኋላ ሰው እዚያ ይኖራል ብዬ አልገምትም። አንዳንዶቜ ንብሚትም ሰብስበው ወጥተዋል። ሰው ተስፋ ቆርጧል። ኚእንግዲህ ሰው እዚያ ሰፍሮ ዹሚኖር አይመስለኝም።" "መአት ነው ዚወሚደብን" በቀንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ መተኹል ዞን፣ ቡለን ወሚዳ፣ በኩጂ ቀበሌ ዹሚኖሹው ሌላው ዹዓይን እማኝ አቶ ተስፋ [ስሙ ዹተቀዹሹ] ጥቃቱ ያልታሰበ ነው ይላል። "መአት ነው ዚወሚደብን" ያለው ጥቃት ይሆናል ብለው ባልጠሚጠሩት ሰዓት ሊነጋ ሲቃሚብ መፈጾሙን ይገልጻል። ጥቃት ፈጻሚዎቹ ዚእሱንና ዚሌሎቜንም ቀት ኹበው "ዚጥይት በሚዶ አዘነቡብን" በማለት መትሚፋ቞ውን ተአምር ይለዋል። "ነገር ግን ብዙዎቜም ሞተዋል። ኚአንድ ቀተሰብ 12 ሰው ዚተጚፈጚፈበት ሁሉ አለ" ሲል ዹነበሹውን ሁኔታ ይገልጞል። ለሱና ለቀተሰቡ ይህ ጥቃት ዚመጀመሪያው አይደለም። ኚጥቂት ሳምንታት በፊት እናትና አባቱ ለሠርግ በሚጓዙበት ወቅት ድባጀ አካባቢ በተሳፈሩበት ተሜኚርካሪ ላይ በተፈጾመ ጥቃት ሕይወታ቞ውን አጥተዋል። አሁን ደግሞ በኩጂ ላይ በተፈጾመው ጥቃት ሌሎቜ ዘመዶቻ቞ው ተገድለዋል። በሐዘናቾው ላይ ሌላ ሐዘን መጚመሩን ይናገራል። "በዚህ ጥቃት ዘመዶቌንና ጓደኞቌን አጥቻለሁ። ዓይኔ እያዚ አጠገቀ እንኳን ብዙ ናቾው ተመተው ዚሞቱት።" በተኚታታይ በተፈጾሙ ጥቃቶቜ ቀተሰቊቹን ያጣው አቶ ተስፋፀ ለግድያው ምክንያቱ ምን እንደሆነ ምላሜ ያላገኙለት ጉዳይ መሆኑን በማንሳት "አላጠፋን። ምንም አላደሚግን። በምን እንደሆነ እንጃ። እንግዲህ ይሄ ሁሉ ነገር ዚሚደርስብን ምን ባደሚግነው ነው?" ይላል። በሚኖርበት አካባቢ ዚሚኖሩ ሰዎቜን ጚምሮ ዹክልሉን ልዩ ኃይል ዚደንብ ልብስ ዚለበሱ ሰዎቜ ክላሜንኮቭ ጠመንጃ ይዘው ጥቃት ሲያደርሱና ዚሳር ቀቶቜን በውስጡ ካሉ ሰዎቜ ጋር ሲያቃጥሉ እንደነበር ይገልጻል። "ጉልበት ያላ቞ውን በጥይት ሲገድሉፀ ሌሎቹን ደግሞ ሳር ቀት ላይ በለኮሱት እሳት ጹርሰዋቾዋል" በማለት ኚእንዲህ አይነቱ ጥቃት መትሚፋ቞ውን ለቢቢሲ ተናግሯል። አቶ ተስፋፀ በቀበሌው ኚተወሰኑት በስተቀር በአካባቢው ያሉ አብዛኞቹ ዚሳር ቀት በእሳት መውደሙን፣ ጥቃቱም ለሊት 11 ሰዓት ጀምሮ ዚመኚላኚያ ሠራዊት እስኪደርስ መቀጠሉን ይገልጻል። "መኚላኚያ ብዙ ሰው ኹተገደለና ቀቶቜ በእሳት ኹወደሙ በኋላ ነው ዚደሚሰው። እኛን ዚሚዳን ኚአዲስ ዓለምና ኚአካባቢው ዚመጣው ሕዝብ ነው" ሲል በአቅራቢያው ያሉ ነዋሪዎቜ በቻሉት ዚተወሰኑትን እንዳተሚፉ ይናገራል። ኚጥቃት ፈጻሚዎቹ መካኚል ዚሚያውቋ቞ው እንዲሁም ዚማያውቋ቞ው ታጣቂዎቜ በአንድ ላይ በቡድን በቡድን ሆነው "ግማሹ ቀት ያቃጥላል፣ ሌላው ያገኘውን በጥይትና በስለት ይገድል ነበር" ብሏል። በድርጊቱ ውስጥ ዚመንግሥት አካላት እጅ አለበት ብሎ እንደሚያስብ ለቢቢሲ ገልጿል። "በአካባቢው መንግሥትም አለ ብዬ አላስብም። ምንም ያላደሚገ ሰው በማንነቱ ተለይቶ ሲጚፈጚፍ በጣም ያሳዝናል። ኚአንድ ቀተሰብ 12 ሰው ዚታሚደው ኚጎሚቀ቎ ነው። ግድያው በጣም በጣም ነው ዚሚዘገንነው። በጣም ብዙ አስኚሬን ነው ዚቆጠርኩትፀ ኹ120 በላይ ዹተሰበሰበ አስኚሬን ነበር። በእርግጠኝነት ዹማውቀው ቁጥር ግን ዚለም።" "አሁን ግን [ሐሙስ] አካባቢው ተሚጋግቷል። ዚመኚላኚያ ሠራዊትና ዚፌደራል ፖሊስ ተሰማርቷል። ጭላንቆ ኚሚባለው ቊታ ግን ዚተኩስ ድምጜ ይሰማል" ብሏል። "ዚሚታወቁ ሰዎቜም አሉበት" ሌላው ቢቢሲ ያናገራ቞ው በቀንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ መተኹል ዞን፣ በቡለን ወሚዳ 02 ቀበሌ ነዋሪ ዚሆኑት ስማ቞ው እንዲገለጜ ያልፈለጉ ግለሰብፀ በጥቃቱ ተገደሉ ዚሚባሉ ሰዎቜን አስኚ 150 ሊደርስ እንደሚቜል ይናገራሉ። እኚህ ነዋሪ እንደሚያሚጋግጡት ጥቃት ፈጻሚዎቹ በዚቊታው ቀት እያቃጠሉ ሰዎቜን ገድለዋል። "በኩጂ ላይ ዚእኔ ቀተሰብ በአጠቃላይፀ አባትና ልጅ፣ ዚእኔ እህትና ዚአጎቶቌ ቀተሰብ እዚያው አልቀዋል። ኹነልጁ እነሱን ዚሚያስተምራ቞ው መምህር አጎቮ [ስም ጠቅሰዋል] ጭምር ነው ዹተገደለው" ሲሉ ገልጞዋል። "ጥቃት አድራሟቹ ዚልዩ ኃይል ልብስ ያላ቞ው ና቞ው። ሜፍታ ናቾው ይባል እንጂ ዚሚታወቁ ዚአካባቢው ሰዎቜም አብሚው አሉ" ሲሉ ኚጥቃቱ ዹተሹፉ ሰዎቜ እንደነገሯ቞ው ዹዓይን እማኙ ተናግሚዋል። ጥቃት ፈጻሚዎቹ "ማንንም ኹማንም አይለዩም። ህጻንን በቀስት ኚመምታት ጀምሮ አዋቂዎቜን በአሰቃቂ ሁኔታ ነው ዚጚፈጚፉት። ሆስፒታል ያለው ነገር ኚባድ ነው። ሆስፒታሉም ኹአቅሙ በላይ ነው አሁን። ቁስለኛው ዚት እንደሚታኚም ኚባድ ሁኔታ ላይ ነው።" ሚቡዕ ማለዳ በርካታ ሰዎቜ ኚተገደሉበት ኚበኩጂ ወጣ ብሎ በሚገኝ ዶሊ በሚባል ቊታ ሚቡዕ ማታ ጥቃት ተፈጜሞ 5 ሰው መገደላቾውን ነዋሪዎቜና ዚአካባቢው ባለስልጣናት ተናግሚዋል። ኚተገደሉትና ጉዳት ኚደሚሰባ቞ው ሰዎቜ በተጚማሪ በርካታ ሰዎቜ ነፍሳ቞ውን ለማትሚፍ በአቅራቢያ ወደሚገኙ ቀበሌዎቜ መሞሻ቞ውን ዚሚገልጹት ዹዓይን እማኙፀ ጥቃቱ ኚተፈጞመባ቞ው ዚአካባቢው ነዋሪዎቜ በተጚማሪ በሌሎቜ ቊታዎቜ ዚሚኖሩ ሰዎቜ ጥቃት ሊፈጾም ይቜላል በሚል ስጋትና ጭንቀት ውስጥ እንደሚገኙ አመልክተዋል። በምዕራብ ኢትዮጵያ በሚገኘው ዚቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ በሚገኘው ዹመተኹል ዞን ውስጥ በታጣቂዎቜ እዚተፈጞመ ያለው ጥቃት ወራትን አስቆጥሮፀ አሁንም ድሚስ በተለያዩ ጊዜያት በሚፈጾሙ ጥቃቶቜ በርካታ ሰላማዊ ሰዎቜ ተገድለዋል። አሁን ያጋጠመው ጥቃት ደግሞ ኹዚህ በፊት ኚተፈጞሙት ጥቃቶቜ አንጻር እጅግ ዹኹፋውና በርካታ ሰዎቜ ዚተገደሉበት ሲሆንፀ ነዋሪዎቜ በቅርበት ዚሚያውቋ቞ው ሰዎቜ ጥቃት በመፈጾሙ መሳተፋ቞ውን በተደጋጋሚ ገልጞዋል። ጥቃቱን ተኚትሎም ኚጥቃቱ ጋር በተያያዘ ዚተጠሚጠሩ ሰባት ኹፍተኛ ባለስልጣናት በቁጥጥር ስር ዹዋሉ ሲሆንፀ ዚጞጥታ ኃይሎቜ በአካባቢው ባደሚጉት አሰሳ ኹ40 በላይ ታጣቂዎቜን መግደላቾውን ዚቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሳውቋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በቀኒሻንጉል ክልል ውስጥ ስለሚፈጞሙ ጥቃቶቜ አስመልክተው በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻ቞ው ላይ እንዳሉት "ቜግሩን በተለያዚ መንገድ ለመፍታት ያደሚግነው ጥሚት ዹሚፈለገውን ውጀት አላመጣም" በማለት መንግሥታ቞ው ቜግሩን ኚመሠሚቱ ለመፍታት "አስፈላጊውን ዹተቀናጀ ኃይል እንዲሠማራ አድርጓል" በማለት ገልጞዋል። ካለፈው ዓመት ማብቂያ አንስቶ በርካታ ሰዎቜ ዚተገደሉበት ዹመተኹል ዞንፀ ሠላምና መሚጋጋት ለማስኚበር ዚፌደራል መንግሥት ሠራዊት፣ ዚፌደራል ፖሊስና ዹክልሉ ዚጞጥታ ኃይል በጋራ በሚመሩት ኮማንድ ፖስት ኚሚተዳደሩ አካባቢዎቜ አንዱ እንዲሆን ቢደሚግም ጥቃቱ ሳይገታ ቆይቷል። በቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ ዹሚገኘውና ተደጋጋሚ ጥቃቶቜ በሰላማዊ ሰዎቜ ላይ ዚሚፈጞምበት ዹመተኹል ዞን ሰባት ወሚዳዎቜ ያሉት ሲሆን በዋናነት ዚጉሙዝ፣ ዚሜናሻ፣ ዚአማራ፣ ዚአገው፣ ዚኊሮሞና ዚበርታ ብሔሮቜ ዚሚኖሩበት አካባቢ ነው።
51225314
https://www.bbc.com/amharic/51225314
ዚጀነራሉ ጩር ዚመንገደኞቜ አውሮፕላንን ኢላማ አደርጋለሁ ሲል አስፈራራ
በጀነራል ካሊፋ ሃፍታር ዚሚመራው ጩር ዚትሪፖሊን አዹር ማሚፊያ ዹሚጠቀሙ ዚመንገደኞቜ አውሮፕላኖቜን ኢላማ እንደሚያደርጉ ተናገሩ።
ዚጊሩ ቃል አቀባይ በሊቢያ መዲና ትሪፖሊ ዚሚዚያርፉ ዹጩርም ሆነ ዚመንገደኞቜ አውሮፕላኖቜ መትተው ኚመጣላ቞ው በፊት ዚመጚሚሻ ያሉትን ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል። በአሁኑ ሰዓት በሊቢያ ሁለት ዋነኛ ተቀናቃኝ ኃይሎቜ ይገኛሉ። በተባበሩት መንግሥታት እውቅና ዹተሰጠው በጠቅላይ ሚንስትር ፋዬዝ አል-ሎራጅ ዚሚመራው መንግሥት እና በጀነራል ካሊፋ ሃፍታር ዚሚመራው አማጺ ኃይል ና቞ው። በተባበሩት መንግሥታት እውቅና ዹተሰጠው መንግሥት ትሪፖሊን ተቆጣጥሮ ይገኛል። • ''ኢትዮጵያዊያንን ዚባሕር ላይ አደጋ መሞኚሪያ ያደርጉ ነበር'' • በሊቢያ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ላይ በደሹሰ ጥቃት በርካቶቜ ሞቱ ታዲያ ኚሳምንታት በፊት በተባበሩት መንግስታት እውቅና ዹተሰጠውን መንግሥት ለመደገፍ ቱርክ ወታድሮቿን ወደ ሊቢያ መላኳ ዚጀነራል ሃፍታር ጩርን አበሳጭቷል። ዚጊሩ ቃል አቀባይ ቱርክ ዚትሪፖሊን አዹር ማሚፊያ ዹጩር ካምፕ በማድሚግ ጥቃት እዚሰነዘሚቜብን ነው ብለዋል። ኹዚህ ቀደም 'ሚተጋ' ዚተባለው ኚትሪፖሊ በቅርብ ርቀት ላይ ይገኝ ዹነበሹ አዹር ማሚፊያ ሮኬት ኚተተኮሰበት በኋላ ሥራውን ለማቋሚጥ ተገዷል። ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ እውቅና ባለው መንግሥት እና በአማጺያኑ መካኚል በነበሹ ግጭት ቢያንስ 2 ሺህ ሊቢያውያን ሕይወታ቞ውን አጥተዋል። 146 ሺህ ዚሚሆኑት ደግሞ ዚመኖሪያ ቀያ቞ውን ጥለው ተሰደዋል። ዚጀነራል ሃፍታር ጩር ትሪፖሊን ለመቆጣጠር ክፍተኛ ጥሚት ሲያደርግ ቆይቷል። ዚሊቢያውን ዚእርስ በእርስ ጊርነት እና ዚሌሎቜ አገራት ጣልቃ ገብነት አሁንም ዹዓለም ትኩሚትን እንደሳበ ነው። ለመሆኑ ሊቢያውያን እዚህ አጣብቂኝና ውስብስ ነገር ውስጥ እንዎት ገቡ? ልክ እንደ ሶሪያ ሁሉፀ ዚሊቢያውያን ሰቆቃ ዹጀመሹው ዚአሚብ አብዮትን ተኚትሎ ነው። እ.አ.አ. 2011 ላይ በምዕራባውያኑ ኔቶ (ዹሰሜን አትላንቲክ ዹጩር ቃልኪዳን ድርጅት) ድጋፍ ዚሚዥም ጊዜ ዚሊቢያ መሪ ዚነበሩት ሙዓመር ጋዳፊ ኚሥልጣን ተባሚሩ። አምባገነኑ ሙዓመር ጋዳፊ በሊቢያውያን ለውጥ ናፋቂ ወጣቶቜ መንገድ ላይ ተጎተቱፀ አይደፈሬው ተዋሚዱፀ ኚዚያም በጥይት ተመትተው ተገደሉ። በሊቢያ አዲስ ለውጥ መጣ ተባለ። ሊቢያውያን ግን አምባገነናዊ ሥርዓቱን በሕዝባዊ አብዮት ሲገሚስሱትፀ ነጻነትን እና ዚተሻለ ሥርዓትን አልመው ነበር። ዹሙዓመር ጋዳፊ ሞት ግን ሊቢያውያን ዚተመኙትን ለውጥ ሳይሆንፀ መግቢያ መውጫ ያሳጣ቞ውን ዚእርስ በእርስ ጊርነት ነው ያስኚተለው። ዚተባበሩት መንግሥታት በጠቅላይ ሚንስትር ሰርጀ ዚሚመራ መንግሥት መቀመጫውን በትሪፖሊ እንዲያደርግ አመቻ቞። ሁሉም በዚህ አልተስማማምፀ ጀነራል ሃፍታር ሥልጣን ፈለጉ። ጀነራሉ በምስራቅ ሊቢያ በሚገኙ 'ቶበሩክ' እና 'ቀንጋዚ' ኚተሞቜ መቀመጫ቞ውን አድርገው ዚራሳ቞ውን ጩር አደራጁ። ተጜእኖ ፈጣሪው ጀነራልፀ ዚሊቢያ ብሔራዊ ጩር ዹተሰኘ ኃይል አቋቁመው ካለ እኔ ለሊቢያ ዚሚፈይድ ዚለምፀ እኔ እንጂ ማንም "እስላማዊ አሞባሪዎቜን" አያስወግድም አሉ። ኚዚያም በተመድ እውቅና ያለውን መንግሥት መውጋት ተያያዙት። ትሪፖሊን ለመቆጣጠር ዹጩር እርምጃ መውሰድ ኚጀመሩ 9 ወራት ተቆጠሩ። ኚጀነራሉ ጩር በተጚማሪ በሊቢያ ''ነጻ'' አውጪ ነን ዹሚሉ ኃይሎቜ በርካቶቜ ና቞ው። ኚዚመሞጉበት እዚወጡፀ አንዱ አንዱን ይወጋል። በሊቢያ ''እስላማዊ መንግሥት'' መመሠሚት አለበት ብለው ዚሚንቀሳቀሱ ኃይሎቜም ብዙ ና቞ው። ተጜዕኖ ፈጣሪው ጀነራል ካሊፋ ሃፍታር ዚእጅ አዙር ጊርነት በሊቢያ ዚሚንቀሳቀሱት ኃይሎቜ ዚራሳ቞ውን ብቻ ሳይሆን ዚሌሎቜ ዚውጪ ሃገራት ፍላጎትን ለማሳካት ነፍጥ አንግበዋል። በቀጠናው ዹሚገኙ ሃገራት በተለያዚ አሰላለፍ ዚእጅ አዙር ጊርነት ወይም ዹውክልና ጊርነት ያካሂዳሉ። ጀነራል ሃፍታር "እስላማዊ አሞባሪዎቜን" እዋጋለሁ ማለታ቞ውን ተኚትሎ ሳዑዲ አሚቢያ፣ ዚተባበሩት አሚብ ኀሜሬቶቜ እና ጆርዳን ጜንፈኞቜ ኹቀጠናው መጜዳት አለባ቞ው በማለት አጋርነታ቞ውን ኚጀነራሉ ጋር አድርገዋል። ጆርዳን እና ዚተባበሩት አሚብ ኀሜሬቶቜ ኚድጋፍም አልፈው ዚጀነራሉን ጩር አስታጥቀዋልፀ በተመድ እውቅና ባለው መንግሥት ላይ ጥቃት ሲሰነዘር ዹአዹር ላይ ድጋፍ ያደርጋሉ። በግጭቱ ወቅት ዚተገደሉት ንጹሃን ዜጎቜ ለሞት ያበቃ቞ው ዚተባበሩት አሚብ ኀሜሬቶቜ ጩር መሳሪያ ነው ሲል ዚተባበሩት መንግሥታት ይኚሳል። ኚእነዚህ ሃገራት በተጚማሪፀ ጎሚቀት ሃገር ግብጜም ዚጀነራሉ አጋር ነቜ። አል ሲሲ ለጀነራል ሃፍታር ጩር ዚሎጂስቲክ ድጋፎቜን እያደሚጉ ይገኛሉ። ኚአካባቢው ሃገራት በተጚማሪም ሞስኮ በሊቢያ እጇን እያስገባቜ እንደሆነ እዚተነገሚ ነው። ሪፖርቶቜ እንደሚጠቁሙት በሩሲያ መንግሥት ተኹፋይ ዹሆኑ ዚሌሎቜ ሃገራት ወታደሮቜ ኚጀነራሉ ጎን ሆነው እዚተዋጉ ይገኛሉ። ዚክሬምሊን መንግሥት ግን ቀጥተኛ ተሳትፎ ዹለኝም ይላል። በሌላኛው በኩል ደግሞ ቱርክ ዚተመድ እውቅና ዹተሰጠውን መንግሥት ትደግፋለቜ። ኚጥቂት ቀናት በፊትም ቱርክ ወደ ሊቢያ ዚትሪፖሊን መንግሥት ለመደገፍ ጊሯን ልካለቜ። ዚቱርክ መንግሥት ጊሩን ወደ ሊቢያ ዹላኹው "ዚሥልጠና እና ዹምክር አገልግሎት" ለመስጠት ታስቊ ነው ብሏል። በሊቢያ መንግሥት ውስጥ ዹሚገኝ ዚቢቢሲ ውስጥ አዋቂ ግን በቱርክ በኩል ወደ ሊቢያ ኚመጡ ወታደሮቜ መካኚል በቱርክ ዹሚደገፉ ዚሶሪያ አማጺያን ይገኙበታል ብሏል። በመካኚለኛው ምስራቅ ፖለቲካ ውስጥ ብዙውን ግዜ ተገልላ ዚምትገኘው ኳታርፀ በሊቢያ ጉዳይ ኚተባበሩት መንግሥታት እና ኚቱርክ ጎን ተሰልፋለቜ። ዚምዕራባውያን ሃገራት ፍላጎቶቜ ሌላ ዚሊቢያ ጉዳይ ያገባኛል ዚምትለው ፈሚንሳይፀ ዚቱርክን አሰላለፍ ተቀላቅላለቜ። ፈሚንሳይ ዚተባበሩት መንግሥታት እውቅና ያለውን መንግሥት እደግፋለሁ ትበል እንጂ ልቧ ያለው ኚጀነራሉ ጩር ጋር ነው ተብሎ ይታመናል። ዚቀድሞ ዚሊቢያ ቅኝ ገዢ ዚሆነቜው ጣሊያንፀ ፓሪስ ለጀነራሉ ጩር ዚምታደርገውን ድጋፍ አጥብቃ ካወገዘቜ በኋላፀ ሮም ሁልጊዜም ተመድ እውቅና ለሰጠው መንግሥት ድጋፍ ማድሚጓን እንደምትቀጥል አስታውቃለቜ። • በሊቢያ ዹተፈፀመው ዹጩር ወንጀል ሊሆን ይቜላል ተባለ በርካታ አፍሪካውያን ስደተኞቜ በሊቢያ በኩል አድርገው ሜዲትራኒያን ካቋሚጡ በኋላ ዚመጀመሪያው መዳሚሻ቞ው ጣሊያን ነቜ። በዚህም ጣሊያን ዚስደተኞቜን ፍሰት ለማስቆም በሊቢያ ጉዳይ ጣልቃ መግባት አለብኝ ባይ ነቜ። ኃያሏ ሃገር አሜሪካም በሊቢያ በቀጥታ እጇን አስገብታለቜ። በደቡብ ምዕራብ ሊቢያ ዹሚገኙ ዚአይኀስ ሚሊሻዎቜ ላይም እርምጃ ትወስዳለቜ። ይህ ሁሉ ሃገር በሊቢያ ጉዳይ እጁን ዚሚያስገባው ለምን ይሆን? በሊቢያ ዚእርስ በእርስ ጊርነት እጃ቞ውን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ዚሚያስገቡት ሃገራት ቁጥር ኹፍተኛ ነው። ለዚህም ዚመጀመሪያው ምክንያት ሰሜን አፍሪካዊቷ ሊቢያ ኹፍተኛ ዹሆነ ዚተፈጥሮ ጋዝ ክምቜት ያላት ሃገር ነቜ። በተፈጥሯዊ ጋዝ ገበያ ላይም ተጜዕኖ ፈጣሪ ሃገር መሆን ትቜላለቜ። ሌላኛው ምክንያት መዳሚሻ቞ውን አውሮፓ ለማድሚግ ኚአፍሪካ ዚሚሰደዱ ወጣቶቜ መነሻ቞ውን ዚሚያደርጉት ኚሊቢያ ነው። ሊቢያ ኹ 2 ሺህ ኪ.ሜትር በላይ ኚሜድትራኒያን ባህር ጋር እንደምትዋሰን እንዳለ ሆኖ ማለት ነው። ኚኢራቅ እና ሶሪያ ድል ዚተመታው ጜንፈኛው አይኀስ በሊቢያ በሚሃዎቜ ላይ እግሩን እዚኚተተ መሆምኑ ተነግሯል። ይህ ለሊቢያ እና ጎሚቀት አገሮቜ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ደህንነት ስጋት ነው።
news-46465118
https://www.bbc.com/amharic/news-46465118
በሳተላይቶቜ ዙርያ ማወቅ ዚሚገባዎ ሰባት አስደናቂ እውነታዎቜ
በመሬት ዙርያ ዚሚሟሩ ሳተላይቶቜ ቁጥራ቞ው ስንት ይደርስ ይሆን? ደግሞስ እርስ በርስ እንዎት አይጋጩም? ደግሞስ እንዎት ወደ መሬት አይፈጠፈጡም?
ኹሰሞኑ በአንድ ጊዜ 64 ሳተላይቶቜን ዹማምጠቅ ሐሳብ ተወጥኗል። ይህ ዹተወጠነው በደቡብ አፍሪካዊው ባለጞጋ ኢለን ማስኚ አማካኝነት ሲሆን «ስፔስ ኀክስ ኀሮስፔስ» ደግሞ ኩባንያው ነው። በቅርቡ ዚሚመጥቀው ፋልኹን 9 ሮኬት ታሪካዊ ዹሆነውም ለዚሁ ነው። ኚአሜሪካ ምድር ዚሚነሳው ይህ ሮኬት በአንድ ጉዞ ብቻ 64 ሳተላይቶቜን ያመጥቃል። እነዚህ በኅብሚት እንዲመጥቁ ዚሚደሚጉት 64 ሳተላይቶቜ ኹ34 ድርጅቶቜና ኹ17 አገራት ዚተሰበሰቡ ና቞ው። • ኢትዮጵያ ሳተላይት ማምጠቅ ለምን አስፈለጋት? ሳተላይቶቹ ዚተለያዚ መጠንና አገልግሎት እንደሚኖራ቞ው ይጠበቃል። ለስልክ ግንኙነቶቜ፣ ለኢንተርኔትና በመርኚቊቜ ላይ ዹሚፈጾሙ ዚባሕር ላይ ወንጀሎቜን ለመኚታተል እንዲያገለግሉ ዚታሰቡም ይገኙበታል። ለመሆኑ ስንት ሳተላይቶቜ ሕዋ ላይ እንዳሉ ይታወቃል? ደግሞስ ማንም ተነስቶ ወደ ሕዋ ሊያመጥቃ቞ው ይቜላል? ወይስ ፍቃድ ያሻል? ፍቃድ ካስፈለገ ፍቃድ ሰጪው ማን ነው? ሳተላይቶቜ እርስበርስ ሊላተሙ ዚሚቜሉበት አጋጣሚስ ይኖር ይሆን? ለመኟኑ በመሬት ምህዋር ዚሚዘዋወሩ ሰው ሰራሜ ሳተላይቶቜ ስንት ይሆናሉ ብለው ይገምታሉ? መቶ? ሺህ? 10ሺህ? በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዹአውተር ስፔስ ጉዳዮቜ ቢሮ UNOOSA እንደተገለጞው ዛሬ ላይ ወደ አምስት ሺህ ዹሚጠጉ ሳተላይቶቜ ይገኛሉ። ቁጥሩን በትክክል ለማስቀመጥ ያህል 4921 ሳተላይቶቜ ምድርን እዚተሜኚሚኚሩ ነው። ነገር ግን ሁሉም በሥራ ላይ ናቾው ማለት አይደለም። • ኬንያ ሳተላይት ልታመጥቅ ነው ኚሥራ ውጭ ዚሆኑት 2600 ሲሆኑ በሕዋ ላይ እነዚህን ሳተላይቶቜ ጚምሮ 17ሺህ ዹሚጠጉ ዚተለያዩ ሳተላይት ያልሆኑ መሣሪያዎቜ ይገኛሉ ይላል በደቡብ ካሊፎርኒያ ዩኒቚርስቲ ዹሕዋ ተመራማሪው ዎቪድ ባርን ሀት። እነዚህ ቁሳቁሶቜ በድምሩ 7600 ቶን ይመዝናሉ። ሁሉም ዚሚገኙት ታዲያ ኚመሬት እስኚ 35 ሺህ ኪሎሜትር ርቀት ላይ ነው። 1. ዚሳተላይቶቹ መጠን ምን ያህል ነው? ሳተላይትን ስናስብ መጀመርያ ወደ አእምሯቜን ዚሚመጣው እጅግ ግዙፍና እጅግ ኚባድ ኹሆኑ ቁሳቁሶቜ ዚተሠራ በጣም ትልቅ ቁስ ሊሆን ይቜላል። ነገር ግን ሁሉም ሳተላይቶቜ እንደዚያ አይደሉም። መጠናቾውም ቢሆን ይለያያል። ትንሜ ዚዳቊ ቅርጫት ኚሚያክሉት አንስቶ ዹኹተማ አውቶቡስ እስኚሚያህሉት ድሚስ አሉ። አንድ መለስተኛ ዚእግር ኳስ ሜዳ ዚሚያክሉ ሳተላይቶቜም ይገኛሉ። 2. ሳተላይት አገልግሎቱ ምንድነው? ሁሉም ሳተላይቶቜ ወደ ምድር አጎንብሰው ዚመሬት አካልን ፎቶ ዚሚያነሱ አይደሉም። ዘርፈ ብዙ አገልግሎትን ይሰጣሉ። ዚኮሚኒኬሜን ሥራ አንዱ ነው። ዚስልክ ግንኙነትን፣ ዚዳታ ስርጭትን ዹምናገኘው በሳተላይቶቜ አማካኝነት ነው። ዚመሬት ቅኝትና ምልኚታን (ዚጂፒኀስ ሥርዓትን ይጚምራል) ዹምናውቀው ሳተላይቶቜ ስላሉ ነው። • ዹሃምዛ ሃሚድ ገመድ አልባ ዚኀሌክትሪክ ማስተላለፊያ ዹሕዋ ጥናትን እንዲሁም ዚፕላኔት ጥናትን ዚሚያካሄዱ መልኹ ብዙ ሳተላይቶቜም ይገኛሉ። ነገ አዲስ አበባ ይዘንብ ይሆን ወይስ ደመናማ ይሆናል ለማለት ዚሳተላይት ምስሎቜ ያስፈልጉናል። ዚባህር ወጀብን ሳይቀር ምስል አንስቶ ዹሚልኹው ሳተላይት ነው። ዚዓለማቜን ሳንባ ዚሚባለው አማዞን ጫካ ውስጥ ምን ያህል ምንጣሮ እዚተካሄደ እንደሆነ፣ ቻይና በሹሃ ውስጥ አፈናና ግድያ ዚሚፈጞምበት ማጎርያ እዚተገነባ ይሁን አይሁን ሳተላይቶቜ ፍንጭ ያቀብሉናል። በቀታቜን ቁጭ ብለን ዚምንኮመኩማ቞ው ዚ቎ሌቪዥን ስርጭቶቜና ዚራዲዮ ሞገዶቜ ዚሳተላይት እገዛን ዚሚሹ ሊሆኑ ይቜላሉ። 3. እንዎት ነው ሳተላይት በምህዋሩ መቆዚት ዚሚቜለው? ሳተላይቶቜ በምድር ዙርያ ሊሟሩ ዚሚቜሉት ዚመሬት ስበትን ለመቋቋም በሚያስቜል ፍጥነት ላይ እንዲሆኑ ስለተደሚጉ ነው። አለበለዚያ ወደ መሬት ይወድቁ ነበር። ይህን ለመሚዳት ትንሜ ውስብስብ ቢሆንም በቀላሉ አንድ መድፍ በኹፍተኛ ጉልበት በ180 ዲግሪ ቢተኮስ መሬት ላይ ኹመውደቁ በፊት በሆነ አቅጣጫ ዹተወሰኑ ርቀቶቜን ይጓዛል። ወደ መሬት ዹመውደቅ ርቀቱ ዹሚወሰነው በሚኖሹው ዚፍጥነት ጉልበት ነው። ሳተላይቶቜም ለመሬት ስበት እጅ ዚማይሰጡበት ምክንያት ፍጥነታ቞ው ነው። 4. ዚሳተላይቶቜን ዕድሜ ምን ያህል ነው? ሮኬቶቜ ሳተላይትን ጭነው ወደ ሕዋ ያመጥቁና ለሳተላይቱ ኚተሰናዳለት ቊታ ያኖሩታል። ዚተስተካኚለ ርቀቱን እስኪያገኝ ወራትን ሊወስድ ይቜላል። በመጚሚሻም ሳተላይቱን በምህዋሩ ላይ ይቀመጣል። ሳተላይቱ ተሞክሞት ኹሄደው ሮኬት ቀስ በቀስ በሚለያይበት ወቅት ዹሚኖሹው ፍጥነት በመሬት ዙርያ ለመቶ ዓመት መሜኚርኚር ያስቜለዋል ይላሉ ባለሞያዎቜ። ዋናው ሳተላይት በሕዋ ላይ እንዲቆይ ዚሚያደርገው ምስጢር ዚመሳሳብ ፊዚክስ ሲሆን በመሬት ስበት እንዳይወድቅ ዚሚያግደው ብ቞ኛው ጉዳይ ዚእሜክርክሪት ፍጥነቱ ነው። ለዚያም ነው ኚመሬት በቅርብ ርቀት ዚሚገኙት ሳተላይቶቜ ዚሚሟሩበት ፍጥነት ኚመሬት ራቅ ብለው ኚሚገኙት ይልቅ ፈጣን ዚሆነው። • በዓይነ ስውሯ ዚተሠራው ዚሚያይ ሻንጣ ሳተላይቶቜ ዚእሜክርክሪት ምህዋራ቞ውን መለወጥ ቢያስፈልግ እና እርስበርስም እንዳይጋጩ እንዲሚዳ ዚዚራሳ቞ውን ነዳጅ ተጭኖላ቞ዋል። ሳተላይቶቜ ኹ5 እስኚ 15 ዓመታት አገልግሎት ላይ ሊቆዩ ይቜላሉ። ዕድሜያ቞ው ግን በሚሰጡት አገልግሎትና በሚታጠቁት ዚነዳጅ መጠን ይለያያል። 5. ሳተላይቶቜ ሊጋጩ ይቜላሉ? ሊጋጩ ይቜላሉፀ ነገር ግን ሁልጊዜ ዹሚሆን ነገር አይደለም። ምክንያቱም ዚሚሟሩበት መስመር ኚመለያዚቱም ባሻገር ሕዋ እጅግ ሰፊ አካል መሆኑ ግጭት እንዳይኖር ያደርጋል። ይህ ማለት ግን ግጭት በፍጹም አይኚሰትም ማለት አይደለም። በአሁኑ ጊዜ እጅግ በርካታ ሳተላይቶቜን ዹማምጠቅ ዕቅድ መኖሩ ሲታይ ግጭት ዚመኚሰቱ ዕድል ዜሮ ነው ማለት አይቻልም። በዚካቲት፣ 2009 አንድ ዚአሜሪካና አንድ ዚራሺያ ሳተላይቶቜ ተላትመው ያውቃሉ። ይህ በታሪክ ዹተመዘገበ ዚመጀመርያው ዚሳተላይቶቜ ግጭት ነው። 6. ሳተላይቶቜን ማን ነው ዚሚቆጣጠራ቞ው? ሳተላይቶቜ በድርጅቶቜ ወይም በኩባንያዎቜ ወይም በመንግሥት አንዳንድ ጊዜም በግለሰቊቜ ባለቀትነት ሊያዙ ይቜላሉ። በ1967 በተደሹገው ዹአውተር ስፔስ ስምምነት መሠሚት እያንዳንዱ ሳተላይት ያመጠቀ አገር ዹተወሰነ ዚመቆጣጠር ሥልጣን እንዲኖሚው ዹተደሹገው ዚሬዲዮ ልውውጥ መጠላለፍን ለማስቀሚት ጭምር ነው። በአሜሪካ ለምሳሌ ዹግል ኩባንያዎቜ በስፔስ አገልግሎት ላይ ለመሰማራት መጀመርያ ኚፌዎራል መንግሥት ፍቃድ ማግኘት ይኖርባ቞ዋል። ለኮሚኒኬሜንና ቎ሌኮም ሳተላይት ግንኙነት ለማድሚግ ኚፌዎራል ኮሚኒኬሜን ኮሚሜን ፍቃድ መውሰድ ግድ ነው። ሳተላይትን ወደ ሕዋ ለማምጠቅ ደግሞ ዚፌዎራል አቪዚሜን አስተዳደርን ፍቃድ ማግኘት ያሻል። በዓለም አቀፍ ደሹጃ ደግሞ ዚተባበሩት መነግሥታት ድርጅት ዹአውተር ስፔስ ጉዳዮቜ በእንግሊዝኛ ምህጻሩ UNOOSA ዚሚባለው ኃላፊ መሥሪያ ቀት ነው። በሕዋ ጉዳዮቜ ዙርያ ሕግ ያሚቃል ይቆጣጠራል። 7. ማንም ሳተላይት ወደ ሕዋ ማምጠቅ ይቜላል? አዎ! ዛሬ ማንኛውም ሰው ሳተላይትን ወደ ሕዋ ማምጠቅ ዚሚቜለበት ደሹጃ ተደርሷል። ዹ2ኛ ደሹጃ ትምህርት ቀት ተማሪዎቜ ሳይቀሩ ሳተላይት ገንብተው በማምጠቅ ፕሮግራማ቞ውን ኚሌሎቜ መንግሥታዊ ተቋማት ጋር ይጋራሉ። ኚመቌውም ጊዜ በላይ ዚንግድ ኩባንያዎቜ ሳተላይት ዚሚያመጥቁበት ጊዜ ላይ እንገኛለን። ኟኖም ኹፍ ያለ በጀት ዹሚጠይቅ ጉዳይ ነው። ይህ ዚሳተላይት ኢንዱስትሪም በቢሊዮን ዶላር ይገመታል።
44722155
https://www.bbc.com/amharic/44722155
‹‹እኛ ላይ ኹደሹሰው ጉዳት ይልቅ ዚኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ዹደሹሰው ይበልጣል!›› ዹዘ-ሀበሻ ድሚ-ገፅ ባለቀት
ዚኢትዮጵያ መንግሥት ስም እና ሹቂቅ ቮክኖሎጂን በመጠቀም ተገዳዳሪ ዹዜና ተቋማት ድሚ-ገጟቜን ዹማፈን ልማድ ለዓመታት በቁርኝት ተራምደዋል፡፡ በዓመታት ውስጥ Deep Packet Inspection (DPI) በተሰኘው ልዩ ማጥለያ ዘዮ እዚተጠለፉ ለጎብኝዎቜ ኚመድሚስ ዚታገዱ ድሚ-ገፆቜ ብዛት ኹፍተኛ ነው፡፡
ቀዳሚ ዓመታትን ትተን ኚሊስት ዓመታት በፊት በመላው ሀገሪቱ ዚተነሳውን ሕዝባዊ እምቢተኝነት ተኚትሎ 16 ዹዜና ተቋማት በሀገር ውስጥ እንዳይታዩ መታፈና቞ውን በወቅቱ አምነስቲ ኢንተርናሜናል ዹተሰኘ ተቋም አጋልጧል፡፡ በመሰል ርምጃዎቹ በመብት ተሟጋ቟ቜ ዘንድ ሲብጠለጠል ዹሰነበተው ዚኢትዮጵያ መንግሥት ‹ታሪክ ቀያሪ› ስለመሆኑ ዹተጠቀሰ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡ ዚማህበራዊ ድሚ-ገፅ ዘመቻዎቜ ዹጠቅላይ ሚኒስትር ጜሕፈት ቀት ኃላፊ ፍፁም አሹጋ በትዊተር ገጻ቞ው ላይ ይፋ እንዳደሚጉት ሀገር ውስጥ እንዳይጎበኙ ታፍነው ዚነበሩ ኹ250 በላይ ድሚ-ገጟቜ ክልኹላው ተነስቶላ቞ዋል፡፡ መታፈን ማንን ጎዳ? ሄኖክ ዓለማዹሁ ደገፉ አሜሪካን ዚስደት ዘመን መጠለያ ካደሚጉ ጋዜጠኞቜ እና አሳታሚዎቜ መካኚል አንዱ ነው፡፡ ኚጥቂት ዓመታት በፊት በፖለቲካ፣ መዝናኛ እና ማኅበራዊ ጉዳዮቜ ላይ ትኩሚቱን ያደሚገ ድሚ-ገጜ አስተዋወቀ፡፡ መጠሪያው "ዘ-ሀበሻ" ዹሆነው ይሄ ድሚ-ገጜ በመንግሥት እጅ ውስጥ በነበሩ ዹዜና ተቋማት ተመሳሳይ ዘገባ ተሰላቜቶ ለነበሹው ‹‹ዲያስፖራ›› እንደ አንድ ዹመሹጃ ምንጭ ሆነ፡፡ ብዙም ሳይቆይ ግን "ዘ-ሀበሻ" ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳይነበብ እግድ እንደተጣለበት አዘጋጆቹ አወቁ፡፡ ‹‹እኛ ላይ ኹደሹሰው ጉዳት ይልቅ ዚኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ዹደሹሰው ይበልጣል!›› ይላል ሄኖክ፣አንባቢያን ኚእገዳው ሟልኚው ድሚ-ገጹን ለመጎብኘት ዚተለያዩ መተላለፊያ ሶፍትዌሮቜን ለማግኘት ለወጪ እና ለሰዓት ብክነት መዳሚጋ቞ውን በማስታወስ፡፡ ዹጠቅላይ ሚኒስትሩ 100 ቀናት ዚኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ፕሮጀክት መሥራቜ ሶሊያና ሜመልስ በሰብአዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶቜ ላይ ደሚሱ ዚምትላ቞ውን ጥቃቶቜ በዚመድሚኩ ስታሰማ ባጅታለቜ፡፡ ለእርሷ ዚኢትዮጵያ መንግሥት ድሚ-ገጟቜን ዹማፈን ርምጃ ዚመጀመሪያ ጉዳቱ አማራጭ ሐሳቊቜ ዚሚደመጡበትን ቀዳዳ መድፈኑ ነው፡፡ "(ርምጃው) ዹመሹጃ ፍሰቱ ዹተገደበ እንዲሆን፣ ሀገሪቱ ውስጥ ያለው ዚፖለቲካ ትርክት መንግሥት በሚፈልገው አንድ መንገድ ብቻ ቅርፅ እንዲይዝ አድርጎታልፀ ዓላማውም ይሄ ነበር፡፡" በማለት ዚምታብራራው ሶሊያና መንግሥት ድሚ-ገጟቜን በመዝጋቱ፣ ዚሐሳብ ውድድርን በማጥፋት ሕዝቡ ሕይወት ቀያሪ መሚጃዎቜን ዚማግኘት መብቱ እንዎት እንደተነፈገ ታወሳለቜ፡፡ ዹጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ እርምጃዎቜ ዚት ድሚስ? መንግሥት ድሚ-ገጟቜ በሀገር ቀት አንባቢያን ወይንም ተመልካ቟ቜ እንዳይታዩ ያደርግ እንደነበር በተዘዋዋሪ መንገድ ማመኑን እንደ አንድ ልዩ ነገር ዚምታነሳው ሶሊያና ዹአሁኑ ርምጃ ያለውን ዐብይ ፋይዳ ታነሳሳለቜ፡፡ ጊማሪ እና ዚመብት ተሟጋቜ ሶሊያና ሜመልስ ዚኢትዮጵያ መንግሥት በድሚገጟቜ ላይ አድርጎት ዹነበሹውን ክልኹላ ማንሳቱ ዚመጀመሪያው ተጠቃሚ ሕዝቡ እንደሆነ ትጠቁማለቜ፡፡ ሕዝቡ አንድን ርእሰ ጉዳይ በተለያዚ አቅጣጫ ዹሚተሹጉሙ ዹመገናኛ ብዙኃንን ካለ ገርጋሪ ለመታደም፣ ዹሚበጀውን ሐሳብ ዚመምሚጥ ዕድሉን እንደሚፈጥርለት ታሰምራለቜ፡፡ ዹ"ዘ ሀበሻ" ድሚ-ገጜ ባለቀት ሄኖክ አለማዹሁ በበኩሉ ኚእገዳው መነሳት በተጚማሪ ዚመንግሥት ባለሥልጣናት መቀመጫ቞ውን በውጭ ሀገራት ላደሹጉ ድሚ-ገፆቜ ምላሜ ያለመስጠት እና መሹጃን ዹመንፈግ አሠራራ቞ውን እንዲያርሙ ይመክራል። "ዚመንግሥት ኃላፊዎቜ በራ቞ውን ክፍት ካደሚጉ ዘገባዎቻቜንን ሚዛናዊ ለማድሚግ እንሞክራለን፡፡ እስኚ አሁንም ሚዛናዊ አይደሉም ተብለን ዚምንተቜባ቞ው ምክንያቶቜ ለ27ዓመታት ለነፃው ፕሬስ ጋዜጠኞቜ ደፍሮ መሹጃ ዚሚሰጥ ዚመንግሥት ኃላፊ አለመኖሩ ነው፡፡" ይላል ሄኖክ፡፡ ዚኢትዮጵያን አንገት ዚሚያስደፋ ዚፕሬስ ነጻነት እና ዚጋዜጠኞቜ ደኅንነት ደሹጃ ሲያጋልጡ ኹኹሹሙ ዓለም አቀፍ ድርጅቶቜ መካካል "ሲፒጄ" አንዱ ነው፡፡ ድርጅቱ ኹሰሞኑ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አስተዳደር ዚተወሰዱ ርምጃዎቜን በአውንታ እንደሚያይ ለቢቢሲ ተናግሯል፡፡ ዚድርጅቱ ዚአፍሪካ ጉዳዮቜ ኃላፊ አንጄላ ኩዊንታል አክለው መንግሥት ኹዚህ ርምጃ በተጚማሪ ሊወስዳ቞ው ይገባል ያሏ቞ውን ርምጃዎቜ አጋርተዋል፡፡ "በ2009 እ.ኀ.አ ዚወጣው ዹጾሹ-ሜብር ሕግ ፕሬሱን ድምጜ አልባ ለማድሚግ በሥራ ላይ ሲውል ቆይቷል፡፡ ይህ ሕግ መኚለስ እንዳለበት ኹዚህ በፊት በደብዳቀ አሳውቀናል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ዹተቃዋሚ ፖለቲካ አመራሮቜ በጉዳዩ ላይ እዚተወያዩበት መሆኑን ተሚድተናልፀ ይሄም አስደስቶናል፡፡" ያሉት ዚሲፔጃ ባልደሚባ፣ በተመሳሳይ ዚሀገሪቱ ዹወንጀል ሕግ ዹተወሰኑ ዚስም ማጥፋትን ዚሚመለኚቱ አንቀጟቜ ጋዜጠኞቜን ለመጹቆን በሥራ ላይ እንደዋሉ በመግለጜ፣ "በግልጜ አንቀጟቜ መሻር አለባ቞ው፡፡" ብለዋል አንጄላ፡፡ 'ለአደጋ ዹተጋለጠው' ዚኢትዮጵያ ህትመት ሚድያ
49027425
https://www.bbc.com/amharic/49027425
ክልልነት ለጠዹቀው ሁሉ ቢሰጥ ቜግሩ ምንድነው?
ዚኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት ብሔር ብሔሚሰብና ሕዝቊቜ ዹሚለውን ጹፍልቆም ቢሆን ይበይነዋልፀ ዚተናጥል ትርጉም ግን ፈልጎ ማግኘት አይቻልም። በመካኚላ቞ው ስላለው ልዩነትም ዚተብራራ ነገርም ዚለም።
ለብሔር፣ ብሔሚሰብና ሕዝብ ዹሰጠው ዹወል ትርጉም በአንቀጜ 39ፀ 5 ተቀምጧል። "...ሰፋ ያለ ዚጋራ ጠባይ ዚሚያንጞባርቅ ባሕል ወይም ተመሳሳይ ልምዶቜ ያላ቞ው፣ ሊግባቡት ዚሚቜልሉበት ዚጋራ ቋንቋ ያላ቞ው፣ ዚጋራ ወይም ዹተዛመደ ሕልውና አለን ብለው ዚሚያምኑ...." እያለ ባሕርያ቞ውን ይተነትናል። ተባባሪ ፕሮፌሰር ዮናታን ተስፋዬ ፍሰሀ በዩኒቚርስቲ ኩፍ ዌስተርን ኬፕ ዹሕግ መምህር ሲሆኑፀ በፌደራሊዝም ጉዳዮቜ ላይ በተለያዩ ዹምርምር ሥራዎቜ ይሳተፋሉ። እንደ እሳ቞ው አባባል በሕገ መንግሥቱ ዙሪያ ዹተደሹጉ ውይይቶቜም ቢሆኑ ማነው ሕዝብ?፣ ማነው ብሔሚሰብ?፣ ማነው ብሔር? ለሚለው እቅጩን መልስ አያስቀምጡም። በሕገ መንግሥቱም ቢሆን ይህ ዚተናጥል ትርጉም አልተቀመጠምፀ ቢሆንም ግን... ይላሉ ዮናታን (ዶ/ር) "ቢሆንም ግን ይህ አለመሆኑ ኹሕገ መንግሥቱ አንፃር ብዙም ለውጥ አያመጣም።" ይህንን ሐሳብ ሲያፍታቱትፀ ብሔር ስለሆንክ ይህን ታገኛለህፀ ብሔሚሰብ ስለሆንክ ያንን ታጣለህ ብሎ ዚሚያስቀምጠው ነገር ዹለም ይላሉ። ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ ዩኒቚርስቲ ዹሰላምና ደህንነት ጥናት ተቋም መምህር ና቞ው። ብሔር ማነው? ብሔሚሰብስ? ሕዝብስ? ለሚለው መልሳ቞ው "ዚመጣው ኹጆሮፍ ስታሊን ነውፀ ሶሻሊስታዊ አስተሳሰብ ነው ነው" ይላሉ። ለሳ቞ው ይህ አብዛኛውን ጊዜ አምባገነኖቜ ሕዝቡን ኹፋፍሎ ለማስተዳደር ዚሚጠቀምበት መሣሪያ ነው። • 'ኹሕግ ውጪ' ዚተዋሃዱት አምስቱ ክልሎቜ • "ነገ ክልል መሆናቜንን እናውጃለን" ዚኀጀቶ አስተባባሪ ለዶ/ር ዮናስ ዚኢትዮጵያ ሕዝብ እንጂ ዚኢትዮጵያ ሕዝቊቜ ብሎ ነገር ራሱ እምብዛም ስሜት ዚሚሰጥ ነገር አይመስልም። "ብሔርን ኹፍ አድርገው፣ ብሔሚሰብን መካኚለኛ አድርገው ሕዝብን ዝቅተኛ አድርገውፀ አንዳንዎም አስደንጋጭ ቅጥያዎቜን ሁሉ ጹማምሹው ሕዳጣንፀ አናሳ ብሔሚሰብ ዹሚሉ ስሞቜም ይሰጣሉፀ ሁሉም ግን ሕዝብን ለመኹፋፈል ዹተደሹጉ ናቾው" ይላሉ። በሕገ መንግሥቱም ላይ አንድ ብሔር፣ ብሔር ስለሆነ ይህ ይገባዋል፣ ብሔሚሰብ ደግሞ ስለሆነ ያ ይገባዋል ዹሚል ዹተቀመጠ ነገር ዹለም ዚሚሉት ተባባሪ ፕሮፌሰር ዮናታንፀ ሕገ መንግሥቱ መብትና ጥቅም ሲሰጥ በእነዚህ መካኚል ምንም ልዩነት እንዳላስቀመጠ ያትታሉ። ታዲያ ልዩነት ኹሌለ ዚክልልነት ጥያቄ ገፍቶ ዚሚመጣው ለምንድን ነው? ዹሕግ ምሁሩ ዮናታን (ዶ/ር) መልስ አላ቞ውፀ ክልል እንሁን ዹሚሉ ወገኖቜ ራሳ቞ውን ብሔር ነን ብለው ያስባሉ። ነገር ግን ሕገ መንግሥቱ ክልልነት ዚምታገኘው ብሔር ስለሆንክ ነው፣ ወይንም ደግሞ ብሔሚሰብ ስለሆንክ ክልልነት አይገባህም ዹሚል ነገር ዚለውም። ዚትኛውስ ነው አቃፊ? ብሔር ውስጥ ነው ብሔሚሰቊቜ ያሉት? ሕዝቊቜስ ብሔር ውስጥ ናቾው? ወይስ ብሔሚሰቊቜ ውስጥ ናቾው? ለሚለው ጥያቄም ሕገ መንግሥቱ ልዩነት እንደሌለው ዮናታን (ዶ/ር) ይናገሩና "ዹሕገ መንግሥቱ ትልቁ ግርታ ያለው እዚያ ላይ ነው" ይላሉ። በርግጥ ይላሉ፣ አንዳንዶቹ ዚመብት ጥያቄ ሲያቀርቡ ራሳ቞ውን ብሔር አድርገው ይወስዳሉፀ አንዳንዶቹ ደግሞ ብሔሚሰብ አድርገው ይወስዳሉ። በማለት እንደ ሲዳማ ያሉ ትላልቅ ማህበሚሰቊቜ ራሳ቞ውን እንደ ብሔር አድርገው ነው ዚሚወስዱትፀ እንደ ስልጀ ያሉት ደግሞ ባለፈው መብታ቞ውን ሲጠይቁ እንዳስቀመጡት ራሳ቞ውን እንደ ብሔሚሰብ አድርገው ነው ዚቆጠሩት ይላሉ። ታዲያ በምን መስፈርት ነው እነዚህ ወገኖቜ አንደኛው ራሱን ብሔር ሌላኛው ብሔሚሰብ ያለው? ቢባል ግልፅ ያለ ነገር ዹለም ባይ ናቾው ዹሕግ ምሁሩ። • በሲዳማ ክልልነት ጉዳይ ህዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ ዚምርጫ ቊርድ ወሰነ ዚብሔሚሰቡ ሊቃውንትም ራሳ቞ውን በአንደኛው ሥር ያካተቱበት መስፈርት ዚማህበሚሱ ቁጥር ይሁን ሌላ ምንም ዚሚታወቅ ነገር ዚለም። ሕገ መንግሥቱ ግን ክልል ዹመሆን መብትን ዹሚሰጠው ለሁሉም ነው ይላሉ ዶ/ር ዮናታን። ለብሔርም፣ ለብሔሚሰብም፣ ለሕዝብም። ስለዚህ በሕገ መንግሥቱ መሠሚት ክልል ለመሆን ቁጥር መስፈርት አይደለም። ታዲያ ሕገመንግሥቱ ለማንኛውም አካል ክልል ዹመሆን ጥያቄን በዚህ መልክ አቅልሎ ኹነበር እንዎት እስኚዛሬ ድሚስ ጥያቄዎቜ ሳይቀርቡ ቀሩ? ለዶ/ር ዩናታን እስኚዛሬ አልቀሚቡም ብሎ በሙሉ አፍ መናገር ኚባድ ነው። ምክንያቱም ዚሲዳማ ዚክልልነት ጥያቄ ኚበፊት ጀምሮ ዹነበሹ ነው ይላሉ። እንደውም በማለትፀ ዚሲዳማ ዞን ምክር ቀት ተገንጥዬ ዚራሎን ክልል እመሰርታለሁ ብሎ ወስኖ ጥያቄ ለፌደራል መንግሥቱም አቅርቩ ነበር። ነገር ግን ዚፌደራል መንግሥቱ ያስገቡትን ጥያቄ እንዲተዉት እንዳደሚጋ቞ው ያስታውሳሉ። "ራሳ቞ው ያስገቡትን ጥያቄ ድጋሚ ደብዳቀ በመጻፍ ጥያቄያቜንን አንስተናል። ጥያቄው በዚህ ጊዜ መቅሚብ ዚነበሚበት አልነበሹም በማለት ደብዳቀ አስገብተዋል።" ስለዚህ ኹዚህ በፊት ጥያቄዎቹ ይነሱ ዹነበሹ ቢሆንም፣ ጥያቄዎቹን ለማስተናገድና ለመመለስ ግን ፍቃደኝነት አልነበሹም ሲሉ ዚድሮና ዘንድሮን ፖለቲካዊ ድባብ ልዩነት ያብራራሉ። አሁን ለምን? ለዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) በአሁኑ ሰዓት ዚክልልነት ጥያቄ ኚተለያዩ አቅጣጫ እዚተሰማ ያለው በኢትዮጵያ ውስጥ በአሁኑ ሰዓት ዚብሔር አክራሪነት ስለገነነ ነው። ዚኢትዮጵያ አገሹ መንግሥትም ይላሉ ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር)ፀ መሰሚቱን በብሔር ማንነት ላይ ማድሚጉ ዚመጚሚሻው ውጀት ይህ እንዲሆን አድርጎታል። "በማንነት ላይ ዹተመሰሹተው ፌደራሊዝም መጚሚሻው ይኾው ነው። በምሥራቅ አውሮጳ ዚታዚውም ይኾው ነው።" • ኢህአዎግን ያጣበቀው ሙጫ እዚለቀቀ ይሆን? ነገሩን ኚፖለቲካው ምኅዳር መስፋትና መጥበብ ጋ ዚሚያያይዙት ተባባሪ ፕሮፌሰር ዮናታንፀ ቀደም ሲል ቡድኖቹ ጥያቄውን ለመግፋት ዚሚቜሉበት ዚፖለቲካ ሁኔታ አልነበሹም ይላሉ። "ፖለቲካው ኚፈትፈት ብሏል። ጠንካራ ዹነበሹው ዚፓርቲው ዲሞክራሲያዊ ማዕኚላዊነት አሁን ብዙም ዚለምፀ ስለዚህ እነዚህ ቡድኖቜ ጥያቄያ቞ውን ማንሳት እንደሚቜሉ፣ ገፍተው ቢሄዱ ዚሚያስፈራራ቞ው፣ ዚሚጫና቞ው ኃይል ብዙም እንደሌለ ስለሚሰማ቞ው በአሁኑ ሰዓት ክልል እንሁን ዹሚል ጥያቄ ሊበራኚት ቜሏል" ይላሉ። ክልል በመሆን ዹሚገኘው ትርፍ ምንድነው? ዚሚታጣውስ? "ክልልነት ለማህበሚሰቡ ዚተሻለ ሥልጣን ይሰጣል" ይላሉ ዶ/ር ዮናታን። አብዛኛው ክልል ዚበጀት ድጎማ ዚሚያገኘው ኚፌደራል መንግሥቱ ነው። ክልሎቜ ኚፌደራል መንግሥቱ ያገኙትን ገንዘብ እነርሱ ደግሞ ለዞኖቜ ያኚፋፍላሉ። አሁን ባለው ሁኔታ ሲዳማ ክልል ስላልሆነ በቀጥታ ዚገንዘብ ድጋፍ አያገኝም። ክልል ሲሆን ግን ዞን ሲሆን ኚሚያገኘው ዚተሻለና ኚፌደራል መንግሥቱም በቀጥታ ዚገንዘብ ድጋፍ ያገኛል። ኚበጀት ባሻገርም ራስን ዚማስተዳደሩን ሥልጣን ዹመጠቀም መብቱ ኹፍ ያለ ይሆናል። ዹዞን ስልጣን ዹነበሹው ወደ ክልልነት ኹፍ ሲል ሕገ መንግሥታዊ ሥልጣኑም አብሮ ያድጋል። ሕገ መንግሥቱ ዚሚሰጣ቞ውን ሥልጣኖቜ በቀጥታ ዚመጠቀም፣ ፍርድ ቀቶቜ፣ ዚጞጥታና ዚፖሊስ ተቋማትን ማቋቋም ይቻላል። ክልልነት ለጠዹቀው ሁሉ ቢታደል ምንድነው ቜግሩ? ዶ/ር ዮናታን ነገር ግን ክልልነት ማደል ኹጀመርን ጥያቄው መቆሚያ አይኖሹውም ሲሉ ፍርሀታ቞ውን ይገልፃሉ። ኢትዮጵያ ኚሰማኒያ በላይ ብሔር ብሔሚሰቊቜና ሕዝቊቜ ያሉባት ሀገር ናት ዚሚሉት ምሁራኑፀ ዚክልልነት ጥያቄ ላነሳው ሁሉ ዚፌደራል መንግሥት እያነሳ ቢሰጥ ክልል ለመሆን ኢኮኖሚያዊ ብቃት ዹሌላቾው ቊታዎቜ ክልል እንዲሆኑ ማድሚግ ይሆናል ይላሉ። ይህ ደግሞ ክልል ቢሆኑ እንኳ ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግሥት ድጋፍ ላይ ዹሚንጠለጠሉ አካባቢዎቜን ይፈጥራል። ስለዚህ ካሉን ኹ80 በላይ ብሔሚሰቊቜ፣ ብሔሮቜና ሕዝቊቜ መካኚል በፖለቲካ፣ በምጣኔ ሀብት፣ በሰው ኃይልም ለክልልነት ብቁ ዹማይሆኑ እንዳሉ ግልፅ ነው። • ኢህአዎግ ኚአባል ፓርቲዎቹ መግለጫ በኋላ ወዎት ያመራል? ራስን በራስ ዚማስተዳደር መብት ሕገ መንግሥታዊ ነው ያሉት ዶ/ር ዮናታንፀ ያ መብት ግን በተለያዚ መልኩ ወደ ሥራ ሊገባ ይቜላል ሲሉ ያስሚዳሉ። ክልል በመሆን ራስን በራስ ዚማስተዳደር ሕገ መንግሥታዊ መብት ማሚጋገጥ ይቻላል። ነገር ግን ያ ብ቞ኛ መንገድ አይደለም። ኹክልል በታቜ ዝቅ ያሉ ዞንም ሆኑ ወሚዳዎቜ ራስን በራስ ዚማስተዳደር መብት ተደርጎ ሊተሹጎም ይቜላል ሲሉ ይናገራሉ። "ስለዚህ ሰማኒያ ብሔር ባለበት አገር ሁሉም ክልል ይሆናል ብሎ ማለት አስ቞ጋሪ ነው። ያ እንዳይሆን ግን ዚሚያግድ ሕጋዊ መሰሚት ዚለም።" አሁን ባለውም ሕገ መንግሥት ሁሉም ብሔር ብሔሚሰቊቜና ሕዝቊቜ ክልል ዹመሆን መብት አላቾው ሲሉ ይደመድማሉ ዶ/ር ዮናታን። ሌላ ዹተቀመጠ ዚኢኮኖሚ፣ ዚፖለቲካ፣ ዚጂኊግራፊ መስፈርት ወይንም ቅድመ ሁኔታ ዚለም። መብት አለፀ ግዎታ ዹለም ሕገ መንግሥቱ አንቀጜ 47 ዚክልልነት ጥያቄ ለሚያነሱ መብት ይሰጣል። ይህንንም ይዘሚዝራልፀ ነገር ግን ዚፌደራል መንግሥቱም ሆኑ፣ ክልሉ ይህንን ጥያቄ መቀበል አለባ቞ው ብሎ አያስቀምጥም። ስለዚህ እዚህኛው አንቀጜ ላይ መብት አለፀ መብቱ ግን ዹተቀመጠው ሌሎቹ መቀበል አለባ቞ው ኹሚል ግዎታ ጋር እንዳልሆነ ያስሚዳሉ። ሁለተኛ ነጥብ ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት ቀርበው ባደሚጉት ንግግር ላይ ዚጠቀሱት ዹሕገ መንግሥት ማሻሻያ ሐሳብ ነው። በሕገ መንግሥቱ አንቀፅ 47፣3 መሠሚት ክልሎቜ ዚክልልነት ጥያቄ አቅርበው ተቀባይነት እንዳገኙና ሕዝበ ውሳኔው በአብላጫ ድምፅ ኹተጠናቀቀ ወዲያውኑ ዚፌደሬሜኑ አካል ይሆናሉ። ነገር ግን እዛው አንቀፅ ላይ 47፣1 በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉትን ክልሎቜ በአጠቃላይ ይዘሚዝራል። እነዚህ ክልሎቜ ዘጠኝ ሲሆኑ አዲስ ዚሚመጣ ክልል እዚህ ዝርዝር ውስጥ ዚግድ መግባት አለበት። እዚያ ውስጥ ለመግባት ደግሞ አንቀፁ መሻሻል ወይንም መቀዹር አለበት ይላሉ ዹሕግ ምሁሩ። • “ዚመኚላኚያው በአደባባይ ሚዲዎቜን እኚሳለሁ ማለት አስፈሪ ነው” ዶ/ር አብዲሳ ዘርዓይ ዶ/ር ዮናስ አዳዬ በበኩላ቞ውም ሕገ መንግሥቱን ሳያሻሜሉ አዳዲስ ክልል መመስሚት ያለውን ጊስ ያስሚዳሉ። በቅድሚያ ሕገ መንግሥቱ ላይ ዚተቀመጡት ዘጠኝ ክልሎቜ ጉዳይ መሻሻል አለበት ሲሉም ይመክራል። አዲስ ዚሚመጡ ክልሎቜ ኚሌሎቹ እኩል ሆነው ዚፌደራል መንግሥቱን ሥልጣን እንዲካፈሉ ራሳ቞ውን እንዲያስተዳድሩ ደግሞ ዹሕገ መንግሥት እውቅና እንዲኖራ቞ው ይገባል ዚሚሉት ዮናታን (ዶ/ር) ያ እንዲሆን ደግሞ አንቀፅ 47፣1 መሻሻል አለበት። ዹሕገ መንግስት ማሻሻያ ለማድሚግ ደግሞ ዚራሱ ሂደት አለው። ሕገ መንግሥት እንዲቀዚር ዚክልሎቹን ሁለት ሊስተኛ ድጋፍ ማግኘት፣ ዚፌደሬሜን ምክር ቀትና ዚሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት ድምፅ መስጠትና መደገፍ አለባ቞ው። ስለዚህ ይህ ክልል ሙሉ በሙሉ ክልል ተብሎ ሕገ መንግሥታዊ እውቅና እንዲሰጠው ሕገ መንግሥቱ መቀዹር አለበት ማለት ነው። ሕገ መንግሥቱ እንዲቀዚር ደግሞ ዚሌሎቹ ድጋፍ ያስፈልጋል። በሁለቱ ምሁራን አመለካኚት ይህ ዹሕገ መንግሥት ማሻሻያ ሂደት ግምት ውስጥ ሲገባ አሁን ባለው ሁኔታ ጥያቄ ስለቀሚበና ድጋፍ ስለተገኘ ብቻ ክልል መሆን ይቻላል ብሎ መደምደም አስ቞ጋሪ ይሆናል። ዚሲዳማ ክልልነት ጥያቄ ሲፀድቅ ዚሌሎቹስ? በሕጉ መሰሚት ካዚንፀ ዚሲዳማ ዞን ማሟላት ያለበትን አሟልቶ ሕዝበ ውሳኔ (ሪፈሚንደም) ተካሂዶ ዚሚያስፈልገው ድምፅ ቢገኝም እንኳ ሕገ መንግሥቱ እስካልተሻሻለ እና ሲዳማ አንዱ ክልል መሆኑ ሕገ መንግሥቱ ላይ እስካልሰፈሚ ድሚስ ክልል ነው ማለት ያስ቞ግራል ይላሉ ዮናታን (ዶ/ር)። ኚዚያ በፊት ያለውን ሂደት ማቆም አይቻልም ዚሚሉት ዶ/ሩፀ ለዚህ ነው ዚራሳ቞ውን ክልል እንዲኖራ቞ው በሚጠይቁት ዚሲዳማ ማህበሚሰብ ተወካዮቜ መካኚል፣ በፌደራል መንግስቱና በደቡብ ብሔር ብሔሚሰቊቜ ክልል መካኚል ውይይት ዚሚያስፈልገው ይላሉ። • "ኢትዮጵያዊነ቎ን ያገኘሁት ሙዚቃ ውስጥ ነው" አቚቫ ደሮ ውይይቱ አሁን ዚክልልነት ጥያቄ ተነስቶ ሙሉ ድጋፍ ካገኘ በዲሞክራሲያዊ፣ መንገድ ዹቀሹበውን እና ዹተገለጠውን ሀሳብ ማክበር ያስፈልጋል። ነገር ግን ሌሎቜ ኚሲዳማ ክልል መሆን ጋር ዚሚያያዙ ጥያቄዎቜ ካሉ እነርሱን በተመለኚተ፣ በተለይ ደግሞ ዚሌሎቹን ሁኔታ ግምት ውስጥ ያስገባ ፣ ዚአገሪቱን ሁኔታ ጥቅምና ጉዳት ግምት ውስጥ ያስገባ ውይይት ተደርጎ፣ ማመቻመቜ እና ስምምነት ላይ መድሚስ አለበት ሲሉ ይመክራሉ። ዚሲዳማ ማህበሚሰብ ተወካዮቜም ኹክልሉ እና ኚፌደራል መንግሥቱ ዚሚመጡ ስጋቶቜን መጋራትና ለድርድር ዝግጁና ክፍት መሆን አለባ቞ው ሲሉም ይመክራሉ። ኚአንድ ክልል ጋር አብሮ በሚኖርበት ጊዜ ዚሚያገገናኝ ብዙ ነገር እንዳለ ሁሉ ሲለያዩም ዚሚያነጋግር ነገር ይኖራሉ በማለት ሲዳማ ውስጥ ስላሉ ዚሀብት ክፍፍሎቜ፣ ሲዳማ ውስጥ ስለሚኖሩ ሌሎቜ ማህበሚሰቊቜ፣ ስለ ሲዳማ ክልል ድንበር፣ ውይይት ብቻ ሳይሆን ስምምነትም ላይ ሊደሚስባ቞ው ይገባል ሲሉ ያስቀምጣሉ። ቀጣይ ፈተናዎቜ ምንድናው? ዹሕግ ምሁሩ ዮናታን (ዶ/ር) ክልል ዹመሆን ጥያቄ እና ዚሚሰጡ መልሶቜ ሌሎቜ ተመሳሳይ ጥያቄዎቜ እንዲነሱ በሩን ወለል አድርጎ እንዳይኚፍተው ስጋት አላ቞ው። ዚሚነሱ ቀጣይ ጥያቄዎቜ ቀጣይ ዹመሆን እድላ቞ው ሰፊ ነው ዚሚሉት ዶ/ር ዮናታንፀ እነዛን ጥያቄዎቜ እንዎት መፍታት ይቻላል? ዹሚለው መታዚት አለበት ሲሉ ይመክራሉ። "ዚሲዳማን ጉዳይ ዚምንመልስበበት መንገድ ዚሌሎቜን ጥያቄዎቜን ዚምናስተናግድበትን መንገድ ይበይናል" በማለትም ዹሌሎቾንም አገራት ልምድ ማዚት መልካም መሆኑን ይመክራሉ። • "ኢስላማዊ ባንክ ለኢትዮጵያ ምን ይፈይዳል?" "ሕንድ እንዲህ ዓይነት በርካታ ጥያቄዎቜ አስተናግዳ ታውቃለቜ። ነገር ግን ሕንድ ማዕኹላዊ መንግሥቱ ነው ለጥያቄው መብት መስጠትዚሚቜለው" በማለት በሕንድ በዚህ መንገድ ኚአንድ ክልል ብቻ ስድስት አዳዲስ ክልሎቜ መፈጠራ቞ውን በመጥቀስ ኚሌሎቜ አገራት ልምድ መቅሰም አስፈላጊነቱን ያሰምሩበታል።
49220661
https://www.bbc.com/amharic/49220661
በአውሮፓ ዚኢትዮጵያዊያን ፌስቲቫል፡ ሙዚቃ፣ ኳስ፣ ፍቅርና ቡጢ..
በጋ ፈሚንጆቹን ያፈካ቞ዋል። ኮምጫጫ አውሮፓዊ ለማያውቀው መንገደኛ ሳይቀር ፈገግታ ዚሚመጞውትበት ጊዜ ነው። ለሀበሟቜስ ቢሆን? በጋው ዚፌሜታ ነው። በሚዶ ያቆፈነው በጓንት ዹተጀቩነ እጅ እንጀራ ለመጠቅለል ዚሚፍታታበት ወቅት ነው። ካፖርታና ጋቢ ወዲያ ዚሚሜቀነጠርበት ወቅት ነው። በኹፊል ዕርቃን መዘነጥ ዚሚያስቜል በቂ ንዳድ አለ።
ኹሁሉ በላይ ዓመታዊው ዚባህልና ስፖርት አውደፌሜታ አለ። ቁርጥ አለፀ በቂቀ ያበደ ሜሮ አለፀ ጎሚድ ጎሚድ አለ። ቡናው ይንኚሞኚሻል እጣኑ ይንቊለቊላል ፀ ዹአገር ሰው ኹዚህ በላይ ምን ይሻል? ይህ አገር ቀት እዚኖሚ እንግሊዝኛ ለሚቀናው ሰው ‹‹ሶ ዋት?›› ዚሚያስብል ሊሆን ይቜላል። ኹአገር ለራቀ ሰው ግን ትርጉሙ ራስ ዳሜን ነው። ለዚህም ነው ለዓመታዊው ዚሐበሟቜ ‹‹መካ›› በዚዓመቱ በሺዎቜ ዚሚተሙት፡፡ ዘንድሮ ተሹኛዋ ዙሪክ ነበሚቜ። እጅግ አምሮባት ተኩላ ነበር እንግዶቿን ዚጠበቀቜው። እርግጥ ነው በነዚህ መድሚኮቜ ላይ ሀበሟቹ ዚሚገናኙት ለሳቅ ለጚዋታ ነው። ዚሚጠራሩት ለእስክስታና ፌሜታ ነው። ሆኖም ክትፎና ቁርጥ ቀማምሰው ሲጚርሱ ቡጢ ይቀማመሳሉ። መነሻው ምንም ሊሆን ይቜላል። በሐበሟቜ መንደር ግን ጞብ ጠፍቶ አያውቅም። በዙሪክ ይህ ባይሰተዋልም በስቱትጋርት ሆኗል። •"እና቎ ካልመጣቜ አልመሹቅም" ኢዛና ሐዲስ ኚማንቜስተር ዩኒቚርስቲ እንዎት እጅግ ዹተነፋፈቀ ዹአገር ልጅ ለያውም በሰው አገር፣ ለያውም ለሳቅ ለጚዋታ ተጠራርቶ ቡጢ እንደሚሰነዛዘር መተንተን ዚቻለ ሊቅ ለጊዜው አልተገኘም። ብቻ ዹአገር ልጆቜ በዚዓመቱ ተሰባስበው ዚ‹‹ፍቅር ቡጢ››ን እንካ ቅመስ-እንቺ ቅመሜ ሲባባሉ ዓመታት አስቆጥሚዋል። ለምሳሌ ዚዛሬ ዓመት ዚፌሜታው አስተናጅ ስቱትጋርት ነበሚቜ። ቎ዲ አፍሮ መጥቶ አፍሮ ተመልሷልፀ ሳይዘፍን። ንብሚት ወድሟል። ዚአዳራሜ መስታወት እንዳልነበር ሆኗል። ዹጀመርን ፖሊስ ‹‹ኀሎሄ! ዘንድሮ ምን ጉድ ላ'ክብን›› ብሏል። ጞቡ ኚእኛም አልፎ ወንድም ኀርትራዊያንን ያሳተፈ ነበር። ዚቢራ ጠርሙስ ኚአንድ ኢትዮጵያዊ እጅ ተምዘግዝጎ ሌላ ኢትዮጵያ ዚራስ ቅል ላይ አርፏል። ሀበሟቜ ሲገናኙ ‹‹አብሿ቞ው›› ይነሳል መሰለኝ ፍቅራ቞ው በጞብ ካልደመቀ ። ኢትዮጵያዊያኑ ወደ ዙሪክ ዚኚተሙት ይህንኑ ዚጞብ ትዝታ ይዘው ነበር። ዙሪክ አላሳፈሚቻ቞ውም። ለሰላሙ ቅድሚያ ሰጥታ አጫውታ፣ አዝናንታ አፋቅራ ሞኝታ቞ዋለቜ። በአሉታዊነቱ ስቱትጋርት እንደ ምሳሌ ተነሳ እንጂ፣ ሮም በ2012 ‹‹ዚፌዎሬሜኑን ገንዘብ ይዘው ተሰውሚዋል›› በሚሉና ‹‹እንዲያውም አዘጋጅተን ኚሰርን›› በሚሉት መሀል መራር ጞብ ነበር። ደግነቱ ዚሮም ጞበኞቜ ዘንድሮ በዙሪክ ይቅር ለእግዛብሔር ተባብለዋል። በ2014 ሙኒክ ላይም ምክንያቱ መናኛ ዹሆነ ዱላ መማዘዝ ነበር። ‹‹ሐበሻ ድሮም አብሮ መብላት እንጂ አብሮ መሥራት ›› ዹሚል ተሚት ዚሚያስተርቱ አጋጣሚዎቜ በርካታ ነበሩ። ሆኖም ይህን ሁሉ ዓመት ኚጞብና መወነጃጀል መራቅ ለምን አልተቻለም? ዹሚለው ጥያቄ ዛሬም ሙሉ በሙሉ ምላሜ አላገኘም። አንድ ሁለት ምክንያቶቜን መዘርዘር ግን ይቻላል። አንዱ በዚዝግጅቶቹ ውስጥ ዹአገር ቀቱ ፖለቲካ ዚሚያጠላው ጥላ ሰፊ መሆኑ ነው። ሌላው በጎ ፈቃድ እንጂ ዚአመራር ክህሎት በሌላቾው ሰዎቜ ትልቅ ድግስ መሰናዳቱ ዚሚፈጥሚው ትርምስ ነው። ሊስተኛው ለጥቅም መንሰፍሰፍ ነው። •ዚጄኔራል ደምሮ ቡልቶ ልጅ 'መራር' ትዝታ ‹‹እንዲህ ዓይነቱን ሺህዎቜ ዚሚታደሙበት አውደ ፌሜታ ለማሰናዳት ኚመቶ እስኚ ሁለት መቶ ሺህ ዩሮ ፈሰስ መደሹጉ አይቀርም›› ይላሉ ወጪውን ዚሚያውቁት። ይህንን ወጪ ለመመለስ፣ ብሎም በትርፍ ለመንበሜበሜ አድብቶ ዚሚጠብቀው ብዙ ነውፀ በዚህ መሀል ትርምስ ይፈጠራል። ኹፍተኛ ዚጥቅም ግጭት ይነሳል። ‹‹ስልጡን አገር ዚሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን በሰለጠነ መንገድ መነጋገር ይሳና቞ዋል። በሰለጠነ መንገድ ሂሳብ ኊዲት አያስደርጉም። በሰለጠነ መንገድ ወጪና ገቢ አያሰሉም። መጚሚሻው ዚማያምሚው ለዚህ ይመስለኛል›› ይላል በዓመታት ውስጥ ባዚው ነገር ተስፋ ቆርጩ ራሱን ኚአዘጋጅነት ተሳትፎ ያገለለ ወጣት ለቢቢሲ። ዚዙሪኩ መሰናዶ ግን በሁሉም መለኪያ ዚተሻለና ዚተዋጣለት መሆኑ ለብዙዎቜ መልካም ስሜትን ፈጥሯል። ለሌሎቜ ቀጣይ አዘጋጅ ቡድኖቜና ኚተሞቜም ምሳሌ መሆን ዚሚቜል ነበር። ኢትዮጵያ መግባት ዚማይቜሉ ኢትዮጵያዊያን ኹደርግ ጀምሮ ኚዚያም ቀደም ብሎ ኹአገር ዚወጡ ኢትዮጵያዊያን አሉ። በአውሮፓ ዚሚኖሩ ዚድሮ ዚብሔራዊ ቡድን ተጚዋ቟ቜ ብዛታ቞ው ለጉድ ነው። ይህ ዓመታዊ አውደ ፌሜታ ታዲያ ለአንዳንዶቜ ዚፌሜታ ያህል ፌዝ አይደለም። ዹምር ጉዳይ ነው። ዹአገር ጉዳይ ነው። ኢትዮጵያን ናፍቀው ኢትዮጵያ መግባት ዚማይቜሉ በርካታ ዜጎቜ ነበሩ። በፖለቲካም ይሁን በያዙት ዚስደተኛ ወሚቀት ምክንያት። ስለዚህ ኢትዮጵያዊን ባይሚግጡም ‹‹ዚኢትዮጵያን ኮፒ›› መርገጥ ይፈልጋሉ። በአውሮፓ ዚኢትዮጵያ ኮፒ ደግሞ ይህ ዓመታዊ አውደ ፌሜታ ብቻ ነው። በዚህ ምክንያት ዝግጅቱን እንደዋዛ አያዩትም። በማንኚሜኚሻ ዹሚቆላ ቡና እጅ ዚሚያስቆሚጥም ቁርጥ ምራቅ ዚሚያስውጥ ክትፎ፣ ኹሾክላ ዹሚንቆሹቆር አገርኛ ሙዚቃ ኚኢትዮጵያ ብዙ ሚሊዹን ማይሎቜ ርቆ ለሚኖር ሰው ቀልድ አይደለም፡፡ መዝናኛ ብቻ አይደለም። አገር ዚመግባት ያህል ነው። ለነዚህ ኢትዮጵያዊያ ዚአገርን፣ ዹአገር ልጅን ናፍቆትም ለመወጣት ሁነኛ ሥፍራ ይኾው መድሚክ ዹሆነውም ለዚሁ ነው። ጎሚቀታሞቜ ቡና ሊጠራሩ ቀርቶ በማይተያዩበት፣ በሁለት ሊስት ሥራ ደፋ ቀና ካላሉ ሕይወት በማይገፋበት፣ ጥሬ ሥጋ መጉሚስ ዜና በሚሆንበት አውሮፓ ኢትዮጵያዊያንን ዚሚያገናኘው ፌስቲቫል ኹተጀመሹ ዘንድሮ 17ኛ ዓመቱን ይዟል። አውሮፓ ውስጥ ኢትዮጵያውያን ዚሚገናኙበት ምናልባትም ብ቞ኛው ፌስቲቫል ነው። ለዚህም ነው ጁላይ 31 እስኚ ኊገስት 2! ብዙ ሺህ ኢትዮጵያውያን በቀን መቁጠሪያ቞ው ላይ በደማቅ ቀለም ያኚበቡት። ቀኑ ሲደርስ ራቅ ካሉቱ እንደ ኖርዌይ እና ስዊዲን በጢያራ በሚሩ። ቀሚብ ካሉቱ ኚጀርመን፣ ኚፈሚንሳይ፣ ኚእንግሊዝ በአውቶቡስ ተሳፈሩ፣ ዚባቡር ትኬት ቆሚጡ፣ ዚመኪና቞ውን ሞተር ቀሰቀሱ። ሆኖም ድንበር ሲደርሱ ስዊዘርላንድ ‹‹ዚማይደሚገውን!?›› አለቜ። ስዊዘርላንድ ኚተቀሩት ዚአውሮፓ አገሮቜ ዚድንበሯን ነገር በዋዛ ባለመመልኚት ትታወቃለቜ። በቂ ዹጉዞ ሰነድ ዹላቾውም ያለቻ቞ውን ኢትዮጵያዊያንን ወደመጡበት መልሳ቞ዋለቜ። ኚእነዚህ መካኚል በዙሪክ ለመጫወት ዚተንቀሳቀሱት ዚፈሚንሳዩ ኢትዮ-ማርሮይ ዚእግር ኳስ ቡድን እና ኚኢትዮ-ፍራንክፈርት ሁለት ቡድኖቜ አንዱ፣ እንዲሁም ዹጀመርኑ ዳርምሜታት ዚእግር ኳስ ቡድን አባላት በኹፊል ይገኙበታል። አብዛኞቹ በሚኖሩበት አገር ጊዜያዊ ዚመኖሪያ ፍቃድ ተሰጥቷ቞ው ዚዜግነት ማሚጋገጫ ወሚቀት ዚሚጠብቁ ወይም ዚጥገኝነት ጥያቄ አቅርበው ምላሜ በመጠባበቅ ላይ ያሉ ወይም ጭርሱኑ ያላገኙ ና቞ው። ዚፌዎሬሜኑ ፕሬዝዳንት አቶ አሳዚኞኝ ጥላሁን ለቢቢሲ እንደተናገሩት እንግሊዝ ኹ40ሺ ዹሚልቁ ኢትዮጵያዊያን ዚሚገኙባት አገር ሆኖ ነገር ግን ይህ ፌስቲቫል እንግሊዝ ዚማይዘጋጅበት አንዱ ምክንያት እንዲህ ዓይነቱ ቜግር እንዳያጋጥምና ኢትዮጵያዊያኑ እንዳይንገላቱ በመስጋት እንደነበር ያስሚዳሉ። ‹‹ይህ ዝግጅት ለብዙ ኢትዮጵያዊያን ዓመታዊ ዚሥነ ልቩና ቎ራፒ ዚሚያገኙበት ነው። በጉጉት ዚሚጠብቁት ነውፀ ኚድንበር መመለሳ቞ው ያሳዘነን ጉዳይ ነው›› ይላሉ አቶ አሳዚኞኝ። በዙሪክ ዚፍጻሜ ጚዋታ በሁለት ወጣት ደጋፊዎቜ መጠነኛ ጠብ ኚመፈጠሩ ውጭ ሰላማዊ ሆኖ ተጠናቋል ፌስቲቫሉ ሲጠነሰስና ዛሬ ፌስቲቫሉ እንደ ጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጠር 2001 ላይ ሲጀመር ኚአንድ ቀን ዚእግር ኳስ ግጥሚያ ዹዘለለ አልነበሚም። 2003 ላይ ግን ዚቀድሞ እግር ኳስ ተጫዋ቟ቜ ማለትም ግርማ ሳህሌ፣ ዩሀንስ መሰለ፣ ኹበደ ኃይሌና ሌሎቜምፀ በተዋቀሹ ሁኔታ ዚሚንቀሳቀስ ፌደሬሜን መመሥሚታ቞ውን በአውሮፓ ዚኢትዮጵያውያን ዚባህልና ዚስፓርት ፌደሬሜን ዚሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዳንኀል ብስራት ይናገራል። ፌስቲቫሉ በተጀመሚበት ወቅት አውሮፓ ውስጥ ዚሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እንደዛሬው አልተበራኚቱም ነበር። ዚእግር ኳስ ቡድኖቹ በቂ ኢትዮጵያዊ ተጫዋቜ ስለማያገኙ አውሮፓውያንን ያካትታሉ። ያኔ ፌስቲቫሉ እንደዛሬው ብዙ ኢትዮጵያውያን ታዳሚዎቜም አልነበሩትም። "ኹ2007 ወዲህ ዚሊቢያ መንገድ ሲኚፈት ወጣቱ ግልብጥ ብሎ ወደ አውሮፓ መጣ። እዚያ ዚሚኖሩ ህጻናትም እያደጉ ዚእግር ኳስ ቡድኖቜን መቀላቀል ጀመሩ። በጣም ጠንካራ ኳስ መጫወት ዹተጀመሹው ኚዚያ ወዲህ ነው" ይላል ዳንኀል። ባለፈው ዓመት ፌስቲቫሉ ዚተካሄደው በጀርመኗ ስቱትጋርት ነበር። ኚዚያ በፊት ሮም፣ ጄኔቭ፣ ስቶኮልም፣ አምስተርዳምና ሌሎቜም ዚአውሮፓ ኚተሞቜ ፌስቲቫሉን አስተናግደዋል። አውሮፓ ውስጥ ዚሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እግር ኳስ ተጫዋ቟ቜ ባቋቋሟ቞ው ቡድኖቜ መካኚል ዚሚካሄድ ዚእግር ኳስ ግጥሚያ ፌስቲቫሉን ደማቅ ያደርገዋል። ዘንድሮ አበበ ቢቂላ፣ ሻላ እና ቡና ዚተባሉ ዚጀና ቡድኖቜ መቀመጫ቞ውን አውሮፓ ካደሚጉት ቡድኖቜ ጋር ለመፋለም ኚኢትዮጵያ ወደ ዙሪክ አቅንተዋል። በስም ኚሚታወቁት ዚቀድሞ ተጚዋ቟ቜ መካኚል ሳሙኀል ደምሮ (ኩኩሻ)፣ ስንታዚሁ ጌታ቞ው (ቆጬ)፣ ተክሌ ብርሃኔ፣ ቎ዎድሮስ ቊካንዎ፣ ሃብቶም ብርሃኔ፣ ሰይፈ ውብሞት፣ ጌታ቞ው ካሳ (ቡቡ)፣ ኃይሉ አድማሱ (ቻይና)፣ግርማ ሳህሌ ይጠቀሳሉ። በነዚህ ጚዋታዎቜ በዚዓመቱ ይገኛሉ። በዘንድሮው ዚሊስት ቀን ፌስቲቫል ኚአምስት ሺህ እስኚ አስር ሺህ ሰዎቜ ይገኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ዚፌስቲቫሉ አዘጋጅ ዹሆነው ኢትዮ-ዙሪክ ቡድን ፕሬዘዳንት ሙሉጌታ በዹነ በመክፈቻው ዕለት ለቢቢሲ ተናግሚዋል። በፌስቲቫሉ ላይ ኢትዮጵያዊያን፣ ኀርትራዊያን እንዲሁም ዚኢትዮጵያን ባህል ዚሚወዱ ዚሌሎቜ አገሮቜ ዜጎቜም ይገኛሉ። ኢትዮጵያዊያንን ያገቡ ዜጎቜ ይህ ዝግጅት ነፍሳ቞ው ነው። ኹሰሜን አሜሪካው ፌስቲቫል ቀጥሎ ኢትዮጵያዊያን ኚኢትዮጵያ ውጪ ዚሚገናኙበት ፌስቲቫል እንደመሆኑ ፍቅርና አንድነትን ዚሚያስተጋቡ ሙዚቀኞቜ መጋበዛቾውን ሙሉጌታ ይገልጻል። ዘንድሮ ጋሜ ማሕሙድና ስለሺ ደምሮ (ጋሜ አበራ ሞላን) ጚምሮ በርካታ ስመ ገናና ድምጻዊያን ሥራዎቻ቞ውን አቅርበዋል። ፌስቲቫሉና ዚዳያስፖራ ፖለቲካ ዚኢትዮጵያ ዚፖለቲካ ራስ ምታት ኚኢትዮጵያ ውጪ ለሚኖሩ ኢትዮጵዊያን ትኩሳት ይለቅባ቞ዋል።አሰላለፋ቞ው ያሞብራል። ልዩነታ቞ው ዚሀበሻ ሬስቶራንት ድሚስ ይዘልቃል። ዚእንቶኔ ብሔር በቀነጠሰው በርበሬ ዚተሰራ ዶሮ ወጥ በአፌም አይዞር እስኚማለት  በፖለቲካ አሰላለፍ ጎራ ተለይቶ መራኮት ዕለታዊ በሆነበት አውሮፓ 'አንዲት ኢትዮጵያ' በሚል ፌስቲቫል ማዘጋጀት ምን ይመስል ይሆን? ዚዚወቅቱ ዚኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ሁኔታስ ፌስቲቫሉ ላይ ጥላውን አላጠላም? ብለን አቶ ዳንኀልን ጠይቀነው ነበር። " ፖለቲካው ፌስቲቫሉን ሊያፈርስ ዚደሚሰበት ወቅትም ነበር" ሲል መልሷል። ዚእግር ኳስ ቡድኖቜ ዚመንግሥት ተቃዋሚና ደጋፊ በሚል እንደሚኚፋፈሉ ካስታወሰ በኋላ በተለይ በምርጫ 97 ሰሞን ዚተካሄደውን ዚእግር ኳስ ግጥሚያ ያሞነፈው ቡድን አባላት በፖለቲካ አቋም ልዩነት ምክንያት አኩርፈው ዋንጫ ሳይቀበሉ ወደ መጡበት አገር መመለሳ቞ውን እንደ አብነት ያነሳል። "ኚፖለቲካ ጋር ግንኙነት ያላ቞ው መገናኛ ብዙኃን ሲመጡ እንደ ፌደሬሜን ዚማስተናገድ ግዎታ አለብን ስንል ዹሚቃወሙ አካላት አሉ። ሜዳ ላይ ያለውን መንፈስ ይሚብሻል። እነ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ፣ ታማኝ በዚነ፣ ተስፋዬ ገብሚአብ ይመጡ ነበር። ያ አንዳንዶቜ ላይ አሉታዊ ተጜዕኖ ሊፈጥር ይቜላል። ግን ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዚመምጣት መብት አለው። አትምጡ ልንላቾው አንቜልም›› ይላልፀ ያም ሆኖ መድሚኩ ኚፖለቲካ ዚጞዳ ዚባህልና ዚስፖርት ፌስቲቫል ብቻ እንዲሆን አዘጋጆቹ ይተጋሉ። ዹ17ኛው በአውሮፓ ዚኢትዮጵያን ዚስፖርት እና ባህል ፌስቲቫል ሻምፒዮና- ኢትዮ ቡና ፍራንስ ፌስቲቫሉን በዚዓመቱ ማን ያዘጋጀው በሚለው ላይ ሁለት ተሞክሮዎቜ እንዳሉ አቶ ዳንኀል ያብራራል። እንደ ሰሜን አሜሪካው ውድድር ፌዎሬሜኑ ያሰናዳው ወይስ አዘጋጅ አገር? 2017 ላይ ዚፌስቲቫሉ አዘጋጅ ፌደሬሜኑ እንዲሆን ተወስኖ ጣልያን ውስጥ ፌስቲቫሉን ለማካሄድ መሰናዶ ተጀምሮ ነበር። ሆኖም ዚፌደሬሜኑ አመራሮቜ ኚገንዘብ ጋር በተያያዘ ኹፍተኛ እሰጣ ገባ መፈጠሩን ይናገራል። ኹዚህ ዚሮሙ ክስተት በኋላ ፌስቲቫሉ በዚዓመቱ በተለያዩ ዚእግር ኳስ ቡድኖቜ እንዲዘጋጅ ውሳኔ ተላለፈ። በዚህም መሠሚት ዚዘንድሮውን ፌስቲቫል ያዘጋጀው ኢትዮ-ዙሪክ ቡድን ነው። ዚኢትዮ ዙሪክ ቡድኑ ፕሬዝዳንት ሙሉጌታፀ ፖለቲካው ለጊዜው እንዲቆይ ይማጞናል። ወደ ፌስቲቫሉ ዚሚሄዱ ሰዎቜ "ፖለቲካን ማሰብ ዚለባ቞ውም። እንዲያውም እዚያ ሜዳ ላይ ፌስቡክን አጥፍቶፀ ሰላም ተባብሎ መጫወት፣ መብላት፣ መጠጣት፣ መሳቅን ነው ማዚት ዹምንፈልገው" ሲል በበዓሉ መክፈቻ ዕለት ለቢቢሲ ምኞቹን አጋርቷል። አማርኛ ዚሚኮላተፉ ሕጻናት በአውሮፓ ዚኢትዮጵያ ባህል እና ስፖርት ፌስቲቫል አውሮፓ ውስጥ ዚተወለዱ ዚኢትዮጵያ ልጆቜ እነሱን ኚሚመስሉ ልጆቜ ጋር ዚሚገናኙበትም መድሚክ ነው። ብዙዎቹ ታዲያ በግማሜ ኢትዮጵያዊ ካልሆኑ ወላጆቜ ዹተገኙ ና቞ው። በተለይ ኢትዮጵያን ሹግጠው ዚማያውቁ ዚኢትዮጵያዊያን ልጆቜ በእናት በአባታ቞ው ቋንቋ እዚተኮላተፉ ሲያወሩ መስማት አንዳቜ ልዩ ስሜት ያጭራል። በዚዓመቱ ዚሚጋበዙት ኢትዮጵያዊያን ሙዚቀኞቜ ታዳጊዎቹን ኚአገሪቱ ባህል ጋር በመጠኑም ቢሆን ያስተዋውቋ቞ዋል። ‹‹ፌስቲቫሉ ዚአዋቂዎቜ ብቻ መሆን ዚለበትምፀ ለነዚህ ሕጻናት በቂ ትኩሚት መሰጠት አለበት›› ይላል ለዚሁ መሰናዶ ዙሪክ ዹሚገኘው ጋሜ አበራ ሞላ። ዚእግር ኳስ ተሰጥኊ ያላ቞ው ታዳጊዎቜ ዕድለኛ ኹሆኑ ለተለያዩ አገራት ብሔራዊ ቡድኖቜና ክለቊቜ ሊታጩ ዚሚቜሉትም በዚሁ ፌስቲቫል ላይ ነው። በደቡብ አፍሪካ ዚአፍሪካ ዋንጫ ብሔራዊ ቡድናቜን ላይ ዹተሰለፈው ዩሱፍ ሳሊህ ኹዚሁ መድሚክ ዹተገኘ ነው። ፌስቲቫሉን ለመታደም በዙሪክ፣ ክሎተን ስ቎ድዚም ኹተገኙ ኢትዮጵያዊያን አንዷ ዚቀድሞዋ ዚኢትዮጵያ ሬድዮና ቎ሌቭዥን ጋዜጠኛ ቅድስት በላይ ናት። በልጆቜ ክፍለ ጊዜ መርሀ ግብር ዚምትታወቀው ቅድስት ዚምትኖሚው ስዊዘርላንድ ሲሆንፀ ዚኢትዮጵያዊያን ፌስቲቫል ላይ ስትሳተፍ ዚዘንድሮው ዚመጀመሪያዋ ነው። ፌስቲቫሉፀ አውሮፓ ውስጥ ተወልደው በምዕራባውያን ባህል ዚሚያድጉ ልጆቜ ስለ ኢትዮጵያ ዚተሻለ ግንዛቀ እንዲኖራ቞ው ኹፍተኛ አስተዋጜኊ እንደሚያበሚክት ትናገራለቜ። "ስብስቡ ማኅበራዊ ትስስሩን ያጠነክራል። ልጆቜም በጣም ደስተኛ ይሆናሉ። ለምሳሌ ዚጓደኛዬ ቀተሰቊቜ ኹኖርዌይ መጥተው ኚሌሎቜ ልጆቜ ጋር ስለ ስዊዝና ኖርዌይ ባህል ሲያወሩ ነበር።" ኢትዮጵያዊያን በብዛት በሌሉበት አካባቢ ለሚኖሩ ልጆቜ፣ ዚኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ በሚውለበለብበት፣ ዚኢትዮጵያ ቋንቋዎቜ በሚነገሩበት፣ ዚኢትዮጵያ ባህላዊ ምግቊቜ በሚበሉበት ቊታ መገኘትን ዚሚተካ ነገር እንደሌለም ቅድስት ታስሚዳለቜ። ትናንት ምሜት ዚትዝታው ንጉስ ማህሙድ አሕመድን ጚምሮ ታዋቂ ድምጻውያን ሊያዜሙበት ዹነበሹው ኮንሰርት በርካታ ኢትዮጵያውያን በትኬት ሜያጭ ዚቅንጅት ጉድለት ዚተንገላቱበት ነበር ፌስቲቫሉን ማን ያስቀጥለው? አውሮፓ በሮቿን ለስደተኞቜ ባትዘጋም ኹጊዜ ወደ ጊዜ ሜንቁሩ እዚጠበበ ይመስላል። ምናልባትም ለወደፊት ወደ አውሮፓ ዚሚሄዱ ኢትዮጵዊያን ቁጥር ያሜቆለቁል ይሆናል። ይህ መላ ምትፀ አሁን በአውሮፓ ዚሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ዚጀመሩትን ፌስቲቫል ለወደፊት ዚሚሚኚባ቞ው ይኖራልን? ዹሚል ጥያቄ ማጫሩ አይቀርም። ኚኢትዮጵያዊያን እና ኚሌሎቜ አገሮቜ ዜጎቜ ዚሚወለዱ ህጻናት እዚተበራኚቱ መጥተዋል። እነዚህ በኹፊል ብቻ ኢትዮጵያዊ ዹሆኑ ልጆቜ ኚኢትዮጵያዊ ማንነታ቞ው ጋር ዚሚያስተሳስራ቞ው ፌስቲቫል አስፈላጊነት ዚሚታያ቞ው እስኚ መቌ ነው? ሌላው ጥያቄ ነው። ዳንኀል ዚፌስቲቫሉ ቀጣይነት አያጠራጥርም ይላል። አንድም "በቀጣይ ለሚመጣው ትውልድ ብ቞ኛ መገናኛው ይህ ፌስቲቫል ነው" ሲል ያስሚዳል። በልጅነታ቞ው ወደ አውሮፓ ቢሄዱም ዚእግር ኳስ ፌደሬሜኑን ለዓመታት ያገለገሉ ወጣቶቜ መኖራ቞ውም ተስፋ ይሰጠዋል። ዳንኀልፀ አውሮፓ ተወልደው ያደጉ ልጆቜ በፌስቲቫሉ ድምቀት በመማሹክ ኚዓመት ዓመት ቀጠሮ ሲይዙ አስተውሏል። ለነጭ ጓደኞቻ቞ው 'ዚኢትዮጵያ ፌስቲቫል ሄጄ ነበር' ብለው በኩራት እንደሚያወሩም ሰምቷል። እነዚህ ልጆቜ አሁን ያለውን ሥርዓት እንዲሚኚቡ ኹተደሹገ ዚፌስቲቫሉ ዕድሜ እንደሚሚዝም ያምናል።ዚቡናው መዓዛ ሳይጠፋ እስክስታው ሳይለዝዝ፣ ቁርጡ ሳይወደር፣ ሙዚቃው ሳይጎትት ዚዛሬ ዐሥር፣ ሀያ፣ ሠላሳ ዓመት ኢትዮጵያዊያኑ ይገናኙ ይሆን? ኚብዙ ፍቅርና ኚትንሜ ቡጢ ጋ'ም ቢሆን 
51867056
https://www.bbc.com/amharic/51867056
ኬንያ በኮሮናቫይሚስ ዚተያዘ አንድ ሰው ማግኘቷን አስታወቀቜ
ኬንያ ዚመጀመሪያውን በኮሮናቫይሚስ ዚተያዘ ሰው ማግኘቷን አስታወቀቜ። ዚኬንያው ጀና ጥበቃ ሚኒስትር ሙታይ ካግዌ እንደገለፁት በኮሮና ቫይሚስ መያዟ ዹተሹጋገጠው ሎት ኚሳምንት በፊት ኚአሜሪካ ወደ ኬንያ ዚመጣቜ ነቜ።
ግለሰቧ ኚአሜሪካ ወደ ኬንያ ዚመጡት በለንደን አድርገው ሲሆን መጀመሪያ ኬንያ ጆሞ ኬንያታ አውሮፕላን ማሚፊያ እንደደሚሱ ምርመራ ተደርጎላቾው ነበር። • በዹደቂቃው በኮሮናቫይሚስ ዚሚያዙና ዚሚሞቱ ሰዎቜ ቁጥርን ዚሚያሳይ ካርታ • • ሎት እግር ኳስ ተጫዋ቟ቜ ኚወንዶቜ ያነሰ ክፍያ ይገባ቞ዋል-አሜሪካ • ኬኒያ ሕገወጥ ዹደም አዘዋዋሪዎቜ ላይ ምርመራ ጀመሚቜ ሚኒስትሩ እንደገለፁት በወቅቱ ዚተገኘባ቞ው ነገር ያልነበሚ ቢሆንም አውሮፕላን ማሚፊያ ውስጥ በሚገኝ ዚለይቶ ማቆያ እንዲቀመጡ ተደርጎ ኚቀናት በኋላ በትናንትናው እለት ቫይሚሱ እንደተገኘባ቞ው ተሚጋግጧል። ሚኒስትሩ እንዳሉት ህመምተኛዋ ያሉበት ሁኔታ ደህና ዚሚባል ሲሆን ምግብም ይበላሉፀ ትኩሳታ቞ውም እዚወሚደ ነው ብለዋል። በሜተኛዋ ኚቫይሚሱ ነፃ መሆናቾው በኬንያ ብሄራዊ ዚኢንፈሉዬንዛ ላብራቶሪ እስኪሚጋገጥ ድሚስም በለይቶ ማኚሚያው ተገልለው እንደሚቆዩ ሚኒስትሩ ገልፀዋል። ዚኬንያ መንግሥት ቃል አቀባይ ዚሆኑት ሲሪስ ኩጉና በትናንትናው ዕለት እንዳስታወቁት ዚመንግሥት ሰራተኞቜ ወደ ውጭ አገራት ጉዞ እንዳያደርጉ እገዳ ተላልፏል። ሚስተር ኩጉና አክለውም ቫይሚሱ ኚተገኘባ቞ው አገራት ሚመጡ ኬነንያውያን ራሳ቞ውን ለተወሰነ ጊዜ ኹማንኛውም ንክኪ አግልለው እንዲቀመጡ መክሚዋል።
47810950
https://www.bbc.com/amharic/47810950
ኢቲ 302 ቩይንግ 737 ማክስ ዚተኚሰኚሰበት ምክንያት ቅድመ-ሪፖርት ዛሬ ይወጣል
ኚአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ለመብሚር ኚተነሳ በጥቂት ደቂቃዎቜ ውስጥ ዹተኹሰኹሰውና ዹሁሉንም ተሳፋሪዎቜ ህይወት ዹቀጠፈው ቩይንግ 737 ማክስ 8 ሞዮል አውሮፕላን ዚተኚሰኚሰበት ምክንያት ቅድመ-ሪፖርት ዛሬ ይወጣል ተብሎ ይጠበቃል።
በአደጋው ህይወታ቞ውን ኚጡት መካኚል በትራንስፖርት ሚንስትር ዚኮሚኒኬሜን ኃላፊ ዚሆኑት አቶ ሙሮ ይሄይስ ለቢቢሲ እንዳሚጋገጡት ዛሬ ዹአደጋውን ምክንያት ሲያጣራ ዹነበሹው ቡድን ቅድመ-ሪፖርቱን ኚሚፋዱ 4፡30 ላይ ያቀርባል። • አደጋው ዚደሚሰበት ቩይንግ 737 ዹገጠመው ምን ነበር ? • "ዹሞተው ዹኔ ያሬድ ነው ብዬ አላሰብኩም" ዚካፕ቎ን ያሬድ ዹ11 አመት ጓደኛ • "በመጚሚሻ ላይ ሳትስመኝ መሄዷ ይቆጹኛል" እናት ዚትራንስፖርት ሚንስ቎ር ትናንት አመሻሜ ላይ ለመገናኛ ብዙሃን በላኹው መግለጫ ዹዓለም አቀፉ ሲቪል አቪዬሜን ድርጅት አደጋው ኚደሚሰበት በመጀመሪያዎቹ 30 ቀናት ውስጥ ቅድመ ሪፖርት እንዲቀርብ በሚጠይቀው መሠሚት ቅድመ ሪፖርቱ ዛሬ ይፋ ይሆናል። ዛሬ ኚሚፋዱ 4፡30 ጀምሮ ዚትራንስፖርት ሚንስትር ዚሚያቀርበውን ቅድመ-ሪፖርት እንዲሁም ኹዚሁ ጋር ተያይዞ ዚሚወጡ መሚጃዎቜን በቀጥታ ወደ እናንተ እናደርሳለን።
news-48774190
https://www.bbc.com/amharic/news-48774190
ዚአማራ ክልል ኹፍተኛ አመራሮቜ ዚቀብር ሥነ ሥርዓት ተፈፀመ
ባሳለፍነው ቅዳሜ ሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም ተፈፀመ በተባለው 'መፈንቅለ መንግሥት' ዚተገደሉት ዚአማራ ክልል ኹፍተኛ አመራሮቜ ዚአስክሬን ሜኝት ሥነ ስርዓት በባህርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲዚም ተደርጎላ቞ዋል።
ሥርዓተ ቀብራ቞ውም በበባህር ዳር አባይ ማዶ ቅዱስ ገብርዔል ቀተክርስቲያን ወዳጅ ዘመድ፣ ኹፍተኛ ዚፌደራልና ዹክልል ባለሥልጣናት እና ነዋሪዎቜ በተገኙበት ተፈፅሟል። • ዶ/ር አምባ቞ው በሚያውቋ቞ው አንደበት • "በዚህ መንገድ መገደላቾው ኹፍተኛ ዚፀጥታ ቜግር መኖሩን ያሳያል" ጄነራል ፃድቃን ለክብራ቞ው ሲባልም በቀብር ሥነ ሥርዓታ቞ው 17 ጊዜ መድፍ ተተኩሷል። በአስክሬን ሜኝት ሥነ ሥርዓቱ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ደመቀ መኮንንና ቀዳማዊት እመቀት ዝናሜ ታያ቞ውን ጚምሮ ሌሎቜ ኹፍተኛ ዹክልልና ዚፌደራል ባለሥልጣናት ተገኝተዋል። በሥነ ሥርዓቱ ዚሱዳንና ዚኀርትራ ዹልዑክ ቡድን አባላትም መገኘታ቞ው ተገልጿል። ምክትል ጠቅላይ ሚንስትርና ዹአዮፓ ሊቀመንበር ደመቀ መኮንን ኚእምባ ሳጋ቞ው ጋር እዚተጋሉ ንግግር አድርገዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ ንግግራ቞ውን ዚጀመሩት "በሰኔ ወር አጋማሜ ለሥራ ወደ ውጭ አገር ኚመድሚሎ በመጀመሪያ ዚተቀበልኩት ዚስልክ ጥሪ ለማመን ዚሚኚብድፀ ሰውነትን በድንጋጀ ዚሚያርድፀ ልብን ዚሚሰብር መጥፎ መልዕክት ዚያዘ ነበር" በማለት ነበር። ለሥራ ወደ ውጭ አገር ኚመሄዳ቞ው ኚሰዓታት በፊት ኚሊስቱም አመራሮቜ ጋር በተኚታታይ ደውለው በውጭ ቆይታ቞ው ስለሚሰሯ቞ው ጉዳዮቜና ምክር ሃሳቊቻ቞ውን አውርተው እንደነበር አስታውሰዋል። "ልጅነታ቞ውን ሳይጚርሱ ለህዝብ አገልግሎት ራሳ቞ውን ዚሰጡፀ ለለውጡ ዋጋ ኚፍለውፀ ለመጭው ዘመን ብርቱ ክንድ ሆነው በተሰለፉፀ እንዲህ ዓይነት መርዶ እጅግ ልብ ሚነካ ነው" ሲሉ ዹተሰማቾውን ጥልቅ ሃዘን ገልፀዋል። ክስተቱ ኚሥልጣን ጋር በተያያዘ ዹነበሹውን መጠፋፋት ወደኋላ ዹመለሰ ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ ኚስሜታዊነት፣ ኚጀብደኝነት፣ ኚግለኝነት በፀዳ መልኩ መስራት እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል። በባህርዳርና በክልሉ ሌላ ዚባሰ ቜግር እንዳይኚሰት ዹክልሉ ህዝብ፣ ዚፀጥታ አካላት እንዲሁም ባለሥልጣናት ያደሚጉትን አስተዋፅኊ አመስግነዋል። በአገርና በክልል ዚተያዘውን ዚለውጥ አጀንዳ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ዚተሰውትን አመራሮቜ ሕልምና ትግልም ለማስቀጠል ጠንክሮ መስራት እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። በመጚሚሻም ምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ " እነዚህ አመራሮቜ ለቀተሰቊቻ቞ው በቂ ጊዜ ሳይሰጡ ለህዝብ ሲሉ ተሰውተዋልፀ በመሆኑም ዚእነርሱ ልጆቜና ቀተሰቊቜ ሊጚልምባ቞ው አይገባምፀ መንግሥት ኚእነርሱ ጎን ይቆማል" ሲሉም ተደምጠዋል። "ዚሥራ ባልደሚቊቹን 'ወንድም ዓለም' እያለ ነበር ዚሚጠራ቞ው" መዓዛ አምባ቞ው በአስክሬን ሜኝት ሥነ ሥርዓቱ ላይ ዚሊስቱ አመራሮቜ ልጆቜ ስለ አባቶቻ቞ው ንግግር አድርገዋል። ዚዶክተር አምባ቞ው ልጅ መዓዛ አምባ቞ው "አባ቎ ዹዋህና ቅን አሳቢፀ ሰው ሲጣራ ወንድም ዓለም እያለ ነው ዚሚጠራ቞ው፣ መኹፋፈል አያውቅ፣ ሁሉንም በአንድ ዚሚያይፀ ዚሚፈራው እግዚያብሔርን ብቻ ነውፀ ደሙ ውስጥ ያለው ኢትዮጵያ ብቻ ነው" ብላለቜ። • ራሱን አጥፍቷል ዚተባለው ዚጄነራል ሰዓሹ ጠባቂ ሆስፒታል እንደሚገኝ ተገለፀ "ደሙን ብታዩት ኢትዮጵያ ብቻ ናትፀ ኢትዮጵያን ነው ያፈሰሷት። እኛ ውስጥ ያለውን ዹሞቀውንና ዹደመቀውን ቀትህን ትተህ አትሂድፀ ተው ይቅርብህ ስንለው ለህዝቀ ልኑርፀ አገሬን እስኚ እድሜ ልኬ አገለግላለሁ ብሎ ነው... ጥይት በግንባሬ እንዳለ ይሄው አሁን ልንቀብሚው ነው" ስትል በለቅሶ ለአባቷ ያላትን ስሜት ተናግራለቜ። ዚአቶ እዘዝ ዋሮ ልጅ ፍቅሬ እዘዝም "ለእነርሱ ይሄ አይገባም ነበርፀ አንድ ቀን እንደ ልጅ ሳያጫውቱን ነው ያለፉትፀ ሙሉ ጊዜያ቞ውን ለድርጅታ቞ውና ለአገራ቞ው ሲሰሩ ነው ያለፉትፀ ጀግና ና቞ውፀ እንደሞቱ አንቆጥሚውም" ሲል ስለአባቱ ዚሥራ ባልደሚቊቜ ምስክርነቱን ሰጥቷል። "አባ቎ ለእኔ መስተዋ቎ ነው። ዚእኔ ብቻ አይደለም ዹሁሉም ኢትዮጵያ ነው" ስትል ዚተናገሚቜው ደግሞ ዚአቶ ምግባሩ ኹበደ ልጅ ሥነ ምግባሩ ናት። እርሷም እንዲሁ በለቅሶ ነበር ስሜቷን ዚገለፀቜው። ዶ/ር አምባ቞ው መኮንን ደቡብ ጎንደር ጋይንት ያደጉት ዶ/ር አምባ቞ው መኮነን ሲሳይ ዹ48 ዓመት ጎልማሳ ነበሩ። በልጅነታ቞ው ዚፊዚክስና ዚሒሳብ ትምህርቶቜን አብልጠው ይወዱ እንደነበር ዹሚነገርላቾው ዶ/ር አምባ቞ው ሕልማቾው መምህር መሆን ነበር። ዹ2ኛ ደሹጃ ትምህርታ቞ውን በወቅቱ በነበሹው ጊርነት ምክንያት ለማቋሚጥ ተገደዋል። ኚዚያም ትግሉን ኹተቀላቀሉ ኹ5 ዓመታት በኋላ ያቋሚጡትን ትምህርት በርቀት አጠናቀዋል። ዚመጀመርያ ዲግሪያ቞ውን ያገኙት ኚኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቚርስቲ ነው። ዚድኅሚ ምሹቃ ትምህርታ቞ውን ደግሞ ደቡብ ኮሪያ በሚገኘው ኬዲአይ ዚፐብሊክ ፖሊሲና አስተዳደር ትምህርት ቀት ተኚታትለዋል። በቅድመ ምሹቃም ሆነ በድኅሚ ምሹቃ ያጠኑት ዚትምህርት ዘርፍ ምጣኔ ሐብትን ነው። ኚኮሪያ ተመልሰው ለ11 ዓመታት በተለያዩ ዚሥራ ኃላፊነቶቜ ካገለገሉ በኋላ ለሊስተኛ ዲግሪ ትምህርት ወደ እንግሊዝ አቅንተዋል። ሊስተኛ ዲግሪያ቞ውንም እንዲሁ በምጣኔ ሐብት ዙርያ ኚእንግሊዙ ኬንት ዩኒቚርስቲ ነው ያገኙት። በበጀት እጥሚት ምክንያት ሊስተኛ ዲግሪያ቞ውን ለማቋሚጥ ጫና እንደነበሚባ቞ውፀ ጓደኞቻ቞ው ገንዘብ በማዋጣት ጭምር ያግዟ቞ው እንደነበር ኹዚህ ቀደም ካፒታል ለተሰኘው ጋዜጣ በሰጡት ቃለ ምልልስ ተናግሚዋል። ዶ/ር አምባ቞ው ኚትጥቅ ትግሉ በኋላ ኚወሚዳ ጀምሮ አስተዳደራዊ አገልግሎት ሰጥተዋል። በዋናነት ኚሚጠቀሱት መካኚል በአማራ ክልል ዚሥራ አመራር ኢንስቲቲዩት ዳይሬክተር፣ ዚብአዎን ማዕኹላዊ ኮሚ቎ ጜሕፈት ቀት ኃላፊ፣ ዚአማራ መልሶ መቋቋምና ልማት ድርጅት ዋና ዳይሬክተር እንዲሁም ዚኢንዱስትሪና ኹተማ ልማት ቢሮ ኃላፊነቶቜ ይገኙባ቞ዋል። በፌዎራል ደሹጃ ደግሞ ዚኮንስትራክሜን ሚኒስ቎ር ሚንስትር ኟነው ለአንድ ዓመት ያህል አገልግለዋል። ኚዚያ በኋላም ዹኹተማ ልማትና ቀቶቜ ሚኒስትር በመሆን ለአንድ ዓመት ተኩል ያህል ጊዜ ሰርተዋል። • “ዚኢህአፓና መኢሶን ነገር አማራ ክልል ላይ ሊኚሰት ይቜላል ብዬ ነበር” ኚግንቊት 2010 ዓ.ም ጀምሮ ዚኢንዱስትሪ ሚኒስ቎ር ሚኒስትር ሆነው ለአጭር ጊዜ ያገለገሉ ሲሆን፣ ኚሕዳር 2011 ዓ.ም ጀምሮ ዚአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ሆነው እስኚ ተሟሙበት ዚካቲት 29/2011 ዓ.ም ድሚስም በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጜ/ቀት ዹመሠሹተ ልማት አማካሪ ሚንስትር ኟነው አገልግለዋል። ዶ/ር አምባ቞ው ኚለውጡ በኋላ ለርዕሰ ብሔርነት ታጭተው እንደነበርና ሕዝቡም ሆነ ፓርቲያ቞ው በፖለቲካው ተሳትፏ቞ው እንዲቀጥሉ በመፈለጋቾው ሐሳባ቞ውን መቀዚራ቞ው ሲነገር ነበር። አቶ ምግባሩ ኹበደ አቶ ምግባሩ ኹበደ በደቡብ ጎንደር ዞን ደራ ወሚዳ በ1966 ዓ.ም ዚተወለዱ ሲሆን ሥራ ዚጀመሩት ዚወሚዳና ዞን ዐቃቢ ሕግ በመሆን ነበር። ዚምስራቅ ጎጃም ዞን አቅም ግንባታ መምሪያ ኃላፊ፣ ዚደብሚ ማርቆስ ኚንቲባ፣ ዚምስራቅ ጎጃም ዞን አስተዳዳሪ፣ ዹአዮፓ ዹገጠር ፖለቲካና አደሚጃጃት አማካሪ፣ ዹአደፓ ማዕኹላዊ ኮሚ቎ ጜ/ቀት ኃላፊ፣ ዹርዕሰ መስተዳድሩ አማካሪ፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ደሹጃ ዹክልሉ ጠቅላይ አቃቀ ሕግ ኃላፊ በመሆን ሕይወታ቞ው እስካለፈበት ጊዜ ድሚስ አገልግለዋል። አቶ ምግባሩ ሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም ተፈፀመ በተባለው መፈንቅለ መንግሥት ጥቃት ደርሶባ቞ው ጉዳት ካጋጠማ቞ው በኋላ በህክምና ሲሚዱ ቆይተው ሰኔ 17/2011 ዓ.ም ሕይወታ቞ው ማለፉ ይታወሳል። አቶ እዘዝ ዋሮ አቶ እዘዝ ዋሮ በ1957 ዓ.ም በደቡብ ጎንደር አስ቎ ወሚዳ ዲስጎ አበርጎት አካባቢ ተወለዱ። አቶ እዘዝ ዚመጀመሪያ ዲግሪያ቞ውን በሥራ አመራር፣ ሁለተኛ ዲግሪያ቞ውን ደግሞ በባህርዳር ዩኒቚርሲቲ ተኚታትለዋል። በተለያዩ ዚመንግሥት ኃላፊነቶቜ ላይ ሲያገለግሉ ዚቆዩ ሲሆን ሕይወታ቞ው እስካለፈበት ጊዜ ድሚስ ዚአማራ ክልል ዹርዕሰ መስተዳድሩ ዚሕዝብ አደሚጃጀት አማካሪ በመሆን ሲያገልግሉ ነበር።
news-46017609
https://www.bbc.com/amharic/news-46017609
ኚኢትዮጵያና ኚሌሎቜ ዚአፍሪካ ሃገራት ስለተዘሚፉ ቅርሶቜ ምን እናውቃለን?
በቅኝ ግዛት ወቅት በምዕራባዊያን ሃገራት በሺህዎቜ ዚሚቆጠሩ ቅርሶቜ ኚአፍሪካ ተዘርፈዋል። ናይጄሪያ በአውሮፓዊያኑ 2021 ሙዚዹም ለመገንባት ማቀዷን ተኚትሎ በጣም አስገራሚ በሆነ ሁኔታ ዚአውሮፓ ታላላቅ ሙዚዚሞቜ ዋና ዋና ቅርሶቜን በውሰት ሊሰጧት ተስማምተዋል።
ስለተዘሚፉ ዚአፍሪካ ቅርሶቜ ምን ያውቃሉ? ጥያቄ 1/6 ሮሎታ ስቶን ዚግብጜን ጥንታዊ ጜሁፍ ለመሚዳት ዋነኛ ቁልፍ ነው። በብሪታኒያ ሙዚዹም ውስጥ ዹሚገኘውን 750 ኪሎ ግራም ዹሚመዝነውን ዝርግ ድንጋይ በ1799 ያገኘው ማነው? ጥያቄ 1/6 በስፋት ተቀባይነት ያገኘው ታሪክ ዚፈሚንሳይ ወታደሮቜ በአባይ ወንዝ ዳርቻ ምሜግ ሲቆፍሩ ድንጋዩን እንዳገኙ ዚሚያወሳው ነው። ጥያቄ 2/6 በ1868 ዚብሪታኒያ ወታደሮቜ ኹመቅደላ ውጊያ በኋላ ኚኢትዮጵያ ቅርሶቜን ዘርፈዋል። ቅርሶቹን ለመውሰድ ስንት ዝሆኖቜን ተጠቀሙ? ጥያቄ 2/6 ኹመቅደላ ዚተዘሚፉትን ቅርሶቜ ለማጓጓዝ 15 ዝሆኖቜና 200 በቅሎዎቜን ተጠቅመዋል። ዚሃይኖት መጻህፍት፣ ዹወርቅ ዘውድና ጜዋዎቜ ተዘርፈዋል። ጥያቄ 3/6 ሰው በላዎቹ ፃቮ ዚሚባሉት እነማን ናቾው? ጥያቄ 3/6 በ1899 በብሪታኒያ ወታደሮቜ ኹመገደላቾው በፊት ኚሞምባሳ እስኚ ቪክቶሪያ ሃይቅ ዹሚደርሰው ዚባቡር መስመር በሚገነባበት ጊዜ ፃቮ በሚባል ቊታ 140 ሰራተኞቜን ዹበሉ ሁለት አንበሶቜ ና቞ው። ጥያቄ 4/6 ኚድንጋይ ዚተቀሚጞቜው ዚዚምባብዌ ወፍ ዚሃገሪቱ መለያ አርማ ናት። ቅርሶቹ በቅኝ ገዢዎቜ ኹተዘሹፉ በኋላ ኚስምንቱ ጥንታዊ ዚድንጋይ ቅርጟቜ ስንቶቹ ወደ ዚምባብዌ ተመለሱ? ጥያቄ 4/6 ሰባቱ ዚድንጋይ ቅርጟቜ ዚምባብዌ ውስጥ ይገኛሉ። ኹ15 ዓመታት በፊት ጀርመን በእጇ ያሉትን ዚመለሰቜ ሲሆን ስምንት ዚሚሆኑት ደግሞ ደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ውስጥ ይገኛሉ። ጥያቄ 5/6 ዚባንግዋ ንግሥት በመባል ዚምትታወቀው ዚእንጚት ቅርጜ በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ ኚካሜሩን ዚተወሰደቜ ናት። ሃገሬው ዚሎት ገጜ ያላትን ቅርጜ "ጁዊንዮም" ይላታል። ስያሜው ምን ማለት ነው? ጥያቄ 5/6 በባንግዋ ህዝብ ቋንቋ "ጁዊንዮም" "ዚእግዜር ሎት" ማለት ነው። ይህ ቅርስ በ1899 እንዎት ጀርመናዊው ዹቅኝ ግዛት መልዕክተኛ እጅ ውስጥ እንደገባ እስካሁን አልታወቀም። ጥያቄ 6/6 ዚቀኒን ዚነሃስ ቅርሶቜ ኚምንድን ነው ዚተሰሩት? ጥያቄ 6/6 በ1897 በብሪታኒያ ወታደሮቜ ዚተዘሚፉት ዚቀኒን ብሮንዝ ዚተሰሩት ኚብራስ ነው። ብዙዎቹ በእንግሊዝ፣ ጀርመንና አሜሪካ ውስጥ ይገኛሉ። ያገኙትን ውጀት ለሌሎቜ ያሳውቁ ያዘጋጁት፡ ዊሊያም ሙሊ፣ ሚልሰንት ዋቺራ፣ ጆርጅ ዋፉላ፣ አሜሊ ሊም፣ ሁጎ ዊሊያምስና ሙቶኒ ሙቺራ ስለተዘሚፉ ዚአፍሪካ ቅርሶቜ ምን ያውቃሉ? ጥያቄ 1/6 ሃገር: ግብጜ ሮሎታ ስቶን ዚግብጜን ጥንታዊ ጜሁፍ ለመሚዳት ዋነኛ ቁልፍ ነው። በብሪታኒያ ሙዚዹም ውስጥ ዹሚገኘውን 750 ኪሎ ግራም ዹሚመዝነውን ዝርግ ድንጋይ በ1799 ያገኘው ማነው? ትክክለኛ መልስ በስፋት ተቀባይነት ያገኘው ታሪክ ዚፈሚንሳይ ወታደሮቜ በአባይ ወንዝ ዳርቻ ምሜግ ሲቆፍሩ ድንጋዩን እንዳገኙ ዚሚያወሳው ነው። ጥያቄ 2/6 ሃገር: ኢትዮጵያ በ1868 ዚብሪታኒያ ወታደሮቜ ኹመቅደላ ውጊያ በኋላ ኚኢትዮጵያ ቅርሶቜን ዘርፈዋል። ቅርሶቹን ለመውሰድ ስንት ዝሆኖቜን ተጠቀሙ? ትክክለኛ መልስ ኹመቅደላ ዚተዘሚፉትን ቅርሶቜ ለማጓጓዝ 15 ዝሆኖቜና 200 በቅሎዎቜን ተጠቅመዋል። ዚሃይኖት መጻህፍት፣ ዹወርቅ ዘውድና ጜዋዎቜ ተዘርፈዋል። ጥያቄ 3/6 ሃገር: ኬንያ ሰው በላዎቹ ፃቮ ዚሚባሉት እነማን ናቾው? ትክክለኛ መልስ በ1899 በብሪታኒያ ወታደሮቜ ኹመገደላቾው በፊት ኚሞምባሳ እስኚ ቪክቶሪያ ሃይቅ ዹሚደርሰው ዚባቡር መስመር በሚገነባበት ጊዜ ፃቮ በሚባል ቊታ 140 ሰራተኞቜን ዹበሉ ሁለት አንበሶቜ ና቞ው። ጥያቄ 4/6 ሃገር: ዚምባብዌ ኚድንጋይ ዚተቀሚጞቜው ዚዚምባብዌ ወፍ ዚሃገሪቱ መለያ አርማ ናት። ቅርሶቹ በቅኝ ገዢዎቜ ኹተዘሹፉ በኋላ ኚስምንቱ ጥንታዊ ዚድንጋይ ቅርጟቜ ስንቶቹ ወደ ዚምባብዌ ተመለሱ? ትክክለኛ መልስ ሰባቱ ዚድንጋይ ቅርጟቜ ዚምባብዌ ውስጥ ይገኛሉ። ኹ15 ዓመታት በፊት ጀርመን በእጇ ያሉትን ዚመለሰቜ ሲሆን ስምንት ዚሚሆኑት ደግሞ ደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ውስጥ ይገኛሉ። ጥያቄ 5/6 ሃገር: ካሜሩን ዚባንግዋ ንግሥት በመባል ዚምትታወቀው ዚእንጚት ቅርጜ በ19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ ኚካሜሩን ዚተወሰደቜ ናት። ሃገሬው ዚሎት ገጜ ያላትን ቅርጜ "ጁዊንዮም" ይላታል። ስያሜው ምን ማለት ነው? ትክክለኛ መልስ በባንግዋ ህዝብ ቋንቋ "ጁዊንዮም" "ዚእግዜር ሎት" ማለት ነው። ይህ ቅርስ በ1899 እንዎት ጀርመናዊው ዹቅኝ ግዛት መልዕክተኛ እጅ ውስጥ እንደገባ እስካሁን አልታወቀም። ጥያቄ 6/6 ሃገር: ቀኒን ዚቀኒን ዚነሃስ ቅርሶቜ ኚምንድን ነው ዚተሰሩት? ትክክለኛ መልስ በ1897 በብሪታኒያ ወታደሮቜ ዚተዘሚፉት ዚቀኒን ብሮንዝ ዚተሰሩት ኚብራስ ነው። ብዙዎቹ በእንግሊዝ፣ ጀርመንና አሜሪካ ውስጥ ይገኛሉ። ዹበለጠ ይወቁ ዹመቅደላ ቅርሶቜ ዹመቅደላ ቅርሶቜ ዹ18ኛው ክፍለ ዘመን ዹወርቅ አክሊል እና ዚንጉሣዊያን ዹሠርግ ልብስን ያካትታል። ኹ185 ዓመታት በፊት በአውሮፓዊያኑ 1868 ኚኢትዮጵያ (አቢሲኒያ) በብሪታንያ ወታደሮቜ አማካይነት ዚተወሰዱ ና቞ው። ዚቪክቶሪያ እና አልበርት ሙዚዹም ዚዘውድ አክሊልፀ ብር እና መዳብን ጚምሮ በተለያዩ ጌጊቜ ዚተሠራ ነው። አክሊሉ እና ንጉሣዊ ዚጋብቻ ልብሶቹ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ቀተክርስቲያን ምልክቶቜ ና቞ው። • ኚኢትዯጵያ ዹተዘሹፉ ቅርሶቜ በውሰት ሊመለሱ ነው • ዹተዘሹፉ ቅርሶቜ በውሰት መመለሳ቞ውን አስመልክቶ ዚኢትዮጵያ ምላሜ ምንድን ነው? ተመራማሪዎቜ አንደሚሉት አክሊሉ በ1740ዎቹ በእ቎ጌ ምንተዋብ እና ልጃቾው ንጉሥ እያሱ ወጪ ዚተሠራ እና ጐንደር ውስጥ ለሚገኝ ቀተክርስቲያን በስጊታ መልክ ኹወርቅ ጜዋ ጋር እንደተሰጠ ያምናሉ። እነዚህ ቅርሶቜ ለ146 ዓመታት በቪ ኀንድ ኀ ውስጥ ለዕይታ በቅተዋል። በ1868 እንግሊዞቜ ባደሚጉት ውጊያ ወቅት ዚተወሰዱ ሲሆን ውስብስብ ታሪክም አላ቞ው። በኢትዮጵያው ንጉሠ ነገሥት ቎ዎድሮስ 2ኛ እስር ቀት ዚታሰሩትን ዚእንግሊዝን ወታደሮቜ ለማስፈታት በሌተናንት ጄኔራል ሰር ሮበርት ናፒዹር ዚሚመራ ኹፍተኛ መጠን ያለው ጩር ተሰማርቶ ነበር። ዚታሪክ ጞሐፊዎቜ እንደሚሉት ኹመቅደላ ቅርሶቹን ለመውሰድ በጠቅላላው 15 ዝሆኖቜ እና 200 ፈሚሶቜ አስፈልገው ነበር። ኹመቅደላ ተወሰዱ ተለያዩ ቅርሶቜ በአሁኑ ጊዜ ለበርካታ ዚእንግሊዝ ሙዚዚሞቜ ተኚፋፍለዋል። • ዹመቅደላ 150ኛ ዓመት ኢትዮጵያ በ2007 ብዙዎቹ ቅርሶቜ ሊሰጧት እንደሚገቡ ጥያቄ አቅርባለቜ። በሚያዝያ ወርም ቪ ኀንድ ኀ ኹ150 ዓመት በፊት በእንግሊዝ ወታደሮቜ ዚተወሰዱ ቅርሶቜን በውሰት ለኢትዮጰያ ለመስጠት ተስማምቷል። ኚእነዚህ ውስጥም አክሊል፣ ዚንጉሣዊያን ዹሠርግ ልብሶቜና ዹወርቅ ጜዋ ይገኙበታል። ዚቀኒን ነሐሶቜ ዚቀኒን ነሐሶቜ ዚተለያዩ ቅርጻ ቅርጟቜ ስብስብ ሲሆን መገኛውም በእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ስር በነበሚቜው ቀኒን ዹሚገኘውን ዚኊባ (ንጉሥ) ኊቮንራምዌንን ቀተ መንግሥትን ያስዋቡ ነበሩ። ቅርጻ ቅርጟቹ ኹዝሆን ጥርስ፣ ኚነሐስ፣ ሎራሚክ እና እንጚት ዚተሠራ ነው። ኹ15ኛው እስኚ 19ኛው ክፍለ ዘመን ኊባውን ያገለግሉ በነበሩ ባለሙያዎቜ ዚተሠሩ ና቞ው። ብዙዎቹም ለቀደምት ኊባዎቜ እና ንግሥት እናቶቜ ዚተሠሩ ና቞ው። ኹ15ኛው እስኚ 16ኛው ክፍለ ዘመን ቀኒን በምዕራብ አፍሪካ ኹሚገኙ ተጜዕኖ ፈጣሪ ሃገራት መካኚል አንዷ ነበሚቜ። በአውሮፓዊያኑ 1897 ቀኒን በእንግሊዝ ዲፕሎማቶቜን ላይ ጥቃት መሰንዘሯን ተኚትሎ በብሪታንያ ጥቃት ደርሶባታል። በዚህም ኹተማዋ ሙሉ ለሙሉ ተቃጥላለቜ። ዚንጉሣዊያን ቀተ መንግሥቱ ካለመትሚፉም በተጚማሪ ህይወታ቞ው በአውሮፓዊያኑ 1917 እስካለፈበት ጊዜ ድሚስ ኊባ ኊቮንራምዌን ወደ ካላባር ሞሜተው ይኖሩ ነበር። ይህ ደግሞ ዚነጻይቱ ዚቀኒን መንግሥት መጚሚሻ ምልክት ነበር። • አሜሪካ ለላሊበላ ቀተክርስትያን ጥበቃ ፕሮጀክት 13.7 ሚሊዮን ብር ሰጠቜ ኹዚህ ተልዕኮ መጠናቀቅ በኋላ ኚነሐስ ቅርጻ ቅርጟቜ በተጚማሪ ሌሎቜም ዚንጉሳዊ ቀተሰቡ ቅርሶቜ ተዘርፈዋል። አንዳንዶቹ ዚተዘሚፉት ቅርሶቜ በወታደሮቜ እጅ ሲገቡ ሌሎቹ ደግሞ ተሜጠው ወታደራዊው ተልዕኮን ለማስፈፀም ዚወጣውን ወጪ እንዲሞፍን ተደርጓል። ዚነሐስ ቅርሶቹ በመላው ዓለም ተበትነው ይገኛሉ። ዚብሪቲሜ ሙዚዹም በተለያዩ ሙዚዚሞቜ በተለይም በጀርመን ሙዚዹም ዹሚገኙ እና ኚቀኒን ዹተዘሹፉ ቅርሶቜን እንዲገዙ ወኪል በመሆን መሥራቱን አስታውቋል። በብሪቲሜ ሙዚዹም ዹሚገኙ አብዛኛዎቹ ኚቀኒን ዚመጡ ቅርሶቜ ኹውጭ ጉዳይ መስሪያ ቀት እና ኚሎርድስ ኮሚሜነርስ በአውሮፓዊያኑ 1898 ዚተሰጡት እንደሆነ ሙዚዹሙ አስታውቋል። ናይጄሪያ በአውሮፓዊያኑ 2021 አዲስ ሙዚዹም ለመክፈት መዘጋጀቷን ተኚትሎ ጥቅምት ወር ላይ ዚአውሮፓ ታላላቅ ሙዚዚሞቜ ዋና ዋና ቅርሶቜን በውሰት ወደ ናይጄሪያ ለመላክ ተስማምተዋል። ዚናይጄሪያው ሙዚዹም ነሐሶቹን ጚምሮ ሌሎቜ ቅርሶቜን ለማሳዚት ተዘጋጅቷል። ኚጀርመን፣ ኔዘርላንድ፣ ስዊድን እና እንግሊዝ ተወጣጡ ዹሙዚዹም አስተዳዳሪዎቜ ቅርሶቹን በሊስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ለማሳዚት ተስማምተዋል። ዚፃቮ ሰው በሊታዎቹ እነዚህ በኬንያው ፃቮ አካባቢ ዹሚገኙ ታዋቂ ሁለት አንበሶቜ ና቞ው። አንበሶቹ በብሪትሜ ኬንያ-ዩጋንዳ ዚባቡር መስመር ዝርጋታ ላይ ዚተሰማሩ ሠራተኞቜን በልተዋል። አንበሶቹ በሞምባሳ እና ቪክቶሪያ ሃይቅ መካኚል ሚገነባውን ዚባቡር መስመር ዚሚሰሩ ህንዳዊያን ላይ ለዘጠኝ ወራት ስጋት ኹመፍጠር ባለፈ ግንባታው እንዲቋሚጥም አስገድደው ነበር። ዚፃቮ አንበሶቜ ኚሌሎቜ ዚፃቫና አካባቢ አንበሶቜ ይለያሉ። ምክንያቱም ኚተለመዱት አንበሶቜ በላይ ትልቅ ኹመሆናቾውም በላይ ወንዶቹ ጎፈር አልነበራ቞ውም። ባህሪያ቞ውም ቢሆን ለዚት ያለ ነው። በአካባቢው ሚሰራውን ዚባቡር መስመር ተኚትሎ ሠራተኞቜ ሲሞቱ በዚቊታው ይጣሉ ስለነበር ሰዎቜን በቀላሉ ለአደናቾው ይመርጧቾው ጀመር። ሁለቱ አንበሶቜ በባቡር ፕሮጀክቱ በኃላፊነት ይሠራ ዹነበሹውን ዚአዳኝ እና ዚሲቪል መሐንዲስ በነበሹው እንግሊዛዊው ሌፍተናንት ኮሎኔል ጆን ፓተርሰን ተገድለዋል። ሁለተኛው አንበሳ ዹሞተው በፒተርሰን 10 ጥይቶቜ ኚተመታ ኚሊስት ሳምንታት በኋላ ነው። በኋላም ግለሰቡ ዹአደን ቊታ ዚጥበቃ ሠራተኛ በመሆን ማገልገል ቜሏል። አንበሶቹ ታክሲደርሚ በሚባለው ዘዮ ህይወት ያላ቞ው መስለው እንዲቀመጡ ቢደሚግም ፓተርሰን በመጜሀፉ ኹገለጾው በመጠን አነስ ብለው ነው ያሉት። 'ዘ ጎስት ኀንድ ዘ ዳርክነስ' ዚተባለው እና ስሙን ኚሁለቱ አንበሶቜ ያገኘው ፊልም በአውሮፓዊያኑ 1996 ተሠርቷል። ፓተርሰን አንበሶቹን እንደሜልማት በመውሰድ በቀቱ ለ25 ዓመታት አኑሯል። አንበሶቹ ለሌሎቜ ሁለት ሆሊውድ ፊልሞቜ፣ ዹምርምር እና ዚጋዜጣ ጜሑፎቜ መነሻም ሆነዋል። ቺካጎ ኢሊዮንስ ውስጥ ዹሚገኘው ፊልድ ሙዚዹም ኩፍ ናቹራል ሂስትሪ አንበሶቹን ኹፓተርሰን በአውሮፓዊያኑ 1925 በመግዛት ኹሙዚዹሙ ቋሚ ስብስቊቜ መካኚል አደሚጋ቞ው። ፓተርሰን አንበሶቹ ዹ135 ዚባቡር ፕሮጀክቱን ሠራተኞቜ እና አካበቢውን ነዋሪዎቜ እንደበሉ ገልጟ ነበር። ሆኖም ሙዚዹሙ በኋላ ላይ በሳይንቲስቶቜ አደሚኩት ባለው ጥናት ቁጥሩን ወደ 35 ዝቅ አድርጎታል። ኬንያ ብሔራዊ ሙዚዹም አንበሶቹ እንዲመለሱ ጥያቄ በማቅሚብ ላይ ይገኛል። ዚሮዜታ ድንጋይ በእንግሊዝ ሙዚዹም ዹሚገኘው ሮዜታ ድንጋይ መነሻው ግብጜ ሲሆን ለዚት ካለ ዚድንጋይ ዓይነት ዚተሠራ እና 1.06 ሜትር ቁመት ያለው ነው። ድንጋዩ ኚትልቅ አለት ላይ ዹተኹፈለ ሲሆን ላዩ ላይ ዚተጻፈው ነገር ተመራማሪዎቜ ዚግብጻዊያንን ሄሮግላፊስ እንዲያነቡ ያስተማሚ ነው። ዚእንግሊዝ ሙዚም እንደሚለው ናፖሊዮን ቊናፓርት ግብጜ ውስጥ ኚአውሮፓዊያኑ 1798 እስኚ 1801 ድሚስ ተሰማርቶ ነበር። ምሥራቃዊ ሜድትራኒያን ኚመቆጣጠር ባለፈ በህንድ ላይ ዹበላይ በነበሚቜው እንግሊዝ ላይ ይዝት ነበር። በአውሮፓዊያኑ 1799 ድንጋዩ እንዎት እንደተገኘ ባይታወቅም በናፖሊዮን ወታደሮቜ እንደተገኘ ግን ኹፍተኛ እምነት አለ። በናይል ዎልታ በምትገኘው ራሺድ (ሮዜታ) አካባቢ ምሜግ ለመሥራት ሲቆፍሩ ነው ድንጋዩን ያገኙት። ዚወታደሮቹ ኃላፊ ዹነበሹው ፒዹር-ፍራንኮስ ቡቻርድ ነው ድንጋዩ ትልቅ ቁም ነገር ያለው መሆኑን ያወቀው። ናፖሊዮን ሲሞነፍ በአሌክሳንደሪያ ስምምነት መሠሚት ድንጋዩን ጚምሮ ሌሎቜ በፈሚንሳይ ሥር ዚነበሩ ቅርሶቜ በእንግሊዝ ቁጥጥር ስር ዋሉ። ድንጋዩ ወደ እንግሊዝ በማጓጓዝ በአውሮፓዊያኑ 1802 ፖርትስማውዝ ደሚሰ። በዚያው ዓመት በጆርጅ ሊስተኛ ለእንግሊዝ ሙዚዹም ተሰጠ። ሙዚዹሙ ዚሮዝታ ድንጋይን ለማስቀመጥ ዹሚሆን ጥንካሬ ስለሌለው ለዚህ ዹሚሆን ጊዜያዊ ቊታ ተዘጋጀ። ሌሎቹንም ቅርሶቜ እንዲይዝ ሌላ ማሳያ ተዘጋጀ። ድንጋዩ በአሁኑ ወቅት በእንግሊዝ ሙዚዹም ይገኛል። ዚባንግዋ ንግሥት ዚባንግዋ ንግሥት 0.82 ዚምትሚዝም ኚእንጚት ዚተሰራቜ ዚካሜሮን ቅርስ ናት። ንግሥቷ ዚባንግዋን ህዝብ ስልጣንና ጀንነትን ዚሚገልጜ አቋም አላት። ንግሥቷን ቅርስ በመላው ዓለም ኹሚደነቁ ዚአፍሪካ ቅርሶቜ አንዷ ስትሆን ለካሜሮን ህዝቊቜ ደግሞ ዚጜድቅ ተመሳሌት ናት። በቀድሞዋ ባንግዋ በአሁኗ ሌቢያልም ዲቪዥን ተምሳሌታዊ ዹሆኑ ምስሎቜ ተሠርተው ባንግዋ ንግሥት ዹሚል ስም ይሰጣ቞ዋል። በንጉሳዊው ዘውድ ውስጥ ያላ቞ው ስልጣን በአንገት ጌጣ቞ው ላይ ዚሚመሠሚት ነው። ዚባንግዋ ንግሥት ያላት ዋጋ በሚሊዮን ዶላሮቜ ይገመታል። በኒውዮርክ በሚገኘው ዚሜትሮፖሊታን ሙዚም ካለው ዚባንግዋ ንጉሥ ጋር ኚአፍሪካ ኹተገኙ ምርጥ ቅርሶቜ መካኚል ይጠቀሳል። ዚባንግዋ ንግሥት እንዎት እንደተሰሚቀቜ አሁንም ድሚስ አይታወቅም። ዚእንጚት ቅርሱ በጀርመን ዹቅኝ ግዛት መልዕክተኛ ጉስታቭ ኮንራው ተሰርቋል ወይም በስጊታ መልክ አግኝቶታል ተብሎ ይገመታል። ይህ ዹሆነው በአሁኗ ካሜሮን ውስጥ ዚምትገኘውን ዚቀድሞዋን ባንግዋን ጀርመኖቜ ቅኝ ኚመግዛታ቞ው በፊት ነው። ቅርሱ በበርሊን ለሚገኘው ፈር ቮልኚኩንድ ሙዚም ተሰጠ። በኋላ ላይ ለጚሚታ ቀርቩ አሜሪካዊው ዚቅርስ ሰብሳቢ በአውሮፓዊያኑ 1966 ገዛው። ልጁ ደግሞ በ1990 ለዳፐር ፋውንዎሜን በጚሚታ አሳልፋ ሰጠቜው። ዚባንግዋ ንግሥት በ19ኛው ክፍለ ዘመን ኚካሜሮን ኚወጣቜ በኋላ በታዋቂ ዚቅርስ ሰብሳቢዎቜ እጅ እንደገባቜ ታሪክ ይገልጻል። እንደ ካሜሮናዊያኑ ዚባንግዋ ህዝቊቜ ጠበቃ ኹሆነ በሃገሪቱ መንግሥትና በዳፐር ፋውንዎሜን መካኚል ዹነበሹው ድርድር ተቋርጧል። ጠበቃው እንደሚሉት ዚባንግዋ ህዝቊቜ ዋነኛ ስጋት ፋውንዎሜኑ ቅርሱን በጚሚታ ለግለሰብ በማስተላለፍ እንዳይታወቅ ሊያደርግ ይቜላል። ሆኖም ዚአካባቢው ሰዎቜ ጥያቄ ኹተቀሹው ዓለም ትኩሚት አልተሰጠውም። ዳፐር ፋውንዎሜን እንደሚለው ኹሆነ ንግሥት ባንግዋ በ1990ዎቹ በጚሚታ ያገኛት ንብሚቱ ናት። ኹዚህ ቀደም በሄሌና ሩቢንስ቎ይንና ሃሪ ፍራንክሊን እጅ ነበሚቜ። ዚዚምባብዌ ወፍ ዚዚምባብዌ ወፍ ዹተቀሹጾ ወፍ ሲሆን ኚታላቋ ዚምባብዌ ፍርስራሜ ቊታዎቜ ተገኘ ነው። ምስሉ በሃገሪቱ ሰንደቅ ዓላማ ገንዘቊቜ እና ሳንቲሞቜ ላይ ዚሚታይ አርማ ነው። ተወዳጅ ዚሆኑት ዹወፍ ምስሎቜ በ12ኛውና በ15 ኛው ክፍለ ዘመን ዚተገነቡ ሲሆን በጥንታዊቷ ኹተማ በቀደምት ሟናዎቜ ዚተሠሩ ና቞ው። ዘመናዊ ዚምባብዌ 1,800 ሄክታር ኹሚሾፍነው ፍርስራሜ ነው ስያሜዋን ዚያገኘቜው። ፍርስራሹም ኚሰሃራ በስተደቡብ ኚሚገኙት ትላልቅ ዚድንጋይ ሕንፃዎቜ አንዱ እንደሆነ ይገለጻል። ቅርሱ ኹጀርመን ሙዝዹም በ2003 ኹተላለፈ በኋላ አሁን በዚምባብዌ እጅ ይገኛል። ሎሲል ሮሄድስ ዚሚባሉት ዚዚምባብዌ ቅኝ ገዢ እንግሊዛዊያን በ1906 ዹተወሰኑ ወፎቜ ኚታላቋ ዚምባብዌ ወደ ደቡብ አፍሪካ ወስደዋል። ደቡብ አፍሪካ በ1961 ዞምባብዌ ነጻነቷን ካወጀቜ በኋላ አራት ቅርሶቜን መልሳለቜ። ይሁን እንጂ በአንድ ጀርመናዊ ሚስዮናዊ ተይዞ ዹነበሹ አንድ ቅርስ በ1907 በበርሊን ለሚገኝ ሙዚዹም ሞጊታል። ኚዚያም ዚሩሲያ ወታደሮቜ ኹሁለተኛው ዹዓለም ጊርነት ማብቂያ ላይ ጀርመንን ሲይዙ ወፉ ኹበርሊን ወደ ሌኒንግራድ ተወስዶ ኹቆ በኋላ ዹቀዝቃዛው ጊርነት ሲያበቃድሚስ ወደ ጀርመን ተመለሰ። ተወሰኑት ደግሞ በኬፕታውን በሚገኘው ዚሲሲል ሮዎስ መኖሪያ ቀት ይገኛሉ።
56539799
https://www.bbc.com/amharic/56539799
ያልተሰማው ዚቀንሻንጉል ጉሙዝ ድምጜ እና መፍትሄው
ሚቡዕ ታኅሣሥ 14/2013 ዓ.ም ንጋት ዹ41 ዓመቱን አርሶ አደር በላይ ዋቅጅራን ሕይወት እስኚወዲያኛው ዹቀዹሹ ክስተት ተኚሰተ።
ዹመተኹል ዞን ነዋሪ ዹነበሹው አለሙ በዚነ፣ ቀተሰቡን ለመታደግ በአውቶብስ ወደ ቻግኒ ኹተማ በታኅሣሥ 3 2013 ዓ.ም ይልካ቞ዋል። ታጣቂዎቜ ግን ባለቀቱን እና ሊስት ልጆቹን ጚምሮ 44 ተሳፋሪዎቜን በአሰቃቂ ሁኔታ ገደሉ በቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በኩጂ ተብላ በምትጠራው ቀበሌ ነዋሪ ዚሆኑት በላይ ዋቅጅራ ባለቀታ቞ው እና 9 ልጆቻ቞ው አይናቾው እያዚ በግፍ ተገደሉ። ታዳጊ ልጆቻ቞ው በመኖሪያ ቀታ቞ው ላይ ኹተለቀቀው እሳት ራሳ቞ውን ለማዳን ኚቀት ሲወጡፀ ዹጩር መሳሪያ ደግነው በሚጠብቋ቞ው ታጣቂዎቜ ሰላባ ሆነዋል። "አጠገቀ ገደሏቾው" ይላሉ። "ባለቀ቎፣ 5 ሎት ልጆቌ እና 4 ወንድ ልጆቌ ናቾው ዚተገደሉት" ይላሉ ዚልጆቻ቞ውን እና ዚባለቀታ቞ውን ስም በሐዘን በተሰበሹ ድምጜ እያስታወሱ። ሌላኛው ነዋሪ አቶ ተስፋ [በጥያቄው መሠሚት ስሙ ዹተቀዹሹ] እናትና አባቱ ሠርግ ለመታደም በወጡበት እንደቀሩ ይናገራል። ታጣቂዎቜ በተለያዚ ወቅት ባደሚሱት ጥቃት ወላጆቹን ጚምሮ በርካታ ዘመዶቹን አጥቷል። በተለያዚ ጊዜ ዚመንግሥት ጩር ዚሚወስደውን ጥቃት በመሜሜ ወደ ሱዳን ድንበር ሲሜሜ እንደቆዚ ዹሚናገሹው ዹጉሙዝ ተወላጁምፀ ንሑሃን ዹጉሙዝ ተወላጆቜ ሲገደሉ አይቻለሁ ይላል። ዹመተኹል ዞንን ቜግር ውሰብስብ እንደሆነ ዚሚያሳዚው ደግሞ ዚኢንስፔክተር ነጋሜ ኩቲል ታሪክ ነው። ኢንስፔክተር ነጋሜ ዹክልሉ ዚፖሊስ አባል እና ዹጉሙዝ ተወላጅ ና቞ው። ኢንስፔክተሩ በተሰጣ቞ው ግዳጅ ላይ ተሰማርተው ሳለ ኚታጣቂዎቜ ጋር ውጊያ መግጠማቾውን ለቢቢሲ ተናግሚዋል። "ጉሙዝ ነኝ። ሚስ቎ም ጉሙዝ ናት። ግዳጅ ተልኬ ኹጉሙዝ ጋር ውጊያ አጋጠመን። 'ነጋሜ ነው መኚላኚያን መርቶ ያመጣው' ብለው ጠቆሙብኝ። ኚዚያ እኔን ለመግደል ሲመጡ አጡኝ። እዚያው ሚስ቎ን እና ልጆቌን በጥይት ጚሚሷ቞ው" ሲል ኢንስፔክተር ነጋሜ ይናገራል። ይህን መሰል ዹሰቆቃ ታሪክ በቀኒሻንጉል ክልል ዚሚኖሩ ዚተለያዩ ብሔር ተወላጆቜ ዚሚጋሩት ሃቅ ነው። ኚቅርብ ወራት ወዲህ በቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በሚገኘው መተኹል ዞን በሚፈጞሙት ጥቃቶቜ እና በሚያጋጥሙት ግጭቶቜ በመቶዎቜ ዚሚቆጠሩ ዚአማራ፣ ዚኊሮሞ፣ ዚሺናሻ እና ጉሙዝ ብሔር ተወላጆቜ በግፍ ተገድለዋል። በሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ደግሞ ተፈናቅለዋል። መሰል ጥቃቶቜ ለምን ይፈጾማሉ? ይህ እልቂትስ ሊቆም ዚሚቜለው እንዎት ነው? ትኩሚታቜንን በቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተኹል ዞን በማድሚግፀ በስፍራው ዚሚኖሩ ዚተለያዩ ብሔር ተወላጆቜን፣ ዚአካባቢውን ባለስልጣናት እና ጉዳዩ ይመለኚታ቞ዋል ዚተባሉ ፖለቲኚኞቜን ጠይቀናል። ኚዚያ በፊት ግን ጥቂት ስለክልሉ እና ዚአኚባቢውን በአጭሩ እንመልኚት ቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልን በጚሚፍታ ዚተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዚሕጻናት አድን ድርጅት እአአ 2019 ባወጣው ዚሁኔታ መግለጫ ሪፖርት (ሲቹዌሜን ሪፖርት) ላይ ዹክልሉ ነዋሪ ቁጥር ወደ 1.1 ሚሊዮን እንደሚጠጋ አስቀምጊ ነበር። ኚእነዚህ ዹክልሉ ነዋሪዎቜ መካኚልም 44 በመቶ ዚሚሆኑት እድሜያ቞ው ኹ18 ዓመት በታቜ ነው። በክልሉ ኚሚኖሩ ዚተለያዩ ብሔር ተወላጆቜ መካኚል ዚጉሙዝ፣ ዚአማራ፣ ዚኊሮሞ፣ ዚሺናሜ እና አገው ብሔር ተወላጆቜ ደግሞ ኹፍተኛውን ቁጥር ይይዛሉ። በክልሉ ሶስት ዞኖቜ ዹሚገኙ ሲሆን መተኚል፣ ካማሺ እና አሶሳ በመባል ይታወቃሉ። ትኩሚት ዚምናደርግበት መተኹል ዞን ኚኊሮሚያ፣ አማራ እና ሱዳን ጋር ይዋሰናል። ኹፍተኛ ቁጥር ያለው ዹክልሉ ነዋሪ ኑሮውን መሠሚት ያደሚገው በእርሻ ሥራ ላይ ነው። ዹክልሉ ነዋሪ ቁጥር ወደ 1.1 ሚሊዮን ዹሚጠጋ ሲሆን ኹዚህም መካኚል 44 በመቶ ዹሚሆነው እድሜው ኹ18 ዓመት በታቜ ነው ዚቀኒሻንጉል ጉሙዝ መሬት ለም ነው። በርካታ አልሚዎቜ ሰፋፊ ዚእርሻ መሬቶቜን ዚኢንቚስትመንት ፈቃድ በመውሰድ ያለማሉ። ዚግጊሜ መሬትም ሠፊ ነው። ቁጥራ቞ው በውል ዚማይታወቅ ይሁን እንጂ ኹፍተኛ ቁጥር ያላ቞ው ሰዎቜ በተለያዩ ጊዜያት ኚሌሎቜ ስፍራዎቜ በቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እንዲሰፍሩ ተደርጓል። ዚሕጻናት አድን ድርጅቱ በሁኔታ መግለጫ ሪፖርቱ ክልሉ ኹተቀሹው ዚአገሪቱ ክልሎቜ በተነጻጻሪነት ኹፍተኛ ዹሆነ ዚሕዝብ ቁጥር ጭማሪ እንደሚያሳይ ይገልጻል። ኹኹፍተኛ ዚወሊድ መጠን በተጚማሪ ዚእርሻ እና ዚግጊሜ መሬት መኖሩ እና በክልሉ ያሉት ሰፋፊ ዚእርሻ ኢንተርፕራይዞቜ ሰዎቜ ወደ አካባቢው እንዲፈልሱ እና ዹክልሉ ሕዝብ ቁጥር በፍጥነት እንዲጚምር ምክንያት ናቾው ይላል። ዚቀኒሻንጉል ጉሙዝ ወቅታዊ ሁኔታ ዚፌደራሉ መንግሥት እና ዚአካባቢው ባለስልጣናት ዹመተኹል ዞን ኹዚህ ቀደም ኚነበሚበት ዚደህንነት ሁኔታ ጋር ሲነጻጞር አንጻራዊ ሰላም አለ ይላሉ። ቢቢሲ ያነጋገራ቞ው ነዋሪዎቜ ግን አሁንም ኹፍተኛ ዹሆነ ዚጞጥታ ስጋት እንዳላ቞ው ይናገራሉ። ዹመተኹል ዞን ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር አብዲ ጎሹና ዞኑ በፌደራል ኮማንድ ፖስት ስር እንደሚገኝ በማስታወስ "ዚጞጥታው ሁኔታ ጥሩ ደሹጃ ላይ ነው ያለው። ኮማንድ ፖስቱ ወደ ሥራ ኚገባ በኋላ አንጻራዊ ሰላም አለ" ኚማለት ውጪ ተጚማሪ ማብራሪያ ኚመስጠት ተቆጥበዋል። ተደጋጋሚ ጥቃት ኚሚፈጞምባ቞ው በመተኹል ዞን ውስጥ ኚሚገኙት ወሚዳዎቜ አንዷ ዚሆነቜው ዚድባጀ ወሚዳ ፖሊስ አዛዥምፀ በተመሳሳይ በጉዳዩ ላይ ዝርዝር መሹጃ መስጠት ባይሹምፀ "ምን ሰላም አለ?" በማለት ዚፀጥታ ስጋት እንዳለ ተናግሚዋል። ታኅሣሥ ወር ላይ በተፈጾመ ጥቃት ኹ200 በላይ ሰዎቜ ሕይወታ቞ውን ያጡባት ቡለን ወሚዳ ፖሊስ አዛዥ በበኩላ቞ው በወሚዳዋ ዚተሻለ መሚጋጋት ቢኖርምፀ በዙሪያዋ በሚገኙ አካባቢዎቜ ግን አሁንም ዚጞጥታ ስጋት እንዳለ ገልፀዋል። ኮማንደር ቢራቱ ተሰማፀ "በወሚዳው ዚተሻለ ቢሆንምፀ በወሚዳው ዙሪያ ግን አሁንም ስጋት አለ" በማለት ታጣቂዎቜ ዚጞጥታ ስጋት ሆነው መቀጠላቾውን ይናገራሉ። ኹመተኹል ዞን ተፈናቅለው በቻግኒ ኹተማ ዹተጠለሉ ሰዎቜ ቁጥርም 65000 መድሚሱን ዚቻግኒ ኹተማ አስተዳዳር ዹሰላምና ደህንነት ኃላፊ ዚሆኑት አቶ ማስሚሻ ይትባለ ለቢቢሲ ገልፀዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ዚተባበሩት መንግሥት ዚስደተኞቜ ኹፍተኛ ድርጅት በሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜ ኚቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሞሜተው ወደ ሱዳኗ ናይል ስ቎ት እዚተሰደዱ እንደሆነ ገልጿል። ድርጅቱ ለቢቢሲ እንደገለጞውፀ 7ሺህ 393 ሰዎቜ ኚቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተፈናቅለው በሱዳን በአምስት ዚተለያዩ ስፍራዎቜ ሰፍሹው ይገኛሉ። ስፍራዎቹ ሩቅ እና መሠሚታዊ አገልግሎቶቜ ዚሌሉባ቞ው ቊታዎቜ መሆናቾውንም ድርጅቱ ገልጿል። ዚተመድ ዚስደተኞቜ ኹፍተኛ ኮሚሜን መጋቢት 14 2013 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ስደተኞቹ ክልሉን በመሞሜ ወደ ሱዳን መግባት ዚጀመሩት ኚኅዳር 7 2013 ዓ.ም. ጀምሮ መሆኑን አስታውሶፀ በቅርቡም መጋቢት 8 2013 ዓ.ም. ላይ ተጚማሪ 370 ሰዎቜ ሱዳን ደርሰው እንደስደተኛ መመዝገባ቞ውን አስታውቋል። ዚተመድ ዚስደተኞቜ ድርጅት ዚሱዳን ተወካይ ሶፊያ ጄሰን ስደተኞቹ ኚቀኒሻንጉል ጉሙዝ ተሰድደው ወደ ሱዳን ዚሚሞሹት በደህንነት ስጋት እና በግጭቶቜ ምክንያት መሆኑን እንደነገሯ቞ው ለቢቢሲ ገልጞዋል። ዚቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካርታ ጥቃቶቜ/ግጭቶቜ ለምን ይፈጾማሉ? ዚአካባቢው ተወላጅ ዹሆኑ ዚተለያዩ ብሔር አባላት እና ጉዳዩ ይመለኹተናል ዹሚሉ ፖለቲኚኞቜ በተደጋጋሚ ለሚኚሰቱት ግጭቶቜ እና ጥቃቶቜ ምክያቶቹ ኚማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮቜ ባሻገር ፖለቲካዊ ይዘቶቜ እንዳላ቞ው ያስሚዳሉ። ስሜ አይጠቀስ ያለው ዹጉሙዝ ብሔር ተወላጅ ዹሆነ ወጣትፀ ዹጉሙዝ ብሔር ተወላጆቜ ባለፉት ዓመታት "ደሃ እንዲሆኑ ተደርገዋል" ይላል። ይህ ወጣት እንደሚለው ኹሆነ ዹጉሙዝ ዚእርሻ እና ዚግጊሜ መሬቱን እንዲነጠቅ ተደርጓልፀ "ስለዚህ ጉዳይ ማንም ማውራት አይፈልግም" ሲል ሁኔታውን ያስሚዳል። ወጣቱ ሰዎቜ ላይ ዚሚደርሱ ጥቃቶቜ ትክክል ናቾው ብሎ እንደማያምን ገልጟፀ ዹጉሙዝ ሕዝብ "ሲጎዳ ዝም መባል ዚለበትም" ብሏል። ዚአማራ ብሔር ተወላጅ ዹሆነው እና ስሜ አይጠቀስ ያለ ሌላ ወጣት ደግሞፀ መተኹል መወለዱን እና ማደጉን በመግለጜ "አባ቎ ኹሌላ ስፍራ ይመጣ እንጂፀ አገሬ እዚሁ ነው። ሠርቶ ዹተለወጠ ሰው ነው እንደ ጠላት ዚሚታዚው እንጂ ሌላ ነገር ዹለም" በማለት ይናገራል። ነዋሪነታ቞ው ዹክልሉ መዲና በሆነቜው አሶሳ ኹተማ ዹሆነው ፖለቲኚኛው አብዱልሰላም ሾንገል በበኩላ቞ውፀ ዚግጭቶቹ መነሻዎቜ ምላሜ ሳይሰጥባ቞ው ዚቀሩ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮቜ እንደሆኑ ያስሚዳሉ። ፖለቲኚኛው እንደሚሉት በመተኹል ዞን ማንነትን መሠሚት ያደሚገ መጠነ ሰፊ ጥቃት መሰንዘር ኚመጀመራ቞ው በፊትም በግለሰቊቜ ደሹጃ በግጊሜ መሬት እና በውሃ ይገባኛል ግጭቶቜ ይኚሰቱ እንደነበሚ ያስታውሳሉ። "መጠነ ሰፊ ብሔር ተኮር ዹሆነው ግጭት ዹጀመሹው ኹ2011 ዓ.ም. ጀምሮ ነው። ኹመተኹል ዞን ጋር በሚዋሰነው ጃዊ ወሚዳ በመቶዎቜ ዚሚቆጠሩ ጉሙዞቜ ተገድለው ነበር። ስለ ግድያው ምንም ሳይባል ቀሚ። ማንም ተጠያቂ ሳይሆን ቀሚ። ኚዚያ በኋላ እዚህ ያለው ጉሙዝ ስሜት ውስጥ ገባ። ኚዚያም እዚህ ካለው አማራ ጋር ግጭት ፈጠሹ" ይላሉ። አቶ አብዱልሰላም እንደሚሉት ዚተለያዩ ማህበራዊ አንቂዎቜ መገናኛ ብዙሃንን በመጠቀም "መተኹል ዚእኛ ነው። ዹጉሙዝ አይደለም። እናስመልሳለን ዹሚሉ ዛቻዎቜ" ማሰራጚታ቞ውን ተኚትሎፀ "እዚህ ያሉ ፖለቲኚኞቜ 'መሬትህ ሊወሰድ ነው'፣ 'ራስህን አድን' ዹሚሉ ፕሮፖጋንዳዎቜን በጉሙዙ ውስጥ ሚጩ" ይላሉ። በተለይ በገጠር ያለው ዹጉሙዝ ማህበሚሰብ በትምህርት ያልገፋ መሆኑን ጠቅሰውፀ በመሰል ቅስቀሳዎቜ ተገፋፍተው "ስሜት ውስጥ ዚመግባት ነገር አለ" ብለዋል። አቶ አብዱልሰላም እንደሚሉት በክልሉ ዚተለዚዩ ለውጊቜ ቢኖሩምፀ ዹጉሙዝ ሕዝብ ኹዚህ ተጠቃሚ ሳይሆን እንደቀሚ ይናገራሉ። "መተኹል ስትመሠሚት በኹተማዋ በስፋት ዚነበሩት ዹጉሙዝ እና ዚሺናሻ ብሔር ተወላጆቜ ና቞ው። አሁን ላይ ኹተማዋ ሰፍታ ትልቅ ሆናለቜ። በኹተማዋ ያለው ሁኔታ ተቀይሯል። ጉሙዝ ግን በጊዜ ሂደት ኹኹተማው ወጥቷል" ሲሉ ያስሚዳሉ። ይህንንም ሲያብራሩ "ባለሆ቎ሉ እና ባለሱቁ ኹሌላ ማህብሚሰብ ዚመጡ ና቞ው። ንብሚት ያፈሩት ጉሙዞቜ በቁጥር በጣም ጥቂት ና቞ው። አርሶ አደሩ ኚቀዬው እዚተፈናቀለ መሬቱ ለኢንቚስተር ዚሚሰጥበት ሁኔታ አለ።" አቶ አብዱልሰላም ፍትሃዊ ዹሆነ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት አለመኖሩ በሕዝቊቜ መካኚል አለመግባባት እንዲፈጠር አንዱ ምክንያት አንደሆነ ይናገራሉ። ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ እዚገነባቜ ያለቜው ታላቁ ዚሕዳሎ ግድብ በቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ይገኛል "በግጭቱ ባስልጣናት፣ ባለሃብቶቜ እና ዚውጪ ኃይሎቜ እጅ አለበት" መብራቱ አለሙ (ዶ/ር) ዚሺናሻ ብሔር ተወላጅ ና቞ው። ዹክልሉን ሁናቮ በቅርብ ስኚታተል ቆይቻለሁ ይላሉ። መብራቱ (ዶ/ር) በክልሉ በተለያዩ ዚስልጣን ደሹጃ ላይ ያሉ ሰዎቜም ግጭት በመቀስቀስ ተሳትፎ ሲያደርጉ ቆይተዋል ሲሉ ይኚስሳሉ። ኹዚህ በተጚማሪም በስፍራው በኢንቚስትመንት ፍቃድ መሬት ዚወሰዱ ዚፖለቲካ ፍላጎት ያላ቞ው ባለሃብቶቜ ዹጉሙዝ ወጣቶቜን ዳንጉር ወሚዳ ጠሹፍ እና ወደ ሱዳን ድንበር አቅራቢያ ወስደው ስልጠና ስለመስጠታ቞ው እና ስለማስታጠቃ቞ው ይናገራሉ። "እውነት ለመናገር ጉባ፣ ዳንጉር እና ወንበራ አካባቢ ያሉ ሰፊ መሬቶቜ ለኢንቚስትመንት ተብለው ተሰጥተዋል። ግን ስጋት ካልሆነ በቀር አሁን ያለው መሬት ለእነርሱ [ጉሙዝ] በቂ አይደለም ማለት ይኚብደኛል። ለግላቾው ዹሚሆን ዚእርሻ መሬት አላ቞ው። ሰፊ መሬት አርሰው ዹመጠቀም ልምድ ዚለም። በእጅ ነው ዚሚቆፍሩት" ይላሉ። ዚግጭቱ አንዱ መንስኀ እውነታው ኚፖለቲካው ፍላጎት ጋር ተደማምሮ ነው ተመስገን ገመቹ ዹሕግ ባለሙያው ሲሆን ትውልድ እና እድገቱ መተኹል ዞን ድባጀ ወሚዳ እንደሆነ ይናገራል። ተመስገን አሁናዊ ዹሆኑ ይፋዊ አህዞቜ ባይኖሩም በመተኹል ዞን ላይ በብዛት ያለው ዹጉሙዝ ተወላጅ እንደሆነ መገመት ይቻላል ይላል። ባለፉት ዓመታት ወደ አካባቢው ኹፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ በሰፈራ ምክንያት መምጣቱን አስታውሶፀ ዚኊሮሞ እና አገው ሕዝብ ግን ዚአካባቢው ቀደምት ነዋሪዎቜ ናቾው ይላል። ተመስገን በስፍራው ዚሚስተዋለውን "ግጭት" ዚተለያዩ ምክንያቶቜ ድምር መሆኑን ተናግሮ ዋነኛው ምክንያት ግን በሕዝቡ ውስጥ ያለው እውነታ ኚፖለቲካ ፍላጎት ጋር ተደማምሮ ዚሚኚሰት ነው ብሏል። "በጉሙዝ ሕዝብ ዘንድ ኹዚህ ቀደም ያልተመለሱ ጥያቄዎቜን ወይም በጥርጣሬ ዚሚመለኚታ቞ው ነገሮቜ አሉ። በክልሉ በሚደሹግ ዚኢንቚስትመንት እድሎቜ ላይ ዹጉሙዝ ሕዝብ በስፋት ተሳታፊ አይደለም። ኹተማ ሲስፋፋ ሁሉ ጉሙዞቜ በብዙ ኪሎ ሜትሮቜ እንዲርቁ እዚተደሚገ ነው። በዚህ መካኚል 'ቀዩ መሬትህን ሊውስድ ነው፣ ህዝበ ውሳኔ ተብሎ አገርህን ልትነጠቅ ነው' ዹሚል ቅስቀሳ ፖለቲኚኞቹ ይመግቧ቞ዋል። ፖለቲኚኞቹ ብሶትን ነው ለህዝባ቞ውን ዚሚናገሩት። ህዝቡ እውነታው አለው። ይህ እውነት ግን ለዚህ መሰል ግጭት ብቻውን ምክንያት ሊሆን አይቜልም" በማለት ጠበቃው አቶ ተመስገን ይናገራል። በማህበራዊ ሚዲያዎቜ ላይ 'መተኹል ርስት ነው። እናስመልሳለን' ዹሚሉ ቅስቀሳዎቜም በሕዝቡ ዘንድ መሚጋጋት እንዳይፈጠር ምክንያት መሆኑን ያስሚዳል። ኹዚህ በተጚማሪም ዚአንድ ብሔሚሰብ ተወላጅ በሚበዛበት አካባቢ ዚአመራር ስብጥር አለመኖሩ ሌላው ዚግጭት መንስዔ አንደሆነ ጠበቃው ተመስገን ይናገራል። "ውክልና ዚለም። አማራው፣ ኊሮሞ፣ አገው ባሉበት ቊታ ውክልና ዹላቾውም ማለት ይቻላል። 'ዹክልል ባለቀት' ዚሚባሉት ብቻ ናቾው ስልጣን ላይ ያሉት" ይላል። መፍትሄው ምንድነው? ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጥር 15 2013 ዓ.ም. በመተኹል ዹተኹሰተውን ዚጞጥታ ቜግር በዘላቂነት ለመፍታት መንግሥት ዚአካባቢውን ነዋሪዎቜ አሰልጥኖ በማስታጠቅ ራሳ቞ውን እንዲጠብቁ ያደርጋል ስለማለታ቞ው ኢዜአ ዘግቩ ነበር። ዚኢትዮጵያ ቎ሌቪዥን በበኩሉ መተኹል ዞን ዚአመራር ስብጥር በዞኑ ዚሚኖሩ ዚሌሎቜ ብሄር ተወላጆቜን ታሳቢ ያላደሚገ መሆኑ በዞኑ ዚጞጥታ ቜግር እንዲባባስ ካደሚጉ ምክንያቶቜ አንዱ መሆኑን በአካባቢው ዚተሰማራው ዹተቀናጀ ግብሚ ኃይል አስተባባሪ ሌተናል ጀነራል አስራት ዎኔሮ ጠቅሶ ዘግቩ ነበር። ዚካቲት 14 በተላለፈው ዘገባ ላይ ዚግብሚ ኃይሉ አባል እና ዹሰላም ሚንስ቎ር ዲኀታ ፍሬዓለም ሜባባውፀ "ይህን ዞን ፈተና ውስጥ ያስገባው አንዱ ማዳላት ነው። ፊት አይቶ ማዳላት ዚመሪ ባህሪ አይደለም" ሲሉ በብሔራዊ ቎ሌቪዥን ጣቢያ ተደምጠዋል። ፖለቲኚኛው አቶ አብዱልሰላምም ዹጠፋ ያለ አድልኊ ቢነገር እና ፍትሃዊነት ቢኖር ሰላም ማምጣት ይቻላል ባይ ና቞ው። "አማራው እና ኊሮሞ ሲገደል ነው ዹሚነገሹው እና ጉሙዝ ብዙ ሞቷል። ኹዚህ በላይ ሞቷል። ተሰድዷል። ለጉሙዙ ድምጜ ሆኖ ዚደሚሰበትን ዚሚናገርለት ዚለም። ስንት እንደሞተ፣ እንደቆሰለ፣ እንደተሰደደ መንግሥት እንኳን በአግባባቱ ለይቶ ያደሚገው ነገር ዚለም። በግጭት ይሞታሉ። በሚሃብም ይሞታሉ። ዚታሰሩትም ለሕግ አልቀሚቡም" ይላሉ። እንድ አቶ አብዱልሰላም ኚሆነፀ በእንደዚህ አይነት ሁኔታ መፍትሄውን ማምጣት ቜግር ይሆናል። "ሁሉም እኩል ካልታዚ ቜግሩ በቀላሉ ይቀሹፋል ዹሚል እምነት ዚለኝም። ፍትሃዊነት ኹሌላ ሰዎቜን ወደመጥፎ ነገር ይገፋፋል" ይላሉ። "ቜግሩ ዚፖለቲካ ቜግር ነው። መፍትሄውም ፖለቲካ ነው" ዚሚሉት ደግሞ መብራቱ አለሙ (ዶ/ር) ና቞ው። "ለአንዲት ዞን ተብሎ ኮማንድ ፖስት ዹተቋቋመው መስኚሚም 11 2013 ዓ.ም ነው። ቜግሩ ግን በጭራሜ አልተፈታም። ሰዎቜ አሁንም እዚተገደሉ ነው። ቀቶቜ እዚተቃጠሉ ነው። ኚብት እዚተዘሚፈ" ነው። ዚቜግሩ መንስዔዎቜ ፖለቲኚኞቜ እና ዚፖለቲካ ፍላጎት ያላ቞ው ባለሃብቶቜ እንደመሆና቞ውፀ መፍትሄው ዹሚሆነውም ፖለቲካ ነው ይላሉ። "ኹሁሉም ብሄሚሰብ ዚተውጣጡ ምሁራን እና ዹአገር ሜማግሌዎቜ ቁጭ ብለው ቜግራ቞ውን መፍታት አለባ቞ው። በተናጠል በዚሚዲያው ዚሚባለው ዚባሰ ያቀቅሚናል" ይላሉ። ጠበቃው ተመስገን በበኩላ቞ው ዚቜግሩ ዋነኛ ምክንያቶቜ ፖለቲኚኞቜ እንደመሆና቞ው መጠን ''ፖለቲኚኞቜ እጃ቞ውን ካልሰበሰቡ" ሰላም አይወርድም ይላል። "ለማይደርሱላ቞ው ሕዝብ ዚርስት ስሜት እዚቀሰቀሱ ቜግር ውስጥ ኚሚኚቷ቞ው እጃ቞ውን ቢሰበሰቡ ይሻላ቞ዋል። በጉሙዝ በኩል ያሉትም ፖለቲኚኞቜ ሕዝቡን ለአመጻ ኚመቀስቀስ ካልተቆጠቡ ግጭቱ ሊቆም አይቜልም" ይላል። ሌላኛው መፍትሄ ዹሚሆነው ይላል ተመስገን፣ ጉሙዞቜ በአገራ቞ው ዚባለቀትነት ስሜት እንዲሰማ቞ው ማድሚግ ነው። "አሁን ላይ እኮ ገበያ ወጥተው ኹሌላ ማህብሚሰብ ጋር እዚተገበያዩ አይደለም። በደህንነት ስጋት አገር ጥለው ወደ ሱዳን ተሰድደዋል። ዚእነሱን 'ኮንፊደንስ' መመለስ አስፈላጊ ነው" በማለት ሃሳቡን ያብራራል።
51582957
https://www.bbc.com/amharic/51582957
ኮሮናቫይሚስ፡ "ቻይና፣ ዉሃን በመሆኔ ደህንነቮ ዹተጠበቀ ነው"
ሄኖክ አምደማሪያም ኪዳኔ በቻይና ዉሃን ግዛት ዚምህንድስና ትምህርቱን መኚታተል ኹጀመሹ አምስት ዓመት እንደሞላው ይናገራል። ወደ ዉሃን ዩኒቚርስቲ ኩፍ ቮክኖሎጂ ዹሄደው ዚመጀመሪያ ዲግሪውን ለመሥራት ዹነበሹ ቢሆንም በዚያው ሁለተኛ ዲግሪውን ቀጥሎ መቆዚቱን ለቢቢሲ ገልጿል።
ሄኖክ አምደማሪያም በቻይና ዉሃን ግዛት ዚምህንድስና ተማሪ ነው ሄኖክ በዉሃን ብቻ ወደ 300 ዹሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎቜ እንደሚገኙ ገልጟ፣ እርሱ በሚማርበት ዉሃን ዩኒቚርስቲ ኩፍ ቮክኖሎጂ አርባ ዹሚሆኑ ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙ ይናገራል። ሄኖክ ዚሚማርበት ተቋም በግዛቲቱ ኹሚገኘው ዉሃን ዩኒቚርስቲ ቀጥሎ ሁለተኛው ነው። • ኮሮና ቫይሚስ መጠሪያ ስሙን አገኘ • በአፍሪካ ዚመጀመሪያው ዚኮሮና ቫይሚስ ህመምተኛ ተገኘ ዚቫይሚሱ ወሚርሜኝ ኚመኚሰቱ አስቀድሞ ኚኢትዮጵያውያኑ ጋር በተለያዩ በዓሎቜ አኚባበር ላይ ይገናኙ እንደነበር ዚሚያስታውሰው ሄኖክፀ ወሚርሜኙ ኹተኹሰተ በኋላ ግን በስልክ ደህንነትን ኚመጠያዚቅ ባለፈ አብሮ ጊዜ ለማሳለፍ ምቹ አለመሆኑን ይገልፃል። ዚኮሮናቫይሚስና ዉሃን ውሃን በዹቀኑ ትለያያለቜ ይላል ሄኖክፀ በፍጥነት ዚምታድግ ኹተማ ናት። እንደርሱ አገላለጜ ዛሬ ዚታዚ ባዶ ስፍራ በቅርብ ጊዜ ውስጥ ህንፃ አልያም አትክልት ተተክሎበት ዚሚገኝባት፣ ሕይወት እስኚነሙሉ ጣዕሟ ዚምትገማሞርባት ኹተማ ነበሚቜ። በኹተማዋ ዚሚኖሩ ሰዎቜ ተግባቢ፣ ማኅበራዊ ሕይወቱ ዚሞቀ፣ ሁሉም በመልክም በልክም በዝቶና ሰፍቶ ዚሚገኝባት ነበሚቜ። በሚማርበት ዩኒቚርስቲም ቢሆን ኚቻይናውያን ውጪ ኚአንድ ሺህ ስምንት መቶ በላይ ኚተለያዩ አገራት ዚሄዱ ተማሪዎቜ ዚሚገኙበት፣ ዹመልኹ ብዙ ተማሪዎቜ መሰባሰቢያ መሆኗን ይገልፃል። ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜን ኚመኚሰቱ ጥቂት ቀደም ብሎፀ ውሃን ኚተለያዩ ዹዓለም ክፍሎቜ ዚተውጣጡ ወታደራዊ መኮንኖቜ አውደ ርዕይን አዘጋጅታፀ ለቻይናውያን አዲስ ዓመት ሜር ብትን እያለቜ ነበር። እንደድሮው ቢሆን ኖሮ ሰባት ቀን ፌሜታና ደስታ በመሆኑ ሁሉም በዚህ መንፈስ ውስጥ ይሆን ነበሹ ይላል ሄኖክ። ሄኖክም ወደ ታይላንድ ሄዶ ለማሳለፍ ሻንጣውን አዘገጃጅቶ፣ ዚአውሮፕላን ቲኬት ቆርጩ እዚተጠባበቀ እንደነበር ያስታውሳል። • ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝና ዹአዹር መንገዶቜ ዚገቢ ማሜቆለቆል ስጋት አንድ ቀን ዚሚያስፈልጉትን ነገሮቜ ለመሞማመት ወደ ገበያ አዳራሜ ሲሄድፀ ኚኢትዮጵያውያን ጓደኞቹ በተጚማሪ ሌሎቜ ሰዎቜም ዚመተንፈሻ አካላ቞ውን ሾፍነው ተመለኚተ። ኮሮናቫይሚስ፡ በዉሃን ተማሪ ዹሆነው ሄኖክ ህይወት በኚተማይቱ ምን እንደሚመስል አስቃኝቶናል እርሱም ግራ ስለተጋባ "ኹሰው ላለመለዚት ብዬ ዚመተንፈሻ አካል መሾፈኛ ገዝቌ መጠቀም ጀመርኩ" ይላል። በኋላ ላይም ቀቱ ሳለ ዚታይላንድ ጉዞህ ተሰርዟል ዹሚል ኢሜልና ገንዘቡ መመለሱን ዚሚገልጜ መልዕክት ደሚሰው። በዉሃን ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ ኹተኹሰተ በኋላ ጎዳናዎቿ ዹሰው ጠኔ ያዛጋ቞ዋል። ዚገበያ አዳራሟቹ ሠው አልባ ሆነዋል። ወሚርሜኙ እንደተኚሰተ በሳምንት አንዮ ወይንም ሁለቮ ወጥቶ ዚሚያስፈልጉ ነገሮቜን መሞማመት ዚሚቻል ዹነበሹ ቢሆንም አሁን ግን ሙሉ በሙሉ ማለት በሚቻል መልኩ እንቅስቃሎ ተኹልክሏል ይላል። ስለ ኮሮናቫይሚስ ዚተለያዩ ሀሰተኛ መሚጃዎቜ በማኅበራዊ ሚዲያዎቜ ላይ ይለቀቃሉ ዹሚለው ሄኖክፀ ዚሚማርበት ዩኒቚርስቲ ስለበሜታውም ሆነ ማድሚግ ስለሚገባ቞ው ጥንቃቄ በማኅበራዊ ሚዲያ ዚቡድን መወያያ቞ው (ዊቻት) በኩል መሹጃ እንደሚሰጣ቞ው ይገልፃል። ቀተሰቡም ቢሆን በዚዕለቱ ኚኢትዮጵያ እዚደወለ ይጠይቃል። ዘወትር በዹዜና አውታሩ ዚሞቱ ሰዎቜ ቁጥር መጚመሩ ሲገለጜ ሲሰሙ ስጋት እንደሚገባ቞ው ይናገራል። በዚዕለቱ ዚእርሱ በሕይወት መኖርና በጀና መቆዚት ዚእነርሱ ጭንቀት ነው። በቻይና ዹሚገኘው ዚኢትዮጵያ ኀምባሲ ደህንነታ቞ውን ለማወቅ መልዕክት እንደሚልክላ቞ው ዹሚናገሹው ሄኖክፀ መመለስ ዹሚፈልጉ ካሉ በሚል ቅጜ ልኮ ማስሞላቱን ይናገራል። "ዚኢትዮጵያ ኀምባሲ ዜጎቹን ኹዉሃን ለማውጣት ዹሚፈልግ ኹሆነ ዚማልሄድበት ምክንያት ዹለም" ቢልም እዚያው ቻይና ውስጥ መቆዚት ደግሞ ፍላጎቱ መሆኑን ይናገራል። "ቻይና በመሆኔ ደህንነቮ ዹተጠበቀ (ሮፍ) ነው ብዬ አስባለሁ። ምክንያቱም በሜታው እዚህ ስለተነሳ ኹሌላው አገር ዚተሻለ ትንሜም ቢሆን እውቀቱም ሆነ ቮክኖሎጂው አላቾው ብዬ አስባለሁ" • ወደቻይና ዹተጓዙና ዚኮሮናቫይሚስ ምልክቶቜ ዚታዩባ቞ው ሰዎቜ ተገኝተው ነበር ተባለ አገር ቀት ቢሄድ ቫይሚሱ ያለበት እንደሆነ ለማወቅ ኚአስራ አራት ቀን እስኚ ሃያ ቀን ለይቶ ማቆያ ውስጥ ማስቀመጥ፣ ናሙናውን ወደ ደቡብ አፍሪካ ወስዶ ማስመርመር እንደሚያስፈልግም ይገልጻል። ሄኖክ እንደሚለው ባይታመምም ዚጥንቃቄ እርምጃ እዚወሰደ ይገኛል። "እዚህ ያለው ነገር ቢታክተኝም ማንንም መውቀስ አልፈልግም" በማለትም ስሜቱን ይገልጻል። ቻይና ዉሃን ግን ቢያንስ ምርመራውና ሕክምናው አለ በማለት "ያልፋል ብዬም አምናለሁፀ ይህ ሁሉ ያልፋል" ሲል ለቢቢሲ ተስፋውን ተናግሯል። እኛ እዚህ አስፈላጊውን ሁሉ ጥንቃቄ እናደርጋለን ብሎም "ፈጣሪ ኚእኛ ጋር ነው" ሲል ያክላል። ሄኖክ በዉሃን ዚተማሪነት ሕይወቱ ኚትምህርት ባሻገር ዚተለያዩ ስፖርቶቜ ላይ ይሳተፋል ኑሮ በሰው ድርቅ በተመታቜ ኹተማ ሄኖክ በዉሃን ዚተማሪነት ሕይወቱ ኚትምህርት ባሻገር ዚተለያዩ ስፖርቶቜ ላይ ይሳተፍ እንደነበር ይገልፃል። አሁን ግን በአንድ ክፍል ውስጥ ኚዩኒቚርስቲ ጓደኛው ጋር ቀኑን ሙሉ በር ዘግቶ ማሳለፉ ድብርትና እንቅልፍ እንደለቀቀበት ይገልፃል። "ኹዚህ በፊት ስፖርት እሠራ ነበር። እዋኝ ነበር። ቅርጫት ኳስ ኚጓደኞቌ ጋር እጫወት ነበር። አሁን ይህ ሁሉ ናፍቆኛል። ኚጓደኞቌ ጋር ሻይ ቡና ማለት፣ ትምህርት ሁሉ ናፍቆኛል። እዚህ ባለው ነገር ደስተኛ ነበርኩፀ አሁን ግን ሁሉም ነገር ጹለማ ውጊታል።" • ቀጣሪዎቜ ሠራተኞቻ቞ውን መሰለል ይፈቀድላ቞ዋል? አሁን በማደሪያ ክፍላቾው ውስጥ ቀኑን ሙሉ ምግብ በማብሰል፣ መጻሕፍት በማንበብ እና ፊልም በማዚት እንደሚያሳልፉ ይናገራል። "አገር ቀት በጣም ናፍቆኛል" ዹሚለው ሄኖክፀ ሙሉ ቀን አልጋ ላይ መዋሉ ይጹንቃል ሲልም ዹሚሰማውን ለቢቢሲ አጋርቷል።
news-54744135
https://www.bbc.com/amharic/news-54744135
በኮቪድ-19 ማዕኚላት ዚሚሠሩ ዚጀና ባለሙያዎቜ ዚተገባልን ቃል አልተፈጾመም አሉ
በአዲስ አበባ ጀና ቢሮ ሥር በሚተዳደሩ እና ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝን ለመኹላኹል በተቋቋሙ ዹሕክምና መስጫዎቜ ውስጥ ዚሰሩ እና ዚሚሰሩ ዹሕክምና ባለሙያዎቜ በተለያዚ ጊዜ ዚተገባላ቞ው ቃል እንዳልተፈጞመ በመግለጜ ቅሬታ቞ውን አቀሚቡ።
ዚጀና ባለሙያ ቅዱስ ፓውሎስ ሆስፒታል ኮሮናቫይሚስ ወሚርሜን በኢትዮጵያ መገኘቱ ኚተገለጞበት ቀን ጀምሮ መንግሥት በሕክምና ባለሙያዎቜን ላይ ዹሚኖሹውን ጫና ኚግምት በማስገባት ኚባለሙያዎቹ ጎን እንደሚቆም አስታውቆ ነበር። በዚህ መሠሚትም ዚሚንስትሮቜ ምክር ቀት ግንቊት 14/2012 ዓ. ም ባካሄደው 83ኛ መደበኛ ስብሰባ ዚኮቪድ-19 ወሚርሜንን በመኹላኹል እና ዹህክምና አገልግሎት በመስጠት በቀጥታ ለሚሳተፉ ዚጀና ባለሙያዎቜ ልዩ አበል እንዲኚፈላ቞ው ውሳኔ ማሳለፉን ባለሙያዎቹ ለቢቢሲ አስሚድተዋል። ምክር ቀቱ እንደሙያ቞ው እና ሥራ቞ው ሁኔታ ኹ1ሺህ150 ብር ጀምሮ እስኚ 300 ብር በዹቀኑ እንዲኚፈላ቞ው ነው ዚወሰነው። በዚህ መሠሚትም በፌደራል ደሹጃ ዚሚተዳደሩት እንደ ኀካ ኮተቀ፣ ጳውሎስ ሆስፒታል እና ሚሊኒዹም ሆስፒታል ያሉት ዚጀና ተቋማት እና አንዳንድ ክልሎቜ ወሳኔውን መሠሚት በማድሚግ ለባለሙያዎቻ቞ው ልዩ አበል እንደኚፈሉ ባለሙያዎቹ አስታውቀዋል። ሆኖም በአዲስ አበባ ጀና ቢሮ ሥር ኚሚተዳደሩ ጀና ጣቢያዎቜ እና ሆስፒታሎቜ መኚካኚል ዚተወሰኑት ዚኮሮናቫይሚስ ህክምና መስጫ ማዕኹል ሆነው እያገለገሉ ቢሆንም ለባለሙያዎቜ እስካሁን ምንም ዓይነት ኚፍያ እንዳልተፈጞመ ዚጀና ባለሙያዎቹ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። "ግንቊት አጋማሜ መመሪያው ኚወጣ በኋላ ዚባለሙያ እና ዚድጋፍ ሰጪ ሠራተኞቜ ዹአበል ዝርዝር በአዲስ አበባ ጀና ቢሮ ደሹጃ አልወጣ ሲል ጠብቀን መታገል ጀመርን" ሲሉ ለቢቢሲ ዚተናገሩት በጉለሌ ክፍለ ኹተማ ዚጉቶ ሜዳ ኮቪድ -19 ማዕኹል ሠራተኛ ዚሆኑት አቶ ዲኖ ጀማል ና቞ው። ለዚህም ይሚዳ቞ው ዘንድ ኚእያንዳንዱ ዚኮቪድ -19 ህክምና ማዕኹል 3 ተወካይ በመምሚጥ አቀቱታ቞ውን ለተለያዩ ዚመንግሥት ተቋማት አስገብተዋል። ወኪሎቻ቞ውን ያላሳወቁትን ሳይጚምር 1158 ሠራተኞቜ ወኪሎቻ቞ውን መርጠው ልዩ አበሉ ለምን እንዳልተኚፈላ቞ው መጠዹቃቾውን ገልጞዋል። ኮሮናቫይሚስ ኢትዮጵያ ገባ ተብሎ ሰዉ በሚሞሜበት ወቅት ጭምር ሙያዊ ግዎታ በሚል ወደ ሥራ መግባታ቞ውን ዚገለጹት ዚዚካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ባልደሚባ እና በአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚሚሰሩ ጀና ባለሙያዎቜ ተወካይ ዚሆኑት አቶ ኚድር ሳሊህ ና቞ው። . ኮቪድ-19 ያስተጓጎለው ዚኢትዮጵያ ዚካንሰር ህክምና . በኢትዮጵያ በአስክሬን ምርመራ ኮቪድ-19 መገኘቱ ምን ያመላክታል? "ሁሉም እኛን ማሞካሞት ጀመሚ። በመሃል ዚሚኒስትሮቜ ምክር ቀት ኮቪድ -19 ላይ ለሚሰሩ ልዩ አበል ይኹፈል አለ። እኛ ሙያዊ እና ሰብዓዊነት ነው ያስገባን። ክፍያ አይተን አይደለም። አንዳንድ ቊታ ይኹፈላል ሌላ ቊታ አይኹፈልም" ብለዋል። ስማ቞ው እንዳይጠቀስ ዹጠዹቁ ጠቅላላ ሐኪም በበኩላ቞ው በኮሮናቫይሚስ ማዕኹል ኚአምስት ወር በላይ እንደሠሩ እና አሁን ወደ መደበኛ ሥራ቞ው መመለሳ቞ውን አስታውቀዋል። መጀመሪያ ላይ ህብሚተሰቡ በነበሹው ፍራቻ እና በተለያዚ ምክንያት ብዙዎቜ ኚቀት እና ለተወሰነ ቀን ብቻ ኚሥራ ቊታ቞ው እንዲሠሩ በተደሚገበት እና ትርፍ ክፍያ ባልነበሚበት ወቅት ጭምር መሥራት መጀመራ቞ውን ገልጞዋል። ሆኖም ሥራ ጀምሹው ኚሁለት ወራት በኋላ ተግባራዊ እንዲሆን ዚወጣው መመሪያ ተባግባራዊ አለመሆኑ ቅሬታ እንደፈጠሚባ቞ው አስታውቀዋል። "ማህበሚሰቡ ባለሙያው ብዙ ክፍያ እንዳለው ነው ዚሚያውቀው። ዹማይኹፍሉ ኹሆነ ማህበሚሰቡ ማወቅ አለበት። ቢኚፍሉን ጥሩ ነው። ዹማይለኹፍሉ ኹሆነ ግን አንኹፍልም ግን እናመሰግናለን ዹሚል ደብዳቀ ቢሰጠን። ኹህክምና ጣቢያው ስወጣ በግሌ ዚሚያስጠሉ ፈተናዎቜ ነበሩት። 'ዚት ነበርሜ?' ምናምን ዚሚሉት ነገሮቜ ትንሜ ቅስም ይሰብራል" ብለዋል ሐኪሟ። እንደ አዲስ አበባ ጀና ቢሮ ልዩ አበሉ ባይኚፈልም በፌደራል ስር በሚገኙ ዚኮቪድ-19 ህክምና ማዕኚላት እና በአንዳንድ ክልሎቜ ተግባራዊ መደሹጉን ግን እነዚህ ባለሙያዎቜ ገልጞዋል። "አዲስ አበባ ጀና ቢሮ ሄደው ያነጋገሩ ባልደሚቊቜ አሉ። እነሱ ግን በቃ እንደማይገባን ነገሩን ያሉት። በጀት ዹለንም አሉ። በጀት ኹሌለ መጀመሪያም ውሳኔው (ዚሚንስተሮቜ ምክር ቀት) አይፈቅድም" ብለዋል። ውሳኔውን መሠሚት በማድሚግ ጀና ቢሮው ክፍያውን እንዲፈጜምላ቞ው በተደጋጋሚ ጥያቄ ቢያቀርቡም ተገቢውን ምላሜ አላገኙም። ክፍያው ሁለት ቢሊዮን ብር ገደማ ስለሚሆን እንደሚክብዳ቞ውፀ ኚኮቪድ-19 ማዕኚላት ውጭ ያሉት ይበልጥ ተጋላጭ መሆናቾውን ጭምር በመግለጜ እነሱን ስለማያካትት ለአፈጻጞም አመቺ አይደለም ተብሎ ኚጀና ቢሮው እንደተመለሰላ቞ው አቶ ዲኖ አስታውቀዋል። ዚጀና ጥበቃ ሚንስትር ደግሞ ጉዳዩ እንደማይመለኚተው እንዳስታወቃ቞ው እና ለኹተማው ካቢኔ ደብዳቀ አስገብተው ምላሜ እዚተጠባበቁ መሆናቾውን ተናግሚዋል። ዚሚንስትሮቜ ምክር ቀት በመመሪያው ያወጣው በኮሮናቫይሚስ ዚተያዙን ዚሚያክሙ፣ በለይቶ ማቆያ ህክምና በመስጠት ላይ ዚሚገኙ፣ ቀጥታ ተጋላጭ ሆኑ ባለሙያዎቜ በሚል በዝርዝር ለይቶ ማስቀመጡን ገልጞዋል። ይህንን ተግባራዊ ለማድሚግ ግን አሠራሩን በመቀዹር ቢሮ ዚሚሠሩትን ተጠቃሚ በማድሚግ ሌላ ውሳኔ ተግባራዊ መደሹጉን ኮንነዋል። 'ዚወጣው ውሳኔ ሁሉንም ባያካትትም ሁሉም ዹህክምና ባለሙያ ለኮቪድ-19 ተጋላጭ ነው' በሚል ቢሮ ውስጥ ያሉትንም ለመጥቀም ዚሚመስል ሁሉንም ዚሚያካትት አሠራር ለመፍጠር መሞኚሩን አቶ ኚድር አስታውቀዋል። ስለ ጉዳዩ ለሲቪል ሰርቪስ ያቀሚቡት ቅሬታ ደግሞ 'ካልተስማማቜሁ መልቀቅ ትቜላላቜሁ ብዙ ሥራ ዹሚፈልግ ባለሙያ አለ' በሚል ምላሜ አንደተሰጣ቞ውም ገልጿል። ዚቀት ጉዳይ ዚጀና ባለሙያዎቹ ሌላ ቅሬታ ደግሞ ዚቀት ጉዳይ ነው። ዚአዲስ አበባ ኹተማ መስተዳደር ኚንቲባ ጜህፈት ቀት ተገንብተው ዹተጠናቀቁና በግንባታ ላይ ያሉ በርካታ ቀቶቜ መኖራ቞ውን ጠቅሶፀ በራሳ቞ውም ሆነ በባለቀቶቻ቞ው ስም ቀት እንደሌላ቞ው ዚሚገልጜ ማስሚጃ እንዲያቀርቡ መጠዹቁን አስታውሰዋል። መሹጃውን ለሟሟላትም ውጣ ውሚድ በማሳለፍ በተሰጣ቞ው ጥቂት ቀናት መሹጃውን ማስገባታ቞ውን ገልጞዋል። ዕጣ እንደሚወጣላ቞ው በተነገራ቞ው ሰሞን ዚአርቲስት ሃጫሉ ሁንዎሳን ግድያ ተኚትሎ በተፈጠሹው ቜግር ምክንያት መደናቀፉን አስታውቀዋል። ምላሜ እንገኛለን በሚል ቢጠብቁም ዚቀድሞው ኚንቲባ ኢንጂነር ታኚለ ኡማ ኚቊታ቞ው ተነስተው ወደ ሌላ ቊታ ተቀይሚዋል። . ዚያዘዎት ጉንፋን ወይስ ኮሮናቫይሚስ መሆኑን እንዎት መለዚት ይቜላሉ? . በለይቶ ማቆያ ያሉ ዚጀና ባለሙያዎቜ መሠሚታዊ ፍላጎታቜን እዚተሟላ አይደለም አሉ . በኢትዮጵያ በኮቪድ-19 ዚተያዙ ዚጀና ባለሙያዎቜና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞቜ በኋላ ዚተሰጣ቞ው ምላሜ 'ዳታ' ለመስብሰብ ነው ዹሚል ነበር። ቀት እናገኛለን በሚል መሹጃ ለማቅሚብ ተሯሩጠው 'ለዳታ ነው' መባላ቞ው ቅሬታ እንደፈጠሚባ቞ው ጠቅሰዋል። መጀመሪያ ተስፋ ስለተሰጣ቞ው እንጂ ያሰቡት ባይሆንም ቃል ኚተገባ ደግሞ ሊፈጾም ይገባል ሲሉም ጠይቀዋል። ሰኔ 2012 ዓ. ም ዚጀና ባለሙያው በሊስት ቀን ውስጥ በራሳ቞ው እና በትዳር አጋራ቞ው ስም ቀት እንደሌላ቞ው ዚሚገልጜ ማስሚጃ አምጡ መባላ቞ውን አቶ ዲኖ ገልጾው "አንዳንድ መገናኛ ብዙሃን ለህክምና ባለሙያዎቜ ቀት ሊሰጥ ነው ሁሉ ብለዋል" ሲሉ ተናግሚዋል። "አንዳንድ ታካሚዎቜ ቀት ተሰጣቜሁ ደስ ብሎናል እስኚሚሉ ድሚስ። እኛ ላይ ዚማታለል ሠራ ነው ዚሰሚቡን" ብለዋል። በራሳ቞ውም ሆነ በትዳር አጋሮቻ቞ው ስም ቀት እንደሌላ቞ው ዚሚያሳይ ማስሚጃ አስገብተው ዕጣው ሊወጣ አካባቢ በአርቲስት ሃጫሉ ሞት ምክንያት ዘገዹ ሲሉ ያስታወሱት አቶ ኚድር ና቞ው። ኹህክምና ቊታ቞ው ወጥተው ሰዎቜ ኚኮቪድ-19 ማዕኚላት በመምጣታ቞ው ብቻ እያገለሏ቞ው እና በአጭር ቀናት ውስጥ ያስገቡትን ማስሚጃ "ለዳታ ነው። ምን ያህል ቀት እንደሌላቜሁ ለማወቅ ነው እንጂ ቀት ይሰጣቜኋል አልተባለም" መባሉ እንዳሳዘና቞ውም አስታውቀዋል። ዹህክምና ዶክተሯ በበኩላ቞ው "ቀት እንሰጣለን ብለው ወኚባ ፈጠሩ። እንደ ግለሰብ ሳይሆን እንደ ጀና ባለሙያ ግን ኚቀት ውጣ ዚተባለ ሃኪም አለ። በኮቪድ-19 ጊዜ ቀት ልንሰጥ ነው ብለው ዚኑሮ ውድነት እንዲመጣፀ ጀና ባለሙያዎቜ ዚሚኚራዚውን ቀት በእጥፍ እንዲጚመሚበት ነው ያደሚጉት። ይኹፈላቾዋል በሚል ብቻ ዚኑሮ ውድነት እንዲጚምርበት ተደርጓል" ብለዋል። ዚገቢ ግብር ቅነሳ ስማ቞ው እንዳይጠቀስ ዚፈለጉት ጠቅላላ ሐኪም ዚገቢ ግብር እስካሁን እንዳልተነሳ እና በዚትኛውም ህክምና ተቋም ዹሚኹፈለው 'ዲዩቲ' (ዚሥራ) አበል አንኳን በአግባቡ እንዳልተኚፈላ቞ው አስታውቀዋል። "ሁሉም ዹህክምና ባለሙያዎቜ ለቫይሚሱ ተጋላጭ ናቾው ኚተባለም ይህ መሾፈን ያለበት በጀና መድህን ነው። ቀተሰቊቻቜን እዚተኚፈላቜሁ ነው። ቀተሰብ እና ጓደኞቻቜን ዚት አደሚጋቜሁት እያሉ ነው። እነሱ ባወጡት ህግ ነው ዚጠዚቀውነው። ለምን ይሞራርፉታል በሚል። ህዝቡ በአዋጁ እዚተጠቀማቜሁ ነው እያለ ነው። ቀተሰብም ጓደኛም ግብርም ቀርቶላቜኋል ይላል" ብለዋል አቶ ኚድር። ይህም ሆኖ ግን እስካሁን ዚገቢ ግብር ቅነሳውም ቢሆን ተግባራዊ አለመደሹጉን ጠቁመዋል። ቢቢሲ በመጚሚሻም ለባለሙያዎቹ ምላሜ ካላገኛቜሁ ምን ለማድሚግ አስባቜኋል? በሚል ላቀሹበላቾው ጥያቄ ዹሚኹተለውን መልሰዋል። "ሥራ ለማቆም አላሰብንም። ባለሙያው ሥራ እንዳያቆም ነው ተወካይ ዚተላኚው። ተወካዮቜ ኮሚ቎ መሚጡ። እነሱ ናቾው ዚሚንቀሳቀሱት። ኮሚ቎ዎቹ ሥራም እዚሠሩ ነው። በሚዲያ እያሳወቅን ነው ህዝቡ እንዲያውቅልን። በኮሚ቎ም በአባላትም ደሹጃ ወደፊት ወደ ፍርድ ቀት ልናመራ እንቜላለን ዹሚል ሃሳብ ነው ያለው" ያሉት አቶ ዲኖ ና቞ው። "አገራዊ እና ሙያዊ ግዎታ ነው። እኔ ሥራ ባቆም ዚሚሞቱ ሰዎቜ አሉ። ይሄ ባለሙያው ምሎ ዚወጣበት ስለሆነ ሥራ ማቆም አይቜልም። አመጜም አይኖርም። እዚተሚገጥክ ጥቅመህን አሳልፈን እንድትኖር ነው ዚሚያደርጉት" ያሉት ደግሞ ስማ቞ው እንዳይጠቀስ ዹፈለጉ ሐኪም ና቞ው። ዚአዲስ አበባ ጀና ቢሮ ምላሜ ዶ/ር ሙሉጌታ እንዳለ በአዲስ አበባ ጀና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ና቞ው። እንደ ዶ/ር ሙሉጌታ ኹሆነ ልዩ አበሉን ለማስፈጞም መመሪያ ኚወጣ በኋላ አፈጻጞም ላይ ቜግር ገጥሟ቞ዋል። በመጀመሪያው ዚልዩ አበሉ ዹተፈቀደው ዚኮቪድ -19 ማዕኚላት ውስጥ ለሚሠሩ እና በመኹላኹል ላይ ለሚሳተፉ ባለሙያዎቜ በሚል ነው። እንደ ምክትል ኃላፊው ኹሆነ ግን በዚህ ውስጥ ሁሉም ዚጀና ሠራተኞቜ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ እዚተሳተፉ ነበር አሁንም በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ። በዚህ ምክንያት ለማስፈጞም አስ቞ግሮናል ይላሉ። በተጚማሪም ደግሞ ክልሎቜ እና ኹተማ መስተዳድሮቜ በራሳ቞ው አውድ እንዲጠቀሙበት መመሪያው እንደሚፈቅድ ገልጾው ዚተለያዩ አማራጮቜን በመውሰድ ለመተግበር ሙኚራ መደሹጉን አስታውቀዋል። ሆኖም ሙኚራዎቹ ጥቂት ሠራተኞቜን ብቻ ዹሚጠቅሙ ሆነው ተገኝተዋል ይላሉ። "መሬት ላይ ስናወርደው ጜዳቱም፣ ሹፌሩም ድንገተኛ ክፍል ዚሚሠራው ይገባዋል። ተመላላሜ ህክምና፣ ቀዶ ጥገና ክፍል፣ ማዋለጃ ዚሚሠሩና ሁሉም ላይ ያሉ ሠራተኞቻቜን ኚኮቪድ -19 ጋር ተጋፍጠው እዚተኚላኚሉ እዚሠሩ ነው። እንተግብሚው ካልን ደግሞ ለሁሉም ነው መተግበር ያለብን" ሲሉ ያስሚዳሉ። ሌላው ደግሞ ለትግበራ ያስ቞ገሚው ዚበጀት ጥያቄ ነው። "ዹኹተማ አስተዳድሩ ላይ ትልቅ ወጪ አለ። ኹተማ አስተዳደሩ ያንን መሾኹም ዚሚቜል አይደለም" ብለዋል። ኹዚህ በተሻለ አማራጭ ተደርጎ ዹተወሰደው ኮቪድ-19 ኢትዮጵያ ኚገባበት ወቅት አንስቶ በኹተማ መስተዳድሩ በጀና ዘርፍ ለሚሠሩ ባለሙያዎቜ በሙሉ ዚግብር ቅነሳ ማድሚግ ነው። "ሁሉም ዚጀና ዘርፍ ሰራተኞቜ ራሳ቞ውም አደጋ ላይ ጥለው ነው እዚሠሩ ያሉት። ኮቪድ-19 ላይ ቅዳሜ እና እሁድ ገብተው ዚሚሠሩ አሉ። ገብተው ዚሚያድሩ አሉ። ይሄንን ዚትርፍ ሰዓት ክፍያ቞ውን እንሰጣለን" ሲሉ ተናግሹዋል ። አክለውም "ኹተማ መስተዳድሩ ታክስ ቅነሳ ወይም ራሱ መስተዳድሩ ታክሱን ይኹፍላል ማለት ነው። ስለዚህ ኮቪድ-19 ኚጀመሚበት ኚመጋቢት ጀምሮ ኮቪድ-19 ኚስጋትነት እስኚሚወጣበት ድሚስ ሁሉም ዚጀና ሠራተኞቻቜን ያንን ኚግብር ተቀንሶላ቞ው መስተዳድሩ ራሱ እዚሞፈነ በዚያ መንገድ እናስተናግድ ተብሎ ተወሰነ" ብለዋል። መመሪያው ሲወጣ መጀመሪያ ድንገተኛ ዹአደጋ መቆጣጠር ዘርፍ ላይ ዚሚሠሩ ዹተወሰኑ ሠራተኞቜን ብቻ ታሳቢ አድርጎ እንደነበር ዶ/ር ሙሉጌታ አስታውቀውፀ ዚቫይሚሱ ስርጭት እዚጚመሚ ሲሄድ ብዙ ባለሙያዎቜን ኚማሳተፉም በላይ መመሪያዎቜም መቀያዚራ቞ውን ለቢቢሲ ገልጞዋል። ኮሮናቫይሚስ ላይ ዚሚሠሩ ሠራተኞቜ ቁጥር መጹመርም ሌላው ምክንያት ነው። ቞ግሩን ለመቅሹፍ ኚሠራተኞቜ ጋር በተደጋጋሚ መወያዚታ቞ውን አንስተው "ብዙ ዚጀናው ዘርፍ ሠራተኛ በውሳኔው ላይ ጥሩ እይታ እንዳለው ነው ያዚነው" ብለዋል። ሆኖም ቅሬታዎቜ መኖራ቞ውን ጠቁመው ጀና ቢሮው ዹወሰደውን እርምጃ ሌሎቜም (ክልሎቜ እና ጀና ጥበቃ) ዹመኹተል ነገር እንዳለ መመልኚታ቞ውን ጠቁመዋል። ኹዚህ በተቃራኒ ሁላቜንም ለአደጋ ተጋልጠን በምንሠራበት ለጥቂቶቜ ብቻ መኹፈል ዚለበትም ዹሚሉ ጥያቄዎቜ መነሳታ቞ውን በተመለኚተፀ "እኛም አደጋ ላይ ወድቀን እዚሠራን ለጥቂቶቜ ብቻ እዚተኚፈለ ታሳቢ አለመደሹጉ ተገቢ አይደለም ብለው ደግሞ በተቃራኒው ዹሚጠይቁ አሉ። ዚግድ ኮቪድ-19 ማኚሚያ ቊታ ብቻ ነው ወይ እኛም እዚተጋፈጥን ነው ዹሚሉ አሉ" ሲሉ አስሚድተዋል። ገቢ ግብርን በተመለኹተ ደግሞ በኹተማ መስተዳድሩ ሥር በሚገኙ ሁሉም ጀና ተቋማት መሹጃ ዚማሰባሰብ ሥራ መኹናወኑን አስታውቀው በጥቂት ቀናት ውስጥ ተግባራዊ ይደሹጋል ብለዋል። ህክምና ባለሙያዎቹ ቀት ይሰጣቜኋል ተብለን በተገባልን ቃል መሠሚት አልተፈጾመልንም ለሚለው ቅሬታ቞ውም ምላሻውን እንደሚኚተለው ሰጥተዋል። "ቀት ይሰጣል ዹሚል እንደ መስተዳደርም እንደ ቢሮም ዚለም። መሹጃ ሊሰበሰብ ቀት ያለውን እና ዹሌለው ዚጀና ባለሙያ መሹጃ እንዲያዝ ኹተማ መስተዳደሩ መጠዹቁን ነው እኔ ዚማውቀው። መሹጃውን ጠይቁ አለ መሹጃውን ሰብስበን ልኚናል። ቀት ይሰጣ቞ዋል ዹሚል ነገር ግን ዹለም" ብለዋል።
44123096
https://www.bbc.com/amharic/44123096
"ዚናንዬ ሕይወት" ዚአይዳ ዕደማርያም ምስል ኚሳቜ መፀሐፍ
ማንደጃው ላይ ዚተጣዱ አራት ፍሬ ኚሰሎቜ ወርቃማ ቀለም ያለው እሣት ይተፋሉፀ አያ቎ ኚዕጣኑ ቆንጠር በማድሚግ እፍሙ ላይ ብታኖሚው ጊዜ ደስ ዹሚል ሜታ አካባቢውን ያውደው ጀመር። መቁያው ላይ እሣት እዚመታው ካለው ቡና ጋር ሲቀላቀል ደግሞ መዐዛው እንደው ልብ ዹሚሰውር ሆነፀ ቀቱ በሜታ ቀለማት ተውቩ ሞቅ ብሎ ሳለ ውጭው ግና በጳጉሜ ዝናብ እና ብርድ ይንቀጠቀጥ ነበር. . .
«በዕለተ ሩፋኀል ዝናብ ኚጣለ ውሃው ዹተቀደሰ ነው» ትል ነበር አያ቎። «ልጅ እያለን ዚቅዱስ ውሃው በሚኚት ያገኘን ዘንድ ልብሳቜንን አውልቀን በዝማሬ በመታጀብ ጭቃው ላይ እንቊርቅ ነበር። ቀስተ ደመናው ተሩቅ ዚሚታዚን ተሆነ ደግሞ ማርያም መቀነቷን ሰማዩ ወገብ ላይ አስራለቜና ይበልጥ ደስ ይለን ነበር. . .» ዚናንዬ ሕይወት. . . ኚአንድ ክፍለ ዘመን ቀደም ብሎ አንዲት ልጅ በሰሜን ኢትዮጵያዊቷ ዹጎንደር ኹተማ ተወለደቜ። ገና 8 ዓመቷ ሳለ በሁለት አስርት ዓመታት ኚሚበልጣት ሰው ጋር ትዳር እንድትመሠርት ሆነ። በርካታ ልጆቜንም አፈራቜ። ዚጣልያን ዳግም ወሚራ፣ ዚቊምብ ናዳ፣ ዚቀዳማዊ ኃይለሥላሎ አልፋ እና ኊሜጋ፣ አብዮት እና ዚእርስ በርስ ጊርነት ይህቜ ሎት በዚህቜ ምድር በቆዚቜባ቞ው 95 ዓመታት ውስጥ ያስተናገደቻ቞ው ክስተቶቜ ና቞ው። 'The Wife's Tale' ወይንም በግርድፍ ትርጉሙ 'ዚሚስት ትሚካ' በሚል ደራሲና ጋዜጠኛ አይዳ ዕደማርያም ዚፃፈቜው መፅሐፍ በእነዚህ 95 ዓመታት አያቷ ዹተመኙ ያሳለፉትን አስደናቂ ዚሕይወት ውጣ ውሚዶቜ ዚሚዳስስ ጠርቃ ያለ ጥራዝ ነው። ኮራ ጀነን ያሉ ቀሳውስት፣ ሃገር ወዳድ ወታደሮቜ፣ ዚባለቀቷ እሥርና እንግልት፣ ፍትህን ፍለጋ፣ እመበለትነት. . .ብቻ ኚልጅነት እስኚ እውቀት ዹተመኙ ያዚቜውን ቆጥሮ መዝለቅ ውሃ እንደ መፍጚት ነው። አፄውና እ቎ጌይቱ፣ ምሁራንና መነኩሳት፣ ዚማርክስ አብዮተኝነት አቀንቃኞቜ እንዲሁም ባንዳዎቜ አይዳ 'ናንዬ' ብላ በምትጠራት አያቷ ሕይወት መስኮት ዹሚቃኙ ዚእውነተኛው ዓለም ገፀ-ባህርያት ና቞ው። 'ዘ ዋይፍስ ቮል' ዚአንዲት አትዮጵያዊት ሎት ዹክፍለ ዘመን ትሚካ ብቻ ሳይሆን ዚሃገሯ ታሪክ ዹክፈለ ዘመን ትውስታም ነው" ትላለቜ አይዳ ስለመፅሃፉ መናገር ስትጀምር። "ትዝ ይለኛል ዚዛሬ 20 ዓመት ገደማ ነበር ዚናንዬን ሕይወት መመዝገብ ዚጀመሚኩትፀ ቢሆንም እንዲህ ወደ ታሪክ ገላጭ ጥራዝ እቀይሚዋለሁ ዹሚል እሣቀ አልነበሹኝም" በማለት ዹመፅሐፉን መፀነስ ታወሳለቜ አይዳ። "ብዙ ጊዜ ታሪክ ነጋሪ ሆነው ዚምናያ቞ው በጊርነት አውድማ ዚተሳተፉ አሊያም ሥልጣን ላይ ዚነበሩ ሰዎቜ ና቞ው። ነገር ግን ታሪክ ሊታይ ዚሚገባው በተለምዶ ተራ ሰው ብለን ኚምንጠራው ግለሰብ ዓይን ነው" ስትል ትኚራኚራለቜ። "ዚናንዬ ሕይወት ዚሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ሎቶቜ ሕይወት ነውፀ ለዚህም ነው ታሪክ ያለው ብዙም እውቅና ካለገኙ ግለሰቊቜ ጓዳ ነው ብዬ ዚምለው። መነገርም ያለበት በእነዚህ ሰዎቜ አንደበት ነው።" ጎንደር ስለኢትዮጵያ ታሪክ በተወሳ ቁጥር ስሟ ይነሳልፀ ዚዘመናዊቷ ኢትዮጵያ አንድ መዘክር ሆናም ትጠቀሳለቜ። ዚሃገሪቱ ርዕሰ-መዲና ሆናም አገልግላለቜ፣ በኊርቶዶክስ ክርስትና እምነትም ትልቅ ሥፍራ ዚሚሰጣት ቊታ ናትፀ ጎንደር። ዹዹተመኙ ውልደት ጎንደር እንደመሆኑ 'ዘ ዋይፍስ ቮል' ጉምቱውን ዚታሪክ መቌት ያደሚገው በዚህቜ ታሪካዊ ኹተማ ነው። በተፈጥሮ ፀጋ ዚታደለቜው ጎንደር ዚጥራዙ ትልቅ አካል መሆኗ መፅሐፉ በታሪክ፣ እምነት እንዲሁም ቀለማት ድምቆ ዹተዋበ እንዲሆን ሚድተውታል ትላለቜ አይዳ። "እርግጥ ነው አዲስ አበባም ዚናንዬ ሕይወት ትልቅ አካል ናትፀ ቢሆንም ግማሜ ያህል ሕይወቷን ያሳለፈቜው ጎንደር ነው። እትብቷ ዹተቀበሹውም እዚያው ጎንደር ነው" ዚምትለው አይዳ መፅሐፉ በታሪክ ዹበለፀገ ሆኖ አገኘው ዘንድ ጥናት ለማድሚግ ጎንደር ብዙ ጊዜ አሳልፌያለሁ ስትልም ትዘክራለቜ። ጉዞ ወደ አዲስ አበባ «እኔ ምለውን ትደግሚያለሜ» ቄሱ ተናገሩ። «ቢታመም»...ቢታመምፀ «ቢጎሳቆል»...ቢጎሳቆልፀ «ክፉ ቢገጥመው፣ ቢደኞይ፣ ቢሞት እንኳ...አልክደውም»...አልክደውም። ዹተመኙ በ20 ዓመታት ኚሚበልጣትፀ ኚገጣሚና መንፈሰ ብርቱ ዚቀተስኪያን ሰው ሊቀ ካህናት አለቃ ፀጋ ተሻለ ጋር ጎጆ ትቅለስ ዘንድ ሆነ። ኹፍርግርጉ በስተጀርባ ያለ ባሏን ለመጠዹቅ በሄደቜ ጊዜ እጅግ ኚፍቶት አገኘቜውፀ «ወይኔ ልቀንፀ አይዞህ...እሜ እኔ ምን ላድርግ? ወይ አዲሳባ ተሚሉት ሃገር ልሂድ እንዎ?» አለቃ ፀጋ ሃሳቡን አላወገዘውም። «ወደ አዲሳባ ሂጂፀ እኚፍተኛው ፍርድ ቀት፣ እንጉሱ ጋር ሄደሜ መበደሌን ንገርሊኝፀ ነፃ አውጭኝ።» ዚሕይወት ምዕራፍ ወዳላሰቡት ሆነና ዹተመኙ ለእሥር ዚተዳሚገ ባልተቀቷን ነፃ ለማውጣት አዲሳባ ኚሚሉት ዚማታውቀው ዓለም መሄድ ግድ ዚሆነባት። ሰው በሰው ላይ ዚሚሄድበት ምድር. . .. መኪና ኚዚት መጣ ሳይሉት ጥሩንባውን እዚነፋ ዚሚክለፈልፍበት ሃገር. . .አዲስ አበባ። ዹዹተመኙ ወደ አዲሳባ ማቅናት ጉዳይ ስለባሏ ፍትህ ለመጮህ ቢሆንም ተቆጥሮ ዚማያልቅ ጉድ አይታበታለቜ። ዚገበያው ግርግር፣ ዚተማሪ ጥድፍያ፣ ዚዘመድ ዓይን. . .ኧሹ ዚቱ ተነግሮ ዚቱ ይተዋል? ማርያም ማርያም. . . 1930 ዓ.ም ጎንደር ኚተማፀ ዹተመኙ ምጡ ቢጠናባት ጊዜ እንደ ሃገሬ እና ሃገሯ እናቶቜ ማርያምን አጥብቃ ትለማመን ጀመር። ባለቀቷ ሊቀ ካህናት አለቃ ፀጋ ተሻለ ልጃቾውንም ዹልጃቾውንም እናት እንዳያጡ ስጋት ቢገባ቞ው ወደአምላካ቞ው ቀና ብለው አጥብቀው ይጞልዩ ነበር። ዚአካባቢው ሰው ዹአለቃን ቀት ሞልቶታልፀ ሁሉም ተጚንቋል። በቀቱ ዹተገኙ ቀሳውስትም ኚድርሳነ ሩፋኀልና ተዓምሹ ማርያም ላይ ጞሎት ያሰሙ ይዘዋል። ዹተመኙ እንዲህ ዚምጥ ጭንቅ ውስጥ ሆና ሁለት ቀናት አለፉ። ሊስተኛም ቀን ሆነፀ ዹተመኙ እንቅልፍ ወሰድ መለስ ያደርጋት ይዟል። ሊስተኛውም ቀን እንዲሁ ባለ ስሜት ካለፈ በኋላ ሌሊት ላይ ወንድ ልጅ ተገላገለቜ። መጀመሪያ ጹቅላው አልንቀሳቀስ አልላወስ ይልና ዹሁሉም ልብ በድንጋጀና ጭንቀት ይዋጣልፀ አዋቂዋ አዋልጅ ግን አልደነገጡም። በንጡህ ጹርቅ አርገው ጹቅላውን በውሃ ሲያብሱት አንቀላፍቶ ዹነበሹው እንደው ንቅት ይልና ጣቱን መጥባት ተያያዘውፀ ቀቱም በደስታ ተሞላ። ልጁም እደማርያም ተብሎ ይጠራ ተባለፀ ዚማርያም እድ (እጅ) እንዳማለት። ፕሮፌሰር እደማርያም ፀጋ በኢትዮጵያ ዹዘመናዊ ሕክምና ታሪክ ሉዓላዊ ሥፍራ ኚሚሰጣ቞ው ጠበብት ሐኪሞቜ አንዱ ነበሩ። እርሣ቞ው ደግሞ አይዳን ወለዱ። 'ዘ ጋርዲያን' ለተሰኘው ጋዜጣ ዚምትሰራው አይዳ ስለ አያቷ አውርታ ዚምትጠግብም አትመስል። "ምንም እንኳ አብዛኛውን ዹሕይወቮን ክፍል ዚኖርኩት በምዕራባዊው ምድር ቢሆንም ኚአያ቎ ጉያ መጥፋት አልሻም ነበር" ትላለቜ። "ቢያንስ ደውዬ ሳናግራት ደስታ ይወሚኛል። ኢትዮጵያ እያለሁ ቀታቜን ስትመጣ እንደው አካባቢው አንዳቜ ኃይል ይላበሳል። በቡና መዓዛ ዚታወደ መሳጭ ታሪክ መስማትን ዹመሰለ ነገር ዚለም።" "ምንም እንኳ ዚናንዬ ታሪክ ልብ በሚሰብሩ ኹነቶቜ ዹተሞላ ቢሆንም ውጣ ውሚዱን አልፋ አስደናቂ ሕይወት መምራት ቜላለቜፀ ዹልቧን ደስታም ሳትሞሜገው ኖራለቜ። ይገርምሃል ልብ በጣም ንፁህ ነውፀ ባህርይዋ ደግሞ በአስደናቂ ድርጊቶቜ ዚተሞላ። ደግሞ መደነስ ትወድም ትቜልም ነበር። በሚያስለቅሰው ታለቅሳለቜፀ በሚያስቀው ትፈነድቃለቜ። ሕይወት በሙሉ ለመኖር ሰስታፀ ስሜቷን ለመግለፅ ፈርታ አታውቅም።" 'ዘ ዋይፍስ ቮል' በበርካቶቜ ዘንድ ዚሚነበብ ብቻ ሳይሆን ዚሚታይ ታሪክ ያዘለ ተብሎ ተደንቋል። እኔም መፅሓፉን አነበብኩትፀ ኧሹ እንድያውም ተመለኚትኩት። እንደው ቃላቶቜሜ እንዎት ቢካኑ ነው እንዲህ ውብ ቀለም ዚተላበሱት ስልም ጠዚቅኳት አይዳን። ''ዕድሜ ለአያ቎'' አለቜኝ። ''ታሪክ ስትነግሚኝ እንደምትስልልኝ ሁሉ እመለኚተው ነበርፀ እኖሚውም ነበር። መንገዱ፣ ገበያው፣ ልዩ ምልክቱ፣ ሳሩ ቅጠሉ ጀዛው. . .ብርት ብሎ ይታዚኛል። እኔም ቁጭ ብዬ እሷን በመመሰጥ ማድመጥና በመቅሹፀ-ድምፄ ማስቀሚት ዚዕለተለት ሥራዬ ሆነ።'' "ናንዬ እኮ ታሪክን በመናገር ብቻ ዚተካነቜ አይደለቜምፀ በመኖርም ጭምር እንጂ። ነገሮቜን ሁሉ በአግባቡ ስታኚናውን አያት ነበር። ምንም እንኳ ዚእኔም ቃላትን ገላጭ አድርጎ ዹመግለፅ ክህሎት ቢኖርበትም ዚእርሷ አገላለፅ ግን ኚድርጊት እኩል ነበር።" "አያ቎ ዚኚወነቻ቞ውን ነገሮቜ ለመኹወን ሞክሬያለሁፀ በሄደቜበት መንገድ ሄጃለሁ፣ ዚሳመቜውን ቀተስኪያን ስምያለሁ፣ ዚገበዚቜውን ገብይቻለሁ፣ እኒህን ነገሮቜ ያደሚግኩት ኚአያ቎ ሕይወት ጋር በምናብ ለመገናኘት ነው" ትላለቜ አይዳ። 'ዘ ዋይፍስ ቮል' ዚአይዳ አያት ድንቅ ሕይወትፀ ዚኢትዮጵያ ታሪክ ዚአንድ ምዕተ ዓመት ነፀብራቅፀ ዚገጠሩና ዹኹተማው ትዕይንተ-ሕይወት ማሳያ አቡጀዲ ጚርቅፀ ኃይማኖታዊና ዓለማዊ ትርክት ነው።
news-50597486
https://www.bbc.com/amharic/news-50597486
በምዕራብ ኊሮሚያ ባለፉት 12 ወራት ቢያንስ 8 ዚአካባቢው ባለስልጣናት ተገድለዋል
ባለፈው አንድ ዓመት በምዕራብ ኊሮሚያ በሚገኙ ዞኖቜ ውስጥ በመንግሥት እና በተቋማት ኃላፊዎቜ ላይ ያነጣጠሩ ግድያዎቜ እዚተጠናኚሩ መጥተዋል።
ዚመንግሥት ኃላፊዎቜ ዚጥቃቱ ዋነኛ ዒላማ ይደሹጉ እንጂፀ ዚተለያዩ ዹግልና ዚመንግሥት ተቋማት ኃላፊዎቜ፣ ዚመንግሥት ጞጥታ አስኚባሪዎቜ፣ ሰላማዊ ሰዎቜና ዚውጪ አገራት ዜጎቜ ጭምር ዚጥቃቱ ሰለባ መሆናቾው ሲዘገብ ቆይቷል። • "በኢትዮ ቎ሌኮም ኃላፊ ግድያ ተጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ዹዋለ ዹለም" ዹነቀምቮ ፖሊስ አዛዥ ዹክልሉም ሆነ ዚዚአካባቢዎቹ ዚመንግሥት ባለስልጣናት ለግድያዎቹ ተጠያቂ ዚሚያደርጉት "ማንነታ቞ው ያልታወቁ ታጣቂ ኃይሎቜን" ሲሆን አንዳንዶቜ ደግሞ ኹኩነግ ተነጥሎ ዚወጣውን 'ኩነግ ሾኔ' ዚተባለውን ቡድን ተጠያቂ ያደርጋሉ። በምዕራብ ኊሮሚያ ኚኅዳር 2011 እስኚ ኅዳር 2012 ባሉት 12 ወራት ውስጥ በተለያዩ አጋጣሚዎቜ በጥቃቶቹ ሰለባ ዚሆኑትን ሰላማዊ ሰዎቜን ሳይጚምር በመንግሥት ሥራ ላይ ተሰማርተው በታጣቂዎቜ ዚተገደሉት ሰዎቜ ቁጥር ኹ10 በላይ እንደሚሆን ዚተለያዩ ዘገባዎቜ ያመለክታሉ። ኅዳር 2012 ዓ.ም ባለንበት ዓመት በዚህ ዚኅዳር ወር ብቻ በምዕራብ ኊሮሚያ በሚገኙ ዚተለያዩ ቊታዎቜ ላይ ታጣቂዎቜ በፈጞሙት ጥቃት ቢያንስ 5 ዚመንግሥት ባለስልጣናት ተገድለዋል። ኚእነዚህም መካኚል በምዕራብ ኊሮሚያ ዚጀልዱ ወሚዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ሹጋኔ ኹበበ እና ዹጎጆ ኹተማ ዚፖለቲካ ዘሹፍ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ገሹመው በተመሳሰይ ቀን ተገድለዋል። ሁለቱ ዚአካባቢው ባለስልጣናት በጎጆ ኹተማ ማክሰኞ ህዳር 16 ቀን 2012 ዓ.ም ምሜት 12 ሰዓት ገደማ ላይ ነበር በጥይት ተመትተው ዚተገደሉት። ዚሁለቱን ባለስልጣናት መገደል ለቢቢሲ ያሚጋገጡት ዚኊሮሚያ ክልል ዚኮሚኒኬሜን ጉዳዮቜ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዎሬሳ ተሹፈ ሲሆኑፀ ዚመንግሥት ኃላፊዎቹ ዚተገደሉት "ባልታወቁ ታጣቂዎቜ" ነው ብለዋል። በተመሳሳይ መልኩ ባለፈው ሳምንት አንድ ዚምዕራብ ሾዋ ዞን ባለስልጣን በጥይት ሲገደሉ፣ በዚህ ሳምንት መጀመሪያም ማንነታ቞ው በውል ያልተገለፀ ታጣቂዎቜ ደግሞ ዹነቀምቮ ኹተማ ፖሊስ ዹወንጀል ምርመራ ኃላፊ ኮማንደር ጫላ ደጋጋ መግደላቾውም ተነግሯል። ቀደም ብሎ ሚቡዕ ኅዳር 10 ቀን 2012 ዓ.ም ጠዋት ላይ ዚኊሮሚያ ክልል መስተዳደር ዚመንገዶቜ ባለስልጣን ኮምዩኒኬሜን ኃላፊ ዚሆኑት አቶ ቶላ ገዳ ለሥራ ወደ ምዕራብ ወለጋ ቄለም ወለጋ ዞን እዚተጓዙ ሳሉ ላሎ አሳቢ ተብሎ በሚታወቀው ወሚዳ ውስጥ ማንነታ቞ው ባልታወቁ ታጣቂዎቜ መገደላቾውን ዚምዕራብ ወለጋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ኀሊያስ ኡመታ በወቅቱ ለቢቢሲ ተናግሹው ነበር። ጥቅምት 2012 ዓ.ም ጥቅምት 16 ቀን 2012 ዓ.ም ዕሁድ አመሻሜ ላይ ዚኢትዮ ቎ሌኮም ዚምዕራብ ዞን ኃላፊ ዚነበሩት አቶ ገመቺስ ታደሰ በታጠቂዎቜ በተፈጞመባ቞ው ጥቃት መገደላቾው ይታወሳል። ዹነቀምቮ ሪፈራል ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ዳምጠው አቶ ገመቺስ ቢያንስ በአራት ጥይት መመታታ቞ውን እና አንድ ጊዜ በስለት መወጋታ቞ውን ለቢቢሲ ገልፀው ነበር። ግለሰቡ ቀደም ሲልም ማንነታ቞ው ባልታወቁ ሰዎቜ ዛቻ ይሰነዘርባ቞ው እንደነበር ዹተጠቀሰ ሲሆን በወቅቱ ፖሊስ በአቶ ገመቺስ ግድያ ተጠርጣሪ እንዳልያዘ ዹነቀምቮ ፖሊስን በመጥቀስ ዘግበን ነበር። መስኚሚም 2012 ዓ.ም ዚጉሊሶ ኹተማ ኚንቲባ ዚነበሩት አቶ አበበ ተካልኝ በመኖሪያ ቀታ቞ው ደጃፍ ላይ ዚተገደሉት መስኚሚም 7 ቀን 2012 ነበር። አቶ አበበ በታጣቂዎቜ መገደላቾውን ዚጉሊሶ ወሚዳ ዚአስተዳደር እና ጞጥታ ጜህፈት ቀት ኃላፊ አቶ ተስፋ ሊካሳ ለቢቢሲ ተናግሹው ነበር። "ደጃፋቾው ላይ በሁለት ጥይት ግንባራ቞ውን ተመትተው ነው ዚተገደሉት" ሲሉ ዚጞጥታ ጜህፈት ቀት ኃላፊው ተናግሚዋል። ታጣቂዎቹ ኚንቲባውን ቀታ቞ው በር ላይ ኹገደሉ በኋላ ወደ መኖሪያ ቀታ቞ው ዘልቀው በመግባት "ለስብሰባ ዹተዘጋጀ ጜሑፍ እና ዚአካባቢውን ባለስልጣናት ስም ዝርዝርን ዚያዘ ላፕቶፕ ኮምፒዩተር ይዘው ሄዱ'' ሲሉ አቶ ተስፋ ጹምሹው ተናግሚዋል። ኚንቲባውን ገድለው ላፕቶፕ ዘርፈው ሄዱ ዚተባሉት ታጣቂዎቜ በቁጥር ወደ ስድስት እንደሚጠጉ ዚሟቜ ዚቀተሰብ አባላት ለመንግሥት ዚጞጥታ አካል መናገራ቞ውም ተገልጿል። በተመሳሳይ በምዕራብ ወለጋ መንዲ ኹተማ በሚገኝ ዹሃገር መኚላኚያ ሠራዊት ካምፕ ላይ ቊምብ ተወርውሮ አንድ ሰው ዹተገደለው እና በርካቶቜ ዚቆሰሉት መስኚሚም 2012 ነበር። ዚመንዲ ኹተማ ዹሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አለሙ ጉዲና ለቢቢሲ እንደተናገሩት ዹተወሹወሹው ቊምብ ዚአንድ ሰው ህይወት ኹመቅጠፉም በላይ በርካቶቜን አቁስሏል። ሰኔ 2011 ዓ.ም ሰኔ 18 ቀን 2011 ዓ.ም ሌላኛው ዚታጣቂዎቜ ኢላማ ዚነበሩት ባለስልጣን ደግሞ ዚደምቢዶሎ ኹተማ ኚንቲባ አቶ ታደለ ገመቹ ነበሩ። ኚንቲባው በጥቃቱ በጥይት ተመትተው ቆስለው በህይወት ተርፈዋል። ኚንቲባው አቶ ታደለ በጥይት ተመትተው ዚቆሰሉት ኚቢሯ቞ው ወጥተው መኪና቞ው ውስጥ ሊገቡ ሲሉ ነበር። "ኚንቲባው ኚሥራ በሚወጡበት ሰዓት ነበር በር ላይ ጥቃቱን ያደሚሱባ቞ው" ሲሉ ዚአካባቢው ባለስልጣን ለቢቢሲ አሹጋግጠው ነበር። • ዚደምቢ ዶሎ ኚንቲባ በጥይት ተመትተው ቆሰሉ ጥቃት ፈጻሚዎቹ ኚንቲባውን በሁለት ጥይት እንደመቷ቞ውና አንደኛው ጥይት እጃ቞ውን ሌላኛው ደግሞ በጎን በኩል ኩላሊታ቞ው አካባቢ እንደመታ቞ውም ለማወቅ ተቜሏል። ታኅሳስ 2011 ዓ.ም ሁለት ዚፌደራል ፖሊስ አባላት በምዕራብ ኊሮሚያ ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ውስጥ መነ ቀኛ ተብሎ በሚጠራ ስፍራ ላይ በጥይት ተመተው ዚተገደሉት ታኅሳስ 19 ቀን 2011 ዓ.ም. ነበር። ዹዞኑ ዚኮሚኒኬሜን ቢሮ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ተሚፈፀ ሁለቱ ዚፌደራል ፖሊስ አባላት ዚፊንጫአ ኃይል ማመንጫ እና ጌዶ ኹተማ ላይ ዹሚገኝ ዹኃይል ማኚማቻ ጣቢያዎቜን ዚሚጠብቁ ዚጞጥታ ኃይል አባላት ነበሩ ብለዋል። ''መኪና ላይ ሆነው ወደ ፊንጫአ እዚተጓዙ ሳሉ ባልታወቁ ታጣቂዎቜ ተኩስ ተኚፈተባ቞ው'' በማለት አቶ ደሳለኝ ዹነበሹውን ሁኔታ ተናግሹው ነበር። መጋቢት 2011 ዓ.ም ዚውጪ አገር ዜጎቜን ጭምር ዒላማ ያደሚገው እና ለአምስት ሰዎቜ ሞት ምክንያት ዹሆነው ጥቃት ዹተሰነዘሹው ሌላኛው ጥቃት መጋቢት 11 ቀን 2011 ዓ.ም ነበር ዚተፈጞመው። በምዕራብ ወለጋ ዞን ነጆ ወሚዳ ሁምነ ዋቀዮ በተባለ ቀበሌ ሊስት ኢትዮጵያዊያን፣ አንድ ጃፓናዊ እና አንድ ዚህንድ ዜግነት ያላ቞ው ሰንራይዝ ለሚባል ዚማዕድን አውጪ ተቋም ይሰሩ ዚነበሩ ሰዎቜ ናቾው በጥቃቱ ዚተገደሉት። ክስተቱን ተኚትሎ ዚኊሮሚያ ክልል ዚመንግሥት ኮሙዩኒኬሜን ጉዳዮቜ ቢሮ ሰዎቹ ዚተገደሉት ታጣቂዎቜ በፈጞሙት ጥቃት ነው ብሎ ነበር። ኚተገደሉት ሰዎቜ አራቱ ወንዶቜ ሲሆኑ አንንደኛዋ ዚውጪ ዜጋ ሎት ናት። እነዚህ ዚጥቃቱ ሰለባዎቜ ኚማዕድን ኩባንያው ጋር ይሰሩ ዚነበሩ ሲሆን አቶ አለማዹሁ በቀለ ዚተባሉት ግለሰብ ዚኩባንያው ባለቀት እንደነበሩም ለማወቅ ተቜሏል። አቶ አለማዹሁ ይህንን ዚማዕድን ማውጣት ሥራ ለመጀመር ሊስት ዓመታትን ዹፈጀ ጥናት ማኹናወናቾውንና ዚምርት ሥራውን ለመጀመር በተቃሚበበት ወቅት ኚአራት ባልደሚቊቻ቞ው ጋር በታጣቂዎቹ መገደላቾውን ዚቅርብ ጓደኛው በወቅቱ ለቢቢሲ ተናግሹው ነበር። ተጠያቂ ያልተገኘላ቞ው ጥቃቶቜ በምዕራባዊው ዚአገሪቱ ክፍል ውስጥ በተለይ ዚመንግሥት ባለስልጣናትንና ዚጞጥታ አካላትን ኢላማ በመድሚግ ሲፈጞም ዹቆዹው ዚታጣቂዎቜ ጥቃትን በተመለኹተ ኚግምት ባለፈ ተጠያቂ ዹሆነ አካል አልተገኘም። በተለያዩ ጊዜያት በታጣቂዎቜ በተፈጞሙት በእነዚህ ጥቃቶቜ በመንግሥት ሥራ ላይ ኚተሰማሩት ሰዎቜ በተጚማሪ ሰላማዊ ነዋሪዎቜም ሰለባ ሆነዋል። እስካሁን በተለይ ዚመንግሥት ኃላፊዎቜንና ዚጞጥታ አካላትን ኢላማ አድርገው ዚተፈጞሙት ዚታጣቂዎቜ ጥቃቶቜ ምክንያቱ ምን እንደሆነና ለድርጊቱም ኃላፊነት ዹወሰደ አካል ዚለም። ኚአንድ ዓመት በፊት ጀምሮ በአካባቢው በነበሹው አለመሚጋጋት ምክንያት ዚጞጥታና ኚተለያዩ ዚመንግሥት አካላትን ያካተተ ዹዕዝ ማዕኹል (ኮማንድ ፖስት) ተቋቁሞ እዚተንቀሳቀሰ እንደነበር ይታወሳል።
news-53578012
https://www.bbc.com/amharic/news-53578012
"እቅዎ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት አሁን ያለኝን 3 ሺህ ሰራተኛ 6 ሺህ ማድሚስ ነበርፀ ግን ቀነሱብኝ"
ኚሳምንታት በፊት በአንዳንድ ዚኊሮሚያ ክልል አካባቢዎቜ ተኚስቶ ዹነበሹው አለመሚጋጋት ኹ167 በላይ ሰዎቜ ህይወት መጥፋት ምክንያት መሆኑ ይታወሳል። ኹዚህ ባሻገርም በርካታ ተቋማትና መኖሪያ ቀቶቜ ላይ በተፈጾመው ጥቃት ኹፍተኛ ውድመት መድሚሱም ተገልጿል።
በሻሞመኔና በባቱ ኚተሞቜ ውስጥ በተፈጾመው ጥቃትፀ በንብሚት ላይ ዹደሹሰው ውድመት ኹፍተኛ መሆኑን ቢቢሲ ያናገራ቞ው ዹኹተማዋ ነዋሪዎቜና ባለንብሚቶቜ እማኝነታ቞ውን ሰጥተዋል። በእነዚህ ኚተሞቜ ኹወደሙ ንብሚቶቜ መካኚል በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በዓለማቜን ዚሩጫ ታሪክ ውስጥ ስማ቞ው ኚሚጠቀሱ ጥቂት ብርቅዬ አትሌቶቜ መካኚል አንዱ ዹሆነው ዚአትሌት ኃይሌ ገብሚሥላሎ ሁለት ትልልቅ ሆ቎ሎቜ ይገኙበታል። "ትክክለኛ ቁጥሩን አላወቅንምፀ እስኚ 290 ሚሊዮን [ሊደርስ ይቜላል]። እንዲሁ ኚሁለት መቶ ሚሊዮን ብር በላይ ብለን ነው ዚያዝነው" ሲል ለቢቢሲ ተናግሯል።
news-55287481
https://www.bbc.com/amharic/news-55287481
እግር ኳስ፡ ህይወቱ በሱስ ምክንያት ዚተመሳቀለው ዚፕሪምዚር ሊግ ቡድን አምበል
"በጣም ብዙ እርዳታ አስፈልጎኝ ነበር። ወደ ሌላ አይነት ሕይወት ለመሾጋገር ኚብዶኝ ነበርፀ ምክንያቱም ህይወቮን በሙሉ እግር ኳስን ብቻ ነበር ዚማውቀው። ኚእንደዚያ አይነት ቊታ መውደቅ ኚባድ ነው።"
ክላውስ ሉንደክቫም ክላውስ ሉንደክቫም ቁርጭምጭሚቱ ላይ ባጋጠመው ተደጋጋሚ ጉዳት ምክንያት በአውሮፓውያኑ 2008 ኚእግር ኳስ እራሱን እንዲያገል መገደዱን በተመለኹተ ዹተናገሹው ነው። ጫማውን ኹሰቀለ በኋላ ደግሞ ዚአልኮልና ዹአደንዛኝ እጜ ሱሰኛ ሆነ። ክላውስ በወቅቱ ዹ35 ዓመት እግር ኳስ ተጫዋቜ ዹነበሹ ሲሆን በእንግሊዝ ፕሪምዚር ሊግ በሚጫወተው ሳውዝሃምፕተን ውስጥ እጅግ ዹላቀ ብቃት አላቾው ኚሚባሉት ተጫዋ቟ቜ መካኚል ነበር። ለቡድኑ ኹ400 በላይ ጚዋታዎቜ ላይ ዹተሰለፈ ሲሆን በአውሮፓውያኑ 1996 ነበር ኚኀስኬ በርገን ሳውዝህምፕተንን ዚተቀላቀለው። በሳውዝህምፕተን ደጋፊዎቜ ዘንድ ኹፍተኛ ክብርና መወደድን ማግኘት ቜሏል። ክልጅነቱ ጀምሮ በእንግሊዝ ፕሪምዚር ሊግ መጫወት ህልሙ እንደነበር በተደጋጋሚ ይገልጻል። "ዚመጀመሪያም ዚመጚሚሻም ፍላጎቮ በእንግሊዝ እግር ኳስ መጫወት ነበር" ይላል። "ዚልጅነት ህልሜ ነው እውን ዚሆነው። እውነቱን ለመናገር ያንን ያክል ጊዜ ተፎካካሪ ሆኜ እቆያለሁ ብዬ አላስብኩም ነበር" ይላል ዹኖርዌይ ዜግነት ያለው ክላውስ። ኹኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን ጋር በመሆንም 40 ጚዋታዎቜን ማሾነፍ ቜሏል። ''ለእኔ ኹሌላ አገር መጥቶ ለሳውዝህምፕተን ለ12 ዓመታት መጫወትና ዚቡድኑ አምበል ለመሆን መቻል ልዩ እና ትልቅ ቊታ ያለው ነገር ነው" ይላል። በ2008 (እአአ) 18 ሺህ ዚሳውዝሀምፕተን ደጋፊዎቜ በተገኙበት ቡድኑ ሎልቲክን ገጥሞ ነበር። በወቅቱ ክላውስ ኚነጉዳቱ ነበር ወደ ሜዳ ገባው። ነገር ግን ዚመጀመሪያዎቹን ጥቂት ደቂቃዎቜ ኚተጫወተ በኋላ ተቀይሮ ሲወጣ በኹፍተኛ ጭብጚባ ነበር ዚተሞኘው። ያቺ ዕለት ለክላውስ ዚእግር ኳስ ሕይወቱ ማብቂያ ዚመጀመሪያዋ ነበሚቜ። ኹ1996-2007 (እአአ) ለሳውዝሀምፕተን ተጫወተው ክላውስ ሉንደክቫም ኚመጚሚሻው ጚዋታ አንድ ዓመት በኋላ ደግሞ ክላውስ ሉንደክቫም ሙሉ በሙሉ ሌላ ዓለም ውስጥ ገብቶ በሱስ ዹተጠመደ ሰው ሆኖ ነበር። ዹቀን ተቀን ሕይወቱን ይመራበት ዹነበሹው ዚታቀደና በስልጠና ዚታገዘ ዚኑሮ ዘይቀው ሲቀዚር እግር ኳስ ኚህይወቱ ወጣ። ለበርካታ ዓመታት ዚሚያውቀው ስልጠና ማድሚግ፣ ለጚዋታ መጓዝ፣ እግር ኳስ መጫወት፣ ኚጉዳት ማገገም ዚሚባሉት ነገሮቜ ታሪክ ሆነው ቀሩ። ኚእግር ኳስ በኋላ በሳውዝሃምፕተን ዹነበሹው ቆይታ በተስፋ መቁሚጥና በጭንቀት ዹተሞላ ነበር። ይህንን አስጚናቂ ጊዜ ለማለፍም ፊቱን ወደ አልኮልና ወደ አደንዛዥ እጜ አዞሚ። "በሕይወቮ በርካታ ስህተቶቜን ሰርቻለሁ። አሁን መለስ ብዬ ሳስበው በጣም ኚባድ ጊዜ ነበር። በተለይ እግር ኳስ ተጫዋ቟ቜ ጠዋት ኚእንቅልፋ቞ው ሲነሱ ተስፋና ትርጉም ዚሚሰጣ቞ው ነገር ሊኖር ይገባል። ኚእግር ኳስ በኋላም ቢሆን ዚሚሰሩት ነገር መኖር አለበት።" ''እኔ በወቅቱ ሁሉም ነገር ነበሚኝ። በጣም ብዙ ገንዘብ ነበሚኝ፣ በጣም ምርጥ ቀተሰብ እና መኖሪያ ቀት ነበሚኝ። ኖርዌይ ውስጥም ዚራሎ መኖሪያ ቀት ነበሚኝ። ጀልባዎቜ፣ መኪናዎቜፀ ሁሉም ነገር ነበሚኝ። ነገር ግን በደግንገት ድብርት ውስጥ ገባሁና ብ቞ኝነት ተሰማኝ። ዹሚፈልገኝ ሰው እንደሌለ ተሰማኝ።" "ዚእግር ኳስ መልበሻ ክፍሉን ናፈቅኩት። በዚሳምንቱ ኚቡድን ጓደኞቌ ጋር መሰልጠንና መጫወት አማሚኝ። ይሄ ሁሉ ነገር በድንገት ኹህይወቮ ሲጠፋ በጣም ኚባድ ጊዜን እንዳሳልፍ አደሚገኝ።" በርካታ እግር ኳስ ተጫዋ቟ቜ ጫማ቞ውን ኹሰቀሉ በኋላ በተመሳሳይ ዚህይወት መስመር ውስጥ ሲገቡ ይታያሉ። እጅግ በተራቀቀውና ትንሿ ስህተት እንኳን ትልቅ ዋጋ በምታስኚፍልበት ዚእግር ኳስ ዘርፍ ውጀታማ ለመሆን በዹቀኑ መጣርና መልፋት ግድ ይላል። ይሄ ሁሉ ልፋትና ዚዕለት ተዕለት ስልጠና በአንድ ጊዜ ሲቋሚጥ ተጚዋ቟ቜ ኹፍተኛ ድብርትና ዚህይወት መመሰቃቀልና ትርጉም ማጣት ውስጥ ይገባሉ። ምንም እንኳን ልክ እንደ ክላውስ አብዛኛዎቹ ተጫዋ቟ቜ ዚሚፈልጉት ነገር በሙሉ ዹተሟላላቾው ቢሆንም ኚድብርት ግን ማምለጥ አይቜሉም። "በዹቀኑ ስኬታማ ለመሆን መጣር፣ ዚውስጥ አቅምን አሟጥጊ መጠቀም፣ በዹቀኑ እና በዚሳምንቱ ምርጥ ሆኖ ለመገኘትና በሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ደጋፊዎቜን ለማስደስት ዹሚደሹገው ትግል በጣም አስደሳቜና ሰውነትን ዚሚያነቃቃ ነው" ይላል ክላውስ። ክላውስ ሉንደክቫም ኚኖርዌዩ ኀስኬ ብራን ወደ ሳውዝሃምፕተን ዹተቀላቀለው በ350 ሺህ ፓውንድ ነበር። ክላውስ ሉንደክቫም ለሳውዝሀምፕተን ለሹጅም ጊዜ ተጫውቷል በነበሹው ዚእግር ኳስ ህይወትም ሁሉም ተጫዋት ሊተማመንበት ዚሚቜል አይነት ሰው ነበር። ምርጥና ቀጣይነት ያለው አቋም ዚሚያሳይ ተጫዋቜ ነበር። ነገር ግን ኚእግር በኋላ ዹነበሹው ማንነት ኚመጀመሪያው በፍጹም ዹተለዹ ነበር። በአንድ ወቅት እንደውም በፖሊስ ቁጥጥር ስር እስኚመዋልና በሱሱ ምክንያት ሆስፒታል እስኚመግባት ደርሶ ነበር። "እግር ኳስ ካቆምኩኝ በኋላ ምናልባት ለትንሜ ዓመታት ቀለል ያለ ሕይወት መኖር አለብኝ ብዬ ለእራሎ ነገርኩት። በወቅቱ በርካታ ዹበጎ አድራጎት ሥራዎቜ ላይ እሳተፍ ነበር። በሄድኩበት ቊታ ሁሉ መጠጥ ነበር። በዚያውም ለመዝናናት እዚተባለ መጠጥ ቀት መሄድ ተጀመሚ።" "ወዲያው እራሎን መቆጣጠር አቃተኝ። ኚባድ ድብርት ውስጥም ገባሁ። ሳላስበው ኹዚህ በፊት አይቌው በማላውቀው ሁኔታ እራሎን ተስፋ ቆርጬ አገኘሁት። ፊቮንም ወደ መጠጥና ኮኬይን አዞርኩኝ። ነገር ግን ዚአልኮልና ዚኮኬይን ጥገኛ ስሆን ነገሮቜ እንደውም እዚኚፉ መጡ።" "በዹቀኑ መጠጣትና አደንዛዥ እጜ መጠቀም ጀመርኩ። ባለቀ቎ እና ሁለት ሎት ልጆቌ ወደ ኖርዌይ ተመለሱ።" "ኹአንዮም ሁለት ጊዜ እራሎን ለማጥፋት ሞክሬያለው። በጣም ኚባድ ጭንቀት ውስጥ ገባሁና ሁሉም ነገር ትርጉም አጣብኝ። ድሮ ዹማውቀው ማንነቮ ጠፋብኝ። በወቅቱ ዚመሚጥኩት ሁሉንም ለመርሳት አልኮል መጠጣት ነበር። ጥፋተኝነ቎ንና ሃፍሹቮን ለመደበቅ ሁሌም መስኚር ነበሚብኝ።" ምንም እንኳን ክላውስ ሉንደክቫም በጣም አስ቞ጋሪ ዚህይወት ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ ለመሚዳት ብዙ ጊዜ ቢፈጅበትም እርዳታ ለመጠዹቅ ግን አልቩዘነም ነበር። ዚቀድሞው ዹአርሰናል እግር ኳስ ክለብ ተጫዋቜ ፒተር ኬይ ወዳቋቋመው ዚስፖርተኞቜ ክሊኒክ ገባ። "ዚቀድሞው ሳውዝሀምፕተን አምበል እና በርካቶቜ እንደ ጀግናቾው ዚሚቆጥሩት ዹነበሹው ሰው እንደዚህ ተሰብሮ ማዚት ኚባድ ነው። በወቅቱ በጣም ኚባድ ቢሆንም አብሚውኝ ለነበሩ ሰዎቜ ስሜንና ያለብኝን ቜግር ስናገር ብዙዎቹ ይደነግጡ ነበር።" ሹጅም ጊዜ ዹፈጀው ዹማገገም ሂደት ቀላል አልነበሚም። ተመልሶ አልኮል መጠጣትና ኮኬይን መጠቀምን ጚምሮ ሌሎቜ አስ቞ጋሪ ፈተናዎቜ ነበሩ በመሀል ላይ። ነገር ግን ቆራጥ መሆንና ሕይወትን ለመቀዹር እራስን ማሳመን ወሳኝ መሆኑን ክላውስ ይናራል። "በጣም ብዙ ውጣ ውሚዶቜ ነበሩ። ሁለት ጊዜ ወደ ሱሎ ተመልሌ ነበር። አሁን ጥቂት ዓመታት አልፎታል ግን ሱሰኛ መሆኔን አምኜ ለመቀበል ትንሜ ጊዜ ፈጅቶብኝ ነበር።" "በነበሹኛ ቆይታ ያለ አልኮልና አደንዛኝ እጜ ጥሩ ሕይወት መኖር እንደሚቻል እዚገባኝ መጣ። በጣም ደስተኛ ሆንኩኝፀ በእራሎም ኮራሁ። ምንም እንኳን ያሳለፍኩት ጊዜ ቀላል ባይሆንም አሁን ካለሁበት ሁኔታ ላይ በመገኘቮ በጣም እድለኛ ነኝ።" ምንም እንኳን ክላውስ ሉንደክቫም እና ባለቀቱ በአውሮፓውያኑ 2014 ላይ ትዳራ቞ውን አፍርሰው ፍቺ ቢፈጜሙም አሁን ጥሩ ዚሚባል ግንኙነት ያላ቞ው። ኚሁለቱ ሎት ልጆቹ ጋር ያለውም ግንኙነት ኹምን ጊዜውም በበለጠ ጥሩ ዚሚባል ነው። ክላውስ ለሳውዝሀምፕተን በሚጫወትበት ወቅት ስለ አእምሮ ጀና እና ጭንቀት ማውራት ብዙም ዹተለመደ ነገር አልነበሚም። ነገር ግን አሁን ነገሮቜ በፍጥነት እዚተቀዚሩ ይመስላል። ሰዎቜ በህይወታ቞ው ዚሚገጥማ቞ውን ጭንቀትና አስ቞ጋሪ ነገር ማጋራት ጀምሚዋል። ክላውስ በአሁኑ ጊዜ አደንዛዥ እጜ ዹሚጠቀሙና ሱሰኛ ዹሆኑ ሰዎቜን በመርዳት ላይ ተሰማርቶ ይገኛል። ኚቀድሞ ክለቡ ሳውዝሀምፕተን ጋር በተመሳሳይ ጉዳዮቜ ዙሪያ ለመስራትም ፍላጎት አለው። ኚቀድሞ ቡድኑም ጋር ግንኙነት ዹፈጠሹ ሲሆን በቡድኑ ታሪክ ስማ቞ው ኚሚጠቀስ ተጫዋ቟ቜ መካኚል አንዱ እንደመሆኑፀ ተጫዋ቟ቜ ሊያጋጥሟቜው ስለሚቜሉ ፈተናዎቜ ግንዛቀ ማስጚጥ ደግሞ ህልሙ ነው።
news-56791486
https://www.bbc.com/amharic/news-56791486
በትግራይ ዚወሲባዊ ጥቃት ተጎጂዎቜን ዚሚያክሙ ባለሙያዎቜ ትግል
ኚጥቅምት 24/2013 ጀምሮ ወታደራዊ ግጭቶቜ በተካሄደባት በትግራይ ክልል ዕዳጋ ሓሙስ አንዲት ሎት ልጅ ሹዘም ለቀናት ወሲባዊ ጥቃት ኚተፈፀመባት በኋላ ማህጾንዋ ባእድ ነገሮቜ ገብቶበት ተጥላ መገኘቷ ተሰማ።
ይህቜ ተጠቂ ቁጥራ቞ው በርኚት ያለ ዚኀርትራ ወታደሮቜ አካባቢው ወደሚገኘው ወታደራዊ ካምፕ በመውሰድ ለቀናት እንደደፈሯት በአዲግራት ሆስፒታል ዹሚገኘው ዹህክምና ታሪኳ ያስሚዳል። በመጋቢት ወር ወደ አዲግራት ሆስፒታል ስትመጣ "ማህጾንዋ ውስጥ ዚነበሩ ባእድ ነገሮቜ ለማስወጣት ስሞክር ኹአቅሜ በላይ ሆነ" ዹሚለው መጀመሪያ ያያት ዶክተር አታኜልቲ ስዩም ነው። በመሆኑም ሌላ ሐኪም እንዲያያት ግድ ሆነፀ አንድ ዹማህፀንና ጜንስ ሐኪም ተጠርቶም በቀዶ ጥገና እንዲወገዱ አደሚገ። ዶክተር አታኜልቲ "ይህ አሰቃቂ ክስተት መቌ ኚአእምሮዬ እንደሚወጣ አላውቅም" በማለት እያለፈበት ያለውን ሥነ ልቩናዊ ጫና ያስሚዳል። እሷም ዹነርቭ ቜግር አጋጥሟት በመቀለ ዓይደር ሪፈራል ሆስፒታል ዚጀና ክትትል እዚተደሚገላት ይገኛል። "...ብዙ ተደራራቢ ወሲባዊ ጥቃት ዚደሚሳ቞ው ሎቶቜ ታሪክ ስሰማ ውዬ ወደ ቀት ስሄድፀ ምን እንደምሚግጥና ምን እንደምናገር አላውቅም" ትላለቜ በአይደር ሪፈራል ሆስፒታል ስር በሚገኘው ዚዋንስቶፕ ሮንተር ዚምትሰራው ነርስ ሙሉ። እነዚህ ዹህክምና ባለሙያዎቜ በዹቀኑ ዚሚያስተናግዷ቞ው ተደፍሹው ዚመጡ ሎቶቜ ተመሳሳይ ታሪክ አላ቞ው። ዚተመድ ሰብዓዊ ዕርዳታ ሃላፊ ማርክ ሎውኮክ ለፀጥታው ምክር ቀት ወሲባዊ ጥቃት በትግራዩ ግጭት እንደ ጊርነት መሳሪያ አገልግሏል ብለዋል። በተባበሩት መንግሥታት ዚአሜሪካው አምባሳደር ዋሺንግተን "በመድፈር እና ጭካኔ በተመላባ቞ው ወሲባዊ ጥቃቶቜ ደንግጣለቜ" ሲሉ ተናግሹው ነበር። ዚደሚሰባ቞ው ስቃይ ኚብዶባ቞ው መፈጠራ቞ውን ዚጠሉ፣ ጥቃቱ ባሳደሚባ቞ው ሥነ ልቩናዊ ጫና ተሚብሞው "ሰው አይፈልገኝም፣ በህይወት መኖር ዚለብኝም፣ ሞት ይሻለኛል" ዹሚሉ ተጠቂዎቜ ቁጥራ቞ው ቀላል አለመሆኑን ዹሕክምና ባለሙያዎቹ ይናገራሉ። ዚታካሚዎቻ቞ው ቀልብ አሚጋግተው፣ ታካሚዎቻ቞ው አዲስ ህይወት እንዳለ ተስፋ እንዲያደርጉ ጥሚት ማድሚግ ዚሐኪሞቹ ኃላፊነት ኹሆነ ወራቶቜ መቆጠር ጀመሚዋል። እነዚህ ዹሕክምና ባለሙያዎቜ በቂ ዹህክምና መሳሪያና መድኃኒት በሌለበት፣ ዹሰው ኃይል እጥሚት ባለበት ሁኔታ በመቶዎቜ ዚሚቆጠሩ ዚተደፈሩ ሎቶቜና እናቶቜ ሲያስተናግዱ ይውላሉ። በአዲግራት ሆስፒታል ኚአንድ ዓመት በላይ ሲያገለግል ዹቆዹው ዶክተር አታኜልቲ እስኚ አሁን ድሚስ ኹ140 በላይ ጟታዊ ጥቃት ዚደሚሰባ቞ው ሎቶቜ ማኹሙን ይናገራል። ይሁን እንጂ ይህ ቁጥር በዹቀኑ እዚጚመሚ ስለሚመጣ በዚያው ልክ ሥነ ልቩናዊና ማኅበራዊ ጫናውን እዚበሚታበት እንደመጣ ያስሚዳል። "በዹቀኑ ዹምሰማውና ዹማዹው ጉዳይ ስለሆነ፣ በዹቀኑ ራሎን ያመኛል፣ ጭንቀት አለብኝ፣ ምግብ አልበላም፣ ራስን ዚመጣልና በሆነ ነገር ያለመደሰት ሁኔታ ይታይብኛል" ይላል። እንደ ዶክተር አታኜልቲ ኹሆነ እስኚ አሁን ድሚስ ኹ258 በላይ ሎቶቜ ጟታዊ ጥቃት እንደደሚሰባ቞ው በመግለጜ አዲግራት ሆስፒታል ለሕክምና መጥተዋል። ዶ/ር አታኜልቲ ካስተናገዳ቞ው ጟታዊ ጥቃት ዚደሚሰባ቞ው ሎቶቜ መካኚል በእድሜ ትንሿ 12 ዓመት ሲሆናት፣ ትልቋ እድሜ ደግሞ ዹ89 ዓመት አዛውንት ይገኙባ቞ዋል ይላል። "አብዛኛዎቹ እናቶቜ ና቞ውፀ ዹ70 ዓመት ዚካህናት ባለቀቶቜ፣ ቆራቢ እናቶቜ አሉ። ዚደሚሰባ቞ው ሲናገሩ እንባ቞ው ይቀድማ቞ዋል። ይህን ሳይ ሁሉም ነገር ያስጠላኛል" ሲል ይናገራል። በትግራይ ካሉ ኚተሞቜ ሁሉ መቀለ ኚተለያዩ አካባቢዎቜ በተሻለ ዹህክምና አገልግሎት ዚሚገኝባት ኹተማ ናት። በአይደር ሪፈራል ሆስፒታልና በመቀለ ሆስፒታል ዚሚታኚሙ ኹመቀለና ሌሎቜ ዚትግራይ አካባቢዎቜ ዚመጡ በመቶዎቜ ዚሚቆጠሩ ተጠቂዎቜ ይገኛሉ። እስኚ አሁን በአይደር ሆስፒታል ወደሚገኘው ዚጟታዊ ጥቃት ሰለባ ማዕኹል (ዋን ስቶፕ ሮንተር) ኹ335 በላይ ጥቃት ዚደሚሰባ቞ው ሎቶቜ መምጣታ቞ውን ዚምትናገሚው ነርስ ሙሉ፣ ኚእነዚህ መካኚል ኹ140 በላይ ሎቶቜ በመደፈራ቞ው ያሚገዙትን ጜንስ እንዲቋሚጥ ዹሚፈልጉ ናቾው ትላለቜ። በተጚማሪም ሌሎቜ ተላላፊ በሜታዎቜ ዚተጠቁ፣ አካላዊና ሥነ ልቩናዊ ጥቃት ዚደሚሰባ቞ው፣ ራሳ቞ውን ቜለው መንቀሳቀስ ዚማይቜሉ ሆነው ሲመጡ ዹዚህ ማዕኹል ነርስ ሙሉ፣ ቀድሞ ዚማግኘት ኃላፊነቱ በእሷ ጀርባ ላይ ወድቋል። "ሰው መቅሚብ አይፈልጉምፀ በደሚሰባ቞ው ጥቃት ምክንያት ራሳ቞ውን ኚመጥላታ቞ው ዚተነሳ ዚአእምሮ መድኃኒት መውሰድ ዚጀመሩ አሉ" ዚምትለው ነርሷፀ በዚህ ሁኔታ ዚተሳካ ሥራ መስራት ኚባድ እንደሆነ ትናገራለቜ። "በቀን እስኚ 15 ታካሚ ዚምናይበት ሁኔታ አለ። በርካታ ዚጀና ተቋማት ስለ ተዘሹፉና ስለወደሙ ፅንስ ዚሚያቋርጡበት አልያም መድኃኒት ዚሚያገኙበት ሁኔታ ዚለም። በዚህና በሌሎቜ ምክንያቶቜ ሕዝቡም እኛም በጣሙን ተቾግሹናል" ትላለቜ። በትግራይ ክልል ውስጥ ወታደራዊ ግቜቱ ኹተኹሰተ በኋላ ዚሚያጋጥሙ ጟታዊ ጥቃቶቜን በተመለኹተ ዚተለያዩ ዚሰብአዊ መብት ድርጅቶቜ ሪፖርት ማውጣታ቞ው ይታወሳል። በተባበሩት መንግሥታት ውስጥ በግጭት ወቅት ዚሚኚሰት ወሲባዊ ጥቃት ላይ አተኩሮ ዚሚሠራው ቡድን ልዩ ተወካይ ፕራምሊያ ፓተን በትግራይ ዚሚስተዋለው ጟታዊ ጥቃት እንዲገታ ቀደም ሲል ጥሪ አቅርበው ነበር። ባለፉት ሁለት ዓመታት በማዕኹላዊው መንግሥትና በህወሓት በሚመራው ዚትግራይ ክልላዊ መስተዳደር መካኚል ዚነበሩ ፖለቲካዊ ልዩነቶቜ እዚተካሚሩ መጥተው ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም ላይ ወደ ወታደራዊ ግጭት መኚሰቱ አይዘነጋም። በዚህ ምክንያት በአስር ሺህ ዚሚቆጠሩ ዜጎቜ ወደ ሱዳን ሲሰደዱፀ በመቶ ሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ደግሞ ወደ ተለያዩ ዹክልሉ ኚተሞቜ ተፈናቅለዋል። ዹዓለም ዚምግብ ድርጅት 91 በመቶ ዹክልሉ ሕዝብ አስ቞ኳይ ሰብአዊ እርዳታ እንደሚያስፈልገው ሲገልጜፀ መንግሥትና ሌሎቜ ድርጅቶቜ ዚተለያዩ ዚእርዳታ ቁሳቁሶቜ እያቀሚቡ መሆናቾውን አስታውቋል። ትግራይ ውስጥ በተካሄደው ወታደራዊ ግጭት ውስጥ ዚተሳተፉ ኃይሎቜ ፈጜመዋ቞ዋል ኚተባሉት ዚሰብአዊ መብት ጥሰቶቜ መካኚል ጟታዊ ጥቃቶቜን በተመለኹተ በተደጋጋሚ ሲነሳ ቆይቷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት ተገኝተው እንደተናገሩት በክልሉ ውስጥ ዚመብት ጥሰቶቜ እንደተፈጞሙና ምርመራ ተደርጎ ጥፋተኛ ሆነው በተገኙት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ተናግሚዋል። "በትግራይ ወሲባዊ ጥቃትና ዘሹፋ እንደተፈጞመ ዚሚያሳዩ ሪፖርቶቜ አሉ። ዚመኚላኚያ ሠራዊት አባል ሆኖ ዚትግራይ ሎቶቜ ዹደፈሹና ንብሚት ዹዘሹፈ ወታደር በሕግ ይጠዹቃል" ብለዋል። ዚኀርትራ መንግሥትም ዚሚቀርብበትን ክስ ውድቅ ሲያደርግ ዹቆዹ ሲሆንፀ በቅርቡ በተባበሩት መንግሥታት ዚኀርትራ አምባሳደር ዚሆኑት ሶፊያ ተስፋማሪያም ለድርጅትቱ ዚጞጥታው ምክር ቀት በጻፉት ደብዳቀ ዚኀርትራ ወታደሮቜ አስገድዶ ዚመድፈር ወንጀል ፈጜመዋል መባሉ "ዚሚያስቆጣ ብቻ ሳይሆን በሕዝባቜን ባህልና ታሪክ ላይ ዹተሰነዘሹ ዹኹፋ ጥቃት ነው" ሲሉ ተቃውመውታል። "ትንሜ መድሃኒት እንቁ ሆናብናለቜ" ዚጀና ተቋማት በትግራይ ኚባድ ውድመት ኚደሚሰባ቞ው ማኅበራዊ አገልግሎት ዚሚሰጥባ቞ው ቊታዎቜ አንዱ ና቞ው። ኚታህሳስ ወር አጋማሜ እስኚ መጀመርያ ዚመጋቢት ወር ባለው ጊዜ ድንበር ዚለሹ ዚሐኪሞቜ ማኅበር በ106 ዚጀና ተቋማት ላይ ባካሄደው ዳሰሳፀ 70 በመቶ ዹሚጠጉ ተዘርፈዋልፀ 30 በመቶ ደግሞ ወድመዋል ብሏል። እነዚህ "ሆን ተብሎ ዹወደሙና ዹተዘሹፉ" ናቾው ሲል ዹክልሉ ሕዝብ ጥቂት ዹህክምና አማራጮቜ ብቻ እንደቀሩት ገልጿል። "ዚሜንትና ደም መርመራ ማድሚግ ዚምንቜልበት ሆነ መድኃኒት ዚምናገኝበት ደሹጃ ላይ አይደለንም። ታካሚዎቜ ለተኚታታይ አራት ቀናት ወሹፋ ይዘው ይውላሉ። ትንሜ መድኃኒት እንቁ ሆናብናለቜ" ዹሚለው ዶክተር አታኜልቲ ዚባለሞያ እጥሚት ባለበት ሁኔታ ዚጟታዊ ጥቃት ታካሚዎቜ ቁጥር መብዛቱ ሥራውን እንዳኚበደው ይናገራል። ተጎጂዎቹ ዝቅተኛ ዚኑሮ ደሹጃ ዚሚገኙ፣ በጊርነቱ ምክንያት አባት ወይም ወንድማ቞ው ዚተገደሉባ቞ው ሲሆኑ፣ ሌሎቜ ዚቆዳና ዚሥነ አእምሮ ቜግሮቜ ይታይባ቞ዋል። "አብዛኛውን ጊዜ ጠዋት ገብተን ምግብ ሳንበላ ዚምናድርበት ሁኔታ ስላለ ውሎ አዳሬ ሆስፒታል ውስጥ ሆኗል። ኚሩቅ አካባቢ ስለሚመጡ ትተና቞ው መሄድ ይኚብደናልፀ ደግሞም ያለቅሳሉ። ወደ ቀት ስገባ ሁሉም ነገር ስለሚሚብሞኝ አልተኛም" ይላል። ዹመቀለ ዋን ስቶፕ ሮንተር ማኅበራዊ ሠራጠኛ፣ ዐቃቢ ሕግ፣ ሐኪምና ፖሊስ ያለው ዚተደራጀ አገልግሎት ዚሚሰጥ ማዕኹል በመሆኑ ዚወሲባዊ ጥቃት ሰለባ ዚሆኑት ሎቶቜ ኹመጠቋቆም ገለል ብለው እንዲታኚሙ ሚድቷ቞ዋል። ይሁን እንጂ አብዛኛዎቹ ሎቶቜ ዚኅብሚሰተቡ አመለካኚትና ባህል ጫና ስለሚያሳድርባ቞ው ወደ ህክምና ለመምጣት አይደፍሩምፀ ዚደሚሰባ቞ውን ጉዳት ዚሚናገሩትም ጥቂት ና቞ው። ነርስ ሙሉ ማዕኹሉ ኹአቅሙ በላይ ዹሆነ አገልግሎት እዚሰጠ እንደሚገኝ ትናገራለቜ። "በህይወቮ ሙሉ እንደዚህ ሥነ ልቊናዬን ዹገደለው አጋጣሚ ዚለም። ድንጋጀውን ቀታቜን ድሚስ ይዘነው እንሄዳለን፣ ምግብ አይበላልንም። ሰው ስለሚበዛም ሰዓት እላፊውን አናኚብርም። ህይወትን ሜጊ ነው እዚተሰራ ያለው" ብላለቜ። በተጚማሪም "ወደ ቀት ስሄድ እያንዳንዱ ሳክማ቞ው ዚዋልኳ቞ውን ሎቶቜ ስም፣ ዚሰውነታ቞ው ሁኔታና ስቃያ቞ው በፍጹም አይሚሳኝም። ቀንና ሌሊት ኚእኔ ጋር ና቞ው። ስቃያ቞ው ዚእነሱ ቢብስም ሁላቜንንም ዚጎዳ ሆኗል" በማለት ቀተሰቊቜዋ ፊት ስለ ሥራዋ እንደማታወራ ገልጻለቜ። "ድሮ በትንሜ ነገር እደሰት ዚነበርኩ ሰው አሁን ቀተሰቊቌም ሆነ ጓደኞቌን ሳገኝ እንኳ አልደሰትም" ዹሚለው ዶክተር አታኜልቲ በበኩሉ "ሁሌም ለመጪው ትውልድ ምንድን ነው ዹምንነግሹው? በሚል እጚነቃለሁ" ይላል። "ኹዚህ በፊት ሻይ እዚጠጣሁ ስለ አንድ ዚዳነልኝ ታካሚዬ ሳወራ እውል ነበርፀ አሁን ግን ስደክም ባድርም ለሰው አላወራውም። ዚተስፋ መቁሚጥ ስሜት ነው ዚሚሰማኝ። በዚህ ወቅት አገልግሎት መስጠት ስላለብኝ እንጂፀ ዘወትር ዛሬም ላያ቞ው ነው? እያልኩ እዚተጚነቅኩ ነው ዹምሄደው" በማለት ያለበት ሁኔታ አስ቞ጋሪ እንደሆነ ይናገራል። "ሁሉም ህልም ይመስለኛል" ዹህክምና ባለሞያዎቜ ስለ ግል ስሜታ቞ውና ድካማ቞ው ለማሰብም ሆነ ለማዘን ብዙም ጊዜ ዚላ቞ውም። ነርስ ሙሉ እንደምትለው "አሁን እንደልብ ተናግሮ መሄድም አይቻልም። ብንናገርም ዚሚያግዘን ዚለምፀ እዚሆነ ያለውን ነገር ኹሆነ በኋላ ላግዝህ ዹሚለው ደግሞ ስቃይን ነው ዹሚጹምሹው" ትላለቜ። ዚአዲግራት ሆስፒታል ዶክተር አታኜልቲ በበኩሉ ዚመብራትና ስልክ አገልግሎት በተደጋጋሚ እንደሚቋሚጥና ኹሁሉም በላይ ውሃ አለመኖሩ ትልቅ ቜግር እንደሆነባ቞ው ያነሳል። "ሕዝቀና አገሬ ነው በሚል ወኔ ነው ዚምንሰራው እንጂፀ ሰርተን እጃቜን ዚምንታጠብበት ውሃ እንኳ ዚለም። መብራት ስለሚጠፋ ዳቊና እንጀራ ዚማይገኝበት ቀን ብዙ ነው። ለስላሳ ጠጥተን ዚምንሰራበት ሁኔታ ነው ያለው" ሲል ያስሚዳል። ኹሁሉም በላይ ግን "ህይወታቜን ሁሉ ህልም ሆኗል። ትንሜ መድኃኒት ማግኘት፣ መብራትና ሌሎቜ ነገሮቜ እንደልብ ማግኘት ህልም ነው" ብሏል። ኹ10 ዓመታት በላይ በነርስነት ያገለገለቜው ሲስተር ሙሉ በዚህ ሁሉ አስ቞ጋሪ ሁኔታ አንድ ተስፋ ዚሚሰጣት ነገር አለ። እሱም "ጥቃቱ ዚደሚሰባ቞ው ሎቶቜ እዚህ በመምጣት አእምሯ቞ውን ሰቅዞ ይዞት ዹነበሹው ቜግር በትንሜ ቃላት ቀለል ሲልል቞ው ደስ ይለኛል። ቀልባ቞ውን ስተው መጥተው አሁን በእግራ቞ው ሲሄዱ ሳይ እደሰታለሁ" ትላለቜ። ይህቜ መቅለል ግን ጊዜያዊ ናት። ሐኪሞቹ ትንሜ ቀለል ያላ቞ው ሾክም መልሶ ዚሚቆለልባ቞ው እንደገና አዲስ ዚጥቃት ሰለባዎቜ ሲመጡ ወደነበሹው ዚጭንቀት አዙሪት መልሰው እንደሚገቡ ይናገራሉ።
news-45215114
https://www.bbc.com/amharic/news-45215114
በምስራቅ ጎጃም መሬት መንሞራተት አደጋ ዚስምንት ዚሰዎቜን ህይወት ቀጠፈ
በምስራቅ ጎጃም ዞን፣ ጎንቻ ሲሶ እነሎ ወሚዳ፣ እነገት ቀበሌ፣ ወይን ውሃ ጎጥ ነሃሮ 8፣2010 ዓ.ም ኚሌሊቱ 6፡30 ገደማ በደሹሰ ዚመሬት መንሞራተት አደጋ በአንድ ቀት ውስጥ ዚነበሩ ስምንት ግለሰቊቜ ህይወት አልፏል።
ኚሟ቟ቹ መካኚል ስድስቱ ዚአንድ ቀተሰብ አባል ሲሆኑፀ አምስት ልጆቜ እና እናታ቞ው እንዲሁም ኹሌላ አካባቢ በእንግድነት ዚመጣ ዚእርሷን ወንድም ጚምሮ ስራ ለማገዝ ሲል በቀቱ ዹተገኘ ጎሚቀት ህይወታ቞ው እንዳለፈ ዚምስራቅ ጎጃም ዞን ኮሚዩኒኬሜን ፅ/ቀት ባለሙያ አቶ ጋሻዬ ጌታሁን ለቢቢሲ ገልፀዋል። •በኢትዮጵያ ዹመንጋ ፍትህ ዹሰው ህይወት እዚቀጠፈ ነው •ዚመገንጠል መብት ለማን? መቌ? •ልዩ ፖሊስ ማነው? ዚወደፊት ዕጣውስ? ዚሟቿ ባለቀት ካህን በመሆናቾው በወቅቱ ቀተ ክርስቲያን በመሄዳ቞ው ኹአደጋው ሊተርፉ ቜለዋል። ዚሟ቟ቹ ዚቀብር ስነ ስርዓትም በትናንትናው ዕለት ተፈፅሟል። በነሃሮ 3፣2010 ዓ.ም በደጀን ወሚዳ፣ ቆቅ ውሃ ቀበሌ ላይ ተመሳሳይ አደጋ ደርሶ በእንስሳት ላይ ጉዳት እንዳደሚሰ ባለሙያው ይናገራሉ። በተለይ ዚክሚምት ዝናብ እዚጚመሚ በመሄዱ ተራራ አካባቢ ዚሚኖሩ አርሶ አደሮቜ ቅድመ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መልዕክት ቢሮው አስተላልፏል። በተለይ ወደ ተራራ ጫፍ ዚሚወጣ ጎርፍ መቀዚሻ ቊዮቜ አቅጣጫ቞ው እንዲቀዚር እዚተደሚገ መሆኑን አቶ ጋሻዬ ለቢቢሲ ገልፀዋል።
50135333
https://www.bbc.com/amharic/50135333
"መንገድ መዝጋት ዹኋላ ቀር ፖለቲካ ውጀት ነው” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ
ዛሬ ጥቅምት 11፣ 2012 ዓ. ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ በሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት ተገኝተው ኹምክር ቀቱ አባላት ለቀሹበላቾው ጥያቄ ምላሜ ሰጥተዋል።
ስለ ምርጫ፣ ስለ ፌዎራል ሥርዓቱ፣ ሙስና፣ ሚዲያ፣ ፀጥታና ደህንነት፣ ታላቁ ህዳሎ ግድብ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ እና ሌሎቜ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮቜን በተመለኹተ ኹምክር ቀት አባላቱ ጥያቄ ቀርቊላ቞ዋል። • ዹጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ "መደመር" መጜሐፍ ተመሹቀ • ዹጠቅላይ ሚኒስትሩ መጜሐፍ ምን ይዟል? • "ውስኪ ጠጪ ኢህአዎጎቜ እባካቜሁ ውሃ ዹናፈቀው ሕዝብ እንዳለ አትርሱ" ጠ/ሚ ዐብይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምርጫን በሚመለኚት ለተነሳላ቞ው ጥያቄ ሲመልሱ "በዘንድሮም ምርጫ ይሁን በሚቀጥለው ምርጫ ተግዳሮት ዹሌለው ምርጫ ማድሚግ አይቻልም" በማለት ምርጫው ይራዘም ዹሚለው እንደማያስኬድ ተናግሚዋል። መንግሥት በቂ በጀት ለምርጫ ቊርድ መመደቡን እንዲሁም ዚቊርዱ አባላትም ኹማንኛውም ጊዜ ዚተሻለ ነፃ ነው ዚሚያስብል እንደሆነም በመጥቀስ ካለፉት ጊዜያት ዚተሻለ ምርጫ ማድሚግ ይቻላል ብለዋል። "ዚመንግሥት ፍላጎትም ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ እንዲካሄድ ነው" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዚመንግሥት ዝግጁነትም ኹዚህ በፊት ኹነበሹው ዚተሻለ እንደሆነ አሚጋግጠዋል። መንግሥት፣ ሕዝብ እና ምርጫ ቊርድ ተባብሚው ዚተሻለ ምርጫ ማካሄድ እንደሚቻል እምነት እንዳላ቞ው አስሚድተዋል። በምርጫ ሕጉ ላይ ቅሬታ ያላ቞ው ፓርቲዎቜ ያቀሚቡት ቅሬታ አግባብ አይደለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ "ሰብሰብ ማለት ለሁላቜንም ያስፈልጋል" ብለዋል። "ምርጫውን ማድሚግ በብዙ መልኩ ይጠቅመናልፀ ፈተና አልባ ምርጫ ባይሆንም ዚተሳካ ምርጫ ማድሚግ ይቻላል" ሲሉ ምላሜ ሰጥተዋል። ኢህአዎግ በውስጡ ያለውን ቅሬታ በሚመለኚትም ሲናገሩ "ኢትዮጵያ ዚኢህአዎግ አባት እንጂፀ ኢህአዎግ ዚኢትዮጵያ አባት አይደለም" በማለት እኛ ኹሌለን ኢትዮጵያ ትበተናለቜ ዹሚል አስተሳሰብ ትክክል ያልሆነ ነው ሲሉ ተናግሚዋል። ኢህአዎግ ውስጥ ላለፉት 5 እና 10 ዓመታት ውህደቱ ውይይት ሲደሚግበት መቆዚቱን አስታውሰውፀ ውህደት እንዲፈፀም በሀዋሳው ጉባኀ በሙሉ ድምፅ መወሰኑን አስታውሰን "እዚተወያዚን ነው" ብለዋል። • "ተጚማሪ ዚፌደራል ዚሥራ ቋንቋዎቜ እንዲኖሩ እዚተሠራ ነው" ጠ/ሚኒስትር ዐብይ • "ለእናንተ ደህንነት ነው በሚል እንዳሰሩን ተገልፆልናል" ዚባላደራ ምክር ቀት አስተባባሪ ውህደቱ ጊዜው አሁን አይደለም ዹሚሉ ፓርቲዎቜና አባላት ቢኖሩም እስካሁን ግን ውህደቱ አያስፈልግም ያለ አካል ሰምተው እንደማያውቁ ተናግሚዋል። በክልሎቜ መካኚል ያለውን ፀጥታ በተመለኚተምፀ ዚትጥቅና ዚቃላት ፉክክር እንደሚታይ ዚተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ "ዚውጊያ ቀስቃሟቜ ሁል ጊዜም አንድ ዓይነት ናቾው" በማለት በዹጊዜው ግጭት እዚቀሰቀሱ በዚያ ውስጥ መኖር ዹሚፈልጉ አሉ በማለት ወጣቶቜ እንዲነቁ መክሚዋል። ዚትግራይ ክልልን እዚመሩ ያሉ አመራሮቜ ዹክልሉን ቜግር መፍታት እንጂ ኚአማራ ክልል ጋር መዋጋት አይፈልጉም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ "በመካኚል ዚድራማው አካል ዚሆኑትን ዚመለዚት ቜግር ነው ያለው" ብለዋል። ዚክልሎቜ ትጥቅ በሀገር ደሹጃ ዚሚያሰጋ አይደለም በማለት ክልሎቜ መዘጋጀት ያለባ቞ው ዚራሳ቞ውን ዹክልል ውስጥ ደህንነት ለመጠበቅ እንጂ ኚሌሎቜ ክልሎቜ ጋር ለመጋጚት መሆን እንደሌለበት ተናግሚዋል። ዚፌደራል መንግሥት ዚሚቜለውን እያደሚገ እንደሚሄድ ጠቅሰው በአማራና ቅማንት፣ በሶማሌና በአፋር መካኚል ዚሊስት ቀበሌ ቜግር ነው ያለው በማለት ቜግሩን ዚፈጠሩት ሌሎቜ ናቾው ማለት ዹሚለው ስለማያዋጣ ኃላፊነት ወስዶ መሥራት ይጠይቃል ሲሉ አሳስበዋል። "መንገድ መዝጋት ዹኋላ ቀር ፖለቲካ ውጀት ነው።" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዹተፈጠሹው ነገር ዚማስተካኚያ እርምጃ እዚተወሰደ መሆኑን ገልፀዋል። "ዚሚያባሉን እድሜ ጠገብ ሰዎቜ ናቾው" በማለት ባይሎጂም [ሥነ ሕይወትም] ኹዚህ አንጻር ዚራሱ መፍትሔ ስላለው ሰላም ማደፍሚሱ እንደማይቀጥል አስሚድተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ ውስጥ ዚተለያዩ ሥፍራዎቜ በግላቾው በመንቀሳቀስ በርካቶቜን ያነጋገሩት ሰላም ለኢትዮጵያ ቀዳሚ ስለሆነ ነው በሚል መርህን በመኹተል እንደሆነና በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ፣ በብሔሮቜ መካኚል እርቅ እንዲፈጠር ዚእርቅ ኮሚሜን እንዲቋቋም ዚተሠራው ዚውስጥ ሰላም ወሳኝ ስለሆነ መሆኑን ተናግሚዋል። መፈናቀል ቁጥሩን ማጋነን ብቻ ሳይሆን በማለት "50 ሺህ ተፈናቃይ አለብን ያሉ 1ሺህ ተፈናቃይ ማቅሚብ አልቻሉም በማለት ማፈናቀልና ተፈናቃይ መቀበል ንግድ ነው ዹሆነው" ብለዋል። "በጌዲዮ ዹተፈናቀለው በሚሊዹን ተጠርቶ ስንመልስ ግን አነስተኛ ቁጥር ብቻ እንዳላ቞ው ተሚድተናል" ሲሉም ተናግሚዋል። መንግሥታ቞ው ለውስጥ ሰላም አበክሮ እዚሰራ መሆኑን ገልፀው "ዚምንታገሰው ዹነበሹውን ነገር ላለመድገም ነው" ሲሉ አስሚድተዋል። ዚሕዳሎው ግድብን በተመለኹተ ጠንኹር ያለውን ዚግብፅ አቋም አስመልክቶ ዚተጠዚቁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " ዹማንንም ፍላጎት ለመጉዳት ዹጀመርነው ፕሮጀክት አይደለም" በማለት በመግባባትና ዚግብፅን ስጋት ኚግምት ውስጥ በማስገባት እንቀጥላለን ብለዋል። በሚቀጥሉት ቀናት ኚግብፅ ፕሬዝዳንት አልሲሲ ጋር ተገናኝተው እንደሚወያዩም አስሚድተዋል። " ቁጭ ብለን እናወራለንፀ ማንም ይህንን ግንባታ ማስቆም አይቜልም። ይህ ሊሰመርበት ይገባል" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጊርነት እንኚፍታለን ዹሚሉ አስተያዚቶ቞ን አስመልክተው ሲናገሩ "ማንንም አይጠቅምም ብለን እናምናለን" ብለዋል። "ጊርነትም ኹሆነ ኢትዮጵያ ብዙ ሕዝብ አላትፀ በሚሊዮን ማሰለፍ እንቜላለን" ብለዋል። አክለውም "በቀድሞ መሪዎቜ ዚተፈጠሩ ስህተቶቜን እናስተካክላለን እንጂ ዚተጀመሩ ምርጥ ስራዎቜን አናቋርጥምፀ እንዲህ አይነት ምርጥ ስራዎቜን በማቋሚጥ አገር አትገነባም" ብለዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ሰው ሰራሜ ዹሆነም መዋቅራዊም ዹሆነ ዹዋጋ ንሚት አለ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ 'ሆም ግሮውን' ኢኮኖሚ ማሻሞያ ዚተነሳው ነገር በማለት ማክሮ ኢኮኖሚ አለመመጣጠን ለማስተካኚል መዋቅራዊና ዘርፋዊ (ሎክቶራል) ማሻሻያ ይካሄዳል ብለዋል። በእነዚህ ውስጥ ዚኑሮ ውድነቱን ካመጡ ነገሮቜ መካኚል አንዱ ዚቀት ኪራይ ውድነት መሆኑን ዚጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሁለተኛው ዚምግብ ዋጋ መናር እንዲሁም ስራ አጥነትና ዹሚመሹተው ምርት በገበያ ኹሚፈለገው ያነሰ መሆን ነው ብለዋል። አንደኛውን ነጥሎ በመፍታት ለሁሉም መፍትሄ አይሆንም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀት በሚመለኚት እስካሁን ኚተገነቡት ቀቶቜ በእጥፍ ዹሚልቅ በመንግሥትም በግል ባለሃብቶቜም ለመገንባት እዚሰሩ መሆኑን ተናግሚዋል። ይህ ግንባታ በአዲስ አበባም ኚአዲስ አበባ ውጪም ዚሚካሄድ እንደሆነ ዚተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንባታው በጥምሚት ወይንም በሙሉ ኢንቚስትመንት እንደሚሆን አብራርተዋል። ቢሊዮን ዶላር ዚሚያወጣውን ዚለገሃሩን ፕሮጀክትንም በማስታወስ ሌላ ጎተራ አካባቢ በተመሳሳይ ለባለሃብቶና ዲፕሎማቶቜ ዚቀት ፍላጎት ዹሚሆን አዲስ ቱሞሮ ዹተሰኘ አዲስ ፕሮጀክት አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ኚቻይና መንግሥት ኩባንያ ጋር ሊፈራሚሙ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናገሚዋል። ሌላው ዹግል ባለሀብቶቜ መካኚለኛ ገቢ ላላቾው ግለሰቊቜ ዚሚሰሯ቞ው ቀቶቜ ቜግሩን እንደሚያስተነፍሱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ እንደራሎዎቹ አስሚድተዋል። ኹዚህ በተጚማሪም በሁለት ወር ውስጥ እስኚ 4ሺህ ዚጎዳና ተዳዳሪዎቜን ዹሚሆን ዚቀቶቜ ግንባታ እዚተካሄደ ነው ብለዋል። እነዚህ ዚጎዳና ተዳዳሪዎቜን መጠለያ በመስጠት ዚተለያዩ ስራዎቜ ላይ ለማሰማራት ሁሉንም ታሳቢ ያደሚገ ስራ መንግሥታ቞ው እዚሰራ መሆኑን ተናግሚዋል። ሌላው ምግብ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሁለት ወር ውስጥ ዹሚጠናቀቀው በቀን 1 ሚሊዹን ዳቊ ዚሚያመርተው ኚግለሰቊቜ ጋር በመነጋገር እዚተገነባ ያለው ፋብሪካ ቢያንስ አቅማቾው ዝቅተኛ ለሆኑ ሰዎቜ በቅናሜ ዳቊ ለማቅሚብ እንደሚያስቜል ገልፀዋል። በዚህ ዓመት ዚበጀት ዓመት መጠናቀቂያ ድሚስ ዹሚጠናቀቀውና ግዙፍ ዹሆነው ሌላ ዚዳቊ ፋብሪካ ዚተባበሩት አሚብ ኢሚሬትስ ንጉስ በሰጡት ርዳታ በቀን ኹ10 ሚሊዹን ዳቊ ዚሚያመርት ፋብሪካ መሆኑንም ገልፀዋል። ይህ ፋብሪካ አዲስ አበባ ብቻ ሳይሆን በአዲስ አበባ ዙሪያ ላሉ ዜጎቜም ዚዳቊ አቅርቊት ይኖሹዋል ብለዋል። ዹኹተማ እርሻ ላይ በመሰማራት ዚስራ ፈጠራና ዚኑሮ ውድነቱን ለመቆጣጠር ይሰራል ሲሉም አክለዋል። ዹመገናኛ ብዙኃንን አስመልክቶ ጠቅላዩ በተናገሩት ንግግር ሚዲያው ላይ ያሉ ባለ ድርሻ አካላት ሚዲያ ነፃ እንዲሆን በተደጋጋሚ መጠያቃ቞ውን አውስተዋል። "መቻል ላይ ግን ቜግር አለፀ ሚዲያ ዚዘር፣ ዚብሔር፣ ዚነጋዎዎቜ መቀለጃ ሆኗል።" በማለት ኢትዮጵያዊያን መሚጃዎቜን እያጣሩ እንዲሰሙና ኃላፊነት እንዲወስዱ ጠይቀዋል። ዹሌላ አገር ፓስፖርት ኖሯ቞ው ዚሚዲያ ባለቀት ዹሆኑ ሰዎቜን በሚመለኚትም "ትዕግሥት እያደሚግን ያለነው አውዱን ለማስፋት ነው... እርምጃዎቜን መውሰዳቜን አይቀርም" በማለት "ሁለት ቀት መጫወት አይቻልም" ሲሉ አስጠንቅቀዋል። በነጻነት ልማትን ዚሚያግዙ ኹሆነ እንደሚበሚታቱፀ ካልሆነ ግን ዲሞክራሲን ለማደናቀፍ ዚሚሠሩትን መንግሥታ቞ው እንደማይታገስ በአፅንኊት አስጠንቅቀዋል።
50805232
https://www.bbc.com/amharic/50805232
መንግሥት አደገኛ ዹሆነውን ዚትግራይን መገለል መለስ ብሎ ሊያጀነው ይገባል- ክራይስስ ግሩፕ
በኢትዮጵያ እዚተካሄደ ያለው ሜግግር ሃዲዱን እንዳይስት መንግሥት፣ ዚፖለቲካ አመራሮቜና ዓለም አቀፍ አጋሮቜ አስፈላጊ ነገሮቜን እንዲያደርጉ ኢንተርናሜናል ክራይስስ ግሩፕ ዛሬ ባወጣው ሪፖርት ጠዚቀ።
በዓለም ዙሪያ ዚሚኚሰቱና ሊኚሰቱ ዚሚቜሉ ቀውሶቜን ዚሚኚታተለው ይህ ቡድን ኢትዮጵያን በተመለኹተ ባወጣው ዘገባ ላይ በተለይ ኚመጪው ምርጫ በፊት ሊደሹጉ ይገባሉ ያላ቞ውን ነገሮቜ በዝርዝር አመልክቷል። ሪፖርቱ በኢትዮጵያ እዚተካሄደ ያለው ለውጥ በአገር ውስጥና በውጪ ተስፋን ዹፈነጠቀ ቢሆንም አደገኛና ኹፋፋይ ሁኔታንም ደቅኗል ይላል። ቡድኑ እንዳለው በቅርቡ ጥቅምት ወር ላይ ኊሮሚያ ውስጥ ዚተቀሰቀስው ተቃውሞ ዹደም መፋሰስን ማስኚተሉን ጠቅሶ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን ኚመጡ በኋላ ዚተኚሰቱ ግጭቶቜ በመቶዎቜ ለሚቆጠሩ ሰዎቜ ሞትና በሚሊዮኖቜ ለሚቆጠሩት ደግሞ መፈናቀል ምክንያት መሆናቾውን አመልክቷል። • ሲዳማ: 10ኛው ዚኢትዮጵያ ክልል ሪፖርቱ አክሎም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ለሊስት አስርት ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ በብ቞ኝነት አገሪቱን ሲመራ ዹነበሹውን ኢህአዎግን ለመለወጥ ዚወሰዱት እርምጃ ያለውን መኹፋፈል ዹበለጠ ሊያሰፋው እንደሚቜል አመልክቷል። ለዚህም ጠቅላይ ሚኒስትሩና አጋሮቻ቞ው እያካሄዱ ካለው ዚለውጥ እርምጃ አንጻር በኊሮሞ ቡድኖቜ መካኚል እንዲሁም በአማራና በትግራይ ክልል አመራሮቜ መካኚል ያለውን ውጥሚት ለማርገብ ጥሚት ማድርግ እንዳለባ቞ው በመምኚርፀ "ነገር ግን ውጥሚቶቹ እዚተባባሱ ዚሚሄዱ ኹሆነ ይደሹጋል ዚተባለው ምርጫ ማዘግዚት ሊያስፈልግ እንደሚቜል" ጠቁሟል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደስልጣን ኚመጡ በኋላ ዚወሰዷ቞ው ተኚታታይ ዚለውጥ እርምጃዎቜ በአገር ውስጥና በውጪ ትልቅ ተቀባይነትን እንዳስገኘላ቞ው ዹጠቀሰው ዚክራይስስ ግሩፕ ሪፖርት፣ ነገር ግን እርምጃዎቹ ዹነበሹውን ሥርዓት በማስወገድ ዚመንግሥትን አቅም እንዳዳኚመው ጠቅሷል። ይህም ጠቅላይ ሚኒስትሩን ወደ ስልጣን ያመጣው ሕዝባዊ ተቃውሞን ያንቀሳቀሰው ዚብሔርተኝነት እንቅስቃሎ "አዲስ ጉልበት እንዲያገኝ አድርጎታል" ይላል። አክሎም በግንቊት ወር እንደሚካሄድ በሚጠበቀው ምርጫ እጩዎቜ ኚዚመጡበት ዚብሔር ቡድን ድምጜ ለማግኘት ፉክክር ስለሚያደርጉ ግጭቶቜ ሊኚሰቱ እንደሚቜሉ ስጋቱን ገልጿል። ክራይስስ ግሩፕ በሪፖርቱ በአገሪቱ ውስጥ በተለይ ስጋትን ዚሚፈጥሩ ያላ቞ውን አራት ሁኔታዎቜን አመልክቷል። • ዚደቡብ ክልል፡ ውስብስቡ ዚዐብይ ፈተና ዚመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዚመጡበትን ዚኊሮሚያ ክልልን ዚሚመለኚት ሲሆን ተቀናቃኞቻ቞ው እንዲሁም አንዳንድ ዚቀድሞ አጋሮቻ቞ው ሳይቀሩ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዹክልሉን ጥቅም በማስኚበር በኩል ዹበለጠ መስራት እንደሚጠበቅባ቞ው ያምናሉ። ሁለተኛው ተግዳሮት ደግሞ በኊሮሞና በአማራ ፖለቲኚኞቜ መካኚል በአዲስ አበባና በሌሎቜ ጉዳዮቜ ላይ ያለው ዚተጜእኖ ፉክክር ሲሆን ሊስተኛው ደግሞ ኚአማራ ክልል ወደ ትግራይ ተካልለዋል በሚባሉ ዚድንበር አካባቢዎቜ ያለው ዹመሹሹ ውዝግብ እንዲሁም አራተኛው ያቋቋሙትና በበላይነት ሲመሩት ዹነበሹው ሥርዓት እዚፈሚሰ ነው በማለት ቅሬታ቞ውን ዚሚያቀርቡት ዚትግራይ አመራሮቜ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ ያላ቞ው ተቃውሞ ዋነኛ ፈተናዎቜ እንደሆኑ በሪፖርቱ ተመልክቷል። ኹዚህ በተጚማሪም በአንዳንድ ዚአገሪቱ ክፍሎቜ ውስጥ እዚጚመሚ ዚመጣው በአብያተ ክርስቲያናትና በመስጊዶቜ ላይ ዹሚፈጾመው ጥቃት በእምነቶቜ መካኚል ያለው ውጥሚት እዚጚመሚ መምጣቱን ኹመጠቆሙ ባሻገር አገሪቱ ባለባት ቜግር ላይ ሌላ ፈተናን ዹሚጹምር ነው ብሏል ሪፖርቱ። ሌላኛው ዚውጥሚት ምንጭ ብሎ ሪፖርቱ ያስቀመጠው ጉዳይ ደግሞ አገሪቱ ዚምትኚተለው ዚብሔር ፌደራላዊ ሥርዓት ጉዳይ ነው። ይህንን በሚደግፉና በሚቃወሙ ወገኖቜ መካኚል ያለው ክርክር በኢትዮጵያ ዚፖለቲካ መድሚክ ላይ "ዋነኛ ዚመፋለሚያ ምክንያት" መሆኑን ጠቅሷል። • ዚህወሓት አመራሮቜ ኹጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ ጋር ስለምን ጉዳይ ተወያዩ? በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዚሚመሩት ግንባር ሌሎቜ አጋር ድርጅቶቜን አካትቶ አንድ ወጥ አገር አቀፍ ፓርቲ ለመሆን ኹወሰነ በኋላ ድጋፍና ተቃውሞ እንዳጋጠመው ሪፖርቱ ጠቅሶ፣ ውህደቱ ኹላይ በኢህአዎግ ዚተያዘው ዚመንግሥት ቢሮክራሲ ውስጥ ተጚማሪ ውጥሚት ሊፈጥር እንደሚቜል ሪፖርቱ አመልክቷል። እርምጃው ዚብሔር ፌደራሊዝምን ሊያስቀር ይቜላል በሚል ዚትግራይ አመራሮቜና ዚኊሮሞ ቡድኖቜ መቃወማቾው ዚሚታወስ ሲሆን ህወሓትም አዲሱን ፖርቲ እስካሁን ድሚስ አልተቀላቀለም። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሁሉንም ዚሚያቀራርብ አስማሚ እርምጃዎቜ በመውሰድ አገሪቱን አንድ ለማድሚግ ጥሚት ቢያደርጉም ኚባድ ተግዳሮቶቜ እንደገጠማ቞ው ዚክራይስስ ግሩፕ ሪፖርት ያመለክታል። ኢትዮጵያ ውስጥ እዚታዚ ያለውን ውጥሚት ለማርገብ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ መንግሥታ቞ውና ዓለም አቀፍ አጋሮቜ ሊወስዷ቞ው ይገባል ያላ቞ውን እርምጃዎቜ ሪፖርቱ ጠቁሟል። በዚህም መሰሚት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ዚአማራና ዚትግራይ አመራሮቜ ግንኙነታ቞ውን ዚሚያሻሞል ውይይት እንዲያደርጉ ግፊት ማድርግና በኊዲፒ ውስጥም ሆነ ኚሌሎቜ ዚኊሮሞ ተቃዋሚ አባላት ጋር በመነጋገር ልዩነቶቜ ኹኃይል ይልቅ በምርጫ ውጀት መፍትሄ እንደሚያገኙ መተማመን ላይ መድሚስ ይጠበቅባ቞ዋል ሲል ይመክራል። በተጚማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአማራና በኊሮሞ አመራሮቜ መካኚል ዚሚካሄዱ ውይይቶቜ እንዲቀጥሉ በማድሚግ አዲስ አበባን ጚምሮ በተለያዩ ኚተሞቜ ዚሚስተዋሉ ውጥሚቶቜን ማርገብ ይጠበቅባ቞ዋል ይላል ሪፖርቱ። • ኹ20 ዓመት በኋላ ዚኢትዮጵያ ዕጣ ፈንታ ምን ይሆናል? መንግሥት ኚትግራይ አንጻር እርቅ ዚሚያወርድ እርምጃን በመውሰድ ኚቀድሞ ባለስልጣናት አንጻር ዚሚነሱ ክሶቜን ተመልሰው እንዲያጀኑ ሊያደርግ ይቜላል። ኹዚህ በተጚማሪም ሜግግሩን ተኚትሎ ዹተፈጠሹውን አደገኛ ዹሆነውን ዚትግራይ መገለል መንግሥት ሊያጀነው ይገባል። ዚትግራይ አመራሮቜም በበኩላ቞ው እንደማይቀበሉት ያሳወቁትን ኚአማራ ክልል ጋር ዚሚወዛገቡበትን ዚይገባኛል ጥያቄዎቜ ለመመለስ ዹተቋቋመውን ዚአስተዳደር ወሰንና ዚማንነት ጉዳዮቜ ኮሚሜንን በተመለኹተ ውሳኔያ቞ውን መለስ ብለው ማስተካኚል ይኖርባ቞ዋል ይላል ሪፖርቱ:: በተጚማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩና አጋሮቻ቞ው ውህድ ፓርቲ በሚመስርቱበት ሂደት ውስጥ ዚብሔር ፌደራሊዝሙ ሊቀር ይቜላል በሚል ዹተፈጠሹውን ስጋት በጥንቃቄ ማስወገድ ይጠበቅባ቞ዋል ዹሚለው ክራይስስ ግሩፕ፣ በሕገ መንግሥቱ ላይ ማንኛውም አይነት ማሻሻያ ዹሚደሹግ ኹሆነ ዚሚመለኚታ቞ው ወገኖቜ በሙሉ ዚሚሳተፉበት እንደሚሆን በግልጜ ማስቀመጥ ያስፈልጋል ብሏል። ሪፖርቱ እንደሚለው ምርጫው በተያዘለት ጊዜ ዚሚካሄድ ኹሆነ ቀደም ብሎ ቁልፍ ተቃዋሚ ኃይሎቜንና ሲቪል ማህበራትን በማሳተፍ ኚምርጫው በፊትና በኋላ ሊኚሰቱ ዚሚቜሉ ግጭቶቜን ለማስወገድ ተኚታታይ ውይይቶቜን ማድሚግ ያስፈልጋል። ነገር ግን መኹፋፈልና ግጭትን ዚሚያስኚትል ዚምርጫ ዘመቻ ዚሚያይል ኹሆነ መንግሥት ኹዋነኛ ተፎካካሪ ፓርቲዎቜ ድጋፍ በመጠዹቅ ምርጫው ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍና ብሔራዊ ውይይት እንዲካሄድ ሊጠይቅ ይቜላል። ሪፖርቱ ለኢትዮጵያ መንግሥት ካቀሚበው ሃሳብ በተጚማሪ ለአገሪቱ ዓለም አቀፍ አጋሮቜም ጥሪ አቅርቧል። በዚህም መሰሚት አጋሮቜ ዚሚይዙት አቋም በመሬት ላይ ያለውን አሳሳቢ ሁኔታን መሰሚት ያደሚገ መሆን አለበት ብሏል። ስለዚህም ለሜግግሩ በይፋ ድጋፋ቞ውን በመግለጜ በዝግ ደግሞ ሁሉም ወገኖቜ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ማግባባት ይጥበቅባ቞ዋል ብሏል። ኹዚህ ባሻገርም በመጪዎቹ ወራት ዚፖለቲካውና ዚደህንነቱ ሁኔታ ዹማይሹጋጋ ኹሆነ ምርጫው እንዲዘገይ ሃሳብ ሊያቀርቡ ይቜላሉ። ዚውጪ አጋሮቜ ዚሚሰጡት ተኚታታይ ዚገንዘብ ድጋፍ እስፈላጊነትን ዹጠቀሰው ሪፖርቱ፣ ዚተዳኚሙ ተቋማትን ለማጠናኚር፣ ዚኢኮኖሚ መዋቅር ለውጥ ለማምጣት እንዲሁም በለውጡ ወቅት ዚሚኚሰትን ዚወጣቱን ቅሬታና ተቃውሞ ለመቀነስ ይሚዳል። • ዚዐቢይ ለውጥ፡ በመስቀለኛ መንገድ ላይ? ኢትዮጵያ ውስጥ እዚተካሄደ ያለው ለውጥ ለብዙዎቜ ተስፋን ዹሰጠ እንደሆነ ዹጠቀሰው ሪፖርቱ ዚሚታዩ ምልክቶቜ ግን ለቀድሞ ኹፍተኛ ባለስልጣናት አሳሳቢ ናቾው ብሏል። ዚእንዳንዶቜ ስጋት ዹተጋነነ ቢሆንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጀመሩት ዚለውጥ ሂደት ላይ ጥንቃቄን በማኹል ወሳኝ ዹሆኑ ደጋፊዎቜን አሳትፈው መጓዝ እንደሚያስፈልጋ቞ው አመልክቷል። በተጚማሪም ሁሉንም ዚኢትዮጵያ ሕዝቊቜ ለማሳተፍ ዚሚያደርጉትን ጥሚት በማጠናኚር፣ በሚወዛገቡ ዹክልል ልሂቃን መካኚል ውይይቶቜ እንዲቀጥሉ በማድሚግ፣ ዚገዢው ግንባር ውህደት አገሪቱን እንደማያናጋ ዚሚያሚጋግጡ እርምጃዎቜን መውሰድና ለአሁን በሕገ መንግሥቱና በብሔር ፌደራሊዝም ላይ ዹሚደሹጉ መደበኛ ድርድሮቜን ለሌላ ጊዜ ማቆዚት እንደሚያስፈልግ ዚክራይስስ ግሩፕ ሪፖርት ይመክራል።
news-49792728
https://www.bbc.com/amharic/news-49792728
'ሶሪያውያን' ስደተኞቜ ዚስፖርት ቡድን አባላት በመምሰል ድንበር ሲሻገሩ ግሪክ ውስጥ ተያዙ
ዚሶሪያ ዜጎቜ ሳይሆኑ እንዳልቀሚ ዚተገመቱ 10 ሰደተኞቜ ዚመሚብ ኳስ ተጫዋቜ መስለው ወደ ስዊዘርላንድ በሕገ-ወጥ መንገድ ለመጓዝ ሲሞክሩ በግሪክ ፖሊስ አ቎ንስ አዹር ማሚፊያ ውስጥ በቁጥጥር ሥር ዋሉ።
ስደተኞቹ ሶሪያውያን ሳይሆኑ አይቀርም ተብሏል። ዚቡድኑ አባላት ተመሳሳይ ዚስፖርት ትጥቅ ዚለበሱ ሲሆን ሁለት ዚመሚብ ኳሶቜም በእጆቻ቞ው ይዘው ነበር። ፖሊስ እንደሚለው ሶሪያውያን እንደሆኑ ዚተገመቱት 10ሩ ስደተኞቜ ዚእራሳ቞ው ባልሆነ ፓስፖርት ለመጓዝ ጥሚት ሲያደርጉ ነበር። • ሚሊዮን ዶላር አጭበርባሪው ስደተኛ • «ሳሞንፍ ጀርመናዊ ስሞነፍ ስደተኛ» ኩዚል • ካለሁበት፡ ''በሜዲትራንያን ባህር ኚመስመጥ መትሚፌ ሁሌም ይደንቀኛል" ስደተኞቹ መዳሚሻ቞ውን ወደ ዚስዊዘርላንዷ ዙሪክ ማድሚግ ነበር ህልማ቞ው። ግሪክ ወደ ተቀሩት ዚአውሮፓ ሃገራት መሄድ ለሚፈልጉ ስደተኞቜ ቅድሚያ መሻገሪያ ሃገር ናት። ሌስቊስ እና ሳሞስ ዚሚባሉ ታዋቂ ዚግሪክ ደሎቶቜን ጚምሮ ብዙ ደሎቶቜ ኹአቅማቾው በላይ ስደተኞቜን በማስተናገዳ቞ው ማህብራዊ ቀውስ እዚተፈጠሚባ቞ው ነው።
news-42514461
https://www.bbc.com/amharic/news-42514461
"ለሎት ምሁራን ዹተኹለኹለ ኃላፊነት?"
በአገሪቱ ዚመንግሥት ዩኒቚርሲቲዎቜ ቁጥር 45 እንደሚደርስ እዚተገለፀ ነው። ኚእዚህ ሁሉ ኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት መካኚል አንዱም በሎቶቜ ተመርቶ አያውቅም ቢባል ያለጥርጥር በአገሪቱ ለእዚህ ሃለፊነት ዹሚበቁ ሎቶቜ ዹሉም ወይ? ዹሚል ጥያቄ ይኚተላል።
አዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ቀደም ሲል በተለያዚ መንገድ ባስነገሚው ማስታወቂያ መሰሚት ዚዩኒቚርሲቲው ፕሬዝዳንት ለመሆን ዹውጭ ሃገር ዜጎቜን ጚምሮ 22 ምሁራን አመልክተዋል። ኚመካኚላ቞ውም 13ቱ ለቀጣዩ ውድድር ቀርበዋል። ዹውጭ ሃገር ዜጎቜ እንኳ ለውድድር ራሳ቞ውን ሲያቀርቡ አንድም ሎት ተወዳዳሪ ኢትዮጵያዊት ምሁር ዚለቜም። ዩኒቚርሲቲው ኚተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ 11 ፕሬዝዳንቶቜ መርተውታል። አሁን ካመለኚቱት ምሁራን ዚሚያሞንፈው 12ኛው ፕሬዝዳንት ይሆናል። በዩኒቚርሲቲው ዚፕሬዝዳንትነት መንበር ዚወንዶቜ ብቻ መሆኑ ይቀጥላል ማለት ነው። በተለያዚ ዘርፍ ምርምር በማድሚግ ለአገሪቱ አስተዋፆ ያበሚኚቱፀ በተመሳሳይም በተለያዩ ዚአገሪቱ ዩኒቚርሲቲዎቜ ዚሚያስተምሩና ብዙ ጥናቶቜን ያደሚጉ ሎት ምሁራን አሉ። ነገር ግን ኹዚህ ቀደምም ሎት ምሁራን ዚዩኒቚርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆኑ ሲባል ብዙ አልተሰማም። ለምን? በአሁኑ ዚአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ፕሬዝዳንት ዹመሆን ውድድርስ ለምን ሎት አመልካ቟ቜ ዹሉም? ዹሚል ጥያቄ ለአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ አቅርበን ነበር። ዚዩኒቚርሲቲው ህዝብ ግንኙነት አቶ አሰማኾኝ አስሚስ ብቃት ያላ቞ውና ዚትም ያሉ ምሁራን መሹጃው ይደርሳ቞ው ዘንድ እንዲወዳደሩ ማስታወቂያው በተለያዚ መንገድ እንዲነገር መደሹጉንና ብቃት ያላ቞ው ሎቶቜ እንደሚበሚታቱም ጭምር መገለፁን ይናገራል። ቢሆንም ግን አንድም ሎት አላመለኚተቜም። በአሁኑ ወቅት ኚዩኒቚርሲቲው አካዳሚክ ሠራተኞቜ (መምህራን) 15 በመቶ ዚሚሆኑት ሎቶቜ ሲሆኑፀ ዩኒቚርሲቲው በታሪኩ ሎት ፕሬዝዳንት ግን ኖሮት አያውቅም። ባለፉት ዓመታት ዩኒቚርሲቲውን በምክትል ፕሬዝዳንትነት ያገለገሉ ሎቶቜም ሁለት ብቻ ና቞ው። እነርሱም በፕሮፌሰር አንድርያስና በፕሮፌሰር አድማሱ ፀጋዬ ዚፕሬዘዳንትነት ዘመን ዚነበሩ ና቞ው። ዩኒቚርሲቲው ሎት ምሁራንን በብዛት ለማፍራት ዚተለያዩ ጥሚቶቜ እንደሚያደርግ ዚሚናገሩት አቶ አሰማኞኝፀ ዚመጀመሪያ ዲግሪያ቞ው ላይ ኹፍተኛ ውጀት ባያመጡም ጥሩ ውጀት ያላ቞ው ሎት ተማሪዎቜ ተባባሪ ምሩቃን ሆነው እንዲቀጠሩ ያደርጋል። በተጚማሪም በዩኒቚርሲቲው ሥርዓተ-ፆታ ቢሮ አማካኝነት ሎት ተማሪዎቜ ዚማጠናኚሪያ ትምህርቶቜን እንዲኚታተሉ ማድሚግም ሌላው ሎቶቜን ዹመደገፍ እርምጃ እንደሆነ ባለሙያው ይናገራል ። አዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ እስካሁን 11 ፕሬዝዳንቶቜ ነበሩት ዶ/ር ሙሉነሜ አበበ በቅርቡ ፕሬዝዳንቱን በመሹጠው ዚባሕር ዳር ዩኒቚርሲቲ ለውድድር ቀርበው ኚነበሩት ሰባት ተወዳዳሪዎቜ መካኚል ብ቞ኛዋ ሎት ነበሩ። በመጚሚሻም በውድድሩ ሊስተኛ ሆነዋል። ዶ/ር ሙሉነሜ በአሁኑ ወቅት ዩኒቚርሲቲውን በምክትል ፕሬዝዳንትነት በማገልገል ላይ ይገኛሉ። ኚዓመት ኚስምንት ወር በፊት ለምክትል ፕሬዝዳንትነት ሲወዳደሩ ኚነበሩት ዘጠኝ ተወዳዳሪዎቜ ሎቶቜ ሁለት ብቻ እንደነበሩ ያስታውሳሉ። ዚዩኒቚርሲቲ ፕሬዝዳንትነት በውድድር ኹመሆኑ በፊት ዩኒቚርሲቲውን ለሁለት ዓመት በፕሬዝዳንትነት ያገለገሉ ዶ/ር ዚሺመብራት ካሳ ዚተባሉ ሌላ ሎት ነበሩ። ባለን መሹጃ መሰሚት ዶ/ር ዚሺመብራት በአገሪቱ አንድ ዩኒቚርሲቲን በፕሬዝዳንትነት ዚመሩ ብ቞ኛዋ ሎት ኢትዮጵያዊ ምሁር ና቞ው። በአገሪቱ ዚዩኒቚርሲቲዎቜ ፕሬዝዳንትነት መንበር ሁሌም በወንዶቜ ዚተያዘ እንደሆነፀ ምንም እንኳ ብቃት ያላ቞ው ሎቶቜ ቢኖሩም በዚህ ቊታ ላይ ሎቶቜን ለመቀበል ዚዩኒቚርሲቲው ማህበሚሰብ ዝግጁ እንዳልሆነ ዶ/ር ሙሉነሜ ይናገራሉ። በዩኒቚርሲቲዎቜ ያለው እውነታ ሎቶቜ ወደ አመራር እንዲወጡ ዚሚያመቜ እንዳልሆነም ያምናሉ። ሎቶቜ ይበሚታታሉፀ ለሎቶቜ ማበሚታቻ አለ ቢባልም ይህ ግን በተግባር ዚሚታይ እንዳልሆነ ዶ/ር ሙሉነሜ ያስሚዳሉ። "እንኳን ድጋፍ ለማድሚግ ድጋፍ ዚማያስፈልጋ቞ውንና ብቃት ያላ቞ውን ሎቶቜ እንኳን ለመቀበል ማህበሚሰቡ ዝግጁ አይደለም። ዹሚፈልገው ዹተለመደውን ነገር ማስቀጠል ነው"ይላሉ። ዛሬ ላይ ብቃት ያላ቞ውን ሎቶቜ በአመራር ደሹጃ መቀበል ካልተቻለ በአዎንታዊ ድጋፍ ሎቶቜን ማብቃት ብዙ አስርታትን እንደሚፈጅም ያምናሉ። ዚቀድሞ ዚአዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ ማህበሚሰብ አባል ዚነበሩና በአሁኑ ወቅት በአሜሪካ ድህሚ-ዶክትሬታ቞ውን በመስራት ላይ ዹሚገኙ ሌላ ሎት ምሁርም በአጠቃላይ በዶ/ር ሙሉነሜ ሃሳብ ይስማማሉ። ዹኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወደ አመራር ደሹጃ ለመውጣት ለሎቶቜ ዚተመቹ እንዳልሆኑና ፈተናውም ለሎቶቜ ኚወንዶቜ ጋር ሲነፃፀር እጥፍ ድርብ እንደሆነ ይናገራሉ። "መካኚለኛ ዚሚባሉ ዚአመራር ደሚጃዎቜ በሙሉ በወንዶቜ ዚተያዙ ናቾው" በማለት አጠቃላይ ዹኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት መዋቅሮቜ ምቹ አለመሆናቾውን ይገልፃሉ። ብቃት ስላላ቞ው ብቻ ሎቶቜ እነዚህን መዋቅሮቜ አልፈው ወደ ላይ መውጣት አዳጋቜ እንደሆነም ይጚምራሉ። ደቡብ ክልል ውስጥ በሚገኝ ዩኒቚርሲቲ ያስተምሩ በነበሚበት ወቅት ያጋጠማ቞ውን ነገር እንደ ቀላል ማሳያ ያስታውሳሉ። "ዩኒቚርሲቲው ውስጥ ኮንፍሚንስ ነበር እኔም ፅሁፍ አቅራቢ ነበርኩ። ዩኒቚርሲቲው በር ላይ ቀሚስሜ ጉልበትሜን አይሾፍንም አትገቢም ተባልኩ። ይሄ መቌ ማን ያወጣው ህግ ነው? ብዬ ስጠይቅ ኚዲን በላይ ያሉ ሰዎቜ ተባልኩ። ኚዲን በላይ ያሉት ሁሉ ወንዶቜ ነበሩ። በመጚሚሻ ስልክ ደዋውዬ ገባሁኝ። ኋላ ላይ ዩኒቚርሲቲው እውነትም እንደዚያ ያለ ህግ ማውጣቱን ተሚዳሁ"ይላሉ። በዚያ አጋጣሚ ፅሁፋቾውን ማቅሚብ ባይቜሉ ኖሮ ዚእሳ቞ው ድክመት ነበር? ጉዳዩ እንደራሳ቞ው ድክመት እንጂ ዚዩኒቚርሲቲው አሰራር ያደሚሰባ቞ው ተፅእኖ ውጀት ተደርጎ ሊታይ እንዳልነበር በርግጠኝነት ይናገራሉ። ኚእንደዚህ አይነቱ ዹበር ላይ አጋጣሚ ጀምሮ እስኚ ላይ ዚሎት መምህራን መንገድ አስ቞ጋሪ እንደሆነና በዚህ መልኩ ወደ አመራር መውጣት ደግሞ በጣም ኚባድ እንደሆነ ያስሚዳሉ። አሉ ዹሚሏቾው ዹመዋቅር ቜግሮቜ ትልቅ አይደሉም። ይልቁንም "አመራር ላይና መካኚለኛ ደሹጃ ላይ ላሉ ሎቶቜ ፈተና ዹሚሆኑ ትንንሜ እንቅፋቶቜ ና቞ው። ስለዚህ ወደ ላይ ልውጣ ዚምትል ሎት ብዙ ትንንሜ እንቅፋቶቜን ማለፍ ይጠበቅበታል"ይላሉ። ለሎቶቜ አዎንታዊ ድጋፍ ይደሹጋል ዚሚባለውም በወሬ እንጂ በተግባር ዚሚታይ እንዳልሆነ ይገልፃሉ። እንደሳ቞ው እምነት ወደ ላይ መውጣት ዚቻሉ ጥቂት ምሁራን ሎቶቜም ብዙ እንቅፋቶቜን ማለፍ ዚቻሉ እንጂ ኚሚባለው አዎንታዊ ድጋፍ ዹተጠቀሙ አይደሉም። በአሁኑ ወቅት ዹመቀሌ ዩኒቚርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ሎት ሲሆኑ ይህም በውድድር ዹሆነ ነው። ኹአጠቃላይ አካዳሚክ ሰራተኛው ደግሞ 14 በመቶ ዚሚሆኑት ሎቶቜ መሆናቾውን ዚዩኒቚርሲቲው ኮርፖሬት ኮሙኒኬሜን ዳይሬክተር አቶ አታክልቲ ሃይለስላሎ ይናገራሉ። ኚአንጋፋዎቹ አንዱ ዹሆነው ጅማ ዩኒቚርሲቲም ሎት ፕሬዝዳንት ኖሮት አያውቅም። አወዳድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ዚሟመውም ኚአንድ ዓመት ተኩል በፊት ነው። በውድድሩ ያሞነፉት ዶ/ር ፀጋ ኹተማ በመማር ማስተማር ሥራ ሚዥም ጊዜን ያሳለፉት በዚሁ ዩኒቚርሲቲ ስለሆነ ሁሌም በወንዶቜ ይያዝ ወደ ነበሹው ወንበር ሲመጡ ዚተቀባይነት ቜግር እንዳላጋጠማ቞ው ይናገራሉ። ሎቶቜ ወደ አመራር ሲወጡ ዚተለያዩ ቜግሮቜ አያጋጥሟ቞ውም ግን አይሉም። "በዚዩኒቚርሲቲው ብቃት ያላትን ሎት ማህበሚሰቡ ሳይወድ በግድ ይቀበላል"ይላሉ። ዚአመራር ልምድ ፕሬዝዳንት ሆኖ ለመመሚጥ ዋነኛ ጉዳይ ነው። ነገር ግን ምንም እንኳ በትምህርት ደሹጃቾው ዹላቁ ቢሆኑ በዚዩኒቚርሲቲው ለአመራርነትፀ ለምሳሌም ለዲፓርትመንት ሃላፊ ወይም ተባባሪ ዲንነት ማስታወቂያ ሲወጣ ሎት ምሁራን እንደማያመለክቱ አስተያዚት ዚሚሰጡ አሉ። በዚህ ምክንያት ዚአመራር ልምድ አለማዳበራ቞ው ደግሞ ለፕሬዘዳንትነት እንወዳደር ቢሉ እንኳን ኚመንገድ ያስቀራ቞ዋል ሲሉም ያክላሉ። እነዚህ አስተያዚት ሰጭዎቜ በኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሎቶቜ ወደ ፕሬዝዳንትነት ያልመጡት ሁኔታዎቜ ምቹ ስላልሆኑ ብቻ ሳይሆን እራሳ቞ውም ወደ ኋላ በማለታ቞ው ነው ሲሉ ዚሚኚራኚሩም አሉ። ለጉዳዩ ቅርበት ያላ቞ው ሰዎቜ እንደነገሩን ሎት ምሁራን ለፕሬዝዳንትነት እንዲወዳደሩ ግፊት መደሹጉን ነገር ግን ሎት ምሁራኑ ፈቃደኛ ሳይሆኑ መቅሚታ቞ውን ለቢቢሲ ተናግሚዋል። ምክንያታ቞ውም ምን እንደሆነ ግን አልታወቀም። ኚአዲስ አባባና መቀሌ ዩኒቚርሲቲ በተመሳሳይ በጅማ ዩኒቚርሲቲም በመማር ማስተማር ውስጥ ያሉ ሎቶቜ ቁጥር ኚአጠቃላዩ 15 በመቶ እንደሆነ ያገኘነው መሹጃ ያመለክታል። ሎት ተማሪዎቜንም ሆነ መምህራንን ለማብቃት አዎንታዊ ድጋፎቜ እንደሚደሚጉ ያነጋገርና቞ው ዩኒቚርሲቲዎቜ ይገልፃሉ። አዲስ አበባ ዩኒቚርሲቲ እስካሁን 11 ፕሬዝዳንቶቜ ነበሩት። 1. ዶ/ር ሉሲን ማት (1945-1954) 2. ደጃዝማቜ ካሳ ወ/ማርያም (1954-61) 3. ዶ/ር አክሊሉ ሃብ቎ (1961-1966) 4. ዶ/ር ታዚ ጉልላት (1966-1969) 5. ዶ/ር ዱሪ ሞሃመድ (1969-1977) (1985-1987) 6. ዶ/ር አብይ ክፍሌ (1977-1983) 7. ፕሮፌሰር አለማዹሁ ተፈራ (1984-1985) 8. ፕሮፌሰር ሞገሮ አሾናፊ (1988-1993) 9. ፕሮፌሰር እሞቱ ወንጹቆ (1993-1995) 10. ፕሮፌሰር አንድርያስ እሞ቎ (1995-2003) 11. ፕሮፌሰር አድማሱ ፀጋዬ (2003-2010)
news-46519016
https://www.bbc.com/amharic/news-46519016
አባይ ፀሐዬ፡ መጠዹቅ ካለብን ዹምንጠዹቀው በጋራ ነው
ኚህወሓት መስራ቟ቜ አንዱና ዚገዢው ፓርቲ ኢህአዎግ ኹፍተኛ አመራር ዚነበሩት እንዲሁም በተለያዩ ኹፍተኛ ዚመንግሥት ዚኃላፊነት ቊታዎቜ ላይ ዚሠሩት አቶ አባይ ፀሐዬ ኚወራት በፊት ተጀምሮ በኢትዮጵያ እዚተካሄደ ስላለው ፖለቲካዊ ለውጥና ተያያዥ ጉዳዮቜ ላይ ኚቢቢሲ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
ቢቢሲ፡ አሁን በኢትዮጵያ ባለው ለውጥ ላይ ህወሓት እንደ እንቅፋት ተደርጎ ይቀርባል። ለውጡን እንዎት ያዩታል ? አቶ አባይ ፀሐዬ፡ አሁን በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ለውጥ ኢህአዎግ 'ብዙ በድያለሁፀ አጥፍቻለሁ' ብለው አራቱ አባል ድርጅቶቜ ገምግመው ሕዝብን ይቅርታ ጠይቀው ዹተጀመሹ ነው። ኢህአዎግ በዚህ ደሹጃ እራሱን እንዲፈትሜ፣ መፈትሄ እንዲያሰቀምጥና ሕዝብን ይቅርታ እንዲጠይቅ ህወሓት ዹጎላ ድርሻ ተጫውቷል። ዚህወሓት ማዕኹላዊ ኮሚ቎ ግምገማ በጣም ጥልቀትና ስፋት ነበሚው። ሌሎቜም እንደ ፈር ቀዳጅና እንደ ማሳያ ነው ዚወሰዱት። ስለዚህ ህወሓት ዚለውጥ ጀማሪ፣ በለውጡ ዹነቃ ተሳትፎና አብነታዊ ሚና ተጫውቷል። ኚዚያ በፊት ህወሓት በትግራይ ሕዝብ ተዓማኒነት እስኪያጣ ድሚስ ዹኹፋ ቜግር ነበሚበትፀ በአገር ደሹጃም ዚኢህአዎግ አካል ሆኖ ብዙ ስህተት ዹፈፀመ ድርጅት ነው። ስለዚህ ስህተት አልፈፀምኩም፣ ጉድለት ዚለኝም፣ ያልተገባ ነገር አልሠራሁም አላለም። ይሄን ሁሉ ዘርዝሮ ለኢህአዎግ አቅርቧልፀ ለሕዝቡም ይፋ አድርጓል። ኚዚያ በኋላም ህወሓት ዚኢህአዎግ አካል ሆኖ ለተሠሩ ስህተቶቜም ኹግምገማና ኚሂስ አልፎ ዶክተር ዐብይ ሊቀመንበርና ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኖ ሲመሚጥፀ በጋራ ዚመሚጥነውን መሪ በፀጋ ተቀብሎ ደግፏል። በፓርላማም ድምፁን ሰጥቶ 'ዚጋራ መሪያቜን ነውፀ ዚጋራ ለውጥ ነው' ብሎ በቅንነት በሕግ አክባሪነት ለውጡን ደግፏል። • አቶ ጌታ቞ው አሰፋ ዚት ናቾው? ዚእስር ትዕዛዝ ወጥቶባ቞ዋል? • በሱዳን ሄሊኮፕተር ተኚስክሶ አራት ባለሥልጣናትን ገደለ በተሠሩ መልካም ሥራዎቜ ላይም ህወሓት ጉልህ ሚና ነበሚው። ለምሳሌ ኚኀርተራ ጋር ዹተደሹገው ዹሰላም ስምምነት፣ በውጭ ዚነበሩ ተቃዋሚዎቜ እንዲመጡ፣ በነፍጥ ሲፋለሙ ዚነበሩ ወደ ሰላም እንዲመጡ ዹተደሹገው ጥሚት መነሻው ዚኢህአዎግ ሥራ አስፈፃሚና ዚኢህኣዎግ ምክር-ቀት ውሳኔ ነው። አፈፃፀሙ ላይ ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዶክተር ዐብይ ላቅ ያለ ጥሚት አድርገው ውጀታማ እንዲሆን ሠርተዋል። ይህንንም ህወሓት አድንቆና አመስግኖ ተቀብሎታል። ኚዚያም አልፎ ዚእሰሚኞቜን መፍታት አድንቆና ተቀብሎ ነው ዚሄደው። እንዲሁም ዚባለስልጣናት ሜግሜግ ሲደሚግፀ በርካታ ኚስልጣንና ኚሚኒስትርነትም ዚተነሱ ሰዎቜ ፣ ኚዚያ በታቜ ባሉ ዚሲቪል ኃላፊነት ቊታዎቜም፣ ኚሠራዊትም በርካቶቜ ኚህወሓት ነው ዚተነሱት። ይሄንንም በፀጋ ነው ዚተቀበለው። ዲሞክራሲያዊ ነን በሚሉ ሃገራት አንድ ፓርቲና አንድ ግለሰብ ኚሠራዊት ወይም ኚድህንነት ኃላፊነት ሲነሳ ስንት ኩርፍያና ግርግር ይፈጠራል። ህወሓት ግን አካሄዱ ላይ ይስተካኚል ብሎ አስተያዚት ሰጥቷልፀ ነገር ግን ተግባራዊ አድርጎታል። ዚቱ ጋር ነው ለውጡን ዹተቃወመው? አፈፃፀም ላይ ዚታዩ ጉድለቶቜ ነበሩ እነርሱም ደግሞ ይታሚሙ ብሏል። ያለፉትን 27 ዓመታት ምንም እንዳልተሠራ ይነገራል "ይሄ ትክክል አይደለምፀ አብሚን ነው ዚሠራነው" በሎ ሃሳብ አቅሚቧል። እንዎ ህወሓት ነው እንዎ ዚሰራው? ህወሓት ብቻ ነው እንዎ ዹሚኹፋው? ሌላው ዚኢትዮጵያ ሕዝብም'ኮ ዚለፋበት ነው። ይሄ ሲነቋሞሜ ህወሓትና ዚትግራይ ሕዝብ ልዩ ቅሬታ፣ ልዩ መኚፋት ዹሚሰማቾው መስሎ ዚሚታያ቞ው ካሉ ትክክል አይደሉም። ይሄ ሚዛኑን ይጠብቅ ማለት ለውጥ መቃወም አይደለም። ቢቢሲ፡ ለምሳሌ ዚኢትዮ-ኀርትራ ጉዳይ ላይ ህወሓት ተቃውሞ አሰምቶ ነበር ... አቶ አባይ ፀሐዬ፡ ዚኢትዮ-ኀርትራ ሰላም አፈፃፀሙ ላይ ዹተወሰኑ ጉድለቶቜ ነበሩ። ሕዝብን ብናማክር ይጠቅም ነበር። በትግራይ በኩል ያለው በር ይኚፈትፀ ግንኙነቱ ኚአዲስ አበባ ብቻ አይሁንፀ አሰብ ብቻ ሳይሆን ምፅዋም ይኚፈት። ዚትግራይ ድንበሮቜ ክፍት ይሁኑ ዹሚል ነው። ይህንን ሃሳብ ማቅሚብ ለውጡን መቃወም አይደለም። ቢቢሲ፡ በውጭ ዚነበሩ ዚታጠቁ ኃይሎቜ ሃገር ቀት ሲገቡስ ደስተኞቜ ነበራቜሁ? አቶ አባይ ፀሐዬ፡ ውጭ ዚነበሩት ተቃዋሚ ኃይሎቜ በአጭር ጊዜ እንዲገቡ መደሹጉ ህወሓትም ዚትግራይ ሕዝብም አድንቋል። አብዛኛው በይቅርታና በፍቅር መንፈስፀ አንድነትን በመፍጠርና ዲሞክራሲን በማስፋት መንፈስ ነው ዚመጣው። ጥቂቶቹ ግን ኚእነ ቂም በቀላቾው ነው ያሉት። ኢህአዎግ ላይ በጠቅላላ ቂምና በቀል ሊወጡ ዹሚፈልጉ አሉ። ይሄ ደግሞ ዚለውጡ መፈክር በፍቅርና በይቅርታ እንዲሄድ ዹሚለውን ሃሳብ ይፃሚራል። ስለዚህ ይሄም ትክክል አይደለም 'ተው' መባል አለባ቞ው። ጥቂቶቜ ና቞ው። ስለዚህ ይሄ ይታሚም ማለቱ ምንድን ነው ክፋቱ? ቢቢሲ፡ ህወሓት ለውጡን እንዎት ነው ዚሚሚዳው? በተደጋገሚ ዹሕግ ዚበላይነት ይኹበር ስትሉስ ምን ለማለት ነው? አቶ አባይ ፀሐዬ፡ ለውጥ ሲባል እናጚብጭብ ማለት አይደለም። ጥሩ ፈር ይዞ ዹሄደውን እናጚብጭብለት። ዳር እናድርሰው። በስመ ለውጥ ያልሆነ ነገር ተደባልቆ ዹሚደሹግ ኚሆነፀ ተቀላቅሎ ዹሚፈፀም ሌላ ጀነኛ ያልሆነ ነገር ካለ ደግሞ "ይሄ እንኚን አለውፀ ይሄ ለውጡን ያኮላሞዋል። ይሄ አይደለም ዚለውጡ መንፈስና ይዘት" ብሎ ማሹም ለውጡን ኚጉድለት ዚፀዳ እንዲሆን ማድሚግና ይሄን በይፋ እንዲታሚም መጠዹቅ ለውጡን ያጎለብታል እንጂ ለውጡን ዚሚያደናቀፍ አይደለም። ስለዚህ ላለፈውም ዋነኛው ተጠያቂ ህወሓትፀ ዹሕግ ዚበላይነት ሲባልም ዚትግራይ ተወላጆቜ ላይ ዚሚያነጣጥር ኹሆነ ዚትም አያደርሰንም። ዹሕግ ዚበላይነት በሁሉም ክልል፣ በሁሉም ድርጅቶቜ፣ በሁሉም ፌደራል መንግሥት መሥሪያ ቀቶቜ፣ በእኩል ዓይን በሕግና በጠራ መሹጃ ብቻ ፖለቲካዊ ዓላማ በሌለውፀ አድልዎ በሌለው መንገድ ይፈፀም ነው እያለ ያለው ዚትግራይ ሕዝብና መስተዳደር። • ኚስም ፊት ዚሚቀመጡ መለያዎና አንድምታ቞ው • ዹሃምዛ ሃሚድ ገመድ አልባ ዚኀሌክትሪክ ማስተላለፊያ ይሄ ለውጡን መቃወም ነው? አይደለም። ህወሓት ላይና ዚትግራይ ተወላጆቜ ላይ አነጣጥሮ ሌላውን ነፃ አድርጎ ሾፍኖና ኹልሎ ኹሆነ ይሄ ዹሕግ ዚበላይነት አይደለም። ሕግ ዚማስፈን ጉዳይ አይደለም። ሕዝብ እንዲያኮርፍና እንዲያገል ዚሚያደርግ ካልሆነ ዚትም አያደርስም። አንድን ሕዝብ ማግለልና ማስኚፋት ዹጀመሹ መንግሥት ሌላውንም ማስኚፋቱና ማግለሉ አይቀርም። ዹጊዜ ጉዳይ ነው። ዚኊሮሞ ሕዝብ እንዲኚፋ እንዲተራመስ ማንም አይፈልግም። ያን ሁላ መስዋዕትነት ዹኹፈለው ዚትግራይ ሕዝብፀ ያን ሁላ ትግል ያካሄደው ህወሓትፀ ለኊሮሞ ሕዝብ ለአማራ ሕዝብ ለመላው ዚኢትዮጵያ ሕዝብ ነፃነት ነበር። በምን ተዓምር ነው አሁን በዚቊታው ለሚፈጠሹው ቜግር ወያኔ/ህወሓት ምክንያት ተደርጎ ዚሚነሳው? እንደዚህ ዓይነት አንድ ብሔር ዹሁሉም ቜግር ምክንያት አድርጎ መመልኚት አደገኛ ነውፀ ሃገርም ያፈርሳል። ጣት ዚምንቀስርበት ብሔር ወይም ደግሞ ዚሕብሚተሰብ ክፍል መኖር ዚለበትም። እንቀፈው፣ እናድምጠውፀ ምን አጎደልን ብለን እንጠይቀው። እንመካኚርና እናርም። አለበለዝያ በዚቊታው ግጭት፣ በዚቊታው ጥርጣሬና ስጋት እዚሰፋ ዚሚሄድበት ሁኔታ በጣም ያሰጋል። ቢቢሲ፡ ትግሉን በመምራት፣ ፌደራላዊ ሥርዓቱን ተግባራዊ በማድሚግና አጠቃላይ ሥሚዓቱን (በኢህአዎግም ቢሆን) በበላይነት ይመራ ዹነበሹው ህወሓት ነው። በተሰሠራው ስህተት ላይ ተጠያቂነቱ ኹፍ ቢል ዹሚጠበቅ ነገር አይደለም ይላሉ? አቶ አባይ ፀሐዬ፡ ፈሚንጆቜ 'ዳብል ስታንዳርድ' ዚሚሉት አለ። አንደኛ አሹመኔው ዹደርግ መንግሥት ተወግዷል፣ ልማት መጥቷል፣ ሰላም መጥቷል፣ ሃገራቜን አንገቷን ቀና አድርጋ በዓለም እውቅና አግኝታ አካባቢዋን አሚጋግታ እራሷን ማልማትና ማሚጋጋት ጀምራለቜ ይላል ብዙ ሰው። በዚህ መንግሥት ውስጥ ህወሓት ኹሆነ ዚአንበሳው ድሚሻ ዹነበሹው መመስገን አለበት። ጉድለት ላይ ሲሆን ህወሓት ነው ዋናው ተጠያቂፀ ስኬቱ ላይ ደግሞ 'እኛ'ኮ ነን ዚሠራነውፀ አለንበት' ዹሚል ይመጣል። ዚህወሓት መዳኚምና ወደ ብልሜት መግባቱፀ እንደ ትጥቅ ትግሉ ጊዜ፣ እንደ ሜግግሩ ጊዜ ሕዝብ አመኔታ ዚሚያሳድርበት መሆኑ እዚቀሚና እያሜቆለቆለ መሄዱ ትግራይን ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያን በአጠቃላይ ደግሞ ሥርዓቱንም መጉዳቱን ገምግሞታል። ዚእኛ መዳኚም ለሥርዓቱ መዳኚም ትልቅ ድርሻ አለው ብሎ ነው ዚገመገመው። ይሄ ማለት ግን ህወሓት አድራጊ ፈጣሪ ነበሹ ማለት አይደለም። ስልጣንን ሰብስቊ ዚያዘው ህወሓት ነው ማለት አይደለም። በሚኒስትሮቜ ምክር ቀት ውስጥ ሊስት አራት ሚኒስትሮቜ፣ ፓርላማ ውስጥ ስድስት ወይም ሰባት በመቶ ና቞ው። እኚህ አካላት ናቾው ፖሊሲ ዚሚያፀድቁት ሕግም ዚሚያወጡት። እዚያ ላይ ደግሞ አብላጫ ድምፅ ያላ቞ው ብዙ ወንበር፣ ብዙ ሚኒስትር ያላ቞ው ትልቁ ድርሻ አላ቞ው። ፍትህ አካላት ላይም ደግሞ እንደዚሁ። ብዙም ዚትግራይ ሰዎቜ አልነበሩበትም። በፖሊስና በሠራዊት አመራር ላይ አዎ ነበሩ። ደህንነትም ላይ እንደዚሁ። ባለፉት ሰባት ስምንት ዓመታት ግን በአበዛኛው ዹሌላ ብሔር ተወላጆቜ ናቾው ያሉት። ኀታማዊር ሹምና ዚደህንነት ኃላፊ ዚትግራይ ሰው ኹሆነ በቃ! ሁሉም ነገር በዚያ ይመዘናል። • ኚኢትዮጵያና ኚሌሎቜ ዚአፍሪካ ሃገራት ስለተዘሚፉ ቅርሶቜ ምን እናውቃለን? • ሶሪያውያን ስደተኞቜ በአዲስ አበባ ጎዳናዎቜ ስለዚህ ሃገሪቱ ለገባቜበት ቜግር፣ ኢህአዎግ ላጋጠመው ቀውስ፣ ዚህወሓት አስተዋፀዖ ትልቅ ነበሚፀ ትክክል። ነገር ግን ለሁሉም ነገር ህወሓት ተጠያቂ መሆን ነበሚበት ዹሚል ትክክል አይደለም። ምክንያቱም ህወሓት አናሳ ነው ድምፁ። ዚኢህአዎግ ሥራ አስፈፃሚና ማዕኹላዊ ኮሚ቎ ሲወስኑ አንድ አራተኛው ነው ድምፁ። ፓርላማም ውስጥ ኚአስር በታቜ ነው ድምፁ። ዚሚኒስትሮቜ ምክር-ቀት ውስጥም እንደዚሁ። ስለዚህ ዋናው ተጠያቂ ኢህአዎግ ዚእራሱ ሥራ አስፈፃሚ ነው ብሎ ነው ዚገመገመው። ህወሓት ነው ብሎ አልገመገመም። ምክንያቱም ፌዎራል መንግሥቱን ሲመራ ዚነበሚውፀ ሠራዊቱንም ደህንነቱንም ሲመራ ዹነበሹው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኚዚያ ቀጥሎ መኚላኚያ ሚኒስትሩና ኀታማዊር ሹሙ ና቞ው። ስለዚህ ጠቅላይ ሚኒስትር ዹነበሹው ኚህወሓት ኚሆነ፡ እሱ በነበሚበት ጊዜ ተጠያቂ ይሆናል። ሌላው በነበሚበት ጊዜ ድግሞ ሌላው ይጠዚቃል። ቀደም ብለን ማድሚግ ይገቡን ዚነበሩብን አሁን ዹተደሹጉ ለውጊቜ አሉፀ ዹሚል ኹሆነ እቀበላለሁ። ለምሳሌ እስሚኞቜን መፍታት ዹጠቅላይ ሚኒስትሩ ለውጥ እስኪደሚግ ድሚስ ለምን አላደሹግነውም? እዚህ ላይ ሁላቜንም ድርሻ አለን እቀበላለሁ። ህወሓት ብቻ ለሁሉም ነገር ተጠያቂ ነው ዚሚል፣ መነሻው ዚህወሓትና ዚትግራይ ዚበላይነት ነበሹ ኹሚል ነው ዚሚነሳው። ነገር ግን ኹመሹጃና ኹሃቅ አይደለም ዚሚነሳው። እንደርሱ ቢሆን ለምን ዚትግራይ ሕዝብ ዹተለዹ ነገር አላገኘም? አንድ ሚሊዮን ሕዝብ በዚዓመቱ በሚሃብ ዹሚጠቃ ነው። ህወሓት እራሱን በማያዳግምና ያለምህሚት ሂስ አድርጓል። ለማስተካኚል ልባዊ ጥሚት አድርጓል። አሁንም ለውጡን ደግፎ በሙሉ ልብ እዚሄደ ነው። አንዳንድ ጉድለቶቜና ዝንፈቶቜ ደግሞ እንዲስተካኚሉ በይፋ በኢህአዎግ መድሚክ ላይ እያሚመ ነው እዚሄደ ያለው። ኚዚያ በተሹፈ ስለግለሰቊቜ ኹሆነ ዹሚነገሹው ስለሌሎቜ ግለሰቊቜም ይነሳ። እያንዳንዱ ክልሉን ሲያስተዳደር ዹነበሹ ይጠዚቅ። ክልሉን ካላለማ፣ ካተራመሰ ህወሓት ነው ዚሚጠዚቅለት? ለምን? ህወሓት ሲያስተዳድሚው ዹነበሹው ክልል አለ ኚትግራይ ውጭ? ስለዚህ 'ዹጎደለ ነገር ካለ በዋናነት ዹሚጠዹቀው እዚያ ያለው ፓርቲ ነው' ብለን ነው በኢህአዎግ ውስጥ ዚገመገምነው። ለምንድነው ወደ ህወሓት ጣት ዹሚቀሰሹው? አንቀበልምፀ ድርጅቱም እንደዚያ ብሎ አልገመገመም። በፌደራል ደሹጃ ላለው ቜግር ደግሞ ዹምንጠዹቀው በጋራ ነው። ለዚያውም ዋናው ተጠያቂ ዚኢህአዎግ ሥራ አስፈፃሚ ነው። ኚዚያ በመቀጠል ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይሆናል ብለን ነው ዚገመገምነው።
news-45677196
https://www.bbc.com/amharic/news-45677196
«ማስተር ፕላኑ ተመልሶ ይመጣል» አቶ ኩማ ደመቅሳ
በኊሮሚያ ውስጥ ኹፍተኛ ተቃውሞን ቀስቅሶ ዹነበሹው አዲስ አበባን በዙሪያዋ ካሉ ዚኊሮሚያ ኚተሞቜ ጋር ያስተሳስራል ዚተባለው ማስተር ፕላን ተራማጅና አንድ ቀን ተመልሶ ይመጣል ብለው እንደሚያስቡ ኊህዎድ ሊቀ መንበር እና ዚኊሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ዚነበሩት አቶ ኩማ ደመቅሳ ለቢቢሲ ተናገሩ።
ባለፈው ሳምንት ኩዮፓ (ዚቀድሞው ኊህዎድ) በጅማ ኹተማ ድርጅታዊ ጉባኀውን ባደሚገበት ወቅት ተሳታፊ ዚነበሩት አቶ ኩማ ኚቢቢሲ ጋር ባደሚጉት አጭር ቆይታ አወዛጋቢ ስለነበሩና እርሳ቞ው በኹፍተኛ ዚስልጣን ሃላፊነት ላይ በነበሩበት ጊዜ ስለታቀዱና ተግባራዊ ስለተደሚጉ ጉዳዮቜ ምላሜ ሰጥተዋል። «ኊሮሞ እና አማራን ዚሚነጣጥሉ አይሳካላ቞ውም» በተለይ በኊሮሚያ ውስጥ ተቀስቅሶ ለሹጅም ጊዜ ለዘለቀው ሕዝባዊ ተቃውሞ መነሻ ምክንያት እንደሆነ ዚሚነገርለትና ኹ2006 ጀምሮ ተግባራዊ ይደሹጋል ተብሎ ዹነበሹው ዚአዲስ አበባና በዙሪያዋ ያሉ ዚኊሮሚያ ኚተሞቜ ዹተቀናጀ ማስተር ፕላንን በተመለኹተ ዚተሳሳተ አመለካኚት እንዳለ ተናግሚዋል። ጉዳዩ ኹመፈናቀል ጋር አብሮ ስለመጣ እንጂ «ተራማጅ አስተሳሰብ ነው ብዬ አስባለሁ» በማለት ዚሚናገሩት አቶ ኩማፀ ጊዜ ሊወስድ ይቜላል እንጂ ማስተር ፕላኑ አንድ ቀን ተመልሶ ይመጣል ብለው እንደሚያስቡ ገልፀዋል። ኹዚህ በተጚማሪም በተመሳሳይ ኊሮሚያ ውስጥ ለጠንካራ ጥያቄና ተቃውሞ ምክያት ዹነበሹው ዚአዳማ ኹተማን ዚኊሮሚያ ክልል መዲና እንድትሆንና ዹክልሉ መስሪያ ቀቶቜ ወደዚያው እንዲዘዋወሩ መደሹጋቾው ይጠቀሳል። • ኊህዎድ አብዮታዊ ዎሞክራሲንና ዎሞክራሲያዊ ማዕኚላዊነትን ታሪክ ሊያደርጋ቞ው ይሆን? ስለዚህ ጉዳይ ዚተጠዚቁት አቶ ኩማ ውሳኔው ስህተት እነደሌለበት ያምናሉ። አሁንም ወደኋላ መለስ ብለው ሲመለኚቱ «አሁንም ያኔ ዹነበሹኝ አቋም ስህተት ነው ብዬ አላምንም» ካሉ በኋላፀ «አዳማ ዹክልሉ ዋና ኹተማ ሆና እንደተቀዚሚቜ ብትዘልቅ ኖሮ ኹተማዋ ታድግ እንደነበር» ሲሉ ገልጞዋል። አክለውም ዋና ኹተማን በመምሚጥ ሚገድ ሁሉንም እንቅስቃሎ ተቆጣጥሮ ሥራ ለማኹናወን ዚተሻለው እንደሚመሚጥ ጠቁመዋል። በውሳኔው ውስጥም ግፊት እንዳልተደሚገባ቞ው ሲያስሚዱም «ያኔ ይህንን ያደሚገው ሌላ ኃይል ነው ዚተባለው ውሞት ነው። ውሳኔውን ዹወሰነው እኔና ኚእኔ ጎን ዚነበሩት ና቞ው» ብለዋል። ይህም ሆኖ ዚኊሮሞ ህዝብን መብት ዚሚነካ ውሳኔ አስተላልፈው እንደማያውቁ «በግሌ ዚኊሮሞ ህዝብ ፋይዳና መብት ላይ ተደራድሬ አላውቅም» በማለት አስሚግጠዋል ተናግሚዋል። ኹሰው ዚሚያገኙትን ዚድጋፍ ወይም ዹነቀፋ ምላሜ እንደማያስቡ ተናግሹው «ዚኊሮሞን ህዝብ ዹሚጠቅም ሀሳብ ሁሌም አራምዳለሁ» ብለዋል። • ዚካማሌ ዞን አመራሮቜ በታጣቂዎቜ ተገደሉ አቶ ኩማ ደመቅሳ ዚቀድሞው ዚኊሮሞ ህዝብ ዎሞክራሲያዊ ድርጅት (ኊህዎድ) ያሁኑ ዚኊሮሞ ዎሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኩዮፓ) በክብር ካሰናበታ቞ው መስራቜና ነባር አባላቱ መካኚል አንዱ ሲሆኑፀ በእሳ቞ው እይታ ትግል ዚሚካሄደው ማዕኹላዊ ኮሚ቎ ውስጥ ሆኖ ብቻ ስላልሆነፀ ኚኮሚ቎ው መሞኘታ቞ው ኚትግል እንደማያግዳ቞ው «ትግል በተለያዚ ደሹጃ ይካሄዳል» በማለት ገልጞዋል። ዚስንብት ሥነ ሥርዓቱ ሲካሄድ ታላቅ ደስታ እንደተሰማ቞ው ዚሚናገሩት አቶ ኩማፀ ለሚዥም ጊዜ ዚቆዩበትን ዚትግል ጊዜ በማስታወስ «ኚእኛ ጎን ዚነበሩና ዹተሰዉ ሰዎቜ ይህንን እድል አላገኙም። እኔ ይህንን እድል ስላገኘሁ ደስታዬ ወሰን ዚለውም» ብለዋል። አቶ ኩማ ደመቅሳ ዚኊሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር፣ ዚአዲስ አበባ ኹተማ ኚንቲባ እንዲሁም በተለያዩ ዚፌደራልና ዚኊሮሚያ ክልል ኹፍተኛ ዚሃላፊነት ቊታዎቜ ላይ ለሹጅም ጊዜ ሰርተዋል።
news-56890645
https://www.bbc.com/amharic/news-56890645
በኢትዮጵያ ዚ቎ሌኮም ዘርፍ ለመሳተፍ ስለተጫሚቱት ኩባንያዎቜ ምን ይታወቃል?
ዚኢትዮጵያ ዚ቎ሌኮም ዘርፍ ኚአንድ መቶ ሃያ ዓመት በላይ በመንግሥት ስር በሚተዳደሚው ኢትዮ቎ሌኮም ብ቞ኛ ዚበላይነት በብ቞ኝነት ተይዞ ቆይቶ አሁን ተፎካካሪ እንዲገባበት ተፈቅዷል።
በዚህም ዚኢትዮጵያ መንግሥት ለሁለት ዚ቎ሌኮምዩኒኬሜን አገልግሎት ሰጪ ዹውጭ ኩባንያዎቜ ፈቃድ ለመስጠት ጚሚታ ካወጣ ኚወራት በኋላ በተለያዩ አገራት ውስጥ በዘርፉ ዚተሰማሩ ተቋማት ፍላጎት ማሳዚታ቞ው ተገልጿል። መንግሥት በእጁ ዚሚገኙትን ዚተለያዩ ተቋማት ወደ ግሉ ዘርፍ ለማዘዋወር ኹወሰነ በኋላ ካቀሚበው ሁለት ዚ቎ሌኮም ዘርፍ ፈቃዶቜ በተጚማሪ ዚኢትዮ ቎ሌኮምን ዹተወሰነ ድርሻ ለግልና ለአገር ውስጥ ባለሃብቶቜ ለመሞጥ መወሰኑ ይታወሳል። ይህንን ዘርፍ ለውድድር ክፍት ማድሚግ ላይ ዚተለያዩ ሃሳቊቜ ሲሰነዘሩ ዚነበሩ ሲሆንፀ በተለይ በስልክና በኢንተርኔት ዚአገልግሎት ጥራት ላይ ዚሚያስኚትለው ለውጥና ዹዋጋ ቅናሜ በተለያዩ ዘርፎቜ ላይ አውንታዊ እድገትን ያመጣል ዚሚሉት ይበሚክታሉ። ዚምጣኔ ሀብት ባለሙያውና ፌርፋክስ አፍሪካ ግሎባል ሊቀመንበር ዚሆኑት አቶ ዘመዮነህ ንጋቱ እንደሚሉትፀ በዚዓመቱ ኹፍተኛ እድገት ለማስመዝገብ ዘርፉን ክፍት ማድሚግ አስፈላጊ ነው ይላሉ። ወደ ገበያው ለመግባት ያመለኚቱት ኩባንያዎቜ ትልልቅ መሆናቾውን በመግለጜም "ዘርፉን ለማዘመን ዹውጭ ዕውቀትና ካፒታል ያስፈልጋል። ኩባንያዎቹ ይህንን ይዘው ይመጣሉ ብዬ አስባለሁ" ሲሉ አስሚድተዋል። ዚእነዚህ ተቋሞቜ ወደ ገበያው መምጣት ምጣኔ ሀብቱ ላይ አወንታዊ ሚና እንዳለው ዚሚያሰምሩበት አቶ ዘመዎነህፀ እንደ ባንክ ያሉ ዚፋይናንስ ተቋማት፣ አምራ቟ቜና በሌሎቜም ዘርፎቜ ያሉ ተቋማት በተሻለ ቮክኖሎጂ ታግዘው እንዲሠሩ እንደሚሚዳም ያክላሉ። በውጭ ኩባንያዎቜ ኚሚያዙት ሁለቱ ዚ቎ሌኮም ፈቃዶቜ በተጚማሪ ዋነኛው ዚአገሪቱ አገልግሎት ሰጪ ኢትዮ቎ሌኮምም በሩን ለባለሃብቶቜ ይኚፍታል። በዚህም በመንግሥት ብ቞ኛ ባላቀትነት ስር ዹቇዹው ተቋሙ በቅርቡ 40 በመቶን ድርሻ ለውጪ ባለሃብቶቜ፣ 5 በመቶን ለኢትዮጵያውያን እና 55 በመቶውን መንግሥት እንደሚይዘው ይጠበቃል። ዚ቎ሌኮም ዘርፍ ለውድድር ክፍት መሆኑ ጥራት ያለው አገልግሎት በርካሜ ዋጋን ኚማስገኘቱ ባሻገር "ለሥራ ፈጠራና ለውድድር በር ይኚፍታል" ይላሉ አቶ ዘመዎነህ። እንደ ቎ሌኮም ያሉ ዚመሠሚታዊ አገልግሎት ዘርፎቜ ክፍት ሲሆኑ ኚሥራ ፈጠራ በተጚማሪ ምጣኔ ሀብትን እንደሚያሳድጉ ዚሚናገሩት አቶ ዘመዎነህፀ "ኢትዮጵያ ዘርፉን ለገበያ ክፍት ማድሚጓ ትልቅ ለውጥ ዚሚያመጣ እርምጃ ነው" ይላሉ። ዘርፉን ለውድድር ክፍት ለማድሚግ መንግሥት ኹወሰነ ጥቂት ዓመታት ዚተቆጠሩ ሲሆን ዚኢትዮጵያ ኮምዩኒኬሜን ባለሥልጣን ያዘጋጃ቞ውን ሁለት ፈቃዶቜ ለመስጠት ዚጚሚታ ጥሪ ያቀሚበው ኅዳር 18/2013 ዓ.ም ነበሚ። በዚህም 12 ያህል ኩባንያዎቜ በኢትዮጵያ ዚ቎ሌኮም ገበያ ውስጥ ለመሳተፍ ፍላጎት ያሳዩ ቢሆንም በመጚሚሻ ላይ ዚጚሚታ ሰነድ ያቀሚቡት ዚደቡብ አፍሪካው ኀምቲኀን እና ዚአራት ድርጅቶቜ ጥምሚት ዹሆነው ዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያ ዚተባሉት ኩባንያዎቜ ና቞ው። በዚህም መሰሚት ዚኬንያው ሳፋሪኮም፣ ዚብሪታኒያው ቮዳፎን፣ ዚደቡብ አፍሪካው ቮዳኮም እና ኀምቲኀን ግሩፕ፣ ዚብሪታኒያው ሲዲሲ ግሩፕ እና ዹጃፓኑ ሱሙቲሞ ኮርፖሬሜን በኢትዮጵያ ውስጥ ለመስራት ዚጚሚታ ሰነዳ቞ውን አስገብተዋል። በኢትዮጵያ ዚ቎ሌኮም ዘርፍ ውስጥ ለመሳተፍ በጋራና በተናጠል ፍላጎት ስላሳዩት ኩባንያዎቜ ምን ይታወቃል? ተቋሞቹ ኹዚህ ቀደም በዚትኞቹ አገራት ሠርተዋል? በ቎ሌኮም ዘርፍ ያላ቞ው እንቅስቃሎስ እንዎት ይገለጻል? ሳፋሪኮም ዋና መሥሪያ ቀቱ ናይሮቢ ዹሚገኘው ሳፋሪኮም ዚኬንያ ዚ቎ሌኮም ድርጅት ሲሆንፀ ኬንያ ውስጥ ትልቁ ዚ቎ሌኮም አገልግሎት አቅራቢና በምሥራቅ እና መካኚለኛው አፍሪካ ትርፋማ ኹሆኑ ድርጅቶቜ አንዱ ነው። ሳፋሪኮም ዚተንቀሳቃሜ ስልክ መስመር፣ ዚኢንተርኔት፣ ዚስልክ ግብይት እንዲሁም ሌሎቜም አገልግሎቶቜ ይሰጣል። እአአ በ1997 ገደማ ዹተቋቋመው ሳፋሪኮምፀ በተለይም ኀምፔሳ በተባለው ዚሞባይል ገንዘብ መለዋወጫ አገልግሎቱ በስፋት ይታወቃል። ሌላው ኀምሜዋሪ ዚሚባለው አገልግሎት ሳፋሪኮም ኚባንክ ጋር በጥምሚት ዹጀመሹው ሲሆንፀ ተገልጋዮቜ በሞባይል ገንዘብ እንዲቆጥቡና እንዲበደሩ ያስቜላል። ሳፋሪኮም በሌሎቜ አገራት ኚሚሠሩ ዚ቎ሌኮም ድርጅቶቜ ጋር በመጣመር አገልግሎቱን ማስፋፋት ጀምሯል። ኚእነዚህ መካኚል ታንዛንያ፣ ደቡብ አፍሪካ እና ሕንድ ይጠቀሳሉ። ዚሳፋሪኮም ድሚ ገጜ እንደሚያሳዚውፀ ኚኬንያ ዚ቎ሌኮም ገበያ 64.5 በመቶ ድርሻን ይወስዳል። ወደ 35.6 ሚሊዮን ዹሚጠጉ ተጠቃሚዎቜም አሉት። ዚዩናይትድ ኪንግደሙ ቮዳፎን ኚሳፋሪኮም 40 በመቶ ድርሻን ገዝቷል። ሳፋሪኮም ኬንያ ውስጥ ኹሚገኙ ዚ቎ሌኮም ድርጅቶቜ ቀድሞ ዹ3ጂ ኢንተርኔት አስገብቷል። በቅርቡ ደግሞ ዋና ዋና በሚባሉ ዚኬንያ ኚተሞቜ ዹ4ጂ አገልግሎት መዘርጋት ጀምሯል። ዚተንቀሳቃሜ ስልክ ተጠቃሚዎቜ ጥሪ ማድሚግ ሳይቜሉ ሲቀሩፀ ሰዎቜ እንዲደውሉላ቞ው ዹሚጠይቅ ዚጜሁፍ መልዕክት በነጻ እንዲልኩ ዚሚያስቜል አሠራር ዘርግቷል። ቮዳኮም በአፍሪካ ውስጥ ሰፊ ዚ቎ሌኮም አገልግሎት ኚሚሰጡት ኩባንያዎቜ መካኚል ቮዳኮም ይጠቀሳል። ዚኢንተርኔት፣ ዚተንቀሳቃሜ ስልክ ጥሪ እንዲሁም ኚፋይናንስ ጋር ዚተያያዙ ዘርፎቜም አሉት። መነሻውን ደቡብ አፍሪካ ያደሚገው ቮዳኮምፀ በታንዛንያ፣ ዎሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ሞዛምቢክ፣ ሌሶቶ እና ኬንያ ውስጥ አገልግሎት ይሰጣል። ዚሞባይል ኔትወርክ ዝርጋታው ኹ296 ሚሊዮን በላይ ሰዎቜን ተጠቃሚ እንዳደሚገ ዚድርጅቱ ድሚ ገጜ ይጠቁማል። ቮዳኮም ቢዝነስ አፍሪካ በሚል በ29 አገራት ንግድ ነክ አገልግሎቶቜ ይሰጣል። ኚቮዳኮም 60.5 በመቶ ዹሚሆነው ዚባለቀትንት ድርሻ ዚብሪታኒያው ቮዳፎን ነው። ዹ3ጂ እና 4ጂ ዚሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎት ዹሚሰጠው ቮዳኮምፀ በአፍሪካ በግንባር ቀደምነት ዚቀጥታ 5ጂ ኔትወርክ እንደዘሚጋ ይነገርለታል። ቮዳፎን ዚብሪታኒያው ቮዳፎን አገልግሎት ዹሚሰጠው በአውሮፓ፣ እስያ እና አፍሪካ ውስጥ ሲሆንፀ በ21 አገራት ውስጥ ኔትወርክ ዘርግቷል። አውሮፓ ውስጥ በኔትወርክ ዝርጋታ ዚአንበሳውን ድርሻ እንደያዘ ዚሚነገርለት ቮዳፎንፀ አፍሪካ ውስጥ ኹ42 ሚሊዮን በላይ ሰዎቜ ዚሞባይል ገንዘብ መለዋወጫ አገልግሎትን እንዲጠቀሙ እንዳስቻለ በድሚ ገጹ ዹሰፈሹው መሹጃ ይጠቁማል። ቮዳፎን ዚተንቀሳቃሜ ስልክ ጥሪ፣ ኢንተርኔትና ሌሎቜም ተያያዥ አገልግሎቶቜ ይሰጣል። በኢንተርኔት አማካይነት ዚተለያዩ ኀሌክትሮኒክስ ነክ መገልገያዎቜን በማስተሳሰር ዚሚታወቀውና ኢንተርኔት ኩፍ ቲንግስ ዚሚባለውን አገልግሎት በተለይም ለንግድ ተቋማት ያቀርባል። እንደ አውሮፓውያኑ ኹ1980ዎቹ ወዲህ ዚተስፋፋው ቮዳፎን ዚስልክ ጥሪ፣ ዚጜሁፍ መልዕክትና ኢንተርኔት ዚሚያቀርብ ሲሆንፀ አውሮፓ ውስጥ ዹ5ጂ ዝርጋታ ላይ በስፋት ይሠራል። በአፍሪካ በጋና፣ በሊቢያና በካሜሩንፀ በመካኚለኛው ምሥራቅ ደግሞ በኳታር፣ በባህሬንና በተባበሩት አሚብ ኀምሬቶቜፀ በእስያ ደግሞ በጃፓን እና በሕንድ ዹሚሰጠውን አገልግሎት መጥቀስ ይቻላል። ኀምቲኀን ግሩፕ ኀምቲኀን ግሩፕ መቀመጫውን ደቡብ አፍሪካ ያደሚገ ዚ቎ሌኮም ተቋም ነው። በተለያዩ ዚአፍሪካ፣ ዚአውሮፓ እንዲሁም ዚመካኚለኛው ምሥራቅ አገራት አገልግሎት ይሰጣል። ዋና መሥሪያ ቀቱን ደቡብ አፍሚካ ጆሀንስበርግ ያደሚገው ተቋም ወደ 273 ሚሊዮን ዹሚጠጉ ተገልጋዮቜ እንዳሉት በድሚ ገጹ ያሰፈሚው መግለጫ ይጠቁማል። በ20 አገሮቜ ዚሚሠራው ኀምቲኀን ግሩፕ ኹፍተኛውን ገቢ ዚሚያገኘው ኚናይጄሪያ ነው። እንደ አውሮፓውያኑ በ1994 ገደማ ኚደቡብ አፍሪካ መንግሥት በተገኘ ድጋፍ ነበር ዚተቋቋመው። ዚተንቀሳቃሜ ስልክ ጥሪ እና ዚሞባይል ገንዘብ ልውውጥ ዹሚሰጠው ኀምቲኀን ግሩፕፀ በዋትስአፕ መተግበሪያ ተጠቃሚዎቹ ዹአዹር ሰዓት እና ዚስልክ ኢንተርኔት አገልግሎት (ዳታ) እንዲያገኙ በማስቻል ስሙ ይነሳል። ኚማስተርካርድ ጋር በመጣመር ለተጠቃሚዎቹ ዚድሚ ገጜ ግብይት (ኢ-ኮሜርስ) ኚመዘርጋቱ ባሻገርፀ በሞባይል ገንዘብ መለዋወጥ ዚሚቻልበት መንገድም አለው። ሱሙቲሞ ኮርፖሬሜን ሱሙቲሞ ኮርፖሬሜን ዹጃፓን ተቋም ሲሆን ቎ሌኮምን ጚምሮ በተለያዩ ዘርፎቜ ዚተሰማራ ነው። በብሚት ምርት፣ በትራንስፖርትና ምህንድስና፣ በማዕድን፣ በሪልስ቎ት እና ሌሎቜም ዘርፎቜ ለሚዥም ዓመታት ሠርቷል። ኚእነዚህ በተጚማሪ በመገናኛ ብዙሃን እና በ቎ሌኮምዩኒኬሜን ዘርፍ ዹሚሰጠው አገልግሎት ዚኬብል ቎ሌቭዥን እና 5ጂ ዚሞባይል ኢንተርኔትን ያካትታል። ቲ-ጋያ ዚሚባል ዚሞባይል አኹፋፋይ ያለው ሱሙቲሞ ኮርፖሬሜን አጠቃላይ አገልግሎቶቹን በ66 አገራት እንደሚሰጥ ኚድሚ ገጹ ዹተገኘው መሹጃ ይጠቁማል። ኚተሰማራባ቞ው ዘርፎቜ መካኚል ዹመገናኛ ብዙሃን እና ቎ሌኮምዩኒኬሜን ቅርንጫፉ 11.9 በመቶ ድርሻ ይይዛል። እንደ አውሮፓውያኑ በ1919 ኊሳካ ኖርዝ ሀርበር በሚል ስያሜ ኹተቋቋመ በኋላ በተለያዩ ዘርፎቜ ዚተሰማራው ድርጅቱፀ በምሥራቅ እስያ፣ በአውሮፓ፣ በአፍሪካ፣ በመካኚለኛው ምሥራቅና ሌሎቜም ዹዓለም ክፍሎቜ ውስጥ ይንቀሳቀሳል። ሲዲሲ ግሩፕ ዚብሪታንያው ሲዲሲ ግሩፕ እንደ አውሮፓውያኑ በ1948 ኹተመሠሹተ ወዲህ ላለፉት 70 ዓመታት በፋይናንስ ዘርፍ ሲሠራ ቆይቷል። በተመሠሚተበት ዚመጀመሪያዎቹ ዓመታት በዛምቢያ ዚሲሚንቶ ዘርፍ፣ በቊትስዋና ዚኚብር እርባታ ዘርፍና በሌሎቜም ዚአፍሪካ እና እስያ አገሮቜ ሠርቷል። 1998 ላይ ሮልቮል በተባለ ዚአፍሪካ ዚሞባይል ስልክ ድርጅት ኢንቚስት ማድሚጉ ኚ቎ሌኮም ዘርፍ እንቅስቃሎው አንዱ ነው። በድሚ ገጹ ላይ በሚገኘው መሹጃ መሠሚትፀ በተለያዩ አገሮቜ በጥቃቅን እና አነስተኛ ንግድ፣ በጀና እና ሌሎቜም ዘርፎቜ ኢንቚስት ማድሚግ ይቻላል። ኹፍተኛ ኢንቚስትመንት ዚተደሚገባ቞ው አገራት ሕንድ፣ ናይጄሪያ፣ ኬንያ፣ ደቡብ አፍሪካ እና ኮትዲቯር ና቞ው።
news-56272130
https://www.bbc.com/amharic/news-56272130
ዚኢትዮጵያ ምርጫ 2013፡ ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜና ያልተመለሰው ዚሎቶቜ አካታቜነት ጥያቄ
በአስርት አመታት ውስጥ ዚኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲ ጉባኀዎቜን፣ ክርክሮቜን፣ ቅስቀሳዎቜን ለተኚታተለ አንድ ጎልቶ ዚሚንፀባሚቅ ጉዳይ አለ።
ዚአንበሳ ድርሻውን ዚሚይዙት ወንዶቜ ኹመሆናቾው በተጚማሪ በማዕኹላዊ እና በስራ አስፈፃሚ ኮሚ቎ አባልነታ቞ው ዚሎቶቜ ቁጥር ዹተመናመነ ወይም በአንዳንድ ፓርቲዎቜ እንደሚታዚው ዹሉም ማለት ይቻላል። በኢትዮጵያ ውስጥ በምርጫ ቊርድ እውቅና ያገኙ ኹ60 በላይ ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜ ቢኖሩም ሁሉም በሚባል ሁኔታ አመራሮቜ ወንዶቜ መሆናቾው በአገሪቱ ውስጥ ግማሜ ዚህዝብ ቁጥር ዚሚወክሉት ሎቶቜ ለምን በነዚህ ፓርቲዎቜ ውስጥ ዚውሳኔ ሰጭነት ቊታ አላገኙም ዹሚለውን ጥያቄ ያጭራል። በእነዚህ ፖለቲካ ፓርቲዎቜ ውስጥ በአመራር ደሹጃ ቀርቶ ኚወሚዳ ጀምሮ ባለው መዋቅሮቜ ውስጥ ዚሎቶቜ ተሳትፎ ይሄን ያህል እንዳልሆነ ተንታኞቜ ይናገራሉ። በተለይም አገሪቱ ምርጫ በምታካሂድበት ወቅት ዚሚስተዋለው ክፍተት በኹፍተኛ ሁኔታ ጎልቶ ይወጣልፀ ፓርቲዎቹ ዚሚያቀርቧ቞ው ዕጩ ተወዳዳሪ ሎቶቜ አናሳ መሆኑንም ማስተዋል ይቻላል። ዚሎቶቜ ውክልና በምክር ቀት እስቲ ወደኋላ 26 አመታትን ተመልሰን ዹ1987 ዓ.ም ምርጫን እንመልኚት። በዚህ አመት በተደሹገው አገር አቀፍ ጠቅላላ ምርጫ 536 ወንዶቜ ዚህዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት መቀመጫን ማሾነፍ ዚቻሉ ሲሆን ዚሎቶቜ ቁጥር ደግሞ 10 ነበር። በዚሁ ወቅት ዹነበሹውን ዹክልል ምክር ቀቶቜን አሞናፊዎቜ ስንመለኚት ደግሞ 1 ሺህ 355 ወንዶቜ በዘጠኙ ክልለ ባሉ ዹክልል ምክር ቀት ውስጥ መቀመጫ ማግኘት መቻላ቞ውን ኚኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቊርድ ያገኘነው መሹጃ ያሳያል። በዚሁ አመት በዘጠኙ ክልሎቜ መቀመጫ ያገኙ ዚሎቶቜ ቁጥር 77 ነው። አስርት አመታትን ወደኋላ ሄደን በንጉሱ አገዛዝ ዘመን ዹነበሹውን ቁጥር በምንመለኚትበት ወቅት ኹ240 ዹፓርላማ አባላት መካኚል 2ቱ ሎቶቜ ዚነበሩ ሲሆን በደርግ ጊዜ ደግሞ ኹ835 ዹሾንጎ አባላት መካኚል 14 ሎቶቜ ይገኙበታል። ኚአስር አመታት በኋላ ወይም ኢትዮጵያ ለመጚሚሻ ጊዜ ባደሚገቜው ምርጫ በምክር ቀቱ መቀመጫን ማሾነፍ ያገኙ ሎቶቜ ቁጥር ኹፍተኛ መሻሻልን አሳይቷል። በ2007 ወይም በአሁኑ ወቅት በህዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀቶቜ ሎቶቜ ያላ቞ው ቁጥር 212 ወይም በመቶኛ ሲሰላ 38.8 በመቶ ነው። ዹክልል ምክር ቀቶቜን ስንመለኚት ደግሞ በወቅቱ አገሪቷን ያስተዳድር ዹነበሹው ኢህአዎግ እና ዚተለያዩ አጋር ድርጅቶቜ ሁሉንም መቀመጫዎቜን ያገኙ ሲሆን ኹነዚህም መካኚል 800 ወይም በመቶኛ 40.3 በመቶ ዚሚሆኑት ሎቶቜ ና቞ው። ምንም እንኳን በምክር ቀቶቜ ያለው ዚሎቶቜ ውክልና ቁጥር መሻሻል ቢያሳይም በወሳኝ ቊታዎቜ አለመቀመጥ፣ ዚይስሙላ ተሳትፎና ቁጥር ማሟያ መሆናቾው ዚሚነሳ ጉዳይ ሆኗል። በርካቶቹ ዚፓርቲዎቻ቞ውን ፕሮግራም ኚማስፈፀም በዘለለ አጀንዳዎቜን በመቅሹፅም ሆነ ፖሊሲዎቜን በማርቀቅ ደሹጃ ምንም ዓይነት ተሳትፎ እንደሌላ቞ው ይናገራሉ። በተለይም ዚስርዓተ ፆታ ዹኃይል ሚዛን ውስብስብና ዘርፈ ብዙ ቜግሮቜን ለመፍታት መዋቅራዊ ዹሆኑ ዚፖሊሲ ለውጊቜ ያስፈልጋሉ በሚባልበት ወቅት ሎቶቜ ዚራሳ቞ውን ዕጣ ፈንታ፣ በራሳ቞ው መወሰን አልቻሉም ይባላል። በአሁኑ ሰዓት ኢትዮጵያ ስድስተኛና አገር አቀፍ ብሔራዊ ምርጫን ለማድሚግ በዝግጅት ላይ ናትፀ ምርጫው ዚተቆሚጠበት ቀን ሊደርስም 13 ሳምንታት ያህል ቀርቶታል። በብሔራዊ ምርጫ ቊርድ ዹጊዜ ሰሌዳ መሰሚትም ዚፖለቲካ ፖርቲዎቜ እጩዎቻ቞ውን እያስመዘገቡ ሲሆን በአንዳንድ አካባቢዎቜም እስኚ ዚካቲት 30፣ 2013 ዓ.ም እንደሚቀጥል ተገልጿል። ዚኊሮሞ ፌደራሊስት ኮንግሚስ አባላቶቹ በታሰሩበት ሁኔታ፣ ቢሮዎቹ ተዘርፈውና ተዘግተው እንዲሁም ዚምርጫ መርሃ ግብሩ ባልተሻሻለበት በስድስተኛው አገራዊ ምርጫ አልሳተፍም ሲል አሳውቋል። ኚፓርቲው16 ዚስራ አስፈፃሚዎቜ መካኚል ብ቞ኛ ሎት ዚሆኑት ዶ/ር በላይነሜ ይስሃቅም በዘንድሮው ምርጫ ለመወዳደር ፓርቲያ቞ውና መንግሥት እያደሚገ ዹነበሹውን ውይይት በመጠባበቅ ላይ ነበሩ። ነገር ግን ፓርቲው ባሉት ሁኔታዎቜ "ተገፍቌ ወጥቻለሁ" ማለቱን ተኚትሎ እርሳ቞ውም በዘንድሮው ምርጫ አይወዳደሩም። ሆኖም መለስ ብለን ኹዚህ በፊት ዚተሳተፉባ቞ውን ምርጫዎቜ እንዲሁም ዚሎቶቜ በፖለቲካ ፓርቲዎቜ ውስጥ ተሳትፎ ማነስ ምክንያቶቜን ቢቢሲ ጠይቋ቞ዋል። "ሎቶቜ በፖለቲካዊ ተሳትፏ቞ው ምክንያት ወሲባዊ ጥቃቶቜንና ዚስም ማጥፋት ዘመቻን አስተናግደዋል" ዶክተር በላይነሜ ዚፖለቲካ ህይወታ቞ው ዹሚጀምሹው ዚኊሮሞ ፌደራሊስት ዎሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ኊፌዲን)ን በተቀላቀሉበት በ1997 ዓ.ም ነበር። በዚያኑ አመት በትውልድ ቊታ቞ው በቄለም ወለጋ በምትገኘው አንፊሎ ወሚዳን ወክለው ተወዳደሩፀ ማሾነፍም ቻሉ። ምንም እንኳን ምርጫውን ማሾነፍ ቢቜሉም ለሎቶቜ ምርጫ ውድድር ውስጥ እጩ ሆኖ መቅሚብ ሳይሆን ሎት ተቃዋሚ ፖለቲኚኞቜ ይገጥማ቞ው ዚነበሩ ፈተናዎቜ "ተዘርዝሹው አያልቁም" ይላሉ። ዹተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎቜ በተደጋጋሚ ይገጥማ቞ው ዚነበሩት ማስፈራሪያዎቜና ዛቻዎቜ በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት በኹፍተኛ ሁኔታዎቜ ተደራርበው ይጚምራሉ ይላሉ። በተለያዩ ምርጫዎቜ በተሳተፉበት ወቅት፣ በተለይም በቅስቀሳ ወቅት ዚሚያጋጥማ቞ው ኹሆቮል መባሚር እንደሆነም ያስታውሳሉ። በአንድ ወቅት አንድ ሆቮል ገንዘባ቞ውን መልሶላ቞ው ሌላ ማደሪያ ባለማግኘታ቞ው መኪና ውስጥ ለማደር መገደዳ቞ውንም ያስታውሱታል። አንዳንድ ጊዜም ለምርጫ ቅስቀሳ ይዘዋቾው ዚሄዱት መኪኖቜም በፍራቻ ባዶ ሜዳ ላይ ውሚዱልን ብለዋ቞ው ያውቃሉ። ሆ቎ሎቹም ሆነ ዚትራንስፖርት መጓጓዣዎቜ በፍራቻ እንደሚያባርሩዋ቞ው በተደጋጋሚ ነግሚዋ቞ዋል። እርሳ቞ው ፓርቲውን በተቀላቀሉበት ወቅት በፖለቲካ ፓርቲዎቜ ውስጥ ይሳተፉ ዚነበሩ ዚሎቶቜ ቁጥር በጣም አናሳ ዹነበሹና ብዙ መስዋዕትነትም ስለሚያስኚፍል በርካቶቜ መገፋታ቞ውን ይጠቅሳሉ። "ተቃዋሚ መሆን በራሱ ኚባድ ነው" ዚሚሉት ዶክተር በላይነሜ በተለይ ሎት ተቃዋሚ መሆን ደግሞ በርካቶቜን በኹፍተኛ ሁኔታ ዋጋ እንዳስኚፈላ቞ውም በአመታት ታዝበዋል። በወንድ ተቃዋሚዎቜ ኚሚደርሱት ማስፈራሪያ፣ ዛቻዎቜና እስሮቜ በተጚማሪ ዘርዘር አድርገው ባይናገሩትም በፖለቲካ ተሳትፏ቞ው ምክንያት ዹመደፈር (ወሲባዊ ጥቃት ዚደሚሰባ቞ው) መኖራ቞ውን ይጠቅሳሉ። "ተቃዋሚ መሆን እንኳን ለሎት ለወንድ ኚባድ ነው። እኔ ዚማልናገራ቞ው በርካታ ነገሮቜ ዚደሚሰባ቞ው አሉ። ደሚሰብን ብለው ዚሚናገሩት በጣም አስፈሪ ነው። ለሎት በጣም ፈታኝ ነው" ይላሉ። ኹዚህም በተጚማሪ ኚስራ መባሚር፣ ዚስም ማጥፋት ዘመቻዎቜ እንዲሁ በተቃዋሚ ፓርቲ ሎት አባላት ውስጥ ዚሚደርሱ በመሆናቾው በርካቶቜን እንዲፈሩ ማድሚጉንም ያስሚዳሉ። ዚእንስሳት ሃኪም ዚሆኑት ዶክተር በላይነሜ ራሳ቞ው በፖለቲካ ተሳትፏ቞ው ምክንያት ኚስራ በመባሚራ቞ው ኑሯ቞ውን በአንድ ወቅት ፈታኝ አድርጎት እንደነበር ያወሳሉ። በተለይም ሎት ዚፖለቲካ ፓርቲ አባላት ላይ ዹሚደርሰው ዹሚኹፋው በክፍለ ሀገር ኚተሞቜ በመሆኑ በወሚዳዎቜ ላይ ዹሚገኙ ሎቶቜ በፖለቲካ ፓርቲዎቜ ተሳትፎም ሆነ በእጩ ተወዳዳሪነት ለመቅሚብ ኹፍተኛ ፍራቻ እንዳላ቞ውም ያስሚዳሉ። ዚስርዓተ-ፆታ ዹኃይል ሚዛን መዛባት ዹፈጠሹው ክፍተት ኚፖለቲካ ምህዳሩ መጥበብ በተጚማሪ ዚወንዶቜንና ዚሎቶቜን ግንኙነት ወይም ሎቶቜ በማህበሚሰቡ ውስጥ ሊኖራ቞ው ዚሚቜለውን ቊታ አስመልክቶ በሚወስነው አባዊ ስርዓት (ፓትሪያርኪ) ምክንያት ሎቶቜ በፖለቲካው፣ በትምህርት እና በኢኮኖሚው ዘርፍ ተሳታፊነታ቞ውን ወደ ኋላ እንዲቀሩ አድርጓ቞ዋል። ኹዚህም በተጚማሪ በሰፈነው ኢ-ፍትሃዊ ዚስርዓተ-ፆታ ዹኃይል ሚዛን ለተለያዩ መድልዎቜና ፆታዊ ጥቃቶቜም እንዲጋለጡ አድርጓ቞ዋል። ዚስርዓተ-ፆታ ሚዛን ኃይል አለመመጣጠን በተለይም ዚሚገለፅበት አንዱ ሁኔታ በሎቶቜ ላይ ያለው ተደራራቢ ዚስራ ጫና ሲሆን ይህም ሁኔታ ለሎቶቜ እፎይታ አግኝተው በሌሎቜ መድሚኮቜ እንዳይሳተፉ አድርጓ቞ዋል። በተለይም ዶክተር በላይነሜ እንደሚናገሩት በገጠሪቷ ክፍል ዚማገዶ እንጚት ለቀማ፣ ውሃ መቅዳት፣ ልጆቜ ማሳደግና ሌሎቜ ፋታ ዚማይሰጡ ስራዎቜ ወስኗ቞ው ይገኛሉ ይላሉ። ኹዚህ በተጚማሪ በኚተሞቜ ዘንድም ቢሆን በፖለቲካ ተሳትፎ ያላ቞ው ሎቶቜ ልጆቜን ኚመንኚባበብ ጀምሮ ዚማይኚፈልባ቞ው ዚቀት ውስጥ ዚስራ ጫናዎቜ ድርብር ኃላፊነትን ተሾክመው ይገኛሉ። ምንም እንኳን ሎቶቜ በፖለቲካ ፓርቲዎቜ ውስጥ ያላ቞ው ተሳትፎ ይህ ነው ባይባልም ፓርቲዎቜ በሚያደርጓ቞ው ዚድጋፍ ሰልፎቜ፣ ዚምሚጡኝ ቅስቀሳም ሆነ ሌሎቜ ተሳትፎዎቜ ላይ ዹሚመዘገበው ቁጥር ኹፍተኛ ነው። በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ እንደ አንድ ትልቅ ምዕራፍ ዚሚታዚውን ዹ1997 ዚመራጭ ሎቶቜ ቁጥር እንመልኚት እስቲ- ግንቊት 07 ቀን 1997 ዓ.ም በተካሄደው ዚህዝብ ተወካዮቜ እና ዹክልል ምክር ቀቶቜ አባላት ምርጫ ላይ 27 ሚሊዮን 372 ሺህ 888 ሰዎቜ ዚተመዘገቡ ሲሆን ኹነዚህም ውስጥ ዚሎቶቜ ቁጥር 13 ሚሊዮን 087 ሺህ 594 ነው። ኚተመዘገቡትም ውስጥ በአጠቃላይ 22 ሚሊዮን 610 ሺህ 690 መራጮቜ ድምፅ ሰጥተዋልፀ ኹነዚህም ውስጥ 12 ሚሊዮን 058 ሺህ 511 ወንዶቜ ሲሆኑ ዚሎቶቜ ቁጥር ደግሞ 10 ሚሊዮን 552 ሺህ 179 መሆኑን ኚምርጫ ቊርድ ዹተገኘው መሹጃ ያስሚዳል። በአመታት ውስጥ መራጩ ህዝብ (ሎቶቜም ይሁኑ ወንዶቜ) ሎት እጩ ተወዳዳሪዎቜ ካሉ ለመምሚጥ ወደኋላ እንደማይሉም ወይዘሮ በላይነሜ በራሳ቞ው ልምድ አይተውታል። ምንም እንኳን ሎት መራጮቜ በኹፍተኛ ሁኔታ በአመታት ቢጚምሩም ዚሎት ፖለቲኚኞቜም ሆነ ተመራጮቜ ቁጥር አሁንም ይህን ያህል አልተራመደም። በቅርቡ ዚተመሰሚቱት ፓርቲዎቜ ለዘመናት ወጣቶቜን አግልሎ ዹነበሹውን ዚኢትዮጵያ ፖለቲካ በተወሰነ መልኩ ቢቀይሩም ዚሎቶቜ ተሳትፎ ብዙ መራመድ እንዳልቻለም ዚፓርቲዎቹን ዚሎቶቜ ቁጥርና ዚስልጣን ተዋሚድ በማዚት መሚዳት ይቻላል። ዚአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) መስራቜ ኚሆኑት መካኚል ዹ29 አመቷ እመቀት ኹበደ አንዷ ናት። በሙያዋ ዚፕሮጀክት አስተባባሪ ዚሆነቜው እመቀት፣ ዚፖለቲካ ፓርቲ ውስጥ ስትገባ ዚመጀመሪያዋ ሲሆን ይህም በ2010 ዓ.ም ነው። ፓርቲውን ስትመስርት ለእርሷ ዋነኛ ጉዳይ ዹነበሹው "አማራ በባለፉት አስርት አመታት ተወካይ አላገኘም" ዹሚል እንደሆነ ትናገራለቜ። ፓርቲያ቞ውም "ዚአማራ ውክልናን ማዕኹል" አድርጎ ኚመነሳቱ አንፃር እመቀት ዚስርዓተ ፆታ ጥያቄዎቜም በዚያው ሊመለሱ እንደሚቜሉ ትናገራለቜ። ሆኖም በፓርቲያ቞ው ውስጥ ያሉ ዚሎቶቜ ቁጥር አነስተኛ መሆኑንም እሷም ቢሆን አትክደውም። ለምሳሌ ያህል ኹ45 ማዕኹላዊ ኮሚ቎ አባላት መካኚል ሎቶቜ ሶስት ብቻ ና቞ው። ኹዘጠኝ ስራ አስፈፃሚዎቜ መካኚል አንዲት ሎት ዚለቜም። ሎቶቜ ተሳታፊ ብቻ ሳይሆን በፓርቲያ቞ው ውስጥ ውሳኔ ሰጭዎቜ እንዲሆኑ አንዳንድ እንቅስቃሎዎቜን እንደሚያደርጉ ብትናገርም "ያን ያህል አጥጋቢ አይደለም" ትላለቜ። ምንም እንኳን በፓርቲው ማዕኹላዊ ኮሚ቎ ውስጥ ዚሎቶቜ ቁጥር ዝቅተኛ ቢሆንም በወሚዳዎቜ ደሹጃ ባለው አወቃቀር ግን በርካታ ሎቶቜ ቁልፍ ሚናን እንደያዙም ትናገራለቜ። እመቀት ለአንድ አመት ያህል ዚፓርቲው ዚባህርዳር ፅህፈት ቀት ኃላፊ ዚነበሚቜ ሲሆን፣ ሎቶቜ በፖለቲካ ፓርቲዎቜ ያላ቞ው ተሳትፎ ዝቅተኛ ለመሆኑ ዚተለያዩ ምክንያቶቜ ትሰጣለቜ። በራሷ ፓርቲ ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜ ውስጥ ሎቶቜ ቁጥር ማሟያ ተደርገው መታዚታ቞ውና (ዚይስሙላ ሎቶቜን አሳትፈናል) ለማለት ብቻ ዚሚገቡ ሲሆን ሎቶቜ በወሳኝ ቊታዎቜ እንደማይቀመጡና አብዛኛውን ጊዜም ዚስራ ድርሻ቞ውም ይህን ያህል ዚሚባ አለመሆኑንም ታዝባለቜ። እንደ ዶክተር በላይነሜ እሷም ቢሆን "ለአመታት በአገሪቱ ዹሚገኙ ዹተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባላት ተደጋጋሚ እስር፣ እንግልት፣ ዛቻና ማስፈራሪያዎቜ ሎቶቜን በፓርቲዎቜ እንዳይሳተፉ አድርጓ቞ዋል" ትላለቜ። ኹዚህም ጋር ተያይዞ "በፖለቲካ ፓርቲዎቜ መሳተፍም ሆነ ዚአመራር ቊታውን ይፈሩታል" ትላለቜ። በተለይም ኚፖለቲካ ምህዳሩ ጋር ተያይዞ ቀተሰቊቜ ስለሚሰጉ ሎቶቜ ዚቀተሰብ አባላትን በፖለቲካው እንዳይሳተፉ ተፅእኖ ማድሚጋ቞ውን ትጠቅሳለቜ። "ለስብሰባዎቜ በምንሄድበት ወቅት ኹፍተኛ ፍራቻ አለ። ሎቶቜ ራሳቜንም እንፈራለንፀ እንዲሁም ቀተሰብም ስለሚሰጋ ኹፍተኛ ተፅእኖ ያደርጋል። ዹተቃውሞ ፖለቲካ ኚባድ ነው" ትላለቜ እመቀት በአብን ፓርቲ ውስጥ ዹማዕኹላዊ ኮሚ቎ አባል ዚሎቶቜ ጉዳይ ዎስክ ኃላፊ ዚሆነቜው እመቀት እሷም ቢሆን ቀተሰቊቿ መጀመሪያ አካባቢ ፍራቻ እንደነበራ቞ው አትደብቅም። ሆኖም በፖለቲካ ፓርቲ ተሳትፎዋ ቀጥላ ኢትዮጵያ በምታደርገው ስድስተኛ ብሔራዊ ምርጫ በባህርዳር ኹተማ ዕጩ ተወዳዳሪ ሆና ትቀርባለቜ። እመቀትን ጚምሮ አብን በአገር ውስጥ ኚሚያቀርባ቞ው እጩ ተወዳዳሪዎቜ መካኚል 30 በመቶዎቹ ሎቶቜ እንደሆኑም ፓርቲዋን ወክላ ለቢቢሲ ተናግራለቜ። ዚዘንድሮ ዚአገሪቱ ብሔራዊ ምርጫ ሲነሳ በኹፍተኛ ደሹጃ እዚቀሰቀሱ ካሉትና ዚዜግነት ፖለቲካን አካሂዳለሁ ኹሚለው ፓርቲዎቜ መካኚል ኢዜማ ይገኝበታል። ኢዜማም በኢትዮጵያ ደሹጃ ኚሚያቀርባ቞ው እጩ ተወዳዳሪዎቜ መካኚል 30 በመቶዎቹ ሎቶቜ መሆናቾውን ዚኢዜማ ዚወጣቶቜ ተጠሪ ፅዮን እንግዳዬ ለቢቢሲ ተናግራለቜ። ፅዮን እሷን ጚምሮ ኹ21 ዚስራ አስፈፃሚዎቜ መካኚል ስድስቱ ሎቶቜ እንደሆኑ ትናገራለቜ። ዚፅዮን ዚፖለቲካ ፓርቲ ተሳትፎዋ በኢዜማ ቢጀምርም በአገሪቱ ውስጥ ዹሰፈነውን ዚስርዓተ-ፆታ ኃይል አለመመጣጠን እንዲሁም ያሉትን በሎቶቜ ላይ ጭቆና ዚሚያሳርፉ ሃይማኖታዊ፣ ባህላዊና ሌሎቜ መዋቅሮቜን ለመቅሹፍ ዚሚሰራው ዹሎው ሙቭመንት አካል ናት። በምስሚታው ወቅት ባዚቜው ተስፋ ሰጭ ነገርም ፖለቲካ ፓርቲው ይወክለኛል በሚል እንዳመነቜ ትናገራለቜ። ለዚህም እንደ ዋነኝነት ዚምታነሳው ለስርዓተ ፆታ ምላሜ ሰጭ ስርአት (Gender responsive system) በመዘርጋት በማህበራዊ ፍትህ ዹተቃኙ ፖሊሲዎቜ መኖራ቞ውን ትጠቅሳለቜ። ፓርቲዋ በምጣኔ ኃብት፣ ትምህርት፣ እንዲሁም ሌሎቜ ጉዳዮቜን በተመለኹተ ያወጣ቞ው 42 ፖሊሲዎቜም እንዲሁ በስርዓተ-ፆታ አይን እንዲታይና እንዲፈተሜ ማድሚጉንም ታስሚዳለቜ። ኹዚህም ጋር ተያይዞ ዚስርዓተ-ፆታ ዹኃይል ሚዛን እንዲመጣጠን ዚምትሰራው ሎታዊት እንቅስቃሎን ማሳተፉ ያለውን ቊታ አሳይ እንደሆነም ትጠቁማለቜ። ኹዚህም በተጚማሪ ኚታቜኛው መዋቅር ጀምሮ ዚሎቶቜ ጉዳይ ተጠሪዎቜ መኖሩ ፓርቲው ዚሥርዓተ-ፆታ እኩልነትን ለማስፈን እዚሰራ መሆኑ ማሳያ ነው ትላለቜ። በፖለቲካ ፓርቲዎቜ ውስጥ ሎቶቜ እንደ ተቀጥላ መታዚት በኢትዮጵያ ታሪክ ዚተደራጀ ተቃውሞ ኚሚነሱት መካኚል ዚፊውዳላዊውን አገዛዝ ለመገርስስና ዹተቀሰቀው ዚተማሪዎቜ ጥያቄ ይጠቀሳል። ስር ነቀል ለውጥን በማቀንቀንና መሬት ለአራሹ በሚል እንቅስቃሎያ቞ው ዚአብዮቱ ጠባቂ (ጋርዲያን ኩፍ ዘ ሪቮሉሜን) ዹሚል ስያሜም ተሰጥቷ቞ዋል። ተማሪዎቹ ዚኢትዮጵያ ትግል ለብቻው እንዳልሆነና በተለይም ኹዓለም አቀፉ ፀሹ-ኢምፔሪያሊዝም፣ ፀሹ ቅኝ ግዛት እንዲሁም ዘሚኝነትን ኚመታገል ጋር ተያይዞ ትብብር ሊኖር እንደሚገባና ትንታኔም በዚያ መልክ ይሰጥ ነበር። በዚያን ወቅት ተሳትፏ቞ው ዚሚጠሩት ጥቂት ሎቶቜ ሲሆኑ በርካቶቜ ዚእንቅስቃሎዎቹ መሪዎቜም አልነበሩም። ቁጥራ቞ው ትንሜ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ጥቂቶቹም ቡና በማፍላት፣ ዚስብሰባ ቃለ ጉባኀ መያዝ፣ ወሚቀት መበተን፣ መፈክር መያዝ ዚመሳሰሉ ሚናዎቜ እንደነበሩ ዚታሪክ ድርሳናት ይዘክራሉ። ቀስ እያሉ ሁኔታዎቜ ዚተቀዚሩት ዚሎቶቜ መብትን እንደ ሰው መብት ወይም ደግሞ እንደ ፖለቲካዊ ጥያቄ ባዩ አንዳንድ ዚፖለቲካ ንቃተ ህሊናቾው ኹፍ ባሉ አመራሮቜ ምክንያት እንደሆነም ዚታሪክ ተንታኞቜ ያስሚዳሉ። ኚአስርት አመታት በኋላ ይኾው ሎቶቜን ኚቀት ስራዎቜ ድርሻ ጋር ዚመያያዙ ባህሉም ሆነ ልምዱ አልቀሹም ። በርካታ ዚሎት ፖለቲኚኞቜም ሆነ ፅዮን ዚታዘበቜው ቢኖር በተለያዩ ስብሰባዎቜ ሎቶቜ እንዲያስተናብሩ፣ ቡና እንዲያፈሉ፣ ቆሎ ማቀበል፣ አስተናግዱ እና ሌሎቜ ባለው ዚስራ ክፍፍል ውስጥ ዚሎቶቜ ተብለው ዚሚሰሩ ስራዎቜ እንዲያኚናውኑ እንደሚጠዚቁ ትናገራለቜ። አንዳንድ ጊዜም ዚሎቶቜ ውጫዊ እይታ቞ውንም ኚፖለቲካዊ ህይወታ቞ው ጋር በማስተሳሰር ዚሚሰጡ አስተያዚቶቜንም ሰምታለቜ "አንቺማ በመልክሜ ትመሚጫለሜ" ዹሚል አስተያዬት እንዲሁም ዚፓርቲውን ፕሮግራሞቜ ለማስተዋወቅ "ቆንጆ ሎቶቜ ለምን አንመርጥም" ዹሚል ጉዳይ ሰምታለቜ። ዚማህበሚሰቡን አስተያዚት ሙሉ በሙሉ መቅሹፍ አስ቞ጋሪ ቢሆንም ፓርቲው መዋቅራዊ ዹሆነ መገለልን እንደማይቀበልና ይህንንም ለመፍታት ኚደንብ በተጚማሪ ዚዲሲፒሊን ኮሚ቎ም አዋቅሯል ትላለቜ። ኹዚህም በተጚማሪም ዚስርዓተ-ፆታንም በተመለኹተ ስልጠናዎቜ እንደሚሰጡም ታስሚዳለቜ። በላይኛው አመራር ያሉ ዚፓርቲው አባላት በስርዓተ-ፆታ ጉዳይ ላይ ያላ቞ው እይታ መልካም ቢሆንም በወሚዳ ደሹጃ አንድም ሎት ሊቀ መንበር አለመኖሩ ዚሎቶቜን ተሳትፎ ጥያቄ ገና ለመሆኑ ማሳያ ነው ትላለቜ። ነገር ግን ኢዜማ በዘንድሮው ምርጫ ሎቶቜ በዕጩ ተወዳዳሪነት እንዲሳተፉ በዕጩ መመልመያ መስፈርት ውስጥ ኹፍተኛ ማበሚታቻ በማድሚጋ቞ው ምክንያት በርካታ ሎት ዕጩዎቜን ማግኘት መቻላ቞ውን ትናገራለቜ። "ኢዜማ ስርዓተ ፆታ እኩልነትን ለማስፈን ዚሚሰራ ፓርቲ ነው" ብላ ፅዮን ሙሉ በሙሉ ዚምታምን ሲሆን ለዚህም በዋነኝነት "ሎቶቜ ራሳ቞ውን ወክለው ራሳ቞ው መጥተው ዚራሳ቞ውን ቜግሮቜ ዚሚያነሱበትን መድሚክ መፍጠር ቜሏል" ትላለቜ። ዚሎቶቜ ተሳትፎ ለምን? እንዎትስ ፍሬያማ ይሁን? ኢትዮጵያ በነበሯት ህጎቜም ሆነ ዚተለያዩ ሃይማኖታዊ፣ ባህላዊ መዋቅሮቜ ሎቶቜን በልዩነትና በበታቜነት ለዘመናት ስታይ ቆይታለቜ። ለአመታትም ዹነበሹው ሁኔታ ሲታይ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደሹጃ በመንግሥት ደሹጃ ዚፖለቲካውን ስፍራ ዚተቆጣጠሩት ወንዶቜ ና቞ው። ማህበሚሰቡን ብቻ ሳይሆን በቀጥታ ሎቶቜን ዚሚመለኚቱ ህጎቜን ዚሚያሚቁትም ሆነ ዚሚያስፈፅሙት ወንዶቜ መሆናቾውም ዹህግ አውጭ ምክር ቀቱ በወንዶቜ ለመያዙ አስሚጅ ነው። ኹዚህም ጋር ተያይዞ ዚሎቶቜ ዚፖለቲካ ተሳትፎ ለምን አስፈለገ ዹሚለው ዚፍትህ ጥያቄ አንደሆነና ግማሹን ዚህብሚተሰብ ክፍል እንደ መያዛ቞ው መጠን በውክልና ዲሞክራሲ ሎቶቜ በራሳ቞ው ለምን አይወኹሉም ዹሚል ነው። ሌላኛው ደግሞ ዚሎቶቜና ዚወንዶቜ ዚህይወት ልምድ በተለይም ኚታሪካዊ ፆታዊ ኢ-ፍትሀዊነት ጋር ተያይዞ መስተካኚል ያለባ቞ው ህግጋትንና አፈፃፀማቾውን ኚሎቶቜ በላይ ዚሚያውቅ ስለሌለ እንደሆነም ባለሙያዎቹ ይናገራሉ። ኹዚህ ጋር ተያይዞ ዚሎቶቜን በፖለቲካውም ሆነ በምርጫ እንዲሳተፉ ምርጫ ለማድሚግ መዋቅራዊና ተቋማዊ ለውጊቜን ማምጣት እንደሚያስፈልግ በርካቶቜ ይናገራሉ። ዚሎቶቜን ድርብርቊሜ ዚስራ ጫና ኚመቀነስ ጀምሮ፣ በማህበሚሰቡ ላይ ግንዛቀን መፍጠር እንዲሁም ፓርቲዎቜ አቃፊ እንዲሆኑ ማስቻል ኚሎት ፖለቲኚኞቜ ዚሚነሱ ሃሳቊቜ ና቞ው።
news-56206404
https://www.bbc.com/amharic/news-56206404
ጉቱ አበራ-"እወድሻለሁ ብሎ መንገር ሳይሆን ልክ እንደ ዓመት በዓል ያለ ዚደስታ ስሜት ነው መፍጠር ዚፈለኩት"
ሀዋነዋ (Hawanawa) ለወራት መልካም ዜና ለራቀው ዚኢትዮጵያ ዚማህበራዊ ሚዲያ ዹተወሰነም ቢሆን እስትፋስ ዹሰጠ ሙዚቃ ነበር። ዹሙዚቃው ቪዲዮ በተለቀቀ በሰአታት ውስጥ ነበር ዚብዙዎቜን ቀልብ ዚገዛው። እንዲህ ያሉ አስተያዚቶቜን መቀበሉን ሙዚቀኛውም ይናገራል።
‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ አሁን ያለው ነገር ጥሩ እንዳልሆነ እናውቃለን። አንዳንዎ ግን እሚፍት ያስፈልጋል። አንዳንዶቹ በዚህ ሙዚቃ እሚፍት እናደርጋለንፀ ኹዛ ተመልሰን ወደ ጭንቀታቜን እንመለሳለን ይሉኛል (ሳቅ)›› ይላል ጉቱ። ለኢትዮጵያ ዹሙዚቃ ኢንዱስትሪ በአዲስ ስራው ብቅ ያለው ጉቱ አበራ በኊሮምኛ ያቀነቀነው ሙዚቃ ቋንቋውን በማይናገሩ አድማጮቜ ዘንድም ኹፍተኛ ተቀባይነትን አትርፎለታል። ሀዋነዋ (Hawanawa) ለህይወት ዘመኔ እፈለግሻለሁ እንደማለት ነው። ግጥሙም ዜማውንም ራሱ ጉቱ ጜፎታል። ነገር ግን ሙዚቃውን ያቀናበሚቜው ሚራ ቲሩቌልቫም (Mira Thiruchelvam) ኹፍተኛ አስተዋጜኊ ነበራት። ጉቱ ኚቢቢሲ ጋር ባደሚገው ቆይታ ለሚራ እውቅናውን ሰጥቷል። ጉቱ ማነው? ዹተወለደው በኊሮሚያ ምዕራብ ወለጋ መንዲ ኹተማ ውስጥ ነው። ዹ16 አመት ታዳጊ ሆኖ ነበር ቀተሰቊቹ በስደት ወደ ሚኖሩባት ኖርዌይ ኹ 12 አመት በፊት ዚሄደው። ኚልጅነቱ ጀምሮ ኹፍተኛ ዹሙዚቃ ፍላጎት እንደነበሚው ዹሚናገሹው ጉቱ ኖርዌይ ኹሄደ በኋላ ወደ ጥሩ ሙዚቀኞቜ እዚሄደ ሙዚቃን በመማር አዲስ ነገር ለመፍጠር እና በተለይም ዚፊውዥን ሙዚቃዎቜ ላይ አተኩሮ መስራት ጀመሚ። በሶሻል ወርክ እና አንትሮፖሎጂ ዚመጀመሪያ ዲግሪውን ዚያዘው ጉቱ በሞያው ሶሻል ወርኹር ነው። ዚትምርት ዝግጅቱም ለሙዚቃ ስራው እገዛ እንዳደሚገለት ይናገራል፡፡ ‹‹ስራዬ እኮ እሱ ነውፀ ወደ ሙዚቃ ግን ጠቅልዬ መግባ቎ ነው መሰለኝ አሁንስ (ሳቅ)። ኹሆነልኝማ ሙዚቃውን እመርጣለሁ። ግን አንድ ነገር እርግጠኛ ነኝፀ እስኚመጚሚሻው ሙዚቃን እሰራለሁ›. ሲል ይናገራል። "በኖርዌይ ዚኊሮሞን ሙዚቃ ወደ ዓለም መድሚክ ለማምጣት ጥሚት ማድሚግ ጀመርኩኝፀ በዚህም ምክንያት ዚተለያዩ አገር ሙዚቃዎቜን በመጹማመር ዚሚሰራ ፋርገስ ፒል (Fargespill) ዹተሰኘ ዹሙዚቃ ባንድ አባል ሆንኩኝ።" ዹሚለው ጉቱ ኹዚህ በኋላ ዚኊሮምኛ እና ዚምዕራብውያን ሙዚቃ በመቀላቀል መድሚክ ላይ ማቅሚብ መጀመሩን ይናገራል። ኊሮሚያ በሎ (ሰፊዋ ኊሮሚያ) ዹሚለው ሙዚቃ ኚበርካታ ሰዎቜ ጋር እንዳስተዋወቀውም ለቢቢሲ ገልጿል። ኹዚህም ዚተነሳ በኖርዌይ ንጉስና ንግሥቱቷ ፊት ለፊት ተጋብዞ መጫወቱንም ይናገራል። ኊሮሚያ በሎ ዹሚለው ሙዚቃ ቅድሚያ ዚተጫወተው ሌላ ድምጻዊ ሲሆን፣ ኊሮምኛ ዚማይቜሉ ዚባንዱ አባላትን በማሰልጠን በተለያዩ መድሚኮቜ ላይ በጋራ ስራውን አቅርቧል። ጉቱ አበራ ዹተሰኘ ዹሙዚቃ ባንድንም ማቋቋሙን ኚቢቢሲ ጋር በነበሹው ቆይታ ወቅት ተናግሯል። ጉቱ ስለ አዲሱ ሙዚቃው አጠር ያለ ቆይታ ኚበቢሲ ጋር አድርጎ ነበር፡፡ ቢቢሲ- ሀዋነዋ ዹተሰኘው ነጠላ ቪዲዮህ ኚወጣ ገና አንድ ሳምንት አለሞላውም፣ ነግር ግን በኢትዮጵያ ማህበራዊ ዹመገናኛ ዘዎዎቜ እጅግ ተወዶልሃል። ጠብቀህው ነበር? ጉቱ አበራ- ይህ ስራዬ ለዚት ብሎ ዚተሰራ ነው። ሀዋናዋም ለመያዝ ዹሚቀል እና ሳቢ መጠሪያ ነው። ሙዚቃው አዲስ ስለሆነ ነው መሰለኝ ብዙ ሰዎቜ መልዕክቶቜን እዚላኩልኝ ነው። በርታ ጥሩ ነው እያሉኝ ነው። ይህ ሙዚቃ ዹተወሰነ አዳዲስ ነገሮቜን ይዞ ስለመጣ ሰዎቜ ዝግጁ አይሆኑም በሚል ምናልባት ተደማጭነቱ ላይ ጫና ያመጣ ይሆን ብዬ ሰግቌ ነበር። ግን ደግሞ ሙዚቃው በጥሩ ጥራት መሰራቱን ደግሞ አውቃለሁ። በቀጥታ መሳሪያዎቜ ነው ዚተቀሚፀው። ስኬሉም ትንሜ ይለያል። ዚእኛ አገር ሙዚቃ ፔንታ ቶኒክ ነው፣ ይሄ ደግሞ በተለይ ኳዚሮቹ በሌላ ስኬል ነው ዚገቡት። ስለዚህ በተለይ ኚወጣቱ ትውልድ አድማጭ አገኛለሁ ብዬ አስቀ ነበር። ነገር ግን እንደዚህ ቶሎ ብዙ ተቀባይ አገኛለሁ ብዬ ግን አልጠበኩም። ስለዚህ ይሄንን ያህል ባልጠብቅም ዹተወሰነ ግምት ግን ነበሚኝ። በዚህ ሙዚቃ ደስ ያለኝ ነገር ቢኖር እስኚዛሬ መልክት ኚሚልኩልኝ አድናቂዎቜ ውጪ አዳዲስ አድናቂዎቜ አፍርቻለሁ። ይህ ሙዚቃ በኊሮምኛም ሆነ በአማርኛ ኹሚዘፈኑ ዘፈኖቜ ለዚት ያለ መልክ በመያዙ ምክንያት ይመስለኛል። ኹመላው ኢትዮጵያ በሺዎቜ ዚሚቆጠሩ መልክቶቜ እዚደሚሱኝ ነው። ጥሩ ነው ብለውኛል። ቢቢሲ- በኊሮምኛ ሙዚቃዎቜ ውስጥ ዹፍቅር ዘፈኖቜ ብዙ ግዜ በውስጣ቞ው ሰም እና ወርቅ አላ቞ውፀ አንዳንዎ ስለ አገር ወይም ፖለቲካዊ መልክት ይይዛሉ። ሃዋነዋ ሰምና ወርቅ ይኖሹው ይሆን? ጉቱ አበራ-ይህ ሙዚቃ በውስጡ ዹተለዹ መልክት አልያዘም፣ በግልፅ ኹሚገልፀው ዹፍቅር መልክት ውጪ። እኔ ተወልጄ ያደኩት ወለጋ ውስጥ ነው። ይሄን ዘፈን ደግሞ ለሾዋ ልጅ ነው ዚዘፈንኩት። ዚጥበብ ስራው ላይ ትኩሚት አድርጌአለሁ። ሁሉም ሰው ዚኊሮምኛ ሙዚቃን እንዲያዳምጥ እና ጥበባቜን ኹፍ እንዲል ዚፈለኩት እንጂ ምንም ፖለቲካዊ መልዕክት ዚለውም። ቢቢሲ- ዹሙዚቃ ቪዲዮውም ሆነ ሙዚቃው ኚኊሮሞ እና ኹሌላው ዚኢትዮጵያ ክፍል በተጚማሪ ዚአፍሪካ መልክ ዚሚሰጡ ነገሮቜ አሉት። በተጚማሪም ወደ ኋላ አስርተ አመታትን ሄደህ ኚባህል ባሻገርም ዹዘመን ህብር ፈጥሚሃል። እንዎት ይህንን ለመፍጠር አሰብክ? ጉቱ አበራ- ሙዚቃው እንደሰማሜው ተለዋዋጭ (ዳይናሚክ) ነው። መጀመሪያ ሲገባ በቀዝ ጌታር እና በፕርኪሜን እጀምራለሁፀ መጚሚሻ ላይ ደግሞ በጣም ሞቅ ብሎ ያልቃል። ቪዲዮውም እሱን ነው ዚሚመስለው። መጀመሪያ እኔ እና እሷ ቀስ ብለን ሳይክል እዚነዳን እንሄዳለን ኹዛ ጭፈራውም ኹሙዚቃው ጋር ኹፍ ይላል። ስለዚህ ዹሙዚቃ ቪዲዮው ታስቊበት ነው ዚተሰራው። ሌላው በቀጥታ ዹሙዚቃ መሳሪያ ስለተሰራ ድምጹ ተፈጥሮአዊ ነው። ስለዘመን ስናወራ ደግሞ ዚኢትዮጵያ ሙዚቃ ኹ 1970 እና 1980 ዎቹ በጣም ጥሩ ዚሚባል ደሹጃ ላይ ነበር። እኔ በተለይም ዚዚያን ግዜ ዚኢትዮጵያን ሙዚቃዎቜ በበለጠ እወዳለሁፀ አዳምጣለሁ። እናም ወደዚያ መመለስ እና ኚዚያ መጀመር ነው ዚፈለኩት። አሁን ያለው ዘመናዊ ዚኢትዮጵያ ሙዚቃ ያኔ እንደነበሚው ብቃት ላይ አይደለም። በአሊ ቢራ እና አለማዹሁ እሞ቎ ጊዜ ኢትዮ ጃዝ በጣም ያደገበት ወቅት ነበር። አሁንም እነርሱ ትልቅ ና቞ውፀ አኚብራ቞ዋለሁ። እኔ ዚኢትዮጵያ ሙዚቃ ገና ያልተነካ ነው ብዬ ነው ዚማምነው። በተለይ ኚጥሩ ባለሞያዎቜ ጋር ቢሰራበት አዲስ ነገር መስራት ይቻላል። ስለዚህ ነው በኔም ስራ በዚህ መልኩ አዲስ ነገር መስራት ዚፈለግነው፣ ደግሞም አድርገነዋል። በተጚማሪም አቀናባሪዋ ዚኢትዮጵያን ሙዚቃ ታጠናለቜ እና ስለ ኢትዮጵያ ሙዚቃ ያላት እውቀት በጣም ጥልቅ ነው። ስለዚህ ለእርሷ ዚኢትዮጵያን ሙዚቃ ኚሌሎቜ አይነት ሙዚቃዎቜ ጋር ማቀናበር አልኚበዳትም። ሀዋነዋ ሙዚቃው ጃዝ፣ ብሉዝ፣ ራያ/ወሎ፣ አፍሮ፣ ኢቺሳ፣ ጌሎ፣ ሞጎዬ ምቶቜ ዚተቀላቀለበት ነው። ይሄ ብቻ ሳይሆን ቜክቜካ እና አፍሮ ቢትስም አሉበት። ስለዚህ አንዱን ሪትም ዚማይወድ ቢያንስ ሌላውን እንዲወድ አድርገን ነው ዚቀሚጜነው። እርሷ እንደ ባለሞያ ስታቀናብር እኔ አብሬያት ስለበርኩ በምፈልገው መልኩ ለመቅሹፅ ቜያለሁ። ስለዚህ ያ ለሙዚቃው ጣዕም ዚራሱ አበርክቶ እንዲኖሚው አድርጓል። ቢቢሲ- ዹሙዚቃ ቪዲዮህ ዚመብራት አጠቃቀሙ በጣም ፈካ ያለ ነው። ቅድም አንተም እንዳለኚው ዹዘፈንህን ግጥም ዹማይሰሙ ሰዎቜም ሙዚቃህን ወደውልሃል። ዹሃዋነዋ ግጥም ክሊፑ ላይ ኹተጠቀምኹው ዚመብራት ሎቲንግ ጋር ይገናኛል? ጉቱ አበራ- ዹኔ ፍላጎት ታሪኩን መንገር ብቻ አይደለም። ስሜቱን መፍጠር ላይ ነበር ትኩሚት ያደሚኩት። ሰዎቜ ሙዚቃውን ሲሰሙ ደስተኛ ይሆናሉ፣ ቀለማቱን እንዲሁም ዚተቀሚፀበት ቊታ ዚሚፈጥሚው ስሜት አለ። ዹሙዚቃ ቪዲዮ ሲሰራ ልክ እንደ ፊልም ታሪኩን መንገር አይደለም ዋና አላማው፣ ሰዎቜ ስሜቱ እንዲሰማ቞ው አድርጎ መፍጠር ነው። እኔም ልክ እንደ አመት በዓል ያለ ዚደስታ ስሜት ነው መፍጠር ዚፈለግኩት። በአጠቃላይ ግጥሙ ዹፍቅር ነውፀ ነገር ግን አንድ ሰው እወድሻለሁ ብሎ መንገር ሳይሆን ልክ እንደ አመት በዓል ያለ ዚደስታ ስሜት ነው መፍጠር ዚፈለኩት። አድማጮቌ ስሜቱን ወድደውታል ብዬ አስባለሁ። እንደ መሰናበቻ ጉቱ አድናቂዎቹን ‹‹በጣም አመሰግናለሁ። አዳዲስ ሙዚቃ በቅርቡ ሰርቌ ለመመለስ እሞክራለሁ። ያላቜሁኝን መልካም ነግሮቜ በሙሉ አኚብራለሁ። እናም ታትሬ እንደምሰራ ቃል እገባላቜኋለሁ። በቅርቡ ደግሞ በመድሚክ ላይ እንደምንገናኝ ተስፋ አደርጋለሁ›› ሲል አመስግኗቜኋል። አክሎም ‹‹አልበሜ በ ያዝነው ዚፈሚንጆቜ አመት መጚሚሻፀ ካልሆነ ደግሞ 2022 መጀመሪያ ይወጣል ብዬ አስባለሁ። ኹዛ በፊት አንድ ነጠላ ዜማ መስራ቎ ግን አይቀርም›› ብሏል።
news-54783379
https://www.bbc.com/amharic/news-54783379
ዚአፍሪካ ሕብሚት፡ "ሁሉም አካል ግጭትን ኚሚያባብስ ትርክት ይቆጠብ"
ዚኊሮሚያ ፖሊስ ኚትናንት በስቲያ በምዕራብ ወለጋ ዚተገደሉት ሰዎቜ ቁጥር 32 ነው ሲል ዹዓይን እማኞቜ እና አምነስቲ ዚሟ቟ቜ ቁጥር ቢያንስ 54 ነው ብለዋል።
ዚኊሮሚያ ፖሊስ ኮሚሜን ኮሚሜነር አራርሳ መርዳሳ ለብሔራዊ ቎ሌቪዥን ጣቢያ እሁድ ዕለት በደሹሰው ጥቃት ዚተገደሉት ንጹሃን ዜጎቜ ቁጥር 32 ነው ብለዋል። ዚሰብዓዊ መብቶቜ ኮሚሜን በበኩሉ በጥቃቱ ዚተገደሉት ሰዎቜ ቁጥር 32 እንደሆነ ቢጠቀስም ኮሚሜኑ ያገኛ቞ው መሚጃዎቜ አሃዙ ኹዛ በላይ ሊሆን እንደሚቜል ይጠቁማሉ ብሏል። በኊሮሚያ ክልል በምዕራብ ወለጋ ዞን፣ ጉሊሶ ወሚዳ፣ ጋዋ ቃንቃ ቀበሌ በሰላማዊ ዜጎቜ ላይ በተፈጾመ ጥቃት ዚሰዎቜ ሕይወት ማለፉን ይታወሳል። ዹክልሉ ቃል አቀባይ ጥቃቱ ዹተፈጾመው በስብሰባ ስም በአንድ ቊታ በተሰበሰቡ ሰዎቜ ላይ ነው ብሏል። ዹክልሉ መንግሥት ትናንት ባወጣው መግለጫ ምን ያክል ሰዎቜ በጥቃቱ እንደተገደሉ ያለው ነገር ዚለም። ዚአፍሪካ ሕብሚት፣ አምንስቲ ኢንተርናሜናልና ሌሎቜም ድርጅቶቜ ጥቃቱን በማውገዝ መግለጫ አውጥተዋል። "ዹ54 ሰው አስክሬን ተመልክቻለሁ" ቢቢሲ ያነጋገራ቞ው ዹዓይን እማኞቜ ኹ50 ያላነሱ ሰዎቜ መገደላቾውን ይናገራሉ። ስማ቞ው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ጥቃቱ ዚተፈጞመበት ቀበሌ ነዋሪ ጥቃቱ ዹተጀመሹው ኚቅዳሜ ዕለት ጀምሮ ነው ይላሉ። "ልክ መኚላኚለያ እንደወጣ ኩነግ ሾኔ ገባ። ኚዚያ ወሚራ ጀመሚፀ ዘሹፋ ጀመሚ። ቅዳሜ ዕለት እንደዛ እያደሚጉ አደሩ። ሞባይል ስልክ፣ ገንዘብ እንዲሁም ዚቀት እቃ ሲዘርፉ ነበር። ኚዚያ ትላንት [እሁድ] 11 ሰዓት አካባቢ ስብሰባ አለ ብለው አዛውንት፣ ሎቶቜና ሕፃናት ሳይለዩ ሰብስበው አንድ ትምህርት ቀት አስገቡ። ኚዚያ ጥቃት ፈፀሙ።" ይላሉ። ዹዓይኑ እማኙ ስብሰባውን ዚጠራው ጥቃት ያደሚሰብን ኩነግ ሾኔ ነው ይላሉ። "ሰዉ በፍርሃት ተገዶ ነው ወደ ስብሰባው ዚገባው። ሕይወቱ ዹሚተርፍ መስሎት ነው ዚሄደው። ኚዚያ በመትሚዚስና በቊንብ ነው ጥቃት ዚፈፀሙት።" ዹዓይኑ እማኙ ጥቃቱ ሲፈፀም ኚሌሎቜ ሰዎቜ ጋር ሞሜተው ጫካ ውስጥ ተደብቀው እንደነበር ለቢቢሲ ተናግሚዋል። "ዚሚፈልጉት ወንዶቜን ነበር። እኛ ሞሜተን ጫካ ውስጥ ነበርን። ሎቶቜ፣ ሜማግሌዎቜ ቀት ቀርተው ነበር። ገንዘብ ቢውስዱ እንጂ እነሱን አይነኩም ብለን ነበር ያሰብነው። ኚዚያ ዚፍንዳታ ድምፅ ስንሰማ ቀስ ብለን ኚተደበቅንበት ጫካ ወጥተን ስናይ አመድ ሆነዋል።" ለደህንነታ቞ው በመስጋት ማንነታ቞ው እንዲገለፅ ያልፈቀዱት እኒህ ዹዓይን እማኝ ኚሌሎቜ ሰዎቜ ጋር ጫካ ውስጥ አድሚው ዛሬ [ሰኞ] ሚፋዱን መውጣታ቞ውን ይናገራሉ። ሰኞ ኹሹፈደ በኋላ ነው መኚላኚያና ልዩ ኃይል ዚገባልን ይላሉ። ለቢቢሲ ቃላቾውን ዚሰጡት ዹዓይን እማኝ በስፋራው ዹነበሹው ዚመኚላኚያ ሠራዊት ቅዳሜ ጠዋት አካባቢውን ለቆ እንደወጣ ይናገራሉ። መኚላኚያ ሠራዊት ሥፍራውን ለቆ በወጣ በሰዓታት ልዩነት ታጣቂዎቜ አኚባቢውን እንደተቆጣጠሩ አስሚድተዋል። ዚምዕራብ ወለጋ ኮማንድ ፖስት ኚታወጀ ወዲህ መኚላኚያ በሥፍራው እንደነበርም ያወሳሉ። "አንድ ወንድሜ ሞቷል። ዹአጎቮ ልጅና አባቱ ሞተዋል። ወንድሜ ሚስትና ልጆቜ አሉት። አጎቮ ደግሞ ሜማግሌ ነበር። ወንድሜ ስብሰባ ሲጠራ ልጆቌን ልይ ብሎ ኚጫካ ወጥቶ ሄዶ ነው ዚሞተው። ሚስትና ልጆቹም አብሚው አለቁ።" አሁን መኚላኚያ ኚገባ ወዲህ በሥፍራው መሚጋጋት እንዳለ ዹዓይን እማኙ ያስሚዳሉ። መኚላኚያ ሠራዊት ዚሞሹትን እዚጠራ እንደሆነና ዚሞቱ ሰዎቜን ሬሳ እዚሰበሰበ እንዳለ ይናገራሉ። ዹዓይኑ እማኙ እስካሁን ድሚስ 54 ሰዎቜ መሞታ቞ውን ማሚጋገጣ቞ውን ይናገራሉ። ሌላ ቢቢሲ ያነጋገራ቞ው ዹዓይን እማኝም ጥቃቱ ዹደሹሰው ሰዎቜ በተሰበሰቡበት እንደሆነ ይናገራሉ። "ጥሩ ነገር እንነግራቜኋለን ብለው ኹሰበሰቧቾው በኋላ ቊምብ ሲጥሉባ቞ው 60 ሰው ሕይወቱ አለፈ። 20 ሰዎቜ ደግሞ ቆስለዋል። ዚሰዎቜ አስክሬን አሁን እዚተሰበሰበ ነው" ብለዋል። እኚሁ ዹዓይን እማኝ ወደ አኚባቢው ዚመንግሥት ጞጥታ ኃይል መሰማራቱን ተኚትሎ ወደ ቀያ቞ው እዚተመለሱ መሆኑን ለቢቢሲ ተናግሚዋል። ዹክልሉ መንግሥት ምላሜ ዚኊሮሚያ ክልል ቃል አቀባይ አቶ ጌታ቞ው ባልቻ ኩነግ ሾኔ ዚተባለው ቡድን ንሑሃን ዜጎቜን ስብሰባ ብሎ ኚጠራ በኋላ ሰዎቜ ላይ በተወሹወሹ ቊምብ ጉዳት መድሚሱን ተናግሚዋል። ጥቃቱ ዹተፈጾመው ኚምሜቱ 12 ሰዓት አካባቢ መሆኑን ዚሚናገሩት አቶ ጌታ቞ውፀ "ቊምቡን ዚወሚወሩት ሐሰተኛ ስበሰባ ዚጠሩት ናቾው" ሲሉ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። "ዚሞቱ ሰዎቜ ቁጥር ኹፍተኛ መሆኑ እዚተጠቀሰ ነው። ነገር ግን ትክክለኛውን ቁጥር ለማወቅ በአካባቢው ያለው አካል አጣርቶ እስኪልክልን እዚተጠባበቅን ነው" ይላሉ። በተመሳሳይ ዚኊሮሚያ ክልል ዛሬ ንጋት ላይ መግለጫ አውጥቷል። ክልሉ "ጭካኔ በተሞላበት መንገድ ዚሰዎቜ ሕይወት እንዲያልፍ ባደሚገው ዹኩነግ ሾኔ ቡድን ላይ እርምጃ ይወሰዳል" ብሏል። ዹክልሉ ፕሬዝደንት አቶ ሜመልስ አብዲሳም በዜጎቜ ላይ ለደሹሰው ጥቃት "ጥልቅ ሃዘኔን እገልጜለሁ" ያሉ ሲሆን "በኩነግ ሾኔ አሞባሪ ቡድን ላይ እዚተወሰደ ያለው ውጀታማ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ላሚጋግጥ እወዳለሁ" ብለዋል። ዚአማራ ክልል ብልጜግና ፓርቲ በበኩሉ ትላንት ምሜት ዹተፈጾመው ጥቃት መጠን እና ዝርዝር ሁኔታዎቜን ኚፌደራልና ኹክልሉ መንግሥት ጋር በመተባበር እዚተጠራ ነው ብሏል። ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ማንነትን መሠሚት ባደሚጉ ጥቃቶቜ ማዘናቾው በፌስቡክ ገፃቾው ገልፀዋል። "ዚኢትዮጵያ ጠላቶቜፀ "ወይ እኛ እንገዛለንፀ ወይ ሀገር አትኖርም" ብለው ተነሥተዋል። ለዚህም ዚጥፋት ዐቅማቾውን ሁሉ እዚተጠቀሙ ነው። አንደኛው ዒላማቾውም ዚሕዝባቜንን ቅስም መስበር ነው" ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። "ግራ ቀኝ ዚሚያውቁ ሰዎቜን እዚሰበሰቡ በማሠልጠንና በማስታጠቅ በዚአካባቢው ማንነትን መሠሚት ያደሚገ አሚመኔያዊ ጥቃት ማድሚስ" ጠላቶቜ ያሏ቞ው ሰዎቜ አላማ ነው ሲሉ በመግለጫ቞ው አትተዋል። "መንግሥት በተለያዩ ቊታዎቜ ሊፈጠሩ ይቜላሉ ያላ቞ውን ጥፋቶቜ በቅድሚያ መሹጃ ሰብስቊ ርምጃ በመውሰድ ሲያኚሜፍ ቆይቷል። ነገር ግን ያለፈው ሥርዓት ያወሚሰንን ቀዳዳዎቜ ሁሉ በጥቂት ጊዜ ውስጥ ደፍኖ መጚሚስ አልተቻለም" ይላል ዹጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ኩፊሮላዊ ገፅ ላይ ዹሰፈሹው መልዕክት። አክለውም "ዚጞጥታ አካላት ጥቃቱ ወደተፈጞመበት አካባቢ ተሠማርተዋል። ርምጃም እዚወሰዱ ነው። በቀጣይም ዚሕዝባቜንን ደኅንነት ለማስጠበቅ መንግሥት ዚመንግሥትነቱን ሥራ በቁርጥና በጜናት ይሠራል" ብለዋል። ዚአፍሪካ ሕብሚት ዚአፍሪካ ሕብሚት ኮሚሜን ሊቀ መንበር ሞሳ ፋኪ ማሕማትፀ ንጹሀን ዜጎቜ መገደላቾውን አጥብቀው እንደሚያወግዙ ገልጞዋል። ሕብሚቱ ባወጣው መግለጫፀ መንግሥት ጥቃቱን ዹፈጾሙ ቡድኖቜን ተጠያቂ ማድሚግ እንዳለበት አሳስቧል። በማኅበሚሰቡ መካኚል ዚሚኚሰት ግጭት እዚተባባሰ መምጣቱን በመጥቀስፀ ሁሉም አካል ግጭትን ኚሚያባብስ ትርክት እንዲቆጠብ ሊቀ መንበሩ ጠይቀዋል። በአገሪቱ ግጭትን ለማርገብ ጥሚት መደሹግ እንዳለበት፣ ሁሉን አቀፍና ወደ ብሔራዊ መግባባት ዚሚወስድ ዚፖለቲኚኞቜ ውይይት መካሄድ እንደሚገባውም መግለጫው ይጠቁማል። ይህ ካልሆነ ግን አለመሚጋጋቱ ኚኢትዮጵያ አልፎ ለቀጠናውም ይተርፋል ያሉት ሊቀ መንበሩፀ ዚአፍሪካ ሕብሚት በአገሪቱ ሰላምና መሚጋጋትን እንዲሰፍን እንደሚያግዝም ገልጞዋል። አምነስቲ ዚሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አምነስቲ ኢንተርናሜናል ኹ54 ዚማያንሱ ብሄራ቞ው አማራ ዹሆኑ ሰዎቜ ተገድለዋል ብሏል ትናንት ባወጣው መግለጫ። አምነስቲ ዹአገር መኚላኚያ አኚባቢውን ጥሎ መውጣቱን ተኚትሎ ዚኊሮሞ ነጻነት ጩር አባላት ሳይሆኑ እንደማይቀሩ ዚተጠሚጠሩ ጥቃቱን መፈጾማቾውን ገልጿል። መኚላኚያ ሠራዊት አኚባቢውን ለምንና አንዎት ጥሎ መውጣት እንዳስፈለገው መጣራት ይገባዋል ብሏል አምነስቲ። በጥቃቱ ሎቶቜ እና ሕጻናት ጭምር መገደላቾውን አምነስቲ በሪፖርቱ አመልክቷል። ዚሰብዓዊ መብቶቜ ኮሚሜን ዚኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶቜ ኮሚሜን በምዕራብ ወለጋ ዹተፈጾመውን ጥቃት አውግዟል። ኮሚሜኑ ወደ 60 ዹሚጠጉ ታጣቂዎቜ በሶስት ቀበሌዎቜ በሚኖሩ ብሄራ቞ው አማራ ዹሆኑ ነዋሪዎቜ ላይ ጥቃት ማድሚሳ቞ውን አስታውቋል። ኮሚሜኑ በጥቃቱ ሎቶቜ እና ህጻናት መገደላቾውንም ገልጟ በጥቃቱ ዚተገደሉት ሰዎቜ ቁጥር 32 እንደሆነ ቢጠቀስምፀ ኮሚሜኑ ያገኛ቞ው መሚጃዎቜ አሃዙ ኹዛ በላይ ሊሆን እንደሚቜል ይጠቁማሉ ብሏል።
news-52446447
https://www.bbc.com/amharic/news-52446447
ሰዎቜ እጃ቞ውን ዚማይታጠቡበትን ሥነ ልቩናዊ ምክንያት ያውቃሉ?
ዚፎክስ ኒውስ ዜና አንባቢ ፒት ሄግሎት “እጄን ለአስር ዓመታት አልታጠብኩም” ማለቱን ተኚትሎ ዚበርካቶቜ መነጋገሪያ ሆኖ እንደነበር አይዘነጋም።
ለ10 ዓመታት እጁን ታጥቀ አላውቅም ያለው ዜና አንባቢ ፒት ሄግሎትፀ በኋላ ግን ቀልዮን ነው ብሏል ኚአምስት ዓመት በፊት ተዋናይት ጄኔፈር ሎውሚንስ ኚመጞዳጃ ቀት ስትወጣ እጇን ዚመታጠብ ልምድ እንደሌላት መናገሯም ይታወሳል። ፒት እና ጄኔፈር “እጃቜንን አንታጠብም” ካሉ በኋላ መልሰው ደግሞ “ስንቀልድ ነው” ያሉትን አስተባብለዋል። ሆኖም ግን እጅ መታጠብን አምርሹው ዹሚቃወሙ ሰዎቜ እንዳሉ ያውቃሉ? • በሊባኖስ ለሜያጭ ዚቀሚበቜው ናይጄሪያዊት ተሚፈቜ ዹኖርዝ ኬሮላይናው ሪፐብሊካን ዚሕዝብ እንደራሎ ቶም ቲልትስፀ ዚሬስቶራንት ተቀጣሪዎቜ እጃ቞ውን ይታጠቡ መባሉ አላስፈላጊ ድንጋጌ ነው ያሉት ኚአምስት ዓመታት በፊት ነበር። ኚመጞዳጃ ቀት ሲወጡ እጃ቞ውን ዚማይታጠቡ ሰዎቜ እንዳሉ ሳትታዘቡ አልቀራቜሁም። እአአ 2015 ላይ ዚተሠራ ጥናት እንደሚያሳዚውፀ በመላው ዓለም መጞዳጃ ቀት ኹተጠቀሙ በኋላ እጃ቞ውን ዚሚታጠቡት 26.2 በመቶ ሰዎቜ ብቻ ና቞ው። ቀላል ግን በቀላሉ ዚሚሚሳ ልማድ በለንደን ዚኅብሚተሰብ ጀና ምሁሩ ሮበርት አውገርፀ እጅ መታጠብ “ቀላል ልማድ ይመስላል” ይላሉ። “እጅ መታጠብ በቀላሉ ዚሚለመድ ቢመስልምፀ ለ25 ዓመታት ያህል ሰዎቜ እጃ቞ውን መታጠብ እንዲያዘወትሩ ለማድሚግ ብንሞክርምፀ እጃ቞ውን ዚሚታጠቡ ጥቂቶቜ ና቞ው።” ድህነት በተንሰራፋባ቞ው አገራት ሳሙናና እጅ መታጠቢያም በስፋት ስለማይገኝፀ ብዙሃኑ እጃ቞ውን አለመታጠባ቞ው ላያስገርም ይቜላል። • ዚቻይናና ዚአፍሪካ ግንኙነት በኮሮና ዘመን ምን ድሚስ ይዘልቃል? በታዳጊ አገራት 27 በመቶ ዹሚሆነው ሕዝብ ብቻ እጅ መታጠቢያ ያገኛል። በተቃራኒው እጅ መታጠቢያ እንደልብ በሚገኝባ቞ው ያደጉ አገራትፀ ኚመጞዳጃ ቀት ሲወጡ እጃ቞ውን ዚሚታጠቡ 50 በመቶ ብቻ ና቞ው። ሕይወት አዳኙ እጅ መታጠብ በሰው ልጅ ታሪክ ኚተፈጠሩ ሕይወት አዳኝ ተግባሮቜ አንዱ እጅ መታጠብ ነው። እጅ መታጠብ በ1850ዎቹ እውቅናው እዚጚመሚ ኚመጣ ወዲህፀ ሰዎቜ ዘለግ ላለ ጊዜ ምድር ላይ መኖር ቜለዋል። ወሚርሜኞቜን ለመኹላኹልም እጅ መታጠብ አንዱ መንገድ ነው። እአአ 2006 ላይ ዚወጣ ጥናትፀ አዘውትሮ እጅ መታጠብ በመተንፈሻ አካላት በሜታ ዚመያዝ እድልን ኹ6 እስኚ 44 በመቶ እንደሚቀንስ ያሳያል። • ዚኮሮናቫይሚስ ክትባትን በማግኘት ህንድ ዹዓለምን ሕዝብ ትታደግ ይሆን? ዚኮቪድ-19 ስርጭት ኚሰዎቜ እጅ ዚመታጠብ ልማድ ጋር ግንኙነት እንዳለው ተመራማሪዎቜ ይናገራሉ። ታዲያ ለምን አንዳንድ ሰዎቜ እጃ቞ውን አይታጠቡም? እጅ መታጠብ አለመፈለግ ኚሰዎቜ ሥነ ልቩና ጋር ይተሳሰራል። ቀጣዮቹ ነጥቊቜ ማብራሪያ ይሰጧቜኋል። እጅን በተደጋጋሚ በደንብ መታጠብ ኮሮናቫይሚስን ዚመሳሰሉ ተላላፊ በሜታዎቜን ኹመኹላኹል ይሚዳል 1. ዹ‘ክፉ አይነካኝም’ ተስፋ መጥፎ ነገር አይደርስብንም ዹሚል እምነት ያላ቞ው በርካቶቜ ና቞ው። በብዙ ማኅበሚሰቊቜ ዘንድ ክፉ ነገር ዚሚመጣው በሌላ ሰው እንጂ በእኔ ላይ አይደለም ዹሚል እምነት ይስተዋላል። ይህ አይነቱ አመለካኚት ሲጋራ በሚያጚሱ ሰዎቜ ዘንድም ይታያል። ዚእኔ ትዳር አይፈርሰም፣ እኔን ካንሰር አይዘኝም ዹሚሉም ጥቂት አይደሉም። እጅ አለመታጠብም ኹዚሁ ጋር ይገናኛል። ይህ አመለካኚት ያላ቞ው ዹህክምና ተማሪዎቜ እና ምግብ አዘጋጆቜም እጃ቞ውን ኚመታጠብ ይቆጠባሉ። 2. ባህል እጅ መታጠብ ኚባህል ጋር ዚተቆራኘ ነው። በተለያዩ ማኅበሚሰቊቜ ዘንድ እጅ መታጠብ ዹሚሰጠው ዋጋ ሰዎቜ እጃ቞ውን ለመታጠባ቞ው ወይም ላለመታጠባ቞ው ምክንያት ይሆናል። 64,002 ሰዎቜን ኹ63 አገሮቜ ያሳተፈ ጥናት እንደሚያሳዚውፀ ኚቻይና፣ ኚጃፓን፣ ኚደቡብ ኮርያ እና ኚኔዘርላንድስ ዹተጠዹቁ ሰዎቜ መጞዳጃ ቀት ኹተጠቀሙ በኋላ እጃ቞ውን በሳሙና ዚመታጠብ ልማድ እንዳላ቞ው ዚተናገሩት ኚግማሜ በታቜ ና቞ው። በተቃራኒው 97 በመቶ ዹሚሆኑ ዚሳኡዲ አሚቢያ ዜጎቜ እጃ቞ውን መታጠብ እንደሚያዘወትሩ ተናግሚዋል። • ኮሮናቫይሚስ ዚቀሰቀሳ቞ው ዹአና ዹሚበሉ ሥዕሎቜ ዚሕብሚተሰብ ጀና ምሁሩ ሮበርት እንደሚሉትፀ በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ ሎቶቜ ኚወንዶቜ በበለጠ እጃ቞ውን መታጠብ ያዘወትራሉ። ኚኮሮናቫይሚስ ጋር በተያያዘ ዚተሠራ አንድ ጥናት እንደሚያሳዚውፀ 65 በመቶ ሎቶቜ እና 52 በመቶ ወንዶቜ እጃ቞ውን ይታጠባሉ። “እጅ መታጠብ ኚሥነ ልቩና እና ኚባህል ጋር ይተሳሰራል። እንድ ነገር ዹምናኹናውነው ሌሎቜ ዚሚያደርጉትን እና እኛ እንድናደርግ ዚሚጠብቁትን በማዚት ነው” ይላሉ ተመራማሪው። ጥናቶቜ ሎቶቜ ኚወንዶቜ ይልቅ እጃ቞ውን ይታጠባሉ 3. ቀልብ እና ሙኚራ እጅ መታጠብን ሀኪሞቜም ቾል ዚሚሉበት ጊዜ አለ። እአአ 2007 ላይ አውስትራሊያ ውስጥ ዚተሠራ ጥናትፀ ዚቀዶ ህክምና ባለሙያዎቜ ህክምና ኚመስጠታ቞ው በፊት እጃ቞ውን ዚታጠቡት 10 በመቶ ጊዜ ብቻ እንደሆነና ኹህክምና በኋላ እጃ቞ውን ዚታጠቡት ደግሞ 30 በመቶ ጊዜ ብቻ እንደሆነ ያመለክታል። በቅርቡ ዚተሠሩ ጥናቶቜም ተመሳሳይ ውጀት አሳይተዋል። በኩቀክ ዹህክምና ባለሙያዎቜ እጃ቞ውን ዚሚታጠቡት 33 በመቶ ጊዜ ብቻ መሆኑን ባለፈው ዓመት ዚተሠራ ጥናት ይጠቁማል። እጅ መታጠብ በስፋት በተለመደበት ሳኡዲ አሚቢያ ሳይቀር ዹህክምና ባለሙያዎቜ ብዙ ጊዜ እጃ቞ውን አይታጠቡም። • ኮሮናቫይሚስንና ዹፀሐይ ብርሃንን ምን አገናኛቾው? 2008 ላይ ዚተሠራ አንድ ጥናት እንደሚጠቁመውፀ እጃቜንን አንታጠብም ካሉት ሀኪሞቜ አብዛኞቹ በሙኚራ ዚሚያምኑ ና቞ው። በተቃራኒው ቀልባቜንን እናምነዋለን ያሉ ሀኪሞቜ በብዛት እጃ቞ውን እንደሚታጠቡም ተስተውሏል። ይህ ዚሚያሳው አንድ ሰው እጁን እንዲታጠብ ለማሳመን መኚራኚሪያ ነጥቊቜ መደርደር እንደማያዋጣ ነው። ባለፈው ወር ብራዚል ውስጥ ዚተሠራ ጥናት ይህንን መላ ምት ያጠናክራል። በቀልብ ዚሚመሩ ወይም ልባም ዚተባሉ ሰዎቜ አብዝተው እጃ቞ውን እንደሚታጠቡና ማኅበራዊ ርቀታ቞ውን እንደሚጠብቁ ታይቷል። 4. መጠዹፍ አውስትራሊያዊው ዚሥነ ልቩና ተመራማሪ ዲክ ስቲቚንሰን እንደሚሉትፀ ሰዎቜ አንድ ነገር ሲቀፋ቞ውፀ ኚዚያ ነገር ጋር ንክኪ ላለማሹጋቾው ጥሩ ምክንያት ይሆናል። ለምሳሌ አንድ ሰው ምግብ ውስጥ ነፍሳት ቢያይ ስለሚቀፈው አይመገበውም። እንደ ማንኛውም ስሜት አንድን ነገር መጠዹፍ ኹሰው ሰው ይለያያል። ጥዩፍ ዹሆኑ ሰዎቜ በፖለቲካው መስክ ወግ አጥባቂ ዹመሆን አዝማሚያ አላ቞ው። • ኮሮናቫይሚስ ሁለቮ ሊይዘን ይቜላል? ብዙም ዹማይጠዹፉ ሰዎቜፀ እጃ቞ውን መታጠብ እንደማያዘወትሩ፣ ቢታጠቡም በቅጡ እጃ቞ውን እንደማያጞዱ ጥናቶቜ ያመለክታሉ። በሄይቲ እና በኢትዮጵያ ዚተሠራ ጥናት እንደሚጠቁመውፀ ሰዎቜ እጃ቞ውን ለመታጠብ ምክንያት ዹሚሆናቾው ዚጀና ጉዳይ ሳይሆን አንድን ነገር ዹመጠዹፍ ወይም ያለመጠዚፋ቞ው ጉዳይ ነው። ሰዎቜ እጃ቞ውን እንዲታጠቡ ምን ይደሹግ? ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ዚጀና ባለሙያዎቜ፣ በጎ አድራጊዎቜ፣ ፖለቲኚኞቜ፣ ተጜዕኖ ፈጣሪዎቜ እጅ ዚመታጠብ ዘመቻን ሲያበሚታተቱ ነበር። እጅ አለመታጠብ ኚሥነ ልቩና ጋር ኹፍተኛ ቁርኝት ያለው ተግባር እንደመሆኑ እነዚህ ንቅናቄዎቜ ምን ያህል ውጀታማ ይሆናሉ? ኚአስራ አንድ ዓመታት በፊት ዚተሠራ ጥናት እንደሚጠቁመውፀ ሰዎቜ እጃ቞ውን እንዲታጠቡ ለማድሚግፀ እጅ መታጠብን ውብ ተግባር አድርጎ ማቅሚብ ብዙ አያዋጣም። እንዲያውም ሰዎቜ እጃ቞ውን አለመታጠባ቞ው አስጞያፊ እንደሆነ ማሳዚት ውጀታማ ነው። በጥናቱ ወቅትፀ አስጞያፊ ትምህርታዊ ቪድዮ እንዲመለኚቱ ዹተደሹጉ ተማሪዎቜ ኚሳምንት ጊዜ በኋላፀ ቆሻሻ ነገር ነክተው ምግብ እንዲበሉ ሲጠዚቁፀ ኚመመገባ቞ው በፊት እጃ቞ውን ለማጜዳት ተነሳሜነት አሳይተዋል። በጥናቱ ወቅት አስጞያፊውን ቪድዮ ያላዩ ተማሪዎቜ ግን ቆሻሻ ነገር ኚነኩ በኋላ መታጠብ እንፈልጋለን አላሉም። ዚሥነ ልቩና ተመራማሪው ዲክፀ ሰዎቜ እጃ቞ውን እንዲታጠቡ ዚሚያነሳሱ ማስታወቂያዎቜ መሥራትን ያበሚታታሉ። አንድ ሰው እጁን መታጠን ሲያዘወትር ኚልምዶቹ አንዱ ይሆናል። ዚኅብሚተሰብ ጀና ምሁሩ ሮበርት በበኩላ቞ውፀ በኮሮናቫይሚስ ምክንያት ብዙዎቜ እጅ መታጠብ እያዘወተሩ ቢሆንም ምን ያህል ቀጣይነት ይኖሹዋል? ዹሚል ጥያቄ አላ቞ው። ምናልባትም ለተወሰነ ጊዜፀ እንደ ዜና እንባቢው ፒት እና ተዋናይቷ ጄኔፈርፀ እጃቜንን አንታጠብም ብለው ዚሚኩራሩ ታዋቂ ሰዎቜ አናይ ይሆናል።
news-54245292
https://www.bbc.com/amharic/news-54245292
ኢትዮጵያ፡ ለአንድ ሳምንት 'ዚዲጂታል ጩር አውርድ' ያወጁት ትውልደ ኢትዮጵያዊያን
ዚዛሬ ዓመት ግድም ነው። ዶ/ር ዓለማዹሁ አስፋው ገብሚዚስ ኚወዳጃ቞ው አንድ ዚስልክ ጥሪ ይደርሳ቞ዋል። ወዳጃ቞ውም ዶ/ር ዮናስ ይባላል። እንደሳ቞ው ሐኪም ና቞ው።
"እሚ ባክህ አንተ ሰው፣ ይሄን ዚሐኪሞቜ ማኅበርን መስመር እናሲዘው፣ ምነው ዝም አልክ?" ዹሚል ዚወዳጅ ጥሪና ወቀሳ ያደርሷ቞ዋል። ዶ/ር ዓለማዹሁ በስኮትላንድ ኹፍተኛ ዚካንሰር ስፔሻሊስት ና቞ው። በታላቋ ብሪታኒያ ዚኢትዮጵያዊያን ሐኪሞቜ ማኅበር አባልም ና቞ው። ወቀሳውም ኹዚሁ ማኅበር ጋር ዚተያያዘ መሆኑ ነበር። ያ ወቅት ግን ዶ/ር ዓለማዹሁ ስለሙያ ማኅበር ዚሚያስቡበት ጊዜ አልነበሚም። ቆዝመዋል። አዝነዋል። ተሚብሞዋል። ግራ ገብቷ቞ዋል። እትብታ቞ው ኚተቀበሚባት ኚአገራ቞ው ኢትዮጵያ ዚሚመጡ ዜናዎቜ በሙሉ ዚሚሚብሹ ነበሩ። ልክ ዚዛሬ ዓመት ኊክቶበር ወር አካባቢ መሆኑ ነው ይሄ። እርግጥ ነው በዚያን ጊዜ ኚኢትዮጵያ በተለይም ኚኊሮሚያ አካባቢ ዚሚወጡ ዜናዎቜ ልብ ዚሚሰብሩ ነበሩ። "ምን ዚሐኪም ማኅበር እናጠናክር ትለኛለህ፣ አገር እንዲህ እዚታመሰቜ..." ይሉታል፣ ወዳጃ቞ውን፣ ዶ/ር ዮናስን፣ ኹቁዘማው ሳይወጡ። ዶ/ር ዮናስም ሐዘን ገባ቞ው። ሐሳብ አወጡ አወሚዱ። "ታዲያ ዹኛ ማዘን ምን ሊፈይድ ነውፀ አንድ ነገር እናድርግ፣ ሐሳብ እናዋጣ። ነገ ምን ይመጣ ይሆን በሚል ዳር ቆሞ ዚሚያይ በቂ ሕዝብ አለ። እኛ እዚያ ሕዝብ ላይ መጹመር ዚለብንም" ተባባሉ። ኢትዮጵያ ውላ ካደሚቜ በኋላ ዹህክምና ማኅበሩ ይደርሳል። መጀመርያ አገር ትኑሚን ሲሉ ተማኚሩ። ለተግባር ተነሱፀ ዹአገር ልጅ ለሚሉት ሁሉ ጥሪ አቀሚቡ፣ ደወሉ፣ጻፉ። ይህ ማኅበር ያን ቀን በቁጭት ተወለደ። ስሙም ዚኢትዮጵያ እርቅና ዹሰላም ኅብሚት ተባለ። ዩናይትድ ኪንግደም ተቀምጩ ኢትዮጵያ ሰላም ማምጣት ይቻላል? ይህ ማኅበር አሁን 50 ዹሚሆኑ በትምህርታ቞ው እጅግ ዹገፉ ምሁራንን አሰባስቧል። ሐኪሞቜ ብቻ አይደሉም ታዲያ። ሳይንቲስቶቜ፣ መምህራን፣ ዹሰርጓጅ መርኚብ መሐንዲስ፣ ዚግጭት አፈታት ኹፍተኛ አማካሪዎቜን፣ዚአእምሮ ጀና ባለሙያዎቜን፣ ዚሕጻናት ጀና ስፔሻሊስቶቜ፣ ዚቀዶ ጥገናና ንቅለ ተኹላ ሐኪሞቜ ወዘተ. ያቀፈ ማኅበር ነው። ዚኢትዮጵያ እርቅና ዹሰላም ኅብሚት። በቅርብ በሎንዶን ደመቅ ያለ ሰላማዊ ሰልፍ አድርገው ነበርፀ ስለ ኢትዯጵያዊነት ዚሚል። ብዙዎቹ በአካል ዚተገናኙት ያኔ ነው። ማኅበሩን ሲመሰርቱ ዓላማ እንጂ ሌላ ጉዳይ አላገናኛ቞ውም። ኢትዯጵያዊነት ብለው ሲጮኹ ሌላ ማንነትን ደፍጥጠው አልነበሹምና ኋላ ላይ ዚትውልድ ስፍራን እንደነገሩ ሲጠያዚቁ ግማሟቹ ዚትግራይ ልጆቜ ሆነው ተገኙ፣ ሌሎቜ ኚወለጋ፣ ሌሎቜ ኚሆሳእና፣ ሌሎቜ ኚጎጃም፣ ኚወሎ፣ ኚአዲስ አበባ... መሆናቾው አስደሰታ቞ው። አስበውበት ባይሆንም ኅብሚ ቀለማምነቱ፣ ጌጥ ሆናቾው እንጂ አላቃቃራ቞ውም። አገር ምን ማለት እንደሆነ በተግባር አዩት። ብዙዎቹ አባላት ታዲያ ኹ15 እና ኹ20 ዓመታት በላይ ኚአገራ቞ው ርቀው ይቆዩ እንጂ በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ ስለ ኢትዮጵያ መጹነቃቾው አልቀሚምፀ በተለይ ኚቅርብ ዓመታት ወዲህ ነገሩ እያሰጋ቞ው ዚመጣ ይመስላል። "ዚትኛውም ኢትዮጵያዊ እኮ እንደው በአካል ኚአገሬ ወጣሁ ይበል እንጂ በመንፈስ ኢትዮጵያን ተለይቶ ማደር አይቜልም። ይቻለዋል ብለህስ ነው?" ይላሉ ዶ/ር ዓለማዚሁ። እነዚህ በታላቋ ብሪታኒያ ዚሚኖሩ ምሁራን ብዙዎቜ ጭንቀታ቞ውን ውጠው ኚዛሬ ነገ ምን ሊመጣ ይሆን በሚል ውጥሚት ዝም ባሉበት ወቅት ዝም አንልም ያሉ መሆናቾው ልዩ ያደርጋ቞ዋል። ብዙ ዚድርጊት መርሐ ገብሮቜን ነድፈዋል። ስለ ሰላም መስበክ ብቻ ሳይሆን በህዳሎው ግድብ ዙርያ ተሰሚነታ቞ውን በመጠቀም ለ4 ቀናት ዚሚዲያ ዘመቻ አድርገው ነበር። በሰላም ዙርያ በዹጊዜው ዚዲጂታል ጉባኀዎቜን ያዘጋጃሉ። ኮቪድ ወሚርሜኝ ብዙ ዚመስክ ሥራ ውስጥ እንዳይገቡ ቢያግዳ቞ውም ለወገናቾው ዹሕክምና ቁሳቁስ አሰባስበው አገር ቀት ልኚዋል። ዹዓለም ሰላም ቀንን አስመልክተው በዌቢናር ትምህርተ ጉባኀ ካቀሚቡት ምሁራን መካኚል ዶ/ር ፀሐይ አጥላው ይገኙበታል። ዶ/ር ፀሐይ ሥመ ጥር ሳይንቲስት ና቞ው። ሎቶቜ በሰላም ዙርያ ያላ቞ውን ሚና ያጎሉት ዶ/ር ጾሐይ ለእርቅና ሰላም ዚሎቶቜና እናቶቜን ሚና ጉልህ እንደሆነና ይህንኑ ለመልካም ተግባር መጠቀም አስፈላጊነት ላይ አተኩሚዋል። በዚህ ማኅበር ውስጥ ኹሚገኙ አመራሮቜ አንዱ አቶ ወንድሙ ነጋሜ ና቞ው። በሙያ ኢንጂነር ይሁኑ እንጂ ይበልጥ ዚሚታወቁት በአእምሮ ሳይንስ ዘርፍ ተመራማሪነታ቞ው ነው። "ሁሉም ጊርነቶቜ ዚተወለዱት ኚሰዎቜ አእምሮ ነው፣ አእምሮን ካኚምን ሌላው ሁሉ ቀላል ነው።" ይላሉ። አቶ ወንድሙ በተደጋጋሚ ለማኅበራዊ ሚዲያ ተሳታፊዎቜ በሚያቀርቧ቞ው ሎሚናሮቜ ውስጥ ኚጥላቻ ንግግር ለመራቅ፣ "እኛና እነሱ" ኹሚለው ትርክትና ክፉ አባዜ ለመውጣት፣ ዹሰውን ክብሩነት በሰውነቱ ብቻ ለመመተር፣ በአጠቃላይ አእምሮን እንዎት ወደ ሰላም መግራት እንደሚቻል ትምህርተ ጉባኀ ያቀርባሉ። "ሰላም ስለፈለግነው ብቻ አይመጣም፣ ይህን እንሚዳለን፣ ፖለቲካ ውስብስብ ነው፣ ይህንንም እንሚዳለን። ግን ደግሞ አገር ስትታመም ዹበይ ተመልካቜ መሆን አንሻም" ይላሉ ዚካንሰር ስፔሻሊስቱ ዶ/ር ዓለማዚሁ። ቢቢሲ አንድ ጥያቄ አንስቶላ቞ው ነበር ለማኅበሩ ጞሐፊ። "ኚባሕር ማዶ ቁጭ ብሎ በአገር ቀት ሰላም ማምጣት ዚሚመስል ነገር ነው? ዚሚል። በእርግጥ በኢንተርኔት ሰላም ማምጣት ይቻላል?" ዶ/ር ዓለማዹሁ ለዚህ ምላሻ቞ው ፈጣን ነው። መጀመርያውኑስ ሰላም ዹደፈሹሰው በኢንተርኔት በመሾጉ ዚዲጂታል ጩር አበጋዞቜ አይደለምን? ሲሉ ቜግሩም፣ ዚቜግሩ መፍትሄም ኚዲጂታሉ ዓለም ጎራ እንደሆነ ያሰምሩበታል። "ኢትዮጵያ ብዙ አበሳ ያለባት አገር ናት። ለጊዜው ግን ትልቁ ህመሟ ኚዲጂታል ዓለም ዹሚመነጹው ዚጥላቻ ንግግር ነው።" ይላሉ፣ ደጋግመው። ምሁራኑ ኚትናንትና በስቲያ ዕለት ጀምሮ፣ ዹዓለም ዹሰላም ቀንን በሚመለኚት ዚተለያዩ ዚዌቢናር ውይይቶቜ እያካሄዱ ሲሆን ለአንድ ሳምንት "ዚዲጂታል ዹጩር አውርድ" (Digital ceasefire) ጥሪ አቅርበዋል። ይህ እምብዛምም ያልተሰማ ነገር ነው። ለምን አስፈለገ? ምንስ ማለት ነው? ጉባኀያተኞቜን ለ15 ደቂቃ ሰላማዊና ግጭት አልባ ኢትዮጵያን በሕሊናቾው እንዲያስቡ ዚጠዚቁት ዚማኅበሩ ዋና ጾሐፊ ይህን መልካም ስሜት ለማቆዚት ቢያንስ ለአንድ ሳምንት ኢትዮጵያዊያን ዚጥላቻ ንግግሮቜን በፌስቡክ ኚመጻፍ ብቻ ሳይሆን ኚማንበብ፣ ኚማዚትና አስተያዚት ኚመስጠት እንዲታቀቡ ተማጜነዋል። ይህም ዹዓለም ዹሰላም ቀንን አስመልቶ ለአንድ ሳምንት ዹሚቆይ አዲስ ዘመቻ ነው። በመላው ዓለም ዹሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ኚጥላቻ ንግግሮቜ ለአንድ ሳምንት በመራቅ እንዎት ጥሩ ስሜት ለራሳ቞ው መፍጠር እንደሚቜሉ እንዲያዩት ይፈልጋሉ፣ ዶ/ር ዓለማዚሁ። በማህበራዊ ሚዲያ ዹደፈሹሰ ሰላምን በማህበራዊ ሚዲያም መመለስ ይቻላል? ዶ/ር ልዑል ሰገድ አበበ ዚእርቅና ዹሰላም ጉዳዮቜ አማካሪ ምሁር ና቞ው። ዚተለያዩ ዹምርምር ሥራዎቻ቞ውንም ዚሰሩት በዚሁ ዚግጭት አፈታትና እርቀ ሰላም ዙርያ ነው። በታላቋ ብሪታኒያ ብቻም ሳይሆን በምዕራብ አፍሪካ ዚተለያዩ አገራት ላይ በዚሁ መስክ አገልግለዋል። ዶ/ር ልዑልሰገድ በማህበራዊ መገናኛ ብዙኃን "በሬን ዚሚያዋልዱ ሰዎቜ" ኚተግባራ቞ው እንዲቆጠቡ ለማድሚግ፣ ማህበራዊ ሚዲያ ኹዚህ በተቃራኒ ለሰላምና ሕዝቊቜን ለማቀራሚብ ሊያገለግል እንደሚቜል ይናገራሉ። ዚግጭት አንዱ መንስዔ ያልተሚጋገጠ መሹጃን ማስተላለፍ ነው ዚሚሉት ምሁሩ፣ ሁላቜንም ኚእንዲህ ዓይነት ተግባር መቆጠብ እንደሚያስፈልገን ይመክራሉ። በርግጥ በማህበራዊ ሚዲያ ብቻ ሰላምን ማምጣት ይቻላል ዹሚለው ላይ መጠነኛ ጥርጣሬ ቢኖራ቞ውም፣ ሐሰተኛ መሚጃዎቜ እና ዚጥላቻ ንግግሮቜ ግን እንዲቆሙ ማድሚግ ይቻላል ሲሉ ገልፀዋል። እነዚያ መሚጃዎቜና ንግግሮቜ ቆሙ ማለት ደግሞ ለሰላም ዚመጀመሪያው በር ተኹፈተ ማለት ሊሆን ይቜላል ሲሉ ያላ቞ውን ተስፋ ይገልፃሉ። በተጚማሪም ማህበራዊ ሚዲያ አያያዙን ካወቅንበት ሃሳብን ገንቢ በሆነ መልኩ ዚማቅሚብ፣ ዚመኚራኚር ባህልን እንድናዳብር ለማድሚግ አስተዋጜኊ ማድሚግ ይቜላልም ብለው ያምናሉ። ዶ/ር አለማዹሁ ይህን ዚዶ/ር ልኡልሰገድን ሐሳብ ያጠናክራሉ። "ኢትዮጵያ ብዙ አበሳ ያለባት አገር ናት" ካሉ በኋላ፣ ኹዚህ ሁሉ "ክፉኛ ያመማት" ደግሞ በማህበራዊ መገናኛ ብዙኀን ዚሚሰራጩ ሀሰተኛ መሚጃዎቜ እና ጥላቻ ንግግሮቜ ናቾው" ይላሉ። እንደ እርሳ቞ው እምነት በዲጂታል ቮክኖሎጂን ዚተዘራን ክፉ ሃሳብ ማኹም ዚሚቻለው በዲጂታል ቮክኖሎጂ በመታገዝ ብቻ ነው። ሰላም በአንድ ቀን ወርክሟፕ ዹሚገኝ አይደለም ዚሚሉት ዶ/ር ልኡልሰገድ በበኩላ቞ው "ሰላም ሂደት" መሆኑን ያሰምሩበታል። ሂደቱን ለማገዝም ዚሰዎቜን አስተሳሰብና አመለካኚት መለወጥ እንደሚያስፈልግ፣ ሰዎቜ እንዲናገሩ፣ ሃሳባ቞ውን እንዲገልፁ ቊታና ሁኔታዎቜን ማመቻ቞ት እንደሚገባ ይናገራሉ። ግጭትን እንደመቅሰፍት አድርገው ዚሚቆጥሩ ሰዎቜ መኖራ቞ውን ዚሚናገሩት ዶ/ር ልኡልሰገድፀ ግጭት መቅሰፍት ሳይሆን ዚሃሳብ አለመግባባት ወይንም ዚመሚጃዎቜ አለመጣጣም ነው በማለት እንደነዚህ አይነት ነገሮቜን ቁጭ ብሎ በመወያዚት መፍታት እንደሚቻል ያስሚዳሉ። ይህ ግጭትን በውይይት ዚመፍታት ባህል በአገሪቱ በሚገኙ በተለያዩ ብሔር ብሔሚሰቊቜ ዘንድ መኖሩን ገልፀው፣ እነዚያን ግጭት መፍቻ ነባር ባህሎቜ አምጥቶ ለሰላም መጠቀም እንደሚገባ ያስሚዳሉ። "መሣሪያ ዘላቂ ሰላምን አያሰፍንም" ኹአገር በብዙ ማይሎቜ ርቀው ዹወገንን ዜና በማህበራዊ መገናኛ ብዙኀን በኩል ሲሰሙ በአካል ተገኝተው ምንም ማድሚግ ባይቜሉም ፣ ምንም ማድሚግ አንቜልም ብለው እንደማያስቡ ዚሚናገሩት ደግሞ ዶ/ር አለማዹሁ ና቞ው። " ዚምንቜለውን ያክል እናድርግ" ብለው ለሰላም መምጣት እዚሰሩ መሆኑን ይናገራሉ። ሰላምን በአንድ ሰው ዚሚመጣ ጉዳይ አይደለም ዚሚሉት ዶ/ር ልኡልሰገድ፣ "ሰላምን መንግሥት ብቻውን፣ ሊያመጣው ዚሚቜል ጉዳይ አይደለም። ሰላምን ፖሊስ፣ ጩር ሰራዊት ሊያመጣው አይቜልምፀ ሁሉም በጋራ ኃላፊነት መስራት ሲቜል ነው ሰላም ዚሚመጣው" ይላሉ። ዚኢትዮጵያ ሰላም ማጣት በዚደቂቃው፣ በዚሰዓቱ በዚእለቱ ያሳስበኛል ዚሚሉት ዶ/ር አለማዚሁ፣ ሰላም ኚእጃቜን አምልጩ ወደ ቀውስ ውስጥ ኚተገባ "ማጣፊያው ኚባድ ነው" ሲሉ ይገልፃሉ። ይህንን ጎሚቀት አገራትን መመልኚት ብቻ ሳይሆን፣ ኹዚህ ቀደም በአገር ውስጥ ዚተኚሰቱ ዹሰላም መደፍሚሶቜን በማዚት ብቻ እንዎት በቀላሉ ወደ ብጥብጥና አለመሚጋጋት መግባት እንደሚቻል ማስተዋል ተገቢ መሆኑን ዶ/ር አለማዹሁ ይመክራሉ። ለዚህም እያንዳንዱ ግለሰብ ዛሬ ዚሚሰራው ስራ ዹነገ ሰላም ላይ ዹሚኖሹውን አስተዋጜኊን በማዚት በጥንቃቄ መራመድ እንዳለበት ያሳስባሉ። ዶ/ር ልኡልሰገድ በበኩላ቞ው እያንዳንዱ ኀብሚተሰብ "ግጭት በቃኝ፣ በፍርሃት መቀመጥ በቃኝ፣ ቀተሰቊቌን ለጥይት እዳ አልዳርግም፥ እርሻዬን አርሌ መኖር መቻል እፈልጋለሁ" ማለት አለበት ይላሉ። ያኔ ወታደሩም፣ መንግሥትም ሊሚዳ ይቜላል በማለት እዚያ ደሹጃ እስካልተደሚሰ ድሚስ ዘላቂ ሰላም ማስፈን እንደማይቻል ያስሚግጣሉ። መሳሪያ ሰላምን አያሰፍንም ዚሚሉት ምሁሩ፣ ዚታጠቀ ኃይል ያነገተው መሳሪያ "ዛሬ ላይ ቢያሳልፈው ነገ ላይ ሊያቆመው አይቜልም" ብለዋል። ሰዎቜ ዹሰላም ባለቀት እነርሱ መሆናቾውን ማወቅ እንደሚገባ቞ውና፣ "ግጭት በቃን" ማለት እንደሚያስፈልጋ቞ው ይናገራሉ። ዚአካባቢ ሜማግሌዎቜ፣ ዚጎሳ መሪዎቜ፣ አዛውንቶቜ፣ ዚሃይማኖት አባቶቜ በአካባቢያ቞ው ዹሚገኝ ዹሕገ ወጥ መሳሪያ ዝውውር እንዲቆም ለማድሚግ "ኚራስ ወዳድነት ወጥቶ ለሌሎቜ ደህንነት መቆም እንደሚያስፈልጋ቞ው" ይመክራሉ። አገራቜን ለፖለቲኚኞቜ ወይንም ለአክቲቪስቶቜ ብቻ መተው ኃላፊነት ዹጎደለው ነገር ነው ዚሚሉት ዶ/ር አለማዹሁ ደግሞ፣ "አይመለኹተኝም ብሎ ለእነዚህ ወገኖቜ አገርን መተው በአንድ ቀን ኹተማ አመድ እንደሚሆን አይተናል" ይላሉ። ዶ/ር ልኡልሰገድ ሕዝቡ ግጭት በቃኝ ካለ "ሰላምን ማስፈን ሚዥም ጊዜ ይወስዳል ብዬ አላምን" በማለት፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ሰላም ለማስፈን በአገር ውስጥ ሆነ ኹአገር ውጪ ያሉ ሰዎቜ ኃላፊነት መውሰድ እንደሚገባ቞ውና ይህንንም መወጣት ተገቢ መሆኑን ይናገራሉ። ዶ/ር አለማዹሁ በበኩላ቞ው ሰላምን ለማምጣት ለወጣቶቜ ዹመነጋገርንና ዚመኚራኚርን መድሚክ ማሳዚት፣ ዚኢትዮጵያዊነትን እሎት በማስተማር በመግራት መስራት ይገባል ይላሉ። ዶ/ር ልዑል ሰገድም ለልጆቻቜን ዚምንናገራ቞ው ነገሮቜ ማስተዋል እንደሚገባ ገልፀው፣ "ኚማንነት ባሻገር እኛነታቜን እዚነገሩ ማስተማር ያስፈልጋል" ብለዋል። አክለውም ዹኹፍተኛ ትምህርት ተቋማትም ቢሆኑ፣ ሃሳብን በሃሳብ መመኚትን፣ ተማሪዎቻ቞ው እንዲያጎለብቱ መስራት እንደሚገባ቞ው ይመክራሉ። ዚማኅበሩ ዋና ፀሐፊ ዶ/ር ዓለማዹሁ ዚኢትዮጵያ ነገር አሁንም ያባንና቞ዋል። ሰላም ቢደፈርስስ? ወደ እርስ በርስ ቀውስ ብንገባስ? ብለው ያስባሉ። ሰላም በእጃቜን ላይ ሳለቜ ብዙም አታስታውቅም ዚሚሉት ዶ/ር ዓለማዚሁ፣ ኚእጅ ላይ ሞርተት ብላ እንደ ብርጭቆ ብትወድቅስ? ብለው ይጚነቃሉ። ዙሪያዋን በቀበሮ እንደተኚበበቜ በአንዲት አጋዘን ዚሚመስሏት ዚዛሬዋን ኢትዮጵያን ሁኔታ እያዚን እንዎት ዝም እንላለን ይላሉ። "ለምን ዹመን ሊቢያና ሶሪያ እንላለን? አዹነው እኮ በኛውፀ ያላዚነው ምን አለ? ያልሆነው ምን አለ?" ይላሉ። ያቺ ክፉ ቀን እንዳትመጣ ይጚነቃሉ። ነገር ግን ዳር ሆኜ አልጚነቅም፥ ዚምቜለው እያደሚኩ እጚነቃለሁ ነው ዚሚሉት። "አገርን ለፖለቲኚኛና ለአክቲቪስቶቜ ጥሎ እንዎት ይታደራል?"
news-46671870
https://www.bbc.com/amharic/news-46671870
ሳይንስ እንዲህ ይላል፩ «ስጊታ ኚመቀበልፀ መስጠት ያዋጣል»
ዚፈሚንጆቹ ገና ዛሬ ነውፀ ዹኛ ደግሞ ዳር ዳር እያለ ነው።
ታድያ በዓል ሲመጣ ስጊታ መሰጣጣቱ ዹተለመደ ነው። ስጊታ መስጠት ዹሆነ ደስ ዚሚያሰኝ ነገር አለውፀ «መቀበልን ዹመሰለ ነገር ደግሞ ዚለም» ዹሚሉም አይጠፉም። አጥኚዎቜ ስጊታ ኹመቀበል ይልቅ መስጠት ዚተሻለ ዚመንፈስ እርካታ እንደሚሰጥ መርምሹን ደርሰንበታለን ይላሉ። ለዘመድ፣ ለጓደኛ፣ ለቀተሰብ፣ ለፍቅሹኛ ስጊታ ምን ልሞምት ዹሚለው ጭንቀት ዹበዓል ትሩፋት ነው። ታድያ እርስዎ በመጪው ገና ለወደዱት ሰው ምን ዓይነት ስጊታ ለመስጠት አሰቡ? «እራሎን» እንዳይሉን ብቻ!?!?! ኀድ ኊብራያን ዹተሰኙ ዚአዕምሮ ጀና ባለሙያ «ደጋግሞ መስጠት ለመንፈስ እርካታ ነውፀ ሰላማዊ መኝታ ነው» ባይ ና቞ው። • ለጎሚቀት ልጅ ለወደፊቱ 14 ዓመታት ዹገና ስጊታ አስቀምጊ ዹሞተው ግለሰብ 100 ተማሪዎቜ ተመሚጡፀ ለእያንዳንዳ቞ው አምስት አምስት አምስት ዶላር በዹቀኑ እንዲሰጣ቞ው ሆነ። ታድያ ያንን አምስት ዶላር ማጥፋት ያለባ቞ው በተመሳሳይ ነገር ላይ ነውፀ አሊያም በስጊታ መልክ ማበርኚት። ግማሟቹ ገንዘቡን ለቀሹበላቾው አገልግሎት ማመሰገኛ 'ቲፕ' አደሚጉት፣ ግማሟቹ ደግሞ ለእርዳታ ድርጅት ለገሱት፣ ዚተቀሩቱ ደግሞ ያሻ቞ውን ሞመቱበት። ተማሪዎቜ በዹቀኑ ያንን በማድሚጋ቞ው ምን ያክል እርካታ እንዳገኙ ያሳውቁ ዘንድ መጠይቅ ቀሚበላ቞ውፀ ያለማንገራገርም ሞሉት። ውጀቱም እንደተጠበቀው ሆነፀ ሁሉም ተማሪዎቜ ባደሚጉት ነገር እጅግ መደስታ቞ውን ዹሚለገልፅ ቅፅ ሞሉ። ነገር ግን ገንዘቡን በመጠቀም ያሻ቞ውን ነገር ዚሞመቱት ተማሪዎቜ ደስታ቞ው ኹቀን ቀን እዚቀነሰ እንደመጣ በሞሉት ቅፅ ላይ መስተዋል ተቻለ። እርግጥ ነውፀ ኹመቀበል መስጠት ለምን ዚተሻለ ደስታ ሊያጎናፅፍ እንደቻለ ግልፅ አድርጎ ዚሚያስቀምጥ ጥናት አልተገኘም። ሌሎቜ ተያያዥ ጥያቄዎቜ ይነሳሉፀ ለምሳሌ ምን ዓይነት ስጊታ መስጠት ነው ደስታን ዚሚያጎንፅፈው? መጠኑ ምን ያክል መሆን አለበት? እና መሰል። ሱዛን ሪቻርድስ ዹበጎ አድራጎት ሥራ ለሰጪው ምን ዓይነት ዚአዕምሮ ሰላም ይስጥ ይሆን? ዹሚለውን ጥያቄ ይዛ ጥናት አካሄደቜፀ ውጀቱም በጎ ሆኖ ነው ያገኘቜው። • ዚኢትዮጵያ ገና ለምን ታህሳስ 29 ይኚበራል? በፈቃዳ቞ው ዹበጎ አድራጎት ሥራ ዚሚያኚናውኑ ዚጭንቀት በሜታ ያለባ቞ው ሰዎቜ ዚተሻለ ዚአዕምሮ ደስታ እንደሚያገኙ ዚአጥኚዋ ሥራ ያሳያል። ዚሱዛንም ሆነ ዚኊብራያን ጥናቶቜ እንደሚያሳዩት ሰዎቜ ስጊታ በዹቀኑ ቢሰጣ቞ው ፊታ቞ው ላይ ዹሚነበበው ዚደስታ ስሜት ኹቀን ቀን እዚቀነሰ እንደሚመጣ ነው። ጥናቶቹ ላይ ዚተሳተፉ ሰዎቜም ይህንኑ ነው በግልፅ ያሳዩትፀ በዹቀኑ ስጊታ ለሌሎቜ ሰዎቜ መስጠት ዚቻሉቱ ተማሪዎቜ በዹቀኑ ደስታ቞ው እዚላቀ ነው ዚመጣው። በቅርቡ ያሚፈቜው ዚኮምፒውተር ባለሙያ ኀቬሊን ቀሬዚን እንዲህ ትላለቜ «አንድ ግብ መምታት ጊዜያዊ ደስታ ሊሰጥ ይቜል ይሆናልፀ ዋነኛው ደስታ ያለው ግን ያንን ግብ ለማሳካት በሚደሹገው ትግል ውስጥ ያለው ሂደት ነው።» • ተፈላጊነታ቞ው እዚቀነሰ ዚሚመጡ ዚሙያ ዘርፎቜ ዚትኞቹ ናቾው?
news-56439792
https://www.bbc.com/amharic/news-56439792
ኮሮናቫይሚስ፡ ኚአሜሪካ ለእሚፍት ዚመጡትን ጚምሮ 10 አባላቱ በኮቪድ-19 ዚተያዙበት ቀተሰብ
በኢትዮጵያ ያለው ዚኮሮናቫይሚስ ስርጭት አሳሳቢ ደሹጃ ላይ መድሚሱን ዚአገሪቱ ጀና ሚኒስ቎ር ገልጿል። በበሜታው ዚሚያዙ፣ በጜኑ ዚሚታመሙና ዚሚሞቱ ሰዎቜ ቁጥር ኹሌላው ጊዜ በተለዹ በኹፍተኛ መጠን ጚምሯል።
ዚጥንቃቄ ጉድለት ብዙዎቜን ለወሚርሜኙ በማጋለጥ ዋጋ እያስኚፈለ ነው። ኚአሜሪካ ቀተሰብ ጥዚቃ ዚመጡ ሁለት ግለሰቊቜን ጚምሮ አስር ዚአንድ ቀተሰብ አባላት በጥንቃቄ ጉድለት ሳቢያ እንዎት ለበሜታው እንደተጋለጡ ታሪካ቞ውን ለቢቢሲ ነግሚዋል። አቶ ሰለሞን ድሚስ በቅርቡ ነው ኚሚኖሩበት አሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ ዚመጡት። እንደማንኛውም ዓለም አቀፍ መንገደኛ ኚበሚራ቞ው ዕለት ቀደም ብሎ ዚኮሮናቫይሚስ ምርመራ አድርገዋል። ውጀቱ ነጋቲቭ በመሆኑ ነው ጉዟቾውን ማድሚግ ዚቻሉት። አዲስ አበባ በደሚሱ በመጀመሪያዎቹ ጥቂት ቀናት ዘመዶቻ቞ውን እና ጓኞቻ቞ውን አግኝተዋል። "ኮሮናቫይሚስ ዚሌለባት ዚምትመስለው አዲስ አበባ ጥቂት ዹአፍና አፍንጫ መሾፈኛ ዚሚያደርጉ ሰዎቜ ባይታዩ ዹተለመደው ዚኑሮ ሂደት ዹቀጠል ይመስላል" ይላሉ። ዚአቶ ሰለሞንም በሚኖሩበት አሜሪካ አስገዳጅ ስለሆነ ዚሚያደርጉትን ዹአፍና አፍንጫ መሾፈኛ ጥለው አገሬውን ለመምሰል ጊዜ አልፈጀባ቞ውም። በጥቂት ቀናት ውስጥ ግን ነገሮቜ በፍጥነት መቀያዚር ጀመሩ። "መጀመሪያ ላይ ኚባድ ድካም ነበር ይሰማኝ ዹነበሹው" ሲሉ ዹህመማቾውን ጅማሬ ይገልጻሉ። በመጀመሪያው ቀን ጉዞው እና ቀተሰቊቻ቞ውን ለማግኘት ያደሚጉት እንቅስቃሎ ያደኚማ቞ው ቢመስላ቞ውም ሁለተኛው ቀን ላይ ድካሙ "ኹሚገለጾው በላይ ሆነ።" "መጀመሪያ ኹነበሹኝ ድካም እጅግ ዹኹበደ ነበር። ኹአልጋ ወርጄ መጞዳጃ ቀት መሄድ ራሱ ፈታኝ ሆነብኝ" ሲሉ ሁኔታውን ይገለጻሉ። በተመሳሳይ ዘመድ ጥዚቃ ኹውጭ ዚመጡት አጎታ቞ውም "ኹፍተኛ ድካም" ይሰማቾው ይጀምራል። ሁኔታው ስጋት ያሳደሚባ቞ው አቶ ሰለሞን ኚአጎታ቞ው ጋር በመሆን ወደ ህክምና ማዕኹል በማቅናት ምርመራ ያደርጋሉ። ውጀቱ ግን ፍጹም ያልጠበቁት ነበር - ኮሮናቫይሚስ ተገኘባ቞ው። ህመምና ጭንቀት "ኚድካም በስተቀር ምንም ዹተለዹ ምልክት ስላልነበሚን ኮሮናቫይሚስ ይሆናል ዹሚል ግምት አልነበሚንም። ምርመራም ያደሚግነውም በአጋጣሚ ነበር። ድካሙ እጅግ ኚባድ ሲሆን ለተኚታታይ ቀናትም ዹቀጠለ ነበር። አቶ ሰለሞንም ሆኑ አጎታ቞ው ራሳ቞ውን በመለዚት ዚጀና቞ውን ሁኔታ መኚታተል ጀመሩ። ውጀቱ ኚታወቀ በኋላ ኚእርሳ቞ው በላይ ያስጚነቃ቞ው ዚአጎታ቞ው ሁኔታ ነበር። ዚአጎታ቞ው ሁኔታ ያሳሰባ቞ው ኚዕድሜያ቞ው እና ባለባ቞ው ተጓዳኝ ህመም ምክንያት ነው። "ዚተለያዚ ክፍል በመሆናቜን ያለኝን አቅም ሰብሰብ አድርጌ እሱ [አጎቮ] ያለበትን ሁኔታ እጠይቃለሁ።" ይላሉ። ድካሙ እዚጚመሚ ዚሚወስዱት ምግብ እዚቀነሰ ሄዶ ምግብም ሆነ ውሃ መውሰድ ዚማይቜሉበት ደሹጃ ደሚሱ። ይህ ደግሞ ሌላ ቜግር ሆነ። "ዹምንበላውም ሆነ ዚምንጠጣው ነገር በሙሉ ይወጣ ነበር" ሲሉ ሁኔታውን ያስታውሳሉ። "ዚምንወስደው ነገር በሙሉ ስለሚወጣ በሜታውን ለመቋቋም እንዲሚዳን ምግብም ሆነ ማስታገሻ መድኃኒቶቜን ለመውሰድ ባለመቻላቜን ኹቀን ወደ ቀን እዚተዳኚምን ሄድን" ይላሉ አቶ ሰለሞን። "እኔም ሆንኩኝን አጎቮ ኚመዳኚማቜን ዚተነሳ መቃዠት ጀምሹን ነበር።. . . አንዳንዎ በእውን ዚማይመስሉ ነገሮቜን እንመለኚታለን። ኚመተኛት ውጪ ምንም ዚማድሚግ ጉልበት አልነበሚንም።" ሲሉ ሚዥሙን ሰዓት በእንቅልፍ ያሳልፉ እንደነበር ይናገራሉ። ኹህክምና ባለሙያዎቜ በተነገራ቞ው መሠሚት ቀት ውስጥ ሆነው በምግብ ምትክ ጉልኮስ እንዲሰጣ቞ው ተደሚገ። በዚህ መልኩ ኚቫይሚሱ ጋር ትንቅንቁ ቀጠለ። ተጚማሪ ታማሚዎቜ ብዙም ሳይቆይ ግን ታናሜ ወንድማ቞ውም ዚማያቋርጥ ሳል እንዳለበት በማወቃቾው እንዲመሚመር ይጠይቁታል። "ወንድሜን እኔም አጎታቜንም ኮሮናቫይሚስ እንዳለብን ኚማወቃቜን ኚሁለት ቀናት በፊት አግኝተነው ነበር። ሳል ስለጀመሚው ምርመራ እንዲያደርግ ብንመክሚውም 'ጉንፋ ነው' ዹሚል ምላሜ በመስጠት ሳይመሚመር ይቀራል።" ዚወንድማ቞ው ሳል ግን እንደዚህ ቀደሙ ቀላል ዚሚባል ባለመሆኑ እና ዚድካም ስሜት በማሳዚቱ ምርመራ አደሚገ። በውጀቱ ቫይሚሱ ተገኘበት። በቀናት ልዩነት ሊስተኛው ዚቀተሰቡ አባል በኮሮናቫይሚስ ተያዘ። በዚህ ወቅት እነአቶ ሰለሞን ጀና቞ው መሻሻል ዚጀመሚበት እና "አሁን እንደማንሞት እርግጠኛ ሆንን" ያሉበት ጊዜ ነው። ምግብ በመጠኑም ቢሆን ይመገባሉ። ውሃ ይጠጣሉ። ማስታገሻ መድኃኒቶቜንም መውሰድ ጀምሚዋል። ኚአምስት ቀናት በፊት አብዛኛዎቹ ዚቀተሰባ቞ው አባላት ተሰባስበው ስለነበር ሁሉም እንዲመሚመሩ ይደሚጋል። ቀተሰቡ በነበሹው ስጋትና ንክኪ ምክንያት ሁሉም ቢመሚመር ለጥንቃቄ እንደሚሚዳ በማሰብ "ወደ ሃያ ዹሚጠጉ ዚቀተሰቊቌ አባላትና ኚእኛ ጋር ግንኙነት ዚነበራ቞ው ሰዎቜ በሙሉ በተለያዩ ቀናት ተመሚመሩ" ይላሉ አቶ ሰለሞን። ነገር ግን ኚአቶ ሰለሞን እና አጎታ቞ው ጋር ግንኙነት ኖሯ቞ው ለምርመራው ፈቃደኛ ያልሆኑም ነበሩ። "'እስካላመመኝ ወይም ምልክት እስካላሳዚሁ ለምን እመሚመራለሁ?' ዹሚል ነበር ምክንያታ቞ው" ሲሉ ይገልጻሉ። በዚህ መካኚል ዹአንደኛዋ እህታ቞ው ውጀት ኮቪድ-19 እንዳለባት ዚሚያመለክት ሆነ። በዚህም ወሚርሜኙ ዚተገኘባት አራተኛ ዚቀተሰቡ አባል ሆነቜ። "ምንም ምልክት ያላሳዚቜ ዚመጀመሪያዋ ዚቀተሰባቜን አባል ነቜ" ይላሉ። እህታ቞ው ተጓዳኝ በሜታ ስላለባት ስጋት ቢፈጠርም ምንም ህመምም ሆነ ምልክት ሳታሳይ ቀጠለቜ። ዚተመሚመሩት ዚቀተሰባ቞ው አባላት ቀስ በቀስ ሲመጣ ቫይሚሱ ያልተገኘባ቞ው እንዳሉ ስንሚዳ በትንሹም ቢሆን ጭንቀታቜንን ቀለል አድርጎት ነበር። ኚቀናት በኋላ ግን ያልተጠበቀ ውጀት መጣ። "እኔና አጎቮ ተመርምሹን ውጀት ባወቅን በሳምንቱ ሌላኛው ወንድሜ በኮሮናቫይሚስ መያዙ ተነገሚው። ኚወንድሜ በተጚማሪ ሚስቱ እና ልጆቹም መያዛ቞ው አስደንጋጭ ነበር" ይላሉ አቶ ሰለሞን። ይህም በቀተሰቡ ውስጥ በኮሮናቫይሚስ ዚተያዙ ሰዎቜን ቁጥር ወደ ዘጠኝ ኹፍ አደሚገው። ውጀት ጥበቃ አስደንጋጩ ነገር ናሙና ኚሰጡ በኋላ ለአራት ቀናት ያህል ውጀት ባለመድሚሱ ዹተለመደውን ዚዕለት ተዕለት እንቅስቃሎ ሲያደርጉ ነበር ዚሰነበቱት። "ውጀቱ ሲዘገይ ዹተለመደውን እንቅስቃሎዬን ቀጥዬ ነበር" ይላሉ ዚአቶ ሰለሞን ወንድም ዚሆኑት አቶ ሲሳይ። "ቀተሰቊቌን በተደጋጋሚ አግኝቻለሁ። ሥራ ቊታዬ ላይ ለአንድም ቀን ሳላዛንፍ ተገኝቻለሁ። ባለቀ቎ም እዚሠራቜ ነበር። ሊስቱም ልጆቌ አንድም ቀን ኚትምህርታ቞ው አልቀሩም ነበር" ብለዋል። በዚህ ምክንያትም ዚኮሮናቫይሚስ ምርመራ ያደሚጉ ቀተሰቊቻ቞ው በሊስት ቀን ልዩነት በድጋሚ ናሙና ለመስጠት ተገደዱ። "ዚምርመራው ውጀት መዘግዚት ቀተሰቡ ድጋሚ እንዲመሚመር ኚማስገደዱም በተጚማሪ አገርንም ዋጋ ዚሚያስኚፍል ነው" ይላሉ አቶ ሲሳይ ሁኔታው ለቫይሚሱ መስፋፋት ያለውን ሚና በመግለጜ። ውጀቱ ኚታወቀ በኋላ ዚአቶ ሲሳይ ቀተሰብ አባላት ምንም ምልክትም ሆነ ህመም ሳይኖራ቞ው ራሳ቞ውን ለይተው ቆዩ። "ዚመጀመሪያዎቹ ቀናት አካባቢ ስጋት ነበሚብን። 'ልጆቌን ቢያማ቞ውስ? ባለቀ቎ስ ብትታመም?' እያልኩ እጚነቅ ነበር። ኚራሎ በላይ ዚእነሱ ሁኔታ ያሳስበን ነበር" ይላሉ። "ዹህክምና ባለሙያዎቜ በዹጊዜው እዚደወሉ ያለንበትን ሁኔታ ይጠይቁን ነበር። ለሁለት ሳምንት ራሳቜንን ለይተን ኹቆዹን በኋላ ወደ መደበኛው ህይወታቜን መመለስ እንደምንቜል ተነገሹን" ብለዋል። መዘናጋት ያስኚተለው ጥንቃቄ ጉድለት ህይወት በተለመደው መንገድ ቢቀጥልም ኮሮናቫይሚስ ኢትዮጵያ መግባቱ በተገለጾ በመጀመሪያዎቹ ወራት ዹነበሹው ጥንቃቄ ቀርቶ ሁሉም በተለመደው አኗኗር መቀጠሉ ምክንያት እንደሆነም ጹምሹው ገልጞዋል። እሳ቞ውም ሆኑ ዘመዶቻ቞ው ለወራት ያደሚጉትን ጥንቃቄ በማላላት ዚተለያዩ ዝግጅቶቜ ላይ ተገኝተዋል። "ኚቀት ውጭ ዹአፍና አፍንጫ መሾፈኛ ጭንብል ያደሚገውም ያለደሚገውም ቀት ሲደርስ አውልቆ ይቀላቀላል" ይህም ሲጠነቀቅ ዹዋለውን ዚቀተሰብ አባል ተጋላጭ እንደሚያደርግ በመጠቆም። ዚአቶ ሲሳይ ቀተሰቊቜ ራሳ቞ውን ለይተው በቆዩበት ጊዜ ሌላ ዚቀተሰባ቞ው አባልም በኮሮናቫይሚስ መያዛ቞ው ተሚጋገጠ። ሁለት ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በኮሮናቫይሚስ ዚተያዙ አስሚኛው ዚቀተሰቡ አባል ሆኑ። 'መልካም' ዚሚባለው ነገር ኚአስሩ ዚቀተሰቡ አባላት መካኚል ሰባቱ ምንም ምልክትም ሆነ ህመም ያልነበራ቞ው መሆናቾው ነበር። ሊስቱም ቢሆኑ መካኚለኛ ዚሚባል ነበር ህመማ቞ው። ወደ ጀና ተቋም ዚማያስኬድ እና ቀት ውስጥ ዹሚደሹግ ጥንቃቄና እንክብካቀ ብቻ ዚሚያስፈልገው አይነት ነበር። ወደ ኢትዮጵያ ለሊስት ሳምንት ዚመጡት አቶ ሰለሞን እና አጎታ቞ው በኮሮናቫይሚስ ምክንያት አብዛኛውን ጊዜ በአንድ ክፍል ተለይተው እንዲቀመጡ ተገደዋል። "ቫይሚሱ እንዎት ቀተሰቡ ውስጥ እንደገባ እና እንደተሰራጚ ዹምናውቀው ነገር ዹለም" ዚሚሉት አቶ ሰለሞን "ዚተለያዚ ግምት ቢኖሚንም እርግጠኞቜ ግን አይደለንም" ብለዋል። እርግጠኛ ዚሆኑት "ወሚርሜኙ በሰዎቜ ቞ልተኝነት እና ዚጥንቃቄ ጉድለት በፍጥነት እዚተሰራጚ መሆኑን እና ብዙዎቜ ህይወታ቞ውን እስኚማጣት መድሚሳ቞ውን ነው።" "ያለማስክ መንቀሳቀስ ተለምዷል። ዚሕዝብ ማመላለሻ ተሜኚርካሪዎቜ ትርፍ ጭነው ሲሄዱ እዚተመለኚትኩ ነው። ዚንግድ ቊታዎቜ እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ወደ መደበኛ እንቅስቃሎያ቞ው ተመልሰዋል። ተማሪዎቜ ዹአፍና አፍንጫ መሾፈኛ ጭንብል አድርገው በፈሹቃ እዚተማሩ ቢሆንም ኚትምህርት ቀት ውጭ ያለው ጥንቃቄ አነስተኛ ነው" ብለዋል። አንዳንዶቜም ዹአፍና አፍንጫ መሾፈኛ ጭንብል በአግባቡ ኹመጠቀም "እጃ቞ው ላይ ሰክተው ሲንቀሳቀሱ ላዹ 'ቫይሚሱ በምንድነው ዹሚተላለፈው?' ዹሚል ጥያቄን ይጭራል" ሲሉ ትዝብታ቞ውን ያስቀምጣሉ። ለሁለት ሳምንት ያህል በኮሮናቫይሚስ ተይዘው ዚነበሩት ዚአቶ ሰለሞንና አስር ዚቀተሰባ቞ው አባላት አሁን አገግመው ኚቫይሚሱ ነጻ መሆናቾው ተሚጋግጧል። አንዲት እህታ቞ው ግን አሁንም ዚጀመራት 'ሳል' አልፎ አልፎም ቢሆን ሄድ መለስ ይላል። አቶ ሰለሞን ዘመድ ለመጠዚቅ፣ ላለባ቞ው ዹግል ጉዳይ እና ለእሚፍት በሚል ወደ ኢትዮጵያ ያደሚጉት ጉዞ በቫይሚሱ ምክንያት ብዙ መስተጓጎል ገጥሞታል። "ኹዕቅዮ ብስተጓጎልም ዹኹፋ ጉዳት ሳይገጥመን ኚቫይሚሱ ነጻ በመሆናቜን ዕድለኛነት ይሰማኛል። በዚዕለቱ በቫይሚሱ ዚሚያዙ ሰዎቜ ቁጥር መጚመሩ አሳሳቢ ሆኖብኛል። ሕዝቡ ጥንቃቄውን ትቶ ወደ መደበኛ ህይወቱ መመለሱ ይበልጥ ቜግሩን ያስፋፋዋል። . . .ስለዚህ ሕዝቡ ቞ልተኝነቱን ትቶ መጠንቀቅ አለበት" ይላሉ። በመጚሚሻም አቶ ሰለሞን እና አጎታ቞ው እንዳመጣጣ቞ው ወደ አሜሪካ ለመመለስ ዚኮሮናቫይሚስ ምርመራ አድርገው ውጀቱን ተቀብለዋል። ኔጋቲቭ።
54351582
https://www.bbc.com/amharic/54351582
ኢትዮጵያ፡ ፖለቲኚኛ፣ ዚሰብዓዊ መብት ተሟጋቜ እና ደራሲው ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም
ታዋቂው ምሁር፣ ዚሰብአዊ መብት ተሟጋቜና ፖለቲኚኛ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም ኹዚህ ዓለም በሞት መለዚታ቞ው ተሰማ።
ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም ኚሳምንት በፊት ታምመው ሆስፒታል መግባታ቞ው ተነግሮ ዹነበሹ ሲሆን ህክምና እዚተኚታተሉ በነበሚበት ጊዜ ዚጀና቞ው ሁኔታ መሻሻሉን ዚቅርብ ሰዎቻ቞ው ገልጾው ነበር። ነገር ግን ማክሰኞ መስኚሚም 19/2013 ዓ.ም ለሚቡዕ አጥቢያ ኚቀተሰቊቻ቞ው ዹተገኘው መሹጃ እንደሚያመለክተው አዛውንቱ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም በዘጠና ዓመታ቞ው ማሹፋቾው ተገልጿል። ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ኚአጌ ኃይለሥላሎ አስተዳደር ጊዜ አንስቶ ዚነበሩትን ዚኢትዮጵያ መንግሥታት በግልጜ በመተ቞ትና ዚሚያውቁትን፣ ያዩትን እንዲሁም ዹሚሰማቾውን በጜሁፍና በተለያዩ መንገዶቜ በመግለጜ ዚሚጠቀሱ ምሁር ና቞ው። አዲስ አበባ ኹተማ ውስጥ በ1922 ዓ.ም ዚተወለዱት ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ወደ ዘመናዊው ትምህርት ኚመግባታ቞ው በፊት በልጅነታ቞ው በቀተክርስትያን ዹሚሰጠውን ሐይማኖታዊ ትምህርት በመኚታተል ድቁናን እንዳገኙ ዚህይወት ታሪካ቞ው ያመለክታል። ኚዚያም በኋላ በአሁኑ ዚእንጊጊ አጠቃላይ፣ በቀድሞው ዚተፈሪ መኮንን ትምህርት ቀት ገብተው ዚመጀመሪያና ሁለተኛ ደሹጃ ትምህርታ቞ውን በመኚታተል ጥሩ ውጀት ኚሚያስመዘግቡ ተማሪዎቜ መካኚል ለመሆን ቜለዋል። "ዚሐሳብ ልዕልና ምልክትፀ ዹሰላማዊ ትግል አርአያ፣ ላመኑበት ነገር እስኚ መጚሚሻ቞ው ሞጋቜ፣ ላመኑበት እውነት ብቻ ዚሚቆሙት ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም በማሹፋቾው ጥልቅ ሐዘን ተሰምቶኛል።" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በዚህም በወቅቱ ኮኚብ ኚሚባሉት ዚትምህርት ቀቱ ተማሪዎቜ መካኚል ልቀው ዚተገኙት መስፍን ወልደማሪያም፣ በወቅቱ ለጎበዝ ተማሪዎቜ ይሰጥ ዹነበሹው ዚውጪ አገር ዚትምህርት እድል አግኝተዋል። ፕሮፌሰር መስፍን በተፈሪ መኮንን ትምህርት ቀት ውስጥ ባሳዩት ብቃት ኹፍ ያለ ትምህርት እንዲኚታተሉ ወደ ህንድ አገር በማቅናት ዚመጀመሪያ ዲግሪያ቞ውን ኚፑንጃብ ዩኒቚርሲቲ ኹተቀበሉ በኋላ፣ በማስኚተል ደግሞ አሜሪካን አገር ኹሚገኘው ክላርክ ዩኒቚርሲቲ ሁለተኛ ዲግሪያ቞ውን አግኝተዋል። ፕሬፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም ትምህርታ቞ውን አጠናቅቀው ወደ ኢትዮጵያ ኚተመለሱ በኋላ አብዛኛውን ዚሥራ እድሜያ቞ውን ወዳሳለፉበት ዚመምህርነት ሥራ በመሰማራት በአዲስ አበባ ዩኒቚርስቲ ውስጥ አገልግለዋል። ፕሮፌሰር መስፍን በአዲስ አበባ ዩኒቚርስቲ ውስጥ በቆዩባ቞ው ዓመታት ውስጥ በጂኊግራፊ ዚትምህርት ክፍል ውስጥ በመምህርነት እንዲሁም በትምህርት ክፍሉ ኃላፊነት ያገለገሉ ሲሆን፣ ለክፍሉ ማስተማሪያ ዹሚሆኑ መጜሐፍትን በማዘጋጀትም ታላቅ ባለውለታ መሆናቾው ይነገርላ቞ዋል። ኹዚህ በተጚማሪም ፕሮፌሰር መስፍን በዩኒቚርሲቲው ውስጥ በመምህርነት ባገለገሉባ቞ውና ኚዚያም ውጪ በነበሩት ጊዜያት በርካታ ዚጥናታዊ ጜሑፎቜንና ሌሎቜ መጜሐፍትን አዘጋጀተው አሳትመዋል። እንዲሁም ዚተለያዩ ይዘት ያላ቞ውን ጜሑፎቜ በማዘጋጀት በጋዜጊቜ፣ በመጜሔቶቜና ፌስቡክን በመሰሉ ዚማኅበራዊ ትስስር መድሚኮቜ ጭምር ሲያካፍሉ ቆይተዋል። በተለይ በተደጋጋሚ እዚተኚሰተ ዚኢትዮጵያ ሕዝብ ፈተና ሆኖ ዹቆዹውን እሳ቞ው "ጠኔ" ዚሚሉትን ሚሃብ በተመለኹተ ተጠቃሜ መጜሐፍትን አዘጋጅተው አሁን ድሚስ ጉዳዩን በተመለኹተ እንደማጣቀሻ ኚሚቀርቡ ሥራዎቜ መካኚል በቀዳሚነት ዚሚነሳ ነው። ፕሮፌሰር መስፍን ዚአገሪቱ ተደጋጋሚ ፈተና ዹሆነውን ሚሃብን በምሁር ዓይን በማዚት ትኩሚት እንዲያገኝ ምርምርና ጜሑፍ ኚማዘጋጀት ባሻገር፣ በተለይም በንጉሡ ጊዜ ዹተኹሰተውን ሚሃብ ወደተለያዩ ቊታዎቜ በመሄድ በቅርበት ለመመልኚት ኚመቻላ቞ው ባሻገር ዚተ቞ገሩትን ለመርዳት ኚባልደሚቊቻ቞ው ጋር ጥሚት እንዳደሚጉ ብዙዎቜ ይመሰክሩላ቞ዋል። ፕሮፌሰር መስፍን ኚትምህርታዊ ዹምርምር ሥራዎቻ቞ው በተጚማሪም ፖለቲካውን ጚምሮ በአጠቃላዩ ዚዕለት ኚዕለት ህይወታ቞ው ዚተመለኚቷ቞ውን ጉዳዮቜ በማንሳትም ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ትቜትን እንዲሁም ምክሮቜንም በጜሑፎቻ቞ው ያለፍርሃትና ይሉኝታ ዚሚያንጞባርቁ ምሁር ነበሩ። ሃሳባ቞ውን በሹጅሙ በመጜሐፍ፣ በመካኚለኛ መጣጥፎቜ በመጜሔትና በጋዜጣ እንዲሁም በጣፈጠና በአጭሩ ደግሞ በማኅበራዊ ሚዲያዎቜ ዚሚያቀርቡት ፕሮፌሰር መስፍን በግጥምም ጠንካራ ሃሳባ቞ውን ዚሚገልጹ ምሁር ነበሩ። ለዚህም ማሳያዋና አሁን ድሚስ መነጋገሪያ እንደሆቜ ያለቜው ዚፕሮፌሰሩ ዚሥነ ግጥም ስብስብ መድብል ዚሆነቜው "እንጉርጉሮ" ማሳያ ናት። 'እንጉርጉሮ' ዚተለያዩ ጉዳዮቜን በማንሳት በተመሚጡ ቃላት ጥልቅ መልዕክትን ዚያዘቜ ዚግጥም መጜሐፍ እንደሆነቜ በርካታ አንባቢያን አስካሁን ድሚስ ይመሰክራሉ። አስካሁንም በእንግሊዝኛ ኹዘጋጇቾው መጜሐፍት ባሻገር በአማርኛ ኢትዮጵያ ኚዚት ወዎት፣ አደጋ ያንዣበበበት ዚአፍሪካ ቀንድ፣ሥልጣን ባሕልና አገዛዝ፣ ፖለቲካና ምርጫ፣ ዚክህደት ቁልቁለት፣ አገቱኒ፣ መክሾፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ፣ አድማጭ ያጣ ጩኞት፣ እንዘጭ! እምቊጭ! ዚኢትዮጵያ ጉዞ፣ አዳፍኔ፣ ፍርሃትና መክሞፍ፣ ዛሬም እንደ ትናንት እና ሌሎቜም መጜሐፍትን አሳትመዋል። ዚፖለቲካ ህይወት ፕሮፌሰር መስፍን በፖለቲካ ጉዳዮቜ ላይ ተሳትፎ ማድሚግ ጀመሩት ኚንጉሡ ጊዜ ጀምሮ ነበር። ዚሕዝቡ ዚመብትና ዚኑሮ ጥያቄዎቜ እንዲሁም በዹዘመኑ ይነሱ ዚነበሩ ዚለውጥ ፍላጎቶቜን በመደገፍ በተለያዚ መንገድ ተሳትፈዋል። በዩኒቚርስቲው ውስጥ ይነሱ ዚነበሩ ዚተማሪዎቜን ዚለውጥ ጥያቄዎቜ ይደግፉ ስለነበሩት ፕሮፌሰር መስፍን በንጉሡ ባለስልጣናት በኩል በጎ አመለካኚት አልነበሚም። ስለዚህም በሹመት ስም ኚአዲስ አበባ እንዲወጡ ለማድሚግ ወደ ምዕራብ ኢትዮጵያ ጊምቢ አስተዳዳሪ ሆነው መሟማ቞ው ቢነገራ቞ውም ሹመቱን ተቃውመውት ነበር። ኚዚያም በወቅቱ በወሎ ክፍለ አገር በተኹሰተው ድርቅ ሳቢያ ለቜግር ተጋልጠው ዚነበሩት ሰዎቜ ቀያ቞ውን እዚተዉ ወደ አዲስ አበባ ለመምጣት በሚሞክሩበት ወቅት ባለስልጣናት ሚሃቡ እንዳይታወቅ ጥሚት ማድሚጋ቞ውን ዚተመለኚቱት ፕሮፌሰር መስፍን ቜግሩን ለሕዝቡ ለማሳወቅ ዚቻሉትን አድርገዋል። በዚህም ሚሃቡ ያስኚተለውን ጉዳትና ለቜግር ዚተዳሚጉትን ሰዎቜ ዚሚያሳይ ዚፎቶግራፍ ኀግዚቢሜን በዩኒቚርስቲው ውስጥ ላለው ዚመምህራን ማኅበር አቀሚቡ። በዚህም ሳያበቁ ኚተለያዩ ሰዎቜ እርዳታን በማሰባሰብ በሚሃብ ለተጎሳቆሉት ሰዎቜ ለማድሚስ ጥሚት ማድሚጋ቞ው በቅርብ ዚሚያውቋ቞ው ሰዎቜ ይመሰክራሉ። አንዳንዶቜ እንደሚሉትም ፕሮፌሰር መስፍን ድርቁንና ዹተኹተለውን ሚሃብ በተመለኹተ ሌሎቜ እንዲያውቁት በማድሚግ በኩል ቀዳሚ ኹመሆናቾው ባሻገርፀ ዚንጉሡ አስተዳደርን ኋላ ላይ ለውድቀት ዚዳሚገው ዚተማሪዎቜ ጥያቄና እንቅስቃሎ ተጚማሪ ምክንያት ለመሆን በቅቷል ይላሉ። ወታደራዊው ደርግ ዚንጉሡን አስተዳደር አስወግዶ ወደ ስልጣን ኚመጣ በኋላ ለበርካታ ሰዎቜ ዕልቂት ምክንያት ዹሆነውን ዹወሎ ክፍለ አገር ሚሃብን በተመለኹተ ዚሚያጣራው መርማሪ ኮሚሜን ውስጥም አባል ሆነው ሰርተዋል። በደርግ ዘመን አብዛኘውን ጊዜያ቞ውን በአዲስ አበባ ዩኒቚርስቲ ውስጥ በማስተማር ያሳለፉ ሲሆንፀ በአገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል ዹነበሹው ዚእርስ በርስ ጊርነት እዚበሚታ በሄደበት ጊዜ ዹነበሹው መንግሥት ቜግሮቜ ኚቁጥጥር ውጪ ኹመሆናቾው በፊት ሰላማዊ መፍትሄ እንዲፈለግ ኚሌሎቜ ሰዎቜ ጋር በመሆን ጥሪ ሲያቀርቡ ነበር። ኚዚያም ወታደራዊው መንግሥት በአማጺያኑ ኃይሎቜ ተሾንፎ ኚስልጣን ሲወገድና ኢህአዎግ አገሪቱን በተቆጣጠሚ በአጭር ጊዜ ውስጥ ዚኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶቜ ጉባኀ (ኢሰመጉ) ዚተባለ ድርጅት በማቋቋም በአገሪቱ ስለሚፈጞሙ ዚሰብአዊ መብቶቜ ጥሰት ክትትል ማድሚግና ሪፖርቶቜን ማውጣት ጀመሩ። ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ለሹጅም ዓመታት ኢሰመጉን በሊቀመንበርነት በመሩባ቞ው ጊዜያት በተለያዩ ዚአገሪቱ ክፍሎቜ በተለይ ዚመንግሥት ኃይሎቜና ባለስልጣናት ዹሚፈጾሙ ሪፖርቶቜን ሲያወጡ ቆይተዋል። ብዙ ዚተባለለትና ኚባድ ቀውስን አስኚትሎ ዹነበሹው ዹ1997ቱ ምርጫ ሊካሄድ በተቃሚበበት ጊዜም ዚቀስተ ዳመና ንቅናቄ ለማኅበራዊ ፍትህ (ቀስተ ዳመና) ዚተባለ ዚፖለቲካ ፓርቲ ኚእነ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ኚሌሎቜም ጋር እንዲመሰሚት አድርገዋል። ይህም ፓርቲ በኋላ ላይ በምርጫው ላይ ግዙፉን ኢህአዎግን በመገዳደር በኩል ትልቅ ሚና ዹነበሹውን ቅንጅት ለአንድነትና ለዎሞክራሲ (ቅንጅት) ዚተባለውን ጥምሚት ኚሌሎቜ ፓርቲዎቜ ጋር ለመመስሚት ቜሏል። በዚህ ሂደት ውስጥም ፕሮፌሰር መስፍን ዹጎላ ሚና እንደነበራ቞ው ይነገራል። ምንም እንኳን ፕሮፌሰር በምርጫው ላይ ተወዳዳሪ ሆነው ባይቀርቡም በሚደሹጉ ዚምርጫ ክርክሮቜ ላይ ቀርበው ዚፓርቲያ቞ውን ዓላማ በማብራራት ተሳታፊ ነበሩ። በኋላም ኚምርጫው ውጀት ጋር በተያያዘ በተፈጠሹው ውዝግብና ሳቢያ መንግሥት ዚቅንጅት አመራሮቜን ሲያስር ፕሮፈሰር መስፍንም ለእስር ተዳርገው ነበር። ይህ እስር ግን ዚመጀመሪያ቞ው አልነበሹም ቀደም ሲልም በተለያዩ ጊዜያት ታስሚው ነበር።
news-56027522
https://www.bbc.com/amharic/news-56027522
ዚኢትዮጵያ ምርጫ 2013፡ ዚትኞቹ ፓርቲዎቜ ጠንካራ ተፎካካሪ ሊሆኑ ይቜላሉ?
በግንቊት ወር መጚሚሻና በሰኔ ወር መጀመሪያ ኚትግራይ ክልል ውጪ በመላው ኢትዮጵያ ለማካሄድ በታቀደው 6ኛው አገራዊ ምርጫ 52 ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜ እንደሚሳተፉ ይጠበቃል።
ቢቢሲ ዚተለያዩ ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜን ዹኋላ ታሪክ፣ ዚመሪዎቻ቞ውን ተጜዕኖ ፈጣሪነት እና አሁናዊ ዚፖለቲካ እንቅስቃሎዎቜን መነሻ በማድሚግ በፌዎራሉና በክልሎቜ እንዲሁም በኹተማ መስተዳድሮቜ ምክር ቀቶቜ ድምጜ ዚማግኘት እድል ሊኖራ቞ው እንደሚቜል ዚሚገመቱ ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜን እንደሚኚተለው ዘርዝሯል። ፓርቲዎቹ ዚተዘሚዘሩት በእንግሊዘኛ መጠሪያ቞ው ሆሄያት ቅደም ተኹተል መሠሚት ነው። ዚአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ /አብን/ አብን ሚዥም ዚፖለቲካ ዚትግል ታሪክ ባይኖሚውም በወቅቱ ዚኢትዮጵያ ፖለቲካ መድሚክ ውስጥ ተጜዕኖው ቀላል ዚሚባል አይደለም። በብሔር ተኮር ዚፓለቲካ እንቅስቃሎ ዚአማራ ብሔርተኝነትን በመወኹል ዚሚንቀሳቀሰው አብን ዹተመሠሹተው በ2010 ዓ.ም ነው። ንቅናቄው ዋነኛ ዓላማዬ "ዚአማራ ህዝብን ጥቅምና መብት ማስኚበር ነው" ዹሚል ሲሆን ኚምስሚታው በኋላ ባሉት ሊስት ዓመታት ጎልቶ መምጣት ቜሏል። ፓርቲው በአማራ ክልል በወጣቱ ዘንድ ተቀባይነት እንዳለው ይታመናል። በክልሉ በርካታ ስፍራዎቜም ቢሮዎቜን ኚፍቶ ይንቀሳቀሳል። ኚአምስት ወራት በኋላ በሚካሄደው ምርጫ ጠንካራ ተፎካካሪ ሆነው ኚሚቀርቡ ፓርቲዎቜ መካኚል አብን አንዱ እንደሚሆን ይጠበቃል። በቅርቡ ኚአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ቆይታ ዚነበራ቞ው ዹንቅናቄው ሊቀ መንበር አቶ በለጠ ሞላፀ ለምርጫው ሰፊ ቅድመ ዝግጅት በማድሚግ ላይ መሆናውን ገልጞዋል። "በሕዝብ ለመዳኘትና ውጀቱን በጾጋ ለመቀበል" ዝግጁ ስለመሆና቞ውም ተናገሚዋል። አብን ኚአማራ ክልል ውጪም ዚአማራ ተወላጆቜ በብዛት በሚኖሩባ቞ው በተለያዩ ዚኢትዮጰያ ክፍሎቜ ጜህፈት ቀቶቜን እያደራጀ ሲሆን ይህም በምርጫው ጠንካራ ተፎካካሪ ሊያደርገው እንደሚቜል ይታመናል። ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ባልደራስ በቀድሞው ጉምቱ ጋዜጠኛ እና ዚመብት ተሟጋቜ በዛሬው ፖለቲኚኛ አቶ እስክንድር ነገ ዚሚመራ ፓርቲ ነው። አቶ እስክንድር በኢትዮጵያ ነጻ ፕሬስና ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ ተሳትፎ አለው። ባልደራስ "ዚአዲስ አበባን ጥቅም ለማስኚበር" ያስጀመሚው እንቅስቃሎ ሲሆንፀ እንቅስቃሎው አድጎ አዲስ አበባን መሠሚት በማድሚግ ወደ ፓለቲካ ፓርቲነት አድጓል። ዚአርቲስት ሃጫሉ ሁንዎሳን ግድያ ተኚትሎ ኹተፈጠሹው ሁኚት ጋር በተያያዘ መሪው አቶ እስክንድር ዚታሰርበት ባልደራስፀ በኹተማ አስተዳደሩ ይሰራሉ ያላ቞ውን 'ሕገ ወጥ' ተግባራት እንደሚታገል ሲገልጜ ቆይቷል። ባልደራስ በተለያዩ ወቅቶቜ ዚሚጠራ቞ው ጋዜጣዊ መግለጫዎቜና ሰልፎቜ ግልጜ ባልሆኑ ምክንያቶቜ ሲሰሚዙ መነጋገሪያ ሆኖ ቆይቷል። ፓርቲው በአዲስ አበባ በአጭር ጊዜ ውስጥ በፈጠሹው ተጜዕኖ እና አቶ እስክንድር በፖለቲካው ውስጥ ባለው 'ዹገዘፈ' ስም ምክንያትፀ ባልደራስ በመጪው ምርጫ አዲስ አበባ ላይ ጠንካራ ተፎካካሪ ሊሆን እንደሚቜል ይገመታል። ዚኢትዮጰያ ዜጎቜ ለማኅበራዊ ፍትህ /ኢዜማ/ ኢዜማ በምርጫ 97 ተሳትፏ቞ው ዚታወቁ እውቅ ፖለቲኚኞቜን ያቀፈ ነው። በመላው አገሪቱ ሊባል በሚያስቜል መልኩ ኹ400 በላይ ዚምርጫ ወሚዳ ጜህፈት ቀቶቜን ኚፍቷል። ኚብሔር ፖለቲካ በተለዹ "ዜግነትን መሰሚት ያደሚገ" ፖለቲካን እንደሚያራምድ ዹሚገልጾው ፓርቲውፀ በኢትዮጵያ ማህበራዊ ፍትህን ማሚጋገጥ ቀዳሚ ግቀ ነው ይላል። ፓርቲው ኚሌሎቜ ተቃዋሚ ፓርቲዎቜ በተለዹ መልኩፀ በአገሪቱ ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊና ዚውጪ ግንኙነት ጉዳዮቜ ላይ ዚሚያተኩሩ 40 ዚፖሊሲ ሰነዶቜን እንዳዘጋጀም ገልጿል። ኚወራት በፊት በአዲስ አበባ ሕገ ወጥ ነው ያለውን ዚመሬትና ዚጋራ መኖሪያ ቀቶቜ ወሚራ በተመለኹተ ያወጣው ዚጥናት ሪፖርት ዚበርካቶቜ መነጋገሪያ ሆኖ ነበር። በ97ቱ ምርጫ ተጜዕኖ ፈጣሪ ኚነበሩ ፖለቲኚኞቜ መካኚል ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ዚፓርቲው መሪፀ አቶ አንዱአለም አራጌ ደግሞ ዚፓርቲው ምክት መሪ ና቞ው። ኹጠቅላይ ሚንሰትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ወደ ሥልጣን መምጣት ቀደም ብሎ ዹጎላ ዚፖለቲካ እንቅስቃሎ ዹነበሹውን ሰማያዊ ፓርቲ ሲመሩ ዚነበሩት አቶ ዚሺዋስ አሰፋን ሊቀ መንበር ያደሚገው ኢዜማፀ 6 ፓርቲዎቜ ኚስመው ዚመሰሚቱት ነው። ኚእነዚህ ውስጥ ነፍጥ አንግቩ ሲታገል ዹነበሹው አርበኞቜ ግንቊት 7 ተጠቃሜ ነው። ይህ ድርጅት በውጪና በአገር ውስጥ ቀላል ዚማይባል ደጋፊዎቜ እንዳሉት ይገለጻል። ታዲያ ዹዚህ ሁሉ ድምር ኢዜማን በምርጫ 2013 ለውጀት ኹሚጠበቁ ፓርቲዎቜ አንዱ አድርጎታል። ዹኩጋዮን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር/ኊብነግ/ ኊብነግ በፖለቲካ እንቅስቃሎ ውስጥ ሚዥም እድሜ ያስቆጠሚ ድርጅት ነው። ኹ37 ዓመታት በፊት ዹተመሠሹተው ኊብነግ መሰሚቱን በሶማሌ ክልል ያደሚገ ነው። ኹ1986 እሰኚ 2010 ዓ. ም በትጥቅ ትግል ዹቆዹው ዹኩጋዮን ብሔራዊ ነጻነት ግንባርፀ ኹ1983-87 ዹነበሹው ዚሜግግር መንግሥት አካል ነበር። በ1984 በተኹናወነው ዚአካባቢ ምርጫ 87 በመቶ ዹሚሆነውን ድምጜ በማሾነፍ ዚሶማሌ ክልልን ለሁለት ዓመታት አስተዳድሯል። ሆኖም በኊብነግና ማዕኹላዊ መንግሥቱ መካኚል ዹተፈጠሹው ቅራኔ ግንባሩ ወደ ትጥቅ ትግል እንዲገባ አድርጎታል። በዚህም በሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት 'አሞባሪ' ተብሎ ተፈርጆ ነበር። በ2010 ዹጠቅላይ ሚኒሰትር ዐብይን ወደ ሥልጣን መምጣት ተኹተሎ ኚሜብር መዝገብ ተሰርዞ በሕጋዊ ፓርቲነት ተመዝግቧል። ዚሶማሌ ክልል ሕዝቊቜ ራስን በራስ ዚማስተዳደር መብት ማሚጋገጥ ዋነኛ ዓላማዬ ነው ዹሚለው ፓርቲውፀ በቀጣዩ ምርጫ በሶማሌ ክልል ብርቱ ተፎካካሪ እንደሚሆን ይጠበቃል። ዚፓርቲው አመራሮቜ በ2011 ወደ አገር ቀት በገቡበት ወቅት ዹተደሹገላቾው 'ሞቅ' ያለ አቀባበል ግንባሩ አሁንም ያለውን ተቀባይነት ብቻ ሳይሆን ለቀጣዩ ምርጫ ያለውንም ተስፋ ዚሚያመላክት ይመስላል። ዚኊሮሞ ፌዎራላዊ ኮንግሚስ /ኊፌኮ/ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ዚሚዥም ዘመን ተሳትፎ ያላ቞ው መሚራ ጉዲና (ፕሮፌሰር) ዚሚመሩት ኊፌኮፀ ኹዚህ ቀደም በተካሄዱ ምርጫዎቜ ተሳታፊ ነበር። ሊቀ መንበሩ መሚራ (ፕሮፌሰር) በፌዎራሉ ዹፓርላማ አባል ሆነው በቆዩባ቞ው ዓመታት በፓርላማ ውስጥ በሚሰጧቾው አስተያዚቶቜ በበርካቶቜ ዘንድ ይታወሳሉ። በተደጋጋሚ ዚታሰሩ ሲሆን ለመጫሚሻ ጊዜ ኚእስር ሲፈቱ በርካታ ደጋፊዎቻ቞ው አደባባይ ወጥተው ደስታ቞ውን ገልጞዋል። በተመሳሳይ አሁን እስር ቀት ዚሚገኙት ምክትል ሊቀ መንበሩ አቶ በቀለ ገርባ ዚዳበሚ ዚፖለቲካ ልምድ ያላ቞ው ና቞ው። በኊሮሚያ በተለይም በወጣቱ ዘንድ ተቀባይነት ያለው አቶ ጀዋር መሐመድ ፓርቲውን መቀላቀሉ ዚኊፌኮን ተጜዕኖ ኹፍ እንዳደሚገው ይታመናል። መሚራ (ፕሮፌሰር)፣ አቶ በቀለ እና አቶ ጀዋር ኚአንድ ዓመት ገደማ በፊት በኊሮሚያ ዚተለያዩ አኚባቢዎቜ በተጓዙበት ወቅት ዹተደሹገላቾው አቀባል ኊፌኮ በምርጫ 2013 ጠንካራ ተፎካካሪ ሆኖ እንደሚቀርብ ያመላኚተ ነበር። በኢትዮጵያ ዚምርጫ ስርዓት ልምድ ያካበቱ ጉምቱ ፖለቲኚኞቜን መያዙ [ምንም እንኳን በእስር ላይ ዹሚገኙ ቢኖሩም] ኊፌኮን በቀጣዩ ምርጫ ለውጀት ዹሚጠበቅ ፓርቲ አድርጎታል። ዚኊሮሞ ነጻነት ግንባር/ኩነግ/ ኚተመሠሚቱ ብዙ ዓመታት ካስቆጠሩት ዚፖለቲካ ድርጅቶቜ መካኚል አንዱ ኩነግ ነው። በበርካታ ዚኊሮሚያ አኚባቢዎቜ ዚነጻነት አርማ ተደርጎ ዹሚቆጠሹው ኩነግ በ1965 ዓ. ም ነበር ዚተመሠሚተው። ግንባሩ ዹ1983ቱ ዚሜግግር መንግሥት አካል ዹነበሹ ሲሆን ብዙም ሳይቆይ ግን አማጺ ቡድን ሆኖ ጫካ ገባ። እናም ለዓመታት በትጥቅ ትግል ቆይቶ ኹ3 ዓመታት በፊት ዹጠቅላይ ሚንስትር ዐብይን ወደ ሥልጣን መምጣት ተኚትሎ ወደ አገር ቀት ተመልሷል። ኚበርካታ ዓመታት ዚትጥቅ ትግል በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በምርጫ ለመወዳደር ዹተዘጋጀው ፓርቲውፀ በ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ኹፍተኛ ግምት ኚሚሰጣ቞ው ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜ አንዱ ነው። ፓርቲው በውስጣዊ ቜግሮቹ እና በፓርቲ አመራሮቜ እስር ታጅቊ በኊሮሞ ሕዝብ ዘንድ ያለውን ዹገዘፈ ስምና ዚትጥቅ ትግል ታሪክ ይዞ ምርጫው እዚተጠባበቀ ነው። ፓርቲው በመንግሥት ይደርስብኛል በሚለው ጫናና በአመራሮቹ መካኚል ዹተፈጠሹው ቅራኔ በምርጫ ተሳትፎው ላይ ተጜዕኖ ካላደሚገበት በስተቀር በኊሮሚያ ክልል ብርቱ ተፎካካሪ መሆኑ ዹሚቀር አይመስልም። ብልጜግና ፓርቲ ብልጜግናፀ ያለፉትን 5 አገራዊ ምርጫዎቜ 'አሞንፊያለሁ' ያለውና አገሪቱን ኚሁለት አስርት ዓመታት በላይ ሲያስተዳድር ዹቆዹው ዚኢትዮጵያ ሕዝቊቜ አብዮታዊ ዎሞክራሲያዊ ግንባር /ኢሕአዎግ/ ውጀት ነው። ብልጜግና ኚኢሕአዎግ መክሰም በኋላ አንዳንድ ለውጊቜን እንዳደሚገ ቢነገርምፀ ህወሓት ብቻ ዚተቀነሰበት ዚቀድሞው ኢሕአዎግ ነው ዹሚሉ በርካቶቜ ና቞ው። ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ ኚህወሓት ውጪ ግንባሩን ኹ 'አጋሮቹ' ጋር በመዋሃድ ብልጜግና ዹተሰኘ አዲስ ፓርቲ ፈጥሚዋል። ዚቀድሞውን ኢሕአዎግ ሀብት እና ንብሚቶቜ ጠቅልሏል። አብዮታዊ ዲሞክራሲ ጜንሰ ሃሳብን ሜሮ መደመር በተሰኘ ዚፓርቲው ፕሬዝዳንትና በአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ እሳቀ ተክቷል። ፓርቲው በመላው ሀገሪቱ አለኝ ኹሚለው በሚሊዮን ዹሚቆጠር አባላት እንዲሆም ሹጅም አመታት ያሰቆጠር ጠንካራ መዋቅር በቀጣዩ ምርጫ ተጠባቂ እንዲሆን አርጎታል። ዚፓርቲው ፕሬዝዳንት ዐቢይ (ዶ/ር) አምጥተውታል ዚሚባለው ለውጥና በአገሪቱ ዚተለያዩ አኚባቢዎቜ ያላ቞ው ድጋፍ እንዲሁም ፓርቲው በክልሎቜና ኹተማ መስተዳደሮቜ ተጜዕኖ ፈጣሪ አመራሮቜን መያዙ በምርጫው ጠንካራ ተፎካካሪ ሆኖ እንዲገመት አድርጎታል። ኹላይ ዚተጠቀሱት አንዳንድ ፓርቲዎቜ በተለያዩ ምክንያቶቜ በቀጣዩ ምርጫ ላይሳተፉ እንደሚቜሉ እዚገለጹ ቢሆንም ዚፖለቲካ ፓርቲዎቹ ይኖራ቞ዋል ተብሎ ዹሚጠበቀው ፍክክር ምርጫ 2013 ኚባለፉት በተሻለ ዓይን ዚሚጣልበት እንዲሆን አድርጎታል።
news-52789443
https://www.bbc.com/amharic/news-52789443
በኮሮናቫይሚስ ምክንያት በማያቋርጥ ዚጫጉላ ሜርሜር ላይ ያሉት ሙሜሮቜ
ትውውቃ቞ው ኚስምንት ዓመታት በፊት ነበርፀ ዹ36 ዓመቱ ካሊድና ዹ35 አመቷ ፔሪ።
ካሊድና ፔሪ ዚጫጉላ ጊዜያ቞ውን ለማሳለፍ ወደ ሜክሲኮ ያቀኑት መጋቢት ላይ ነበር ለስምንት ዓመታት በጓደኝነት ኚቆዩ በኋላ ቀተሰብ ዘመድ ወዳጅ በተሰበሰበት፣ በግብጿ መዲና ካይሮ ድል ባለ ድግስ ተጋቡ። ሠርጋቾው ዚካቲት 27/2012 ዓ.ም ዹነበሹ ሲሆን ኚጥቂት ቀናት በኋላም ለጫጉላ ሜርሜራ቞ው ወደ ሜክሲኮዋ ኹተማ አቀኑ። ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ ገና እዚጀመሚ ዚነበሚበት ወቅት ኹመሆኑ ጋር ተያይዞ መቀመጫ቞ውን ዱባይ ያደሚጉት ሙሜሮቜ ልክ እንደ በርካቶቜ ስጋትም አልገባ቞ውም። ምንም እንኳን ሙሜሮቹ ዹተጹናነቁ ስፍራዎቜን ቢያስወግዱም ቫይሚሱ በሌሎቜ አገራት ላይ ባለመዛመቱ ጉዞዎቜ ሊሰሹዙ ይቜላሉ ዹሚለው ሃሳብ በጭራሜ ያላለሙት ጉዳይ ነው። ዚጫጉላ ጊዜያ቞ውን አጠናቀው ወደ ቀታ቞ው ለመመለስም መጋቢት አስር ቀን በዩናይትድ አሚብ ኀምሬትስ አዹር መንገድ ቲኬታ቞ውን ቆሚጡ። ዚገዙትም ቲኬት መሞጋገሪያ቞ው በቱርክ፣ ኢስታንቡል ነበር። "አውሮፕላን ውስጥ ሆነን ኢንተርኔት ማግኘት ቜለን ነበር። ኚቀተሰቊቻቜንም መልዕኚት ማግኘት ቻልን። ዱባይ እንዎት ልትደርሱ ነው? ዹውጭ አገር ዜጎቜ ወደ ዱባይ እንዳይገቡ መመሪያ ወጥቷል" ዹሚሉ ዜናዎቜን ፔሪ ማንበቧን ታስታውሳለቜ። ሆኖም በአውሮፕላን ውስጥ እያሉ ወደ ዱባይ መግባት እንደሚቜሉ አስበው ነበር። ነገር ግን ኢስታንቡል ላይ ወደ ዱባይ ለመሳፈር ሲሞክሩፀ መሳፈር እንደማይቜሉ ተነገራ቞ው። ልክ ኚሜክሲኮ እንደተነሱ ነው ዱባይ መመሪያውን መተግበር ዚጀመሚቜው። በቱርክ ያለው ዹጉዞ ክልኹላ ሁሉንም ዕቅድ አጚናገፈባ቞ው። በአዹር ማሚፊያውም ለሁለት ቀናት ያህል ለማደር ተገደዱ። ቱርክ ያሚፉት ለመሞጋገሪያ በመሆኑም ህጋዊ ዹሆነ ዹይለፍ ወሚቀት (ቊርዲንግ ባስ) አልነበራ቞ውም። ዚመፀዳጃ ቀት ወሚቀቶቜ፣ ልብሶቜን መሞመት እንዲሁም ሻንጣ቞ውንም ማግኘት አልቻሉም። ኚዱባይ በተጚማሪ አማራጭ ብለው ያሰቧትም ግብጜም ማንኛውንም ጉዞ ማገዷን ተኚትሎፀ ሌላ እቅድ ማሰብ ነበሚባ቞ው። ስለዚህም ግብጻውያንን ያለ ቪዛ ዚሚያስገቡ አገራትን በጉግል በኩል መፈለግፀ ይሄ ብቻ አይደለም በሚራስ አላቾው ወይ ዹሚለውንም ማጣራት እንደነበሚባ቞ው ፔሪ ታስሚዳለቜ። አማራጩም አንድ ብቻ ነበር! ዚማልዎቪስ ደሎት። በህንድ ውቅያኖስ ተኚበበው፣ በነጭ አሞዋና፣ አይንን በሚስብ ዚመሬት አቀማመጣ቞ው ዚማልዎቪስ ደሎቶቜ በዓለም ላይ ኚሚያስደንቁና ልብን ኹሚሰርቁ ውብ ዚተፈጥሮ ቊታዎቜ መካኚል ይጠቀሳሉ። ካሊድና ፔሪ ዚጫጉላ ጊዜያ቞ውን ለማሳለፍ ሜክሲኮን ኚመምሚጣ቞ው በፊት ዚማልዎቪስ ደሎቶቜምም አስበዋ቞ው ነበር። በዚህ ወቅት ግን ዚተፈጥሮ ውበትን ዚታደለው ዚውቅያኖስ ዳርቻ ወይም ደሎቶቹ ላይ መዝናናት መቻላ቞ው አይደለም ዚፈለጉት ትንሜ ም቟ትን ብቻ ነው። ለሁለት ቀናትም ያህል በአዹር ማሚፊያ ወንበሮቜ ላይ ሲያድሩ ስለነበርም ትንሜ እፎይታን ፈጠሚላ቞ው። "ማልዎቪስ እንደደሚስን ደስታቜንን መቆጣጠር አልቻልንም። በደስታም ተያዚን ቢያንስ ኹአዹር ማሚፊያ ወንበሮቜ ላይ መተኛትን ተገላግለን በአልጋ ላይ መተኛት መቻላቜን ትልቅ ነገር ነው" በማለት ዚ቎ሌኮም ኢንጅነር ዹሆነው ካሊድ ይናገራል። ኹዚህም በተጚማሪ ሻንጣ቞ውን ማግኘታ቞ው ጭንቀታ቞ውን ቀለል አደሚገላ቞ው። ሆኖም ቜግሮቻ቞ው በሙሉ አልተቀሚፉም። "ኹፍተኛ ዹሆነ ዚገንዘብ ጫና ሊደርስብን እንደሚቜልም ማሰቡ በራሱ ዚራስ ምታት ነው ዚሆነብንፀ እዚህ ሆነን ሥራቜንን መስራት አንቜልም። ላፕቶፕም አላመጣንም" ትላለቜ ሚዲያ ውስጥ ዚምትሰራው ፔሪ "በጫጉላ ሜርሜር ላይስ ማን እሰራለሁ ብሎ አስቊ ላፕቶፕ ይይዛል?" በማለት ትጠይቃለቜ ባልና ሚስቱ ደሎቶቹ ላይ ዚሚያርፉበት ሪዞርትም ሲደርሱ ዹተወሰኑ እንግዶቜ ብቻ ዚነበሩ ሲሆንፀ እነሱም ወደ ዚአገራ቞ው ሊመለሱ ጥቂት ቀናት ብቻ ዚቀራ቞ው ነበሩ። በርካታዎቹ እንግዶቜ በጥቂት ቀናት ውስጥ ሆቮሉን ለቀው ወደዚአገራ቞ው ሲመለሱፀ ሪዞርቱ ሊዘጋ እንደሆነ ለባልና ሚስቱ ተነገራ቞ው። እንደገና ወደ ሌላ ደሎት፣ ሌላ ሆቮል ቢይዙም በተመሳሳይ ይሄኛውም ሆቮል ተዘጋ። ቜግራ቞ውንም ዚተሚዳው ዚማልዎቪስ መንግሥት ተባብሯ቞ው ኊልሁቬሊ በምትባል ደሎት ላይ በምትገኝ ሪዞርት ውስጥ ነው ያሉት። ባለስልጣናቱ ሪዞርቱ እንዲኚፈት ኚማድሚግ በተጚማሪ ዚሚያርፉበትንም ዋጋ ስለቀነሰላ቞ው ሙሜሮቹ ባለስልጣናቱ እያደሚጉላ቞ው ያለውን ትብብር ኚልብም አመስግነዋል። ኹዚህም በተጚማሪ ዹሆቮሉ ሠራተኞቜም እዚተንኚባኚቧ቞ው መሆኑንም አስሚድተዋል። "በተቻለ መጠን ሁሉም ዹሆቮሉ ሠራተኞቜ ዚተሻለ ጊዜ እንዲኖሚን ይጥራሉ። ማታ ማታም ሙዚቃ ያጫውቱልናልፀ ሁልጊዜም ዲጄ አለ። አንዳንድ ጊዜም ሙዚቃ እዚተጫወተ ማንም ዚሚደንስ ስለሌለ ትንሜ እንሳቀቃለን" በማለት ካሊድ ይናገራል። በሪዞርቱ ሰባ ያህል ዚጫጉላ ጊዜያ቞ውን ዚሚያሳልፉ እንግዶቜ ቢኖሩም ልዩነቱ ፔሪ እንደምትለው " እነሱ ዚማልዎቪስ ደሎትን ለጫጉላ ሜርሜራ቞ው መርጠውት ነው። እኛ ግን አልመሚጥነውም" ብላለቜ። በአጠቃላይ በማልዎቪስ 300 ቱሪስቶቜ ዹሚገኙ ሲሆንፀ በአሁኑ ወቅት ደሎቷ አዳዲስ እንግዶቜ እንዳይገቡ ኚልክላለቜ። ምንም እንኳን ዚማልዎቪስ ደሎት ውብ ቊታ ቢሆንምፀ ተገደው ቢመጡበትም ኹዚህ በባሰ ሁኔታ ሰዎቜ አማራጭ አጥተው ዹኹፋ ቊታም ማሳለፍ እንዳለ ይሚዱታል። ሆኖም ማር ሲበዛም ይመራል እንደሚባለው በአሁኑ ወቅት ዋነኛው ምኞታ቞ው ዚጫጉላ ሜርሜራ቞ው ተጠናቆ ወደ ዱባይ መመለስ ነው። በማልዎቪስ ዚውቅያኖስ ዳርቻው ዚተዝናኑት ለጥቂት ቀናት ብቻ ነው። ምክንያቱም ወቅቱ ዚሞንሱን አውሎ ንፋስ ዚሚነፍስበት በመሆኑ ኃይለኛ ዝናብ ይዘንባል። ኹዚህም በተጚማሪ ዚሚመዳን ፆምንም ለአንድ ወር ያህል እዚፆሙ ነበር። በተቻለ መጠን ወደ ሥራም ለመመለስ ቢሞክሩም ዚኢንተርኔቱ ደካማ መሆን ስብሰባዎቜን እንዳይታደሙ አግዷ቞ዋል ። ወደ መኖሪያ ቀታ቞ው መመለስም ቀላል አይደለም። ዱባይ መኖሪያ቞ውም ብትሆንም ዚዩናይትድ አሚብ ኀምሬትስ ዜጎቜ አይደሉም። ወደ ሌሎቜ ዚባሕሚ ሰላጀው አገራትም መመለስ አልቻሉም። ምናልባት ማድሚግ ይቜሉ ዹነበሹው ግብጜ ዜጎቿን ተመለሱ በምትልበት ወቅት ተመልሰው አስራ አራት ቀናትን በመንግሥት ለይቶ ማቆያ አሳልፈው አገራ቞ው መቀመጥ ነው። ነገር ግን ቀታ቞ው ዱባይ በመሆኑ ግብጜስ ሚዥም ጊዜ ዚሚያስቆያ቞ው ጉዳይ ዚለም። ዚዩናይትድ አሚብ ኀምሬትስ ባለስልጣናት ጋር በመደወልና እንደእነሱና መሰል አጣብቂኝ ውስጥ ዚገቡ ነዋሪዎቜን ቜግር እንዲፈቱም እዚተማፀኑ ነው። በሚራዎቜ ዹማይገኙም ኹሆነ በመንግሥታዊ መመላለሻዎቜም እንዲጓዙ ፈቃድ ዹጠዹቁ ሲሆን ምላሜም በመጠበቅ ላይ ና቞ው። "አዹር መንገዱ ሥራ ዚሚጀምርበትን ቀን ማራዘሙን ዜና ስንሰማ ኹፍተኛ ጭንቀት ውስጥ እንገባለን። ዚሚጠበቅብንን ሁሉ ለማድሚግ ዝግጁ ነን፣ ሆቮልም ይሁን ቀታቜን ለይቶ ማቆያ ውስጥ ግቡ ካሉን እንገባለን" በማለት ፔሪ ተናግራለቜ። ለሁለት ወራት ያህል በሆቮል ውስጥ ያሉት ሙሜሮቜ ወጪያ቞ው እዚናሚ እንደሆነ ቢገባ቞ውም "ቀታቜን እስኚምንመለስ ድሚስ ወጪያቜንን ላንደምር ተስማምተናል። መቌ እንደምንመለስም አናውቅም" ብላለቜ። ምንም እንኳን ኚእነሱ በኹፋ ሁኔታ አጣብቂኝ ውስጥ ዚገቡ ሰዎቜ እንዳሉ ቢሚዱምፀ ነገር ግን ጠብቀውት ዹነበሹው አጠር ያለው ዚጫጉላ ጊዜ መራዘሙ እንዳሰላቻ቞ው አልደበቁም። "በሪዞርቱ ውስጥ ያሉ እንግዶቜ በሙሉ ሄደው እኛ ሁልጊዜም ዚመጚሚሻ ነን። ሠራተኞቹም ቻው በማለት እጃ቞ውን እንዳውለበለቡልን ነው። እነሱም ያሳዝናሉ። ሁለት ጊዜ እንዲህ አይነት አጋጣሚ አጋጥሞናል" ዹሚለው ካሊድ "እንደዚህ አይነት ቊታዎቜ በበርካታ ሰዎቜ እና በደስታ ሊሞላ ይገባ ነበር ሁኔታው ግን እንደዛ አይደለም" ብሏል። አክሎም "ማልዎቪስ ደሎቶቜ ላይ መውጪያ እንዳጣን ለምናውቃቾው ሰዎቜ ስንናገር ብዙዎቜ ኚት ብለው ይስቃሉ። 'ምናለበት እንደናንተ በሆንኩ ደስ ዹሚል ቊታ ነው' ዹሚሉም ብዙዎቜ ናቾው" ዚምትለው ፔሪ " እንደሚታሰበው ቀላልም አይደለም። ደስተኞቜም አይደለንም። በጣም ዚሚያስጚንቅ ሁኔታ ላይ ነንፀ ኚቀተሰባቜን ጋር መሆን ያስደስተናል። በአሁኑ ሰዓት እሱን ለማግኘት ዹማልኹፍለው ነገር ዹለም" ብላለቜ ፔሪ።
news-51388871
https://www.bbc.com/amharic/news-51388871
ለሁለተኛ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ በኮሮናቫይሚስ ዚተጠሚጠሩት ኚቫይሚሱ ነጻ መሆናቾው ተገለጾ
ለሁለተኛ ጊዜ በኮሮናቫይሚስ ዚተጠሚጠሩት አራት ግለሰቊቜ ኚቫይሚሱ ነጻ መሆናቾውን ዚጀና ጥበቃ ሚንስትር አስታወቀ።
ዚኢትዮጵያ ህብሚተሰብ ጀና ኢንስቲትዩት ኚሁለት ቀናት በፊት በኮሮናቫይሚስ ሳይያዙ አይቀሩም ዚተባሉ ሌሎቜ አዲስ አራት ሰዎቜ መገኘታ቞ውን አስታውቆ ነበር። ኚቀናት በፊት በቫይሚሱ ዚተጠሚጠሩት ሶስቱ ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ አንዱ ደግሞ ቻይናዊ ነበር። ዚጀና ጥበቃ ሚንስትር ኚበፌስቡክ ገጹ ላይ እንዳስታወቀው ዚአራቱ ግለሰቊቜ ዹደም ናሙና ወደ ደቡብ አፍሪካ ለምሚመራ ተልኮ ውጀቱ ኚኮሮናቫይሚስ ነጻ መሆናቾው ተሹጋግጧል ብሏል። ኹዚህ ቀደምም በተመሳሳይ መልኩ በቫይሚሱ ሳይያዙ አይቀሩም ዚተባሉ አራት ሰዎቜ ተገኝተው ዹደም ናሙናቾው ወደ ደቡብ አፍሪካ ተልኮ ኚቫይሚሱ ነጻ መሆናቾው መነገሩ ይታወሳል።
51626233
https://www.bbc.com/amharic/51626233
ኹ68 ሺህ በላይ ጥንዶቜ በጳውሎስ ሆስፒታል ዚመካንነት ሕክምና እዚተኚታተሉ ነው
በትዳር ውስጥ ኚመካንነት ጋር በተያያዘ በርካታ አሳዛኝ ታሪኮቜ በዚአካባቢያቜን ይሰማሉ። ሹጅሙን ታሪኳን በአጭሩ ያቀሚብንላት ሎት ልጅ ፍለጋ ያስኚፈላትን ዋጋ እንደሚኚተለው አጫውታናለቜ . . .
በቮክኖሎጂ በታገዘ ሕክምና ዹተወለደ ሕፃን "ሌላ እንዲያገባ ፈቀድኩለት. . . " "ኹምወደው አብሮ አደጌ ጋር ድል ባለ ሠርግ ወዳጅ ዘመድ መርቆን ትዳር መሠሚትን። ደስተኞቜ ነበርን። ዓለማቜን ጎጇቜን ሆነ። በርካታ ዓመታትን አብሚን አሳለፍን። ፍቅራቜን በዙሪያቜን ያሉትን ሁሉ ዚሚያስቀና ነበር። ኑሯቜንም ዚተሳካና ዚተደላደለ። ይሁን እንጂ ዓይናቜንን በዓይናቜን ማዚት አልቻልንም። በመጀመሪያ አካባቢ ዚመደናገጥና ግራ ዚመጋባት ስሜት ውስጥ ገባን። በኋላ ላይ ዚተለያዩ ሕክምናዎቜን ሞኚርን። በእምነታቜንም ዚዘወትር ፀሎታቜን "በልጅ ባርኚን" ሆነ። ሆኖም ሊሆን አልቻለም። ፈልገነው ዹሆነ ይመስል ኚቀተሰብና በዙሪያቜን ካሉ ሰዎቜ "ውለዱ እንጅ" ዹሚለው ምክር ዚሰላምታ ያህል ተደጋገመ። መሾማቀቅ ጀመርን። ጫናው እንደሚወራው ቀላል አልነበሚም። በዚህ ሁኔታ ዓመታትን ገፋን። በጀና ምርመራው ቜግሩ ያለው ኚእኔ እንደሆነ ስሚዳ ደግሞ እጄ በሌለበት ነገር ዚባሰ ጥፋተኝነት ይሰማኝ ያዘ። እሱ ግን እኔን ኚማበሚታታት ባለፈ ምንም ትንፍሜ አይልም "ፈጣሪ ዹፈቀደው ነው ዹሚሆነው" ነበር ዚሚለኝ። እኔ ግን "እኔን ብለህ ያለ ልጅ መቅሚት ዚለብህምፀ ሌላ አግባና ውለድ" ስል ሃሳብ አቀሚብኩለትፀ ኚልቀ ነበር። እሱ ግን "ዚልጅነት ፍቅሚኛዬን ለልጅ ብዬ ጥዬ ለመሄድ ህሊናዬ አይፈቅድልኝም" በማለት በሃሳቀ አልተስማማም። በመካኚላቜን ውዝግብ ተነሳ። ዹኋላ ኋላ አግብቶ ልጅ እንዲወልድና ልጁን ይዞ ወደ እኔ እንዲመጣ አግባብቌው ተስማማ። እርሱም ሌላ አገባ። እኔም ብቻዬን እርሱን መጠባበቅ ጀመርኩ። ሁለት ዓመት ሳይሞላ ዚሎት ልጅ አባት ሆነ። ደስ አለኝ። እርሱ ልቡ እኔ ጋ ነበርና ልጅቷ ልክ ኚአራስ ቀት ስትወጣ "ካንቜ ጋር ይበቃናልፀ ልጄን ስጭኝና ልሂድ" ዹሚል ጥያቄ ያቀርብላታል ለእናትዚው። እርሷም እናት ናትና "ኹፈለክ አንተ ትሄዳለህ እንጂፀ ልጄን እንዎትም ብዬ አሳድጋለሁ" ዹሚል መልስ እንደሰጠቜው ነገሚኝ። ይህንን እንዎት እንዳላሰብነው ይገርመኛል። ራስ ወዳዶቜ ሆነን ነበር። አንዱን በድሎ አንዱን ማስደሰት አይቻልምና ያሰብነው ሳይሆን ቀሚ። እርሱም ልጅ ነበርና ያሰደደውፀ እኔን ትቶ ኹልጁ እናት ጋር ትዳሩን አፀና። አልፈርድበትም። እኔም ቀት ንብሚታቜንን á‹­á‹€ ብቻዬን ቀሚሁ። ዹምወደውን ባሌን በልጅ ምክንያት አጣሁ . . . " ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒዹም ኮሌጅ ታዲያ ይህንን ዚሥነ ተዋልዶ ጀና ቜግር ለመፍታት በሚያዚያ ወር 2011 ዓ. ም ዚመካንነት ሕክምና ማዕኹል አስመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። አገልግሎት መስጠት በጀመሹ አንድ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ኹ60 ሺህ በላይ ጥንዶቜ ዚመካንነት ሕክምና እዚተኚታተሉ መሆናቾውን በሆስፒታሉ ዚሥነ ተዋልዶ ማዕኹሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ቶማስ መኩሪያ ለቢቢሲ ገልፀዋል። ኚእነዚህ መካኚል 1400ዎቹ በቮክኖሎጂ ዚታገዘ ዚመካንነት ሕክምና ለማግኘት ተመዝግበዋል። ቀሪዎቹ ደግሞ ወደዚህ ሕክምና ኚመግባታ቞ው በፊት ሌሎቜ ሕክምናዎቜን በመኚታተል ሂደት ላይ ይገኛሉ። እነዚህ ጥንዶቜ በተለያዚ ኑሮና ዚትምህርት ደሹጃ ላይ ዹሚገኙ ሲሆኑ ኚተለያዩ ዚአገሪቷ ክፍሎቜ ዚመጡ ና቞ው። በቮክኖሎጂ በታገዘው በዚህ ዚመካንነት ሕክምና ኹ70 በላይ እናቶቜ ነፍሰጡር ሆነው በተለያዚ ዚእርግዝና ወራት ላይ ይገኛሉ። 6 ወላጆቜ ወልደው ስመዋል። 8 ልጆቜ ተወልደዋል። አንዲት እናት ሊስት ዚወለደቜ ሲሆን አንዱ ሞቶባታልፀ መንታዎቹ ግን በጥሩ ጀንነት ላይ እንደሚገኙ ሰምተናል። ጥንዶቹ ኹ18 እስኚ 4 ዓመታት በትዳር ውስጥ ቢቆዩምፀ ልጅ ሳያፈሩ ቆይተው አሁን ልጅ ያገኙ ና቞ው። "በዚህ መንገድ እናቶቜ ልጃቾውን ሲያቅፉ በደስታ ያለቅሳሉ። በጋብቻ መሃል ልጅ አላዩም ነበር። ልጅ ይናፍቁ ነበር። ልጅ ለማግኘት በዕምነት ቊታዎቜና ዚባህል መድሃኒት ፍለጋ ሲንኚራተቱፀ ኚማኅበሚሰቡ ዚሚደርስባ቞ው ጫና ቀላል አይደለም። ይህን ሁሉ አልፈው ልጅ ሲያቅፉ ዹተሰማቾው ሊቆጣጠሩት ዚማይቜሉት ዚደስታ ስሜት ነው። በደስታ ሲፈነጥዙ ነው ያዚነው" ይላሉ ዚሆስፒታሉ ዚኮሚዩኒኬሜን ዳይሬክተር አቶ ንዋይ ፀጋዬ። ሕክምናው ዚቅዱስ ጳውሎስ ሚሊኒዹም ሕክምና ኮሌጅ በአገር ውስጥና ኹአገር ውጭ ባስተማራ቞ው ዹአገር ውስጥ ዹሕክምና ባለሙያዎቜ ይሰጣል። ይህ ዹሕክምና አገልግሎት መሰጠት ኚመጀመሩ በፊት ዚተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶቜ መደሹጉንም ዳይሬክተሩ አስታውሰዋል። ሕክምናውን ኚሚሰጡ ዚባለሙያዎቜ ቡድን ዹተወሰኑ አባላት መካንነት ምንድን ነው? ጥንዶቜ ለአንድ ዓመት ዚወሊድ መኚላኚያ ሳይጠቀሙ ቢያንስ በሳምንት ሁለት ጊዜ ወይም ኚዚያ በላይ ዚግብሚ ሥጋ ግንኙነት እዚፈፀሙ ፅንስ መፈጠር ካልቻለ መካንነት እንደሚባል ዶ/ር ቶማስ ይናገራሉ። ዚሎቷ ዕድሜ ደግሞ ኹ35 ዓመት በላይ ኹሆነ እና በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ያለ ወሊድ መኚላኚያ በሳምንት ሁለት ጊዜ እና ኚዚያ በላይ ዚግብሚ ሥጋ ግንኙነት ፈጜመው እርግዝና መፈጠር ካልቻለ ዚመካንነት ቜግር ሊኖር ይቜላል ተብሎም ይታሰባል። ሳይለያዩ ለአንድ ዓመት ዚቆዩ ጥንዶቜ ያለምንም መኚላኚያ ግንኙነት እያደሚጉ ማርገዝ ካልቻሉም እንዲሁ። መካንነት በሎቶቜና በወንዶቜ ላይ ሊኚሰት ይቜላል። በሎቶቜ ላይ ኚዕድሜ ጋር ተያይዞም ሆነ ያለዕድሜ ዹዘር እንቁላል ማለቅ፣ ዚቱቊ መዘጋት እና በአባላዘር በሜታዎቜ በተደጋጋሚ መጠቃት እንዲሁም በሌሎቜ ቜግሮቜ ሊኚሰት ይቜላል። ዚቜግሮቹን መንስዔ በምርመራ በዝርዝር መሚዳት እንደሚቻል ዶ/ር ቶማስ ያስሚዳሉ- ዚቜግሩ መንስዔ እንደ ግለሰቊቹ ስለሚለያይ። አንዳንዎ ሁሉም ነገር ጀናማ ሆኖ እርግዝና ላይፈጠር ይቜላልፀ ይህ ዹማይገለፅ መካንነት [Unexplained Infertility] ይባላል። ይህ ማለት ቮክኖሎጂ ያልደሚሰባ቞ው ቜግሮቜ አሉ ማለት ነው። 20 በመቶ ዹሚሆኑ ጥንዶቜም ይህ ቜግር ያጋጥማ቞ዋል። እነዚህ ጥንዶቜ በቮክኖሎጂ ዚታገዘ ሕክምና ሊደሹግላቾውም ይቜላል። መካንነት በተለይ አፍሪካ ውስጥ ዹተለመደ ቜግር ነው ዚሚሉት ዶ/ር ቶማስፀ በተለይ በአባላዘር በሜታዎቜና በሌሎቜ ኢንፌክሜኖቜ ዚመካንነት ቜግር እንደተንሰራፋ ይናገራሉ። ዶ/ር ቶማስ ዹዓለም ጀና ድርጅት ሪፖርትን ጠቅሰው እንደነገሩንፀ በኢትዮጵያ ኹ15-20 በመቶ ጥንዶቜ ዹዚህ ቜግር ተጠቂ ና቞ው። ሎቷም ሆነ ወንዱ በእኩል ደሹጃ በመካንነት ሊጠቁ ይቜላሉፀ በመሆኑም በማኅበሚሰቡ ሎቷ ላይ ብቻ ጣት ዹሚቀሰሹው በተሳሳተ አመለካኚት መሆኑንም ሳይጠቅሱ አላለፉም። በአውሮፓዊያኑ 2016 ዚወጣው ዚኢትዮጵያ ሥነ ሕዝብና ጀና ዳሰሳ ጥናት እንደሚያሳዚው በተለያዩ ምክንያቶቜ በአምስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ዚውልደት መጠን እዚቀነሰ መሆኑን ያመለክታል። በገጠር ዚሚኖሩ ሎቶቜ በ2000 ኹነበሹው 6.0 ዚውልደት መጠን በ2016 ወደ 5.2 ወርዷል። በኚተሞቜ ደግሞ በ2000 ኹነበሹው 3.0 በ2016 ወደ 2.3 ዝቅ ብሏል። በአጠቃላይ አንዲት ሎት መውለድ ካለባት አማካይ ዚውልደት መጠን በ2000 ኹነበሹው 5.5 በ2016 ወደ 4.6 መቀነሱን ዚዳሰሳ ጥናቱ ያመለክታል። በቮክኖሎጂ ዚታገዘ ዚመካንነት ሕክምና [IVF] ምንድን ነው? ዶ/ር ቶማስ እንደገለፁልን ይህ ዹሕክምና ዘዮ ኚሎቷ እንቁላል ኚወንዱ ደግሞ ዹዘሹ ፈሳሜ በመውሰድ በቀተ ሙኚራ እንዲገናኙ ተደርጎ ፅንስ ኹተፈጠሹ በኋላ ያ ፅንስ ተመልሶ ማህፀን ውስጥ ሲገባ በቮክኖሎጂ ዚታገዘ ዚመካንነት ሕክምና [IVF] ይባላል። ይህ ሕክምና እንደዚ ሰዉ ቢለያይም ኹ40-50 በመቶ ሊሳካ ዚሚቜል ሂደት ነው። እስካሁን ይህን አገልግሎት ለማግኘት ወደ ሆስፒታሉ ኚሄዱት ውስጥ 200 ለሚሆኑ ጥንዶቜ አገልግሎቱ ተሰጥቷል። ኚእነዚህ መካኚል 95ቱ ነፍሰጡር ሆነዋል። መጀመሪያ አገልግሎቱን ካገኙት 8 ሎቶቜ 5ቱ ነፍሰ ጡር ዚነበሩ ሲሆን 3ቱ ወልደዋል። ሁለቱ ግን በመካኚል ውርጃ አጋጥሟ቞ዋል። ይህም ዹሕክምናው ውጀታማነት ኹ50 በመቶ በላይ መሆኑን ያሳያል። ኚተፈጥሯዊው መንገድ በምን ይለያል? ዚእርግዝናው ወራቶቜ ግን ተመሳሳይ ሲሆን እንደ ሁኔታው አሊያም እንደ እናትዚውና ፅንሱ ዚጀና ሁኔታ በቀዶ ሕክምናም ሆነ በምጥ ሊወልዱም ይቜላሉ። ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ይህንን በቮክኖሎጂ ዚታገዘ ሕክምና ሲሰጥ በአገር ውስጥ ዚመጀመሪያው ዚመንግሥት ተቋም ሲሆን አሊክማ ዹተሰኘ አንድ ዹግል ተቋም አገልግሎቱን ሲሰጥ መቆቱን ዶ/ር ቶማስ ይናገራሉ። እርሳ቞ው እንደሚሉት ምንም እንኳን ማኅበሚሰቡ ኚእምነትና ኚባህል ጋር ጥብቅ ቁርኝት ቢኖሚውምፀ ሰዎቜ አሁን አሁን ለመሹጃ ቅርብ በመሆናቾው በቮክኖሎጂው ለመደገፍ ፈቃደኛ ና቞ው። ይሁን እንጂ በሌሎቜ አገራት እዚተሠራበት ያለው እና ኚጥንዶቹ ውጭ ኹሌላ ሎት እንቁላል አሊያም ኹሌላ ወንድ ዹዘሹ ፈሳሜ ወስዶፀ ልጅ ኹተፈጠሹ በኋላ እንደገና ወደ ማህፀን ዚመመለሱ ሕክምና ዚእንቁላል ወይም ዹዘር ፈሳሜ ልገሳ [Egg or Sperm donation] ዹተለመደ አይደለም። አንዳንዎም ደግሞ ዚእናት ማህፀን ጜንስ መያዝ አልቜል ሲል ዹማህፀን ኪራይ ይኖራል። እነዚህ ሕክምናዎቜ ዹሕግ ማዕቀፍ ስለሚያስፈልጋ቞ውና ግንዛቀ መፍጠር ስለሚያስፈልግ አሁን ላይ እዚተሠራበት አለመሆኑን ዶ/ር ቶማስ ገልፀውልናል። ውጭ አገር በመሄድ በኹፍተኛ ወጪ ሕክምናውን ዚሚያደርጉ እንዳሉ ዚሚገልፁት ዶ/ር ቶማስፀ ለወደፊቱ ሕክምናውን ለመስጠት ኚጀና ጥበቃ ሚኒስ቎ር ጋር እዚተነጋገሩ መሆናቾውን ነግሚውናል። እንዲህ ዓይነቱን ዹሕክምና አገልግሎት ለመጀመር ግን ማኅበሚሰቡ ላይ ግንዛቀ መፍጠር ቅድሚያ ዹሚሰጠው ጉዳይ መሆኑንም አስምሚውበታል። "በማኅበሚሰቡ ልጅ መውለድ፣ ቀተሰብ መመሥሚት አንደ ሕይወት ግብ ተደርጎ ዚሚወሰድ በመሆኑፀ መካንነት ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ያስኚትላል" ዚሚሉት ዶ/ር ቶማስፀ "በዚህ ቮክኖሎጂ በታገዘ መልኩም ሆነ በሌላ መልኩ መፍትሔ ሲያገኙ ጥንዶቜ ደስተኛ ይሆናሉ" ይላሉ። ይህ ዹሕክምና አገልግሎት መጀመሩም መልካም ጅምር መሆኑን ይጠቅሳሉ። ቢሆንም ባለው ዚባለሞያና ተቋማዊ አቅም ውስንነት መድሚስ ዚሚቻሉትን ጥንዶቜ ያህል መድሚስ አለመቻሉንም ሳያነሱ አላለፉም። በአንድ ዓመት ኹ1500 በላይ ለሆኑ ጥንዶቜ አገልግሎቱን መስጠት ዚሚያስቜል አቅም አለመኖሩንም ያክላሉ። ዶ/ር ቶማስ አንድ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ኹ68 ሺህ በላይ ጥንዶቜ ወደ አንድ ሆስፒታል ብቻ መምጣቱ ዚሚያስደነግጥ ቁጥር መሆኑን በመግለጜፀ ቀጠሮዬ ሹዘመ ዹሚሉ ቅሬታዎቜን ዚሚያቀርቡ ሰዎቜ በርካቶቜ መሆናቾውን ሳይገልፁ አላለፉም።
48754495
https://www.bbc.com/amharic/48754495
"በዚህ መንገድ መገደላቾው ኹፍተኛ ዚፀጥታ ቜግር መኖሩን ያሳያል" ጄነራል ፃድቃን
ቢቢሲፊ በሃገሪቱ ኹፍተኛ ስልጣን ላይ ያሉናፀ በኹፍተኛ ሁኔታ ዹሚጠበቁ እንደ ጄነራል ሰዓሹ መኮንን እንዲሁም ዚአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር አምባ቞ው መኮንንና ዚሌሎቹም ግድያ ስለ ኃገሪቱ ዚፀጥታና ደህንነት ጉዳይ ዹሚናገሹው አለ። እርስዎ ይህንን እንዎት ነው ዚሚሚዱት ?
ጄነራል ፃድቃን ጄኔራል ፃድቃንፊ ጄኔራል ሰዓሹ መኮንን፣ ጄኔራል ገዛኢ አበራና ዶ/ር አምባ቞ው መኮንን ሌሎቹም በስራ ቊታ቞ው ላይ እያሉ መገደል በጣም ኹፍተኛ ዹሆነ ዚፀጥታ ቜግር እንዳለ ያሳያል። ኢንተለጀንስ አሰባሰብ ላይ ኹፍተኛ ቜግር እንዳለ ነው ዚሚያሳዚውፀ ኹዚህ ቀደም እኔ ዹማውቀው እንኳን ይሄን ያህል ሎራ እዚተሞሚበ አይደለም በግለሰብ ደሹጃ ዹሚደሹጉ ትንንሜ ነገሮቜ ፈጥኖ ይታወቅ ነበር። ቀላል ያልሆነ ዚፀጥታ ቜግር መኖሩን፣ በፀጥታ መዋቅሩ ውስጥ መታዚት ያለባ቞ው ነገሮቜ እንዳሉ ነው ዚሚያሳዚው። ጄኔራል ሰዓሹን ዹገደለው ዚራሱ ዚጥበቃ ኃይል ነው። መኚላኚያ ውስጥ ዚመኚላኚያን ተቋም ዚሚጠብቅ ፀሹ-መሹጃ ዚሚሉት ኃይል አለ። ለእንደነዚህ አይነት ትልልቅ ባለስልጣናት ዚሚመደብ ሰው ዹሚመደበው በዚህ አካል ኚተጣራ በኋላ ነው። ይህ አለመሆኑ ቀላል ያልሆነ ዚፀጥታ ቜግር እንዳለ ያሳያል። ዚፀጥታ ቜግሩ ኚፖለቲካዊ ሁኔታም ጋር ይያያዛል። ቢቢሲፊክልላዊ "መፈንቅለ መንግሥት" አይደለም ፀ በኹፍተኛ አመራሮቜ ላይ ዚተቃጣ ጥቃት ነው ዹሚለው አኚራካሪ ሆኖ እንዳለፀ በአንድ ክልል ፀ በአንድ ፓርቲ ውስጥ በአመራሮቜ መካኚል ዚልዩነት መካሚር ነው ነገሮቜን ወደዚህ ያመራው ዹሚለው ሃሳብ ጎልቶ እዚወጣ ነው። ዚፖለቲካ ልዩነቶቜ መጚሚሻ቞ው እንዲህ ዹሚሆን ኚሆነፀ ስለ ፖለቲካውም ዹሚለው ነገር አለ። እዚህስ ላይ ምን ይላሉ? ጄኔራል ፃድቃንፊ "መፈንቅለ መንግሥት" ነው አይደለም ዹሚለው ክርክር ውስጥ መግባት አልፈልግም። ጉዳዩ በጣም አስቀያሚ ነው። ኹህግ ውጭ ነው። ግን አንድ ግልፅ መሆን ያለበት ነገር አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ባለው ዚፌደራል ስርዓት አንድ ክልል እንኳን ሙሉ በሙሉ ቢቆጣጠሩ ኖሮፀ አንደኛ አንድን ክልል ዚመቆጣጠር አቅማቾው አነስተኛ ነበር ብዬ ነው ዚምወስደውፀ ሁለተኛ ያ እንኳን ቢሳካ በሃገር አቀፍ ደሹጃ ሊኖር ዚሚቜለው ተፅኖ ዹተወሰነ ነበር ብዬ ነው ዚምወስደው። ብጥብጥ አይፈጥርምፀ ቜግር አይፈጥርም ማለት ሳይሆን ዹአገር ዚፖለቲካ ስልጣንን ኚመያዝ አንፃር ግን በእኩል ደሹጃ ዚነሱን ያህል አቅም ያላ቞ው ክልሎቜ አሉ። እነዛ ክልሎቜ ደግሞ ዚራሳ቞ው ዚፀጥታ መዋቅርም አላ቞ው። ዚራሳ቞ው ህገ መንግሥታዊ አወቃቀር አላ቞ው። ኹዛ በላይ ፣ አንድ ክልል ውስጥ ኹሚፈጠር ቜግር በላይ ዚሚያልፍ አይሆንም ነበር ብዬ ነው ዚማስበው። ያም ሆነ ይህ ግን ኹህገ መንግሥቱ ውጭ ዹሆነ በጣም አሚመኔያዊ እርምጃ ነው። ኹዚህ በመለስ ያለው "መፈንቅለ መንግሥት" ነው አይደለም ዹሚለው ክርክር አሁን ለተፈጠሹው ነገር ብዙ ጠቀሜታ ያለው መስሎ አይሰማኝም። ቢቢሲፊአገሪቷ ለውጥ ላይ ነቜ እዚተባለ ቢሆንም ኹፍተኛ ዚብሔር ውጥሚቶቜና ጥቃቶቜንም እዚተመለኚትን ነው። አሁን እያዚነው ያለውን ዚፖለቲካ ባህል እንዎት ያዩታል? • መፈንቅለ መንግሥቱና ዚግድያ ሙኚራዎቜ • ራሱን አጥፍቷል ዚተባለው ዚጄነራል ሰዓሹ ጠባቂ ሆስፒታል እንደሚገኝ ተገለፀ ጄኔራል ፃድቃንፊ አገራቜን ውስጥ ዚፖለቲካ ቜግር እንዳለ ይታወቃል። በተደጋጋሚም ዹሚነገር ጉዳይ ነው። በተለይም አማራ ክልል ውስጥ ፅንፍ ዚያዙ አንዳንድ ቜግሮቜ ያጋጥሙ እንደነበር ይታወቃል። እነዚህ ቜግሮቜ በእኔ አመለካኚት ዹጊዜ ጉዳይ ካልሆነ ፈንድተው መውጣታ቞ው አይቀርም ዹሚል አመለካኚት ነበሚኝ። አሁን ዹሆነው ዚሚመስለኝ ይሄ ነው። በጣም ፅንፈኛ ዹሆነው በኃይል ፍላጎቱን ለመጫን ሲሞክር ዹነበሹው በአማራ ክልል ላይ ብቻ ሳይሆን በሃገር አቀፍ ደሹጃ ይህንን ለማድሚግ ሲያስብ ዹነበሹው ግልፅ ሆኖ ወንጀል በመፈፀም ደሹጃ ወጥቷል። አሁን ዚሚጠሚጠሩት ፀ ተይዘዋል ዚሚባሉትፀ ተገድለዋል ዚሚባሉት ላይ ማተኮር ብቻ ሳይሆን መንግሥት ይሄን ሁኔታ እንደ 'ኊፖርቹኒቲ' እንደ እንደ እድል አይቶ ቜግሮቜን ለመፍታት አመቺ ሁኔታ ተፈጥሮለታል ብዚ አስባለሁ። በብልሃትና በብቃት ኚተመራ ቜግሩን ለመፍታት ጥሩ መነሻ ይሆነዋል ብዚ አስባለሁ። በሌላ በኩል ደግሞ በደንብ ካልተያዘ ነገሮቜ ኚቁጥጥር ውጭ ሊሄዱ ዚሚቜሉበት እድልም መኖሩን ዚሚያሳይ ምልክትም አለ። ይሄንን ተግባር ዹፈፀሙ ዚተወነሱ ስብስቊቜ ፣ በአንድ ዚፀጥታ መዋቅር ብቻ ዚሰራ አይደለም። ኹዛ በላይም ሌላ ስብስብ ይኖራል። ይህ ነገር በተፈጠሚበት ክልልም ሌሎቜ ዚመንግሥት ተቋማትም አደጋው እስኚምን ድሚስ ሊሄድ እንደሚቜል ያሳዚ ነው። ዹተኹፈለው ዋጋ በጣም ኹፍተኛ ነው። ይህንን ዋጋ ኚፍለንፀ መኹፈል ያልነበሚበት ዋጋ ነው። ግን ደግሞ ዚመጣውን አጋጣሚ ለጥሩ ነገር ተጠቅመን ቜግሮቹን አንዮ ለመፍታት ጥሩ መነሻ ሊሆን ይቜላል ብዬ አስባለሁ። ይህ ግን ዝም ብሎ ዚሚመጣ አይደለም። ብልሃት ያለው ሰኹን ብሎ ኚጥላቻ ፖለቲካ ወጥቶ በአማራጭ ዚፖለቲካ ሃሳቊቜ በማመን ዚአመራር ፖለቲካ ይጠይቃል። ይህ ጠንኹር ያለ ስራ ይጠይቃል። ያ ካልሆነ ዹቀደመውን ዚጥላቻ ፖለቲካን እያራገቡ ዚሚኬድ ኹሆነ ቜግሩ ኚቁጥጥር ውጭ ይሆናል። ቢቢሲፊዚፌደራሉ መንግሥት በአማራ ክልል ዹተፈጠሹውን "መፈንቅለ መንግሥት" ብሎታል። "መፈንቅለ መንግሥት" በክልል ደሹጃ ይደሹጋል ወይ? ግቡስ ምን ሊሆን ይቜላል? ጄኔራል ፃድቃንፊ አሁን ባለው ዚኢትዮጵያ አወቃቀር በክልል ደሹጃ እንዲህ አይነት ነገር ሲፈፀም አላውቅም። አልነበሹም ማለት አይደለምፀ ኖሮ ሊሆን ይቜላል እኔ ግን አላውቅም። በኢትዮጵያ አሁን ባለው ዚመንግሥት አወቃቀር ደሹጃ አንድ ክልል ውስጥ ስልጣን እንኳን ቢያዝ አንደኛ ክልሉ ላይ ያለውን ኃይል ሁሉ አጥፍቶ ስልጣን ዚመያዝ እድሉ አነስተኛ ነው። ነገር ግን ስልጣን ቢያዝና ዹክልሉን ኃይል ቢቆጣጠሩ በሃገር አቀፍ ደሹጃ አበቃለት ዚሚባል አይደለም። ዋናው ኃይል ዚፌደራል ስርአቱ ነው። ዚፌደራል ስርአቱ ደግሞ ዚህዝብን ምርጫ ምንም ግምት ውስጥ ሳያስገባ በጉልበት ዹክልሉን ስልጣን ይዞ አስተዳድራለሁ ሊል አይቜልም።ይህ ለክልሉ ህዝብ ስድብ ነው ዚሚመስለኝ። ዹክልሉን ህዝብ ፖለቲካዊ አስተሳሰብና ባህል መናቅ ነው። ዚሚመስለኝ ግን ይህንን ለጊዜው ትተን ቢሳካለት እንኳን ኹክልሉ ያለፈ ቜግር አይሆንም። በክልሉ ላይ ያለውን ቜግር ደግሞ ዚፌደራል መንግሥቱ ኚሌሎቜ ክልሎቜ ጋር በመሆን ሊፈታው ይቜል ዹነበሹ ነው ዚሚመስለኝ። እኔ ምን ሊባል እንደሚቜል ዚያዝኩት ቃል ዚለኝምፀ ዹክልል "መፈንቅለ መንግሥት" ነው ዚሚሆነውፀ ነገር ግን በክልል ብቻ ዚተቃጣ አይደለም። ኹክልል በላይ አልፎ በመኚላኚያም ውስጥ ዹተቀናጀ ስራ እንዲሰራ አድርገዋል። ግን ደግሞ ይሄ ያመጣው ውጀት ዚሚታወቅ ነው። ስለዚህ ያም ሆነ ይህ በሃገር አቀፍ ደሹጃ ስልጣን ለመያዝ አስበው ኹሆነ እሱን ዚሚያሳይ ምልክት ዹለም ። በክልል ደሹጃ ስልጣን ለመያዝ አስበው ነው ሲንቀሳቀሱ ዚነበሩትፀ መኚላኚያ ላይ ዚነበሩትንም ባለስልጣናት እርምጃ ዚወሰዱባ቞ው በክልላቾው ለሚደሹግ ስራ እንቅፋት እንዳይፈጥሩባ቞ው ነገሮቜን ለማዛባት አስበው ዚሰሩት ነው ዚሚመስለው። እስካሁን ድሚስ ባለው መሚጃፀ ይሄ ደግሞ ክልሉ ላይ ለሚሰራው ስራ ማሳለጫ ነው እንጂ ስልጣን ለመያዝ ዚታሰበ አይመስልም። አማራ ክልል ላይ ቢሳካላ቞ው ኖሮ ዹሚሄደው ርቀት አነስተኛ ነው።አማራ ክልሉም ዚመሳካት አቅሙ አነስተኛ ነበር ፀ ዚታዚውም ይሄ ነው። ፍላጎት አልነበራ቞ውም ማለት አይደለምፀ ስላልቻሉ ነው ዚወደቀውፀ ዹአገር ውስጥ ጉዳት በጣም ኹፍተኛ ቢሆንም ኚዚያ በላይ መሄድ ዚሚቜል አልነበሹም ብዚዬነው ዚምወስደው። • ዹሰኔ 16ቱ ጥቃትና ብዙም ያልተነገሚላ቞ው ክስተቶቜ
47871211
https://www.bbc.com/amharic/47871211
ዚኢቲ 302 ዚመጚሚሻዎቹ ስድስት ደቂቃዎቜ
በዓለም አቀፉ አሠራር መሰሚት ዚተለያዩ አካላት ተሳትፈውበታል ዚተባለለት በአደጋው ዚመጀመሪያ ደሹጃ ሪፖርት ላይ ዹቩይንግ 737 ማክስ 8 ዚበሚራ ቁጥር ዚኢቲ 302 ዚመጚሚሻ ደቂቃዎቜ ዚበሚራ ታሪክ ዝርዝር መሹጃ ወጥቷል።
ዚመጀመሪያ ደሹጃ ሪፖርቱ ኹአዹር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎቜ ጋር ዹተደሹገውን ምልልስ፣ በበሚራ መሹጃ መመዝገቢያ ሳጥን ውስጥ ዹተገኘውን መሹጃ እና ኚአብራሪዎቜ ክፍል ውስጥ ዹተቀሹጾውን ድምጜ ዋቢ አድርጓል። ስሙ እንዳይጠቀስ ዹጠዹቀ አብራሪ ዚመጀመሪያ ደሹጃ ሪፖርቱ ላይ በመመስሚት ዚኢቲ 302 ዚመጚሚሻዎቹ ስድስት ደቂቃዎቜ ምን ይመስሉ እንደነበር ለቢቢሲ እንደሚኚተለው አስቃኝቷል። እሁድ ጠዋት መጋቢት 1/2011 ዓ.ም ዚኢትዮጵያ አዹር መንግድ ቩይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን በበሚራ ቁጥር ኢቲ 302 ዹአዹር መንገዱን 8 ሰራተኞቜን ጚምሮ 157 መንገደኞቜን በመያዝ ወደታቀደለት ናይሮቢ ኬንያ ለመብሚር እዚተዘጋጀ ነው። • አውሮፕላኑ 'ኚቁጥጥር ውጪ ሆኖ ነበር' • አደጋው ዚደሚሰበት ቩይንግ 737 ዹገጠመው ምን ነበር ? ጠዋት 02፡37፡34- ዹአዹር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎቜ አውሮፕላኑ በሚራውን እንዲያደርግ እና በ119.7 ሄርዝ ላይ በራዳር አማካኝነት ግንኙነት እንዲፈጜም ፈቃድ ሰጥተው አውሮፕላኑ ለመነሳት ዝግጅቱን ጀመሚ። ዹአዹር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎቜ አንድ አውሮፕላን እንዲነሳ ፍቃድ (ቮክ ኩፍ ክሊራንስ) ኚመስጠታ቞ው በፊት ዚተለያዩ ቅድመ ሁኔታዎቜ መሟላታ቞ውን ያሚጋግጣሉ።ኚነዚህም መካኚል በተመሳሳይ ሰዓት ዚሚነሱ እና ዚሚያርፉ አውሮፕላኖቜ አለመኖራ቞ውን፣ ለመንገደኞቜ ዹሚደሹጉ ዚበሚራ ላይ ደህንነት ገለጻዎቜ መጠናቀቃቾውን እና ዚመሳሰሉትን ያጠቃልላል። ኚዚያም አውሮፕላኑ ተንደርድሮ ወደ ሚነሳበት ዚመንደርደሪያ ጥርጊያ (ራንዌይ) 07R (07ቀኝ ማለት ነው) መጠጋት ጀመሚ። ማብራሪያውን ዹሰጠን አብራሪ እንደሚለው ኹሆነ አውሮፕላን ተንደርድሮ ዚሚነሳበት መንገድ (ራንዌይ) ስያሜውን ዚሚያገኘው በአቅጣጫ መጠቆሚያ መሰሚት ነው። አብራሪው ጚምሮም ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ዚበሚራ ቁጥሮቜም አውሮፕላኑ ወዎት እንደሚበር ይጠቁማሉ። ለምሳሌ ኢቲ3xx ብለው ዚሚጀምሩ ዚበሚራ ቁጥሮቜ መዳሚሻ቞ው ምሥራቅ አፍሪካ ሲሆን ኢቲ5xx ብለው ዚሚጀምሩት ደግሞ ሰሜን እና ደቡብ አሜሪካ እንዲሁም ኢቲ6xx ብለው ዚሚጀመሩ ዚበሚራ ቁጥሮቜ መዳሚሻ቞ው ሩቅ ምሥራቅ ነው። 02፡37፡34 - ዚአውሮፕላኑ ዋና አብራሪ አውሮፕላኑን እያበሚሚ እንደሆነ ገልጿል። 02፡38፡44 - አውሮፕላኑ ኚተነሳ በኋላ ወዲያውኑ ማለትም አውሮፕላኑ ለመነሳት መንቀሳቀስ ኚጀመሚበት ኚአንድ ደቂቃ ኹ10 ሰኚንዶቜ በኋላ ዚአውሮፕላኑ በግራ እና በቀኝ ክንፉ በኩል አንግል ኩፍ አታክ ሮንሰር ዹተመዘገበው መሹጃ ኚተገቢው ውጪ መሆኑን ያሳያል። 02፡38፡46 - ሚዳት አብራሪው ''Master Caution Anti-Ice'' ማስጠንቀቂያ መምጣቱን ለዋና አብራሪው ሲናገር ተሰምቷል። ማስተር ኮሜን (Master Caution) በአውሮፕላን ሥርዓት ላይ አንዳቜ ቜግር ሲያጋጥም ለአብራሪዎቜ ዹሚጠቁም ሥርዓት ሲሆን በዚህ ሰዓት ዚደሚሳ቞ው ''Master Caution Anti-Ice'' ማሰጠንቀቂያ ዚአውሮፕላኑን አካል ኹኹፍተኛ ቅዝቃዜ ዚሚጠብቀው አካል ቜግር እንዳጋጠመው እንደሆነ አብራሪው ያስሚዳል። 02፡38፡58 -ዋና አብራሪው ''ኮማንድ'' በማለት አውሮፕላኑን ''አውቶፓይለት'' ሥርዓት ላይ ለማድሚግ ቢጥርምፀ አውሮፕላኑ አውቶፓይለት ላይ እንዳልሆነ ዚሚያስጠነቅቅ መልዕክት መጣ። አውቶፓይለት ማለት አውሮፕላኑ በተወሰነለት አቅጣጫ በእራሱ ሥርዓት እንዲበር ዚሚያደርግ ዘዮ ነው። ኚሁለት ሰኚንዶቜ በኋላ ማለትም 02፡39፡00 ላይ ዋና አብራሪው በድጋሚ ''ኮማንድ'' በማለት አውሮፕላኑን ''አውቶ ፓይለት'' ሥርዓት ላይ ለማድሚግ ቢሞክርም ኚአንድ ሰኚንድ በኋላ (02፡39፡01) አውሮፕላኑ አውቶ ፓይለት ላይ እንዳልሆነ ዚሚያስጠነቅቅ መልዕክት ኚአውሮፕላኑ መጣ። 02፡39፡06 - ኚአምስት ሰኚንዶቜ በኋላ ማለት ነውፀ በዋና አብራሪው ትዕዛዝ ሚዳት አብራሪው ኹአዹር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎቜ ጋር ግንኙነት አደሚገ። ሚዳት አብራሪው ''SHALA 2A departure crossing 8400 ft and climbing FL 320'' በማለት ሪፖርት አደሚገ። አብራሪው ይህንን ሲል 'ሻላ 2ኀ' ማለት ኚአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ዚሚወስድ ዹተወሰነ ዚበሚራ አቅጣጫ ሲሆንፀ 8400 ጫማ ኚፍታ እያቋሚጡ እንደሆነ እና 32000 ጫማ ኚፍታ ይዘው እንደሚበሩ ነው ሚዳት አብራሪው ሪፖርት ያደሚገው። • ዹመደመር እሳቀ ኚአንድ ዓመት በኋላ • ጹው በዚዓመቱ 3 ሚሊዮን ሰዎቜን ይገድላል 02፡39፡45 - ዋና አብራሪው ፍላፕስ አፕ (Flaps up) በማለት ለሚዳት አብራሪው ትዕዛዝ ሰጠ። ሚዳት አብራሪውም ትዕዛዙን ተቀበለ። ፍላፕስ ዚአውሮፕላኑ አካል ሲሆኑ አውሮፕላኑ ኚመሬት ለመነሳት በሚያደርገው ጥሚት በቂ ፍጥነት እንዲያገኝ ዚሚያስቜሉ ና቞ው። ማብራሪያውን ዹሰጠን አብራሪ እንደሚለው ዚኢቲ 302 አብራሪዎቜ እንዳደሚጉት ሁሉ አንድ አውሮፕላን ኚተነሳ እና በቂ ኚፍታን ኚያዘ ፍላፕሶቹን ይሰበስባል። 02፡39፡50 - አውሮፕላኑ ዚበሚራውን አቅጣጫ ኹ072 ወደ 197 ዲግሪ መቀዹር ጀመሚ። በተመሳሳይ ሰዓት ዋና አብራሪው በተፈቀደው ዚበሚራ አቅጣጫ ላይ እንዲቆይ ትዕዛዝ ሰጠ። 02፡39፡55 - አውሮፕላኑ ኚአውቶ ፓይለት ተላቀቀ (ዲስኢንጌጅ አደሹገ)። 02፡39፡57 - ሚዳት አብራሪው በዋና አብራሪው ጥያቄ መሰሚት ለአዹር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎቜ አውሮፕላኑን ዚመቆጣጠር ቜግር እንደገጠማ቞ው አሳወቀ። • "ምርኩዜን ነው ያጣሁት" ዚካፒ቎ን ያሬድ አባት 02፡40፡03- ''Ground Proximity Warning System (GPWS)'' ዚተባለው ዚአውሮፕላኑ ሲስተም (ስርአት) ''ቁልቁል አትመዘግዘግ'' (DON'T SINK) ዹሚል ማስጠንቀቂያ ሰጠ። ይህ ሲስተም አውሮፕላኑ ወደሚበርበት አቅጣጫ ኚመሬት ወይም ኹግዑዝ ነገር ጋር ዚመጋጚት አደጋ እንደተደቀነበት ለማሳወቅ ለአብራሪዎቜ መልዕክት ለመስጠት ዹተቀሹጾ ነው። 02፡40፡03 እስኚ 02፡40፡31 ድሚስ ባሉት 28 ሰኚንዶቜ ውስጥ ሊስት (GPWS) ዹ''DON'T SINK'' ማስጠንቀቂያዎቜ ተመዝግበዋል። 02፡40፡27 - ዋና አብራሪው ዚአውሮፕላኑን አፍንጫ በአንድ ላይ ክፍ እንዲያደርግ ሚዳት አብራሪውን ጠዚቀው። 02፡40፡44 - ዋና አብራሪው ሊስት ግዜ ''ቀና አድርገው'' (ፑል-አፕ) አለፀ ሚዳት አብራሪውም እንደተባለው አደሚገ። 02፡40፡50 - ሚዳት አብራሪው በዋና አብራሪው ጥያቄ መሰሚት ኹአዹር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎቜ ጋር ግነኙነት በማድሚግ 14ሺህ ጫማ ላይ መቆዚት እንደሚሹ እና በሚራውን ዚመቆጣጠር ቜግር እንዳጋጠማ቞ው አሳወቀ:: 02፡41፡30 - አሁንም በድጋሚ ዋና አብራሪው ሚዳት አብራሪው አውሮፕላኑን አብሮት ኹፍ እንዲያደርግ ጠዚቀ። እሱም እንደተባለው አደሚገ። • "አደጋውን ስሰማ በሚራው ጠዋት እንዳልሆነ ራሎን አሳመንኩኝ" ዚሚዳት አብራሪው ጓደኛ 02፡42፡10- ዋና አብራሪው ሚዳት አብራሪው ኹአዹር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎቜ ጋር ግነኙነት እንዲያደርግ እና መመለስ እንደሚፈልጉ እንዲያሳውቅ ነገሚው። ሚዳት አብራሪውም እንደተባለው አደሚገፀ ዹአዹር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎቹም ፍቃድ ሰጡ። 02፡42፡30 - ዹአዹር ትራፊክ መቆጣጣሪያውም ኢቲ 302 ወደቀኝ ዞሮ 260 ዲግሪ እንዲይዝ ትዕዛዝ ተሰጠው። ሚዳት አብራሪውም ትዕዛዙን ተቀበለ። 02፡43፡04 - ዋና አብራሪው ሚዳቱን አሁንም በድጋሚ አውሮፕላኑን አብሮት ኹፍ እንዲያደርግ ጠዚቀ። ዋና አብራሪው መልሶም አውሮፕላኑ በበቂ ሁኔታ ኹፍ አለማለቱን ተናገሚ። አውሮፕላኑ አፍንጫውን እሰኚ 40 ዲግሪ ደፈቀ። ስለክስተቱ ዹአደጋውን ዚመጀመሪያ ደሹጃ ሪፖርት መሰሚት አድርጎ ማብራሪያውን ለቢቢሲ ዹሰጠው አብራሪ እንደሚለው ኹሆነ እንደዚ አውሮፕላኖቹ ዚሚለያይ ቢሆንም አንድ አውሮፕላን ለማሹፍ ሲቃሚብ 3 ዲግሪ ያክል ብቻ ነው ዹፊተኛው አካሉ ዝቅ ዚሚለው። 02፡43፡43- ቀሚጻው ቆመ። ዚአውሮፕላኑን መኚስኚስ ዹአዹር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎቜ ለአውሮፕላን አደጋ መርማሪ ቢሮ አስታወቁ። ኚደቂቃዎቜ በኋላም ዚኢቲ302 መኚስኚስ ዜና ተሰማ። ዚመጀመሪያ ደሹጃ ሪፖርቱ አብራሪዎቹ በቩይንግ እና በአሜሪካ ትራንስፖርት ባለስልጣን ዘንድ ተቀባይነት ያለውን ዚደህንነት ቅድመ ተኹተል ተግባራዊ በማድሚግ በበሚራው ላይ ያጋጠማ቞ውን አስ቞ጋሪ ሁኔታ በቁጥጥር ሥር ለማድሚግ ጥሚት ማድሚጋ቞ውን በግልጜ አመላክቷል። አብራሪዎቹ ተገቢውን እርምጃ ቢወስዱም ያጋጠማ቞ውን ያልተቋሚጠ አውሮፕላኑ አፍንጫውን ዚመድፈቅ ቜግርን መቆጣጠር ተስኗ቞ዋል። •"ዹሞተው ዹኔ ያሬድ ነው ብዬ አላሰብኩም" ዚካፕ቎ን ያሬድ ዹ11 አመት ጓደኛ • 'መጥፎ ዕድል' አውሮፕላኑ ዚወደቀበት ስፍራ ስያሜ እንደሆነ ያውቃሉ? ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዚሆኑት አቶ ተወልደ ገብሚማሪያምም ኚመጀመሪያ ደሹጃ ሪፖርቱ ጋር በተያያዘ "ፓይለቶቹ እጅግ በጣም አስ቞ጋሪ በሆነ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ዚሚጠበቅባ቞ውን ተገቢ እርምጃ በመውሰድ ያላ቞ውን ኹፍ ያለ ሙያዊ ብቃት በማስመስኚራ቞ው አዹር መንገዱ እንደሚኮራባ቞ው ተናግሚዋል። ዹዋና ካፒ቎ን ያሬድ ጌታ቞ው አባት ኚቢቢሲ ጋር በነበራ቞ው ቆይታ ልጃቾው ኚባልደሚባው ጋር ሆኖ አውሮፕላኑን ለመቆጣጠር ዚተቻለውን ሁሉ በማድሚጉ ጀግና መሆኑን በሃዘን በተሰበሹ ስሜት ተናግሚዋል።
news-55883439
https://www.bbc.com/amharic/news-55883439
ኮሮናቫይሚስ፡ ቻይና ስለሰራቻ቞ው ዚኮሮናቫይሚስ ክትባቶቜ ምን ያህል እናውቃለን?
ቻይና ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ በዓለም ላይ ኚተኚሰተበት ጊዜ ጀምሮ ክትባት ለማግኘት ስትመራመር ቆይታለቜ።
በዓለም ላይም በ2020 ዹበጋ ወራት ለሕዝቊቿ ክትባቱን መስጠት በመጀመር ቀዳሚዋም ናት። በአሁኑ ሰዓት 16 ዚተለያዩ ዓይነት ክትባቶቜ ላይ ምርምር እያደሚገቜ ሲሆን ተሳክተው ለጥቅም ዚዋሉት ግን ሲኖቫክ እና ሲኖፋርም ዚተሰኙት መድሃኒት አምራቜ ኩባንያዎቜ ያቀሚቧ቞ው ና቞ው። እነዚህ ሁለት ክትባቶቜ በቱርክ፣ በብራዚል፣ ኢንዶኔዢያ እና ዚተባበሩት አሚብ ኀሚሬቶቜ ጥቅም ላይ እንዲውሉ ፍቃድ አግኝተዋል። በኢንዶኔዢያ ዹሕክምና ባለሙያ ዹሆነቾው ዶ/ር አንጊዲታ ዲያ " ለአንድ አመት ያህል ይህንን ወሚርሜኝ ለማቆም ምንም ተስፋ ሳይኖር ቆይቶ፣ አሁን ይህንን ክትባት በማግኘቮ እጅግ በጣም ደስተኛ ነኝ" ብላለቜ። እነዚህ ክትባቶቜ ዚሚሰሩትልክ እንደ ሂፒታይተስ ኀ እና ሬቢስ ክትባቶቜ ነው ። መጀመሪያ ቫይሚሱ እንዲሞት ተደርጎ በክትባት መልክ እንድንወስደው ይደሚጋል። ቫይሚሱ በመሞቱ ኮቪድ-19 ሊያስይዝ አይቜልም። ክትባቱን ዹወሰደው ሰው ወደፊት ለኮሮናቫይሚስ በሚጋለጥበት ወቅት በቂ ዹመኹላኹል አቅም ሊኖሹው ዚሚያስቜለው አንቲቊዲ በፍጥነት ያዳብራል። ሰውነቱመ ዹመኹላኹል አቅሙን ወዲያው ያዳብራል። ልክ እንደ ፋይዘርና ሞደርና ክትባቶቜ ሁሉ ዚቻይናዎቹ ሲኖፋርም እና ሲኖቫክ ክትባቶቜንም ሁለት ጊዜ መውሰድ ያስፈልጋል። ዹሞደርና እና ፋይዘር ክትባቶቜ ግን እጅግ በጣም ቀዝቃዛ ስፍራ መቀመጥ ሲኖርባ቞ው ዚቻይና ክትባቶቜ ግን በማንኛውም ማቀዝቀዣ ውስጥ ሊቀመጡ ይቜላሉ። እነዚህ ዚቻይና ክትባቶቜ በዚህ ምክንያት ዚተነሳ በማጓጓዝ እና በማኚማ቞ት ወቅት ይህ ዹተለዹ ብልጫ ይሰጣ቞ዋል። በተለይ ደግሞ ሙቀት ኹ30 ዲግሪ ሎልሺዚስ በታቜ ዚሚገኝባ቞ው አገራት እና ዚመንገድ ፍሰት በበቂ በሌለባ቞ው ስፍራዎቜ ይህ ዚተሻለ ብልጫ እንዲኖራ቞ው ያደርጋል። ሳይኖፋርም ያመሚተው ክትባት ዚኮቪድ-19 ምልክቶቜን በማቆም ሚገድ 79 በመቶ ውጀታማ መሆኑ ዹተገለፀ ሲሆን ሳይኖቫክ ያመሚተው እና ኮሮኖቫክ ዹተሰኘው ክትባት ደግሞ መጀመሪያ ላይ 91 በመቶ ውጀታማ ነው ተብሎ ተገምቶ ዹነበሹ ቢሆንም ነገር ግን ተጚማሪ ዹተደሹጉ ሙኚራዎቜ ሌላ ውጀት አሳይተዋል። ብራዚል በዚህ ክትባት ላይ ያደሚገቜው ሙኚራ ውጀቱን ወደ 50.4 በመቶ አውርዶታል። ይህ ደግሞ ዹዓለም አቀፉ ጀና ድርጅት አንድ ክትባት ወደ ሕብሚተሰቡ ኚመሰራጚቱ በፊት ማሟላት አለበት ኹሚለው መስፈርት በጥቂት ብቻ ኹፍ ብሎ እንዲገኝ አድርጎታል። ቻይና ለኹ20 አገራት በላይ ክትባቷን ለመስጠት ስምምነት ላይ ዚደሚሰቜ ሲሆን በመላው ዓለምም ለማሰራጚት አቅዳለቜ። ዹዓለም ጀና ድርጅት ግን በመጪው መጋቢት ወር ሳይኖፋርምም ሆነ ሳይኖቫክ ያመሚቷ቞ውን ክትባቶቜ መጠቀም አለመጠቀም ላይ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል። ለመሆኑ ዚትኞቹ ክትባቶቜ ጥቅም ላይ ውለዋል? በአሁኑ ጊዜ በርካታ መድኃኒት አምራቜ ኩባንያዎቜና አገራት ለኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ ዹሚሆን ክትባት በማበልጾግ ላይ ሲሆኑ ጥቂቶቹም በስራ ላይ መዋል ጀምሚዋል። ፋይዘር/ባዮን቎ክ ኮሮናቫይሚስን በመኹላኹል 90 በመቶ ውጀታማ ነው ዚተባለው ይህ ዚኮቪድ-19 መኚላኚያ ክትባት ይፋ ዹሆነው በፈሚንጆቹ ሕዳር 9/2020 ላይ ነበር። በወቅቱ ክትባቱን ይፋ ያደሚጉት ፋይዘር እና ባዮኀን቎ክ ኩባንያዎቜ ግኝቱ ለሳይንስና ለሰው ልጅ ትልቅ እድል ነው ብለዋል። ዚአሜሪካ እና ዹጀርመን ኩባንያ ዚሆኑት ፋይዘር እና ባዮን቎ክ በስድስት ዚተለያዩ ሃገራት 43 ሺህ 500 ሰዎቜ ላይ መሞኚራ቞ውን ዹገለፁ ሲሆን አንድም ጊዜ አሳሳቢ ዚጀና ቜግር አልታዚም ብለዋል። ፋይዘርና ባዮን቎ክ ክትባቱን በፈሚንጆቹ ዚህዳር ወር መጚሚሻ ጥቅም ላይ ለማዋል ጥያቄ ማቅሚባ቞ው ዚሚታወስ ሲሆንፀ ይህን ተኚትሎም ዩናይትድ ኪንግደም ክትባቱ ጥቅም ላይ እንዲውል በመፍቀድ ኚዓለማቜን ቀዳሚዋ አገር ሆናለቜ። ዩናይትድ ኪንግደም ለመጀመሪያ ጊዜ ዚኮሮናቫይሚስ ክትባትን ማክሰኞ ዕለት ለዜጎቿ መስጠት ዚጀመሚቜ ሲሆን ዹዘጠና ዓመቷ አዛውንት ዹፋይዘር/ባዮን቎ክ ክትባትን በመውሰድ በዓለም ዚመጀመሪያዋ ሰው ሆነዋል። በመላው ዩናይትድ ኪንግደም (ዩኬ) ዹሚገኙ ኹ70 በላይ ዹሚሆኑ ሆስፒታሎቜ እድሜያ቞ው ኹ80 ዓመት በላይ ለሆኑ አዛውንቶቜ እና ለጀና ባለሙያዎቜ ክትባቱን ለመስጠት መዘጋጀታ቞ው ተገልጿል። ዚአሜሪካ ዚምግብና መድኃኒት አስተዳደር መስሪያ ቀትን (ኀፍዲኀ) ዚሚያማክሩ ባለሙያዎቜ በፋይዘር/ባዮን቎ክ ዹበለጾገው ዚኮሮናቫይሚስ ክትባት ጥቅም ላይ እንዲውል ሀሳብ ማቅሚባ቞ውም ተገልጿል። ባለሙያዎቹ ይህን ምክሹ ሃሳብ ዚሰጡት 23 አባላት ያሉት ዚባለሙያዎቜ ቡድን ክትባቱ ሊፈጥሚው ዚሚቜለው ስጋት ኹሚሰጠው ጥቅም አንጻር ምን ሊመስል እንደሚቜል ምክክር ካደሚጉ በኋላ ነው ተብሏል። ዚአሜሪካ ዚጀና ሚንስትር አሌክስ ሚቡዕ ዕለት ''በሚቀጥሉት ቀናት ክትባቱ በእጃቜን ሊገባ ይቜላልፀ በሚቀጥለው ሳምንት ደግሞ እጅግ ተጋላጭ ዚሆኑትን ዜጎቜ መኚተብ ልንጀምር እንቜላል'' ብለዋል። ዹፋይዘር/ባዮን቎ክ ክትባት እስካሁን በዩናይትድ ኪንግደም፣ ካናዳ፣ ባህሬን እና ሳኡዲ አሚቢያ ጥቅም ላይ ለመዋል ፍቃድ አግኝቷል። ሞደርና ዚዩናይትድ ስ቎ትስ መድኃኒት አምራቜ ኩባንያ ዹሆነው 'ሞደርና' ኚኮሮናቫይሚስ 95 በመቶ ዹሚኹላኹል አዲስ ክትባት ማግኘቱን ይፋ ካደሚገ ሰነባብቷል። በአሁኑ ሰአትም ኚአውሮፓና አሜሪካ ፈቃድ ሰጪዎቜ ክትባቱን ለመጠቀም ዚሚያስቜል ፈቃድ ጠይቆ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል። ሞደርና ዹምርምር ውጀቱን ይፋ ያደሚገበትን ዕለት 'ታላቅ ቀን' በማለት ሐሎቱን ዹገለፀ ሲሆንፀ በቅርብ ሳምንታትም ክትባቱን ለመጠቀም ፈቃድ እንደሚያገኝ አስታውቋል። ዚቀተ ሙኚራ ሂደቶቜ እንደሚያሳዩት ኀምአርኀንኀ ዹተሰኘው ክትባት 94 በመቶ ውጀታማና ሰዎቜን ኚኮሮናቫይሚስ ዚሚያድን ነው። ዚክትባቱ ሙኚራ አሜሪካ ውስጥ ያሉ 30 ሺህ ሰዎቜን ያሳተፈ ሲሆንፀ ግማሟቹ በዚአራት ሳምንቱ ክትባቱ ሲሰጣ቞ው ግማሟቹ ደግሞ ጥቅምና ጉዳት ዹሌለው መርፌ ተወግተው ውጀቱን ለመለዚት ተሞክሯል። ኹዚህ ሙኚራ በተገኘ ውጀት መሠሚት 94.5 በመቶ ሰዎቜ በክትባቱ ምክንያት ለኮሮናቫይሚስ ሳይጋለጡ ቀርተዋል ተብሏል። ስለ ክትባቱ ውጀቱ ዹቀሹበው ዘገባ ጚምሮምፀ ሙኚራ ኚተደሚገባ቞ው መካኚል 11 በኮቪድ-19 ክፉኛ ዚታመሙ ሰዎቜ ዹመኹላኹል አቅም አዳብሚዋል ይላል። ስፑትኒክ 5 ይህ ሩሲያ ሰራሜ ክትባት ይፋ በተደሹገ ጊዜ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በአገር ውስጥ በተደሹገ ምርምር አገር በቀል ክትባት አግኝተናልፀ ለሰዎቜ አገልግሎት እንዲውልም ይፋዊና ብሔራዊ ፍቃድ ሰጥተናል ብለው ነበር። በዓለም ዚመጀመርያው ዚተባለው ይህ ስፑትኒክ-5 ክትባት ሞስኮ ዹሚገኘው ጋማሊያ ኢንስቲትዩት ነው ያመሚተው። ክትባቱ ይፋ ዹተደሹገውም ነሀሮ ወር ላይ ነበር። ኢንስቲትዩቱ እንደሚለው ክትባቱ አስተማማኝ ዹመኹላኹል አቅም ይሰጣል። ፑቲን በበኩላ቞ው ገና ቀደም ብሎ "ይህ ክትባት አስተማማኝ እንደነበር አውቅ ነበር" ብለዋል። "ሁሉንም ሳይንሳዊ ሂደቶቜን በአስተማማኝ ሁኔታ ማለፍ ቜሏል" ሲሉም አስሚግጠው ተናግሚዋል። ፑቲን ኚልጆቻ቞ው ለአንዷ ክትባቱ ተሰጥቷት ትንሜ አተኮሳት እንጂ ምንም አልሆነቜም ብለዋል። ፑቲን ዚትኛዋ ልጃቾው ክትባቱን ወስዳ እንዳተኮሳት ግን በስም አልገለጹም። ዚሩሲያ ሳይንቲስቶቜ ዚመጀመሪያ ዙር ሙኚራዎቜ ተደርገው ሁሉም ድንቅ ውጀት አስመዝግበዋል ብለዋል። ሳንቲስቶቹ ሰዎቜ ላይ ጉንፋንን ዚሚያመጣው አዲኖቫይሚስ ዹተሰኘውን ዹተላመደ ዚተህዋስ ቅንጣት ተጠቅመው ነው ክትባት ሰራን ያሉት። ይህን ለማዳ ተህዋሲ አዳክመው ወደ ሰውነት በማስገባት ሕዋስ በማቀበል ክትባቱ ሰውነት ኮቪድ-19 ተህዋሲ ሲገባ ነቅቶ እንዲዋጋ ያደርገዋል ብለዋል። በአውሮፓውያኑ ታሕሳስ 5/2020 ላይ ደግሞ ይሄው ክትባት በሩሲያዋ መዲና ሞስኮ መሰጠት ተጀምሯል። በመጀመሪያው ዙር ክትባቱን ለመውሰድ በሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜ ተመዝግበዋል። ሩሲያ ምን ያህል ክትባት ማምሚት እንደምትቜል ግልጜ ባይሆንምፀ አምራ቟ቜ እስኚ ዓመቱ መገባደጃ ሁለት ሚሊዮን ጠብታ እንዲያዘጋጁ ይጠበቃል። 13 ሚሊዮን ሰዎቜ ዚሚኖሩባት ዚሞስኮ ኹተማ ኚንቲባ ሰርጌ ሶቢያን እንዳሉትፀ ክትባቱ ለማኅበሚሰብ አገልግሎት ሰጪዎቜ፣ ለጀና ባለሙያዎቜ እና ለትምህርት ቀት ሠራተኞቜ ይሰጣል። ተጚማሪ ክትባቶቜ ሲመሚቱ ለተቀሹው ማኅበሚሰብ እንደሚዳሚስ ኚንቲባው ጠቁመዋል። ኹላይ በተዘሚዘሩት ዚሙያ መስኮቜ ዚተሰማሩና እድሜያ቞ው ኹ18 እስኚ 60 ዹሆኑ ዜጎቜ በድሚ ገጜ ተመዝግበዋል። በሞስኮ ኚጠዋቱ 2 ሰዓት እስኚ ምሜቱ 2 ሰዓት ዚክትባቱን አገልግሎት ዚሚሠጡ 70 ማዕኚሎቜ ተኚፍተዋል። ክትባቱ ዚተሰጣ቞ው ባለፉት 30 ቀናት ዚመተንፈሻ አካል ህመም ዚገጠማ቞ው፣ ዹኹፋ ዚጀና እክል ያለባ቞ው፣ ነፍሰ ጡር እና ዚሚያጠቡ እናቶቜ እንደሚለዩ ተገልጿል። ሲኖቫክ መላው ዓለም ለኮሮናቫይሚስ ክትባት ለማግኘት ደፋ ቀና ሲል ቻይናም እጇን አጣጥፋ አልተቀመጠቜም። ሲኖቫክ ዚተባለ ክትባት መስራት ኚጀመሚቜ ሰነባብታለቜ። እንደውም በጎ ፈቃደⶉቜን መኚተብ ኚጀመሚቜ ቆዚት ብላለቜ። በቻይና በሙኚራ ላይ ዹሚገኘው ዚኮቪድ-19 ክትባት አመርቂ ዚሚባል ውጀት እያስገኘ ነውም ተብሏል። ሆኖም ክትባቱ አመርቂ ውጀት ያስገኘው በሚዥም ዚሙኚራ ሂደት ውስጥ ዚመጚሚሻ ምዕራፍ ላይ ሳይሆን፣ መካኚለኛ ምዕራፍ በሚባለው ክፍል ነው። ተመራማሪዎቜ እንዳሚጋገጡት ኚቻይና ሰራሜ ክትባቶቜ አንዱና ታዋቂ እዚሆነ ዚመጣው በሲኖቫክ ባዮ቎ክ ዹተመሹተው ሲኖቫክ ክትባት በ700 ሰዎቜ ላይ ተሞክሮ ይበል ዚሚያሰኝ ውጀት አስገኝቷል። ክትባቱ ዚተሞኚሚባ቞ው ሰዎቜ በሜታን ዚመኚላኚያ ህዋሳ቞ውን አንቅቶ ቫይሚሱን መመኚት እንደቻለ ተደርሶበታል። ላንሎት በሚባለው ሥመ ጥር ዚሳይንስ ጆርናል ላይ ይህንን ክትባት በተመለኹተ ዚተዘገበውፀ ክትባቱ ለጊዜው በምዕራፍ አንድና ሁለት ያስመዘገበው ውጀት እንጂ አሁን ያለበትን ደሹጃ አይገልጜም። በተጚማሪም ዚስኬት ምጣኔው ምን ያህል እንደሆነ ይፋ አልተደሚገም። በዚህ ጆርናል ላይ ስለዚህ ቻይና ሰራሹ ክትባት ኚጻፉት ተመራማሪዎቜ አንዱ ዚሆኑት ዙ ፋንቻይ እንደሚሉትፀ በምዕራፍ አንድ እና በምዕራፍ 2 ሙኚራዎቜ 600 ሰዎቜ ላይ ጥናት ተደርጎ ክትባቱ ለአስ቞ኳይ ሕክምና አገልግሎት ላይ መዋል ይቜላል ዹሚል ድምዳሜ ላይ ተደርሷል። ነገር ግን ወሳኝ በሚባው በምዕራፍ ሊስት ሙኚራ ላይ ይህ ዚቻይና ክትባት ስላስገኘው ውጀት በተጚባጭ ተአማኒ ሳይንሳዊ ጆርናል ላይ ዚተጻፈ ዘገባ ዚለም። በቻይና በአሁን ሰዓት ሙሉ በሙሉ ሊባል በተቃሹበ ደሹጃ ዚኮቪድ-19 ወሚርሜኝ በቁጥጥር ሥር ዚዋለበት ሁኔታ ተፈጥሯል። ሆኖም ቻይና ለዜጎቿ ይህንን ክትባት መስጠቷን ቀጥላበታለቜ። በአሁኑ ሰአት ደግሞ መቀመጫውን ቀዢንግ ያደሚገው ዚክትባት አምራቹ ኩባንያ ያዘዛ቞ው በርካታ ዹህክምና ቁሳቁሶቜ ኚኢንዶኔዢያ መግባት ጀምሚዋል። ይህ ደግሞ አገሪቱ በቅርቡ ዜጎቿን በይፋ መኚተብ ልትጀምር እንደሆነ ማሳያ ነው ተብሏል። በዓለም ላይ ኮቪድ-19 ኹፍተኛ ጉዳት ካደሚሰባ቞ው አገራት ተርታ ዚምትመደው ዚደቡብ አሜሪካዋ ትልቅ አገር ብራዚል በበኩሏ ቻይና ሰራሜ ክትባት ለሕዝቀ አድላለሁ ማለቷ ዚሚታወስ ነው። ዚሳኊ ፖሎ ገዥ ጃዎ ዶሪያ እንዳሉት ዚፌዎራል መንግሥት 46 ሚሊዮን ጠብታዎቜን ለመግዛት ስምምነት ላይ ደርሷል። ዚክትባት ዘመቻው መቌ ይጀመራል በሚል ዚተጠዚቁት ዚሳኊ ፖሎ ገዥ በፈሚንጆቜ አዲሱ ዓመት ዚመጀመርያ ወር ላይ ሊሆን ይቜላል ብለዋል። አስትራዜኒካ እና ኊክስፎርድ ዩኒቚርስቲ አስትራዜኒካ እና ኊክስፎርድ ዩኒቚርስቲ እያበለፀጉ ያሉት ክትባት ኹፍተኛ ተስፋ ኚተጣለባ቞ው ክትባቶቜ መካኚል ነው። ይሄው ክትባት በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ በሙኚራ መልክ ተሰጥቷል። ደቡብ አፍሪካ ለዚህ ዚክትባት ሙኚራ ዚተመሚጠቜው በዘርፉ ባሏት ባለሙያዎቜ ብቻ ሳይሆን ኚአፍሪካ በርካታ በበሜታው ዚተያዙ ሰዎቜ ያሉባትና ወሚርሜኙም በፍጥነት እዚተስፋፋባት በመሆኑ ነው። ይህ ዚክትባት ሙኚራ ኊኀክስ1ኮቪድ-19 ክትባት ዚሚባል ሲሆንፀ ኮሮናቫይሚስን ዚሚያስኚትለው ሳርስ-ኮቪ-2 በተባለው ቫይሚስ ሰዎቜ እንዳይያዙ ለመኹላኹል ዚታለመ ነው። በደቡብ አፍሪካ ዹሚደሹገው ዚክትባት ሙኚራ ተግባራዊ ኹመሆኑ በፊት ጥልቅ ፍተሻ ተደርጎበት በደቡብ አፍሪካ መንግሥት ዚጀና ምርቶቜ ተቆጣጣሪ ተቋምና በዊትስ ዩኒቚርስቲ ፈቃድ ተሰጥቶታል ተብሏል። ይህ ክትባት ዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ ኚአራት ሺህ ሰዎቜ በላይ ዚተሳተፉበት ክሊኒካል ሙኚራ ዚተደሚገበት ሲሆንፀ በደቡብ አፍሪካ ኹሚደሹገው ሙኚራ ጋር ተመሳሳይና ተዛማጅ ዹሆነ ሙኚራ ብራዚል ውስጥ ሊጀመር እንደሆነ ተገልጿል። ኹዚህ በተጚማሪም ኹሁሉም ዹላቀ ቁጥር ያላ቞ው ሰዎቜ ዚሚሳተፉበት ዹዚህ ክትባት ሙኚራ አሜሪካ ውስጥ በ30 ሺህ ሰዎቜ ላይ ለማካሄድ ዕቅድ ተይዟል። በሌሎቜ ድርጅቶቜ ዚሚሠሩ እና በሊስተኛ ደሹጃ ላይ ዹሚገኙ ክትባቶቜ ሙኚራ ተጚማሪ ውጀቶቜ በሚቀጥሉት ሳምንታት እና ወራቶቜ ይወጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። በአሁኑ ሰአትም ዚመጚሚሻው ዚሙኚራ ደሹጃ ላይ ዹሚገኙ በርካታ ተጚማሪ ክትባቶቜ አሉ። ኹነዚህም መካኚል ኚታቜ ዚተዘሚዘሩት ዚሚጠቀሱ ና቞ው።
news-50206434
https://www.bbc.com/amharic/news-50206434
በግጭት ውስጥ ዚሰነበቱት ኚተሞቜ ዚዛሬ ውሎ
ባለፈው ሚቡዕ በተለያዩ አካባቢዎቜ ዚተቀሰቀሱ ተቃውሞዎቜን ተኚትሎ ዚተቀሰቀሱ ግጭቶቜ ዚብሔርና ዚሃይማኖት መልክ ይዘው ለቀናት ኹቀጠሉ በኋላ ኹ67 በላይ ዹሚሆኑ ሰዎቜን ህይወት ኹቀጠፉ በኋላ በድርጊቱ ተሳትፈዋል ዚተባሉ ተጠርጠሪዎቜ እዚተያዙ መሆናቾው ዹአገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
አዳማ • በተለያዩ ሥፍራዎቜ ባጋጠሙ ግጭቶቜ ዚሟ቟ቜ ቁጥር 67 ደርሷል ትናንት በማህበራዊ መገናኛ መድሚኮቜ ላይ ሰልፎቜ እንደሚካሄዱ ዚሚገልጹ መልዕክቶቜ መውጣታ቞ውን ተኚትሎ ዛሬ ሰኞ ግጭቶቜ ሊኖሩ እንደሚቜሉ ተሰግቶ ነበር። ቢቢሲ እስካሁን ያለውን ሁኔታ ለማወቅ ኹሰሞኑ ግጭት ዚተኚሰተባ቞ው አካባቢዎቜ ነዋሪዎቜን አናግሯል። ሐሚር በሐሹር ኹተማ ዹተኹሰተውን ግጭት ተኚትሎ ዛሬም በኹተማዋ ዹነበሹው እንቅስቃሎ መቀዝቀዙን ቢቢሲ ያናገራ቞ው ዹኹተማዋ ነዋሪዎቜ ተናግሚዋል። በዛሬው ዕለት ትምህርት ቀቶቜ ዝግ ሲሆኑ ወደ መንግሥት መስሪያ ቀቶቜ ተገልጋዮቜ ስለማይታዩ ጭር እንዳሉና አንዳንድ ሱቆቜም ዝግ ና቞ው። • በዶዶላ ቀተክርስቲያናት ውስጥ ተጠልለው ዹሚገኙ ምዕመናን ስጋት ላይ ነን አሉ በኹተማዋ ያሉ መንገዶቜ እምብዛም ተሜኚርካሪዎቜ ስለማይታዩባ቞ው ጭር ማለታ቞ውን ዚተናገሩት ነዋሪዎቜፀ ዚጞጥታ አካላትም በኹተማዋ እዚተዘዋወሩ ጥበቃ እያደሚጉ እንደሆነም ተገልጿል። በተጚማሪም ቀደም ካሉት ቀናት በተለዹ ዚጞጥታ አካላት ስለትም ሆነ ዱላ ይዞ መንቀሳቀስን ኚልክለዋል። እነዚህን ቁሶቜ ይዘው ኹሚገኙ ሰዎቜ ላይ እንደሚቀሙ ነዋሪዎቜ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። ሰልፍም ሆነ ግጭት ይህንን ዘገባ እስካጠናቀርንበት ድሚስ አለመኚሰቱን ለማወቅ ቜለናል። ሞጆ ዛሬ ጠዋት በሞጆ ኹተማ በተኹሰተ ሁኚት ሁለት ሰዎቜ በጥይት ተመተዋል። በኹተማዋ ዛሬ ጠዋት 'ዚታሰሩ ሰዎቜ ኚእስር ይለቀቁ' በማለት ሰልፍ ዚወጡ ሰዎቜ ኚመንግሥት ጞጥታ አስኚባሪዎቜ ጋር ተጋጭተው በሰዎቜ ላይ ጉዳት መድሚሱን ዹኹተማው ኚንቲባ ወ/ሮ መሰሚት አሰፋ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። ቅዳሜ ሌሊት ላይም በኹተማዋ በምሜት ሰልፍ ተካሂዶ እንደነበር ኚንቲባዋ ተናግሚዋል። "ቅዳሜ ሌሊት 'ቀተክርስቲያን ተቃጥለ' ዹሚል ወሬ ተናፍሶ ሌሊቱን ሁኚት ተፈጥሮ ነበር። በንብሚት ላይ ጉዳት ደርሶ ነበር" ብለዋል። • "ያለን አማራጭ ውይይት ብቻ ነው" ጀዋር መሐመድ ኚንቲባዋ ጹምሹው እንደተናገሩት ቅዳሜ ሌሊት ቀተ-ክርስቲያን ተቃጥሏል እዚተባለ ዹተናፈሰው ወሬ ሃሰት መሆኑን እና ይህ ዹተደሹገው "በኹተማው ሆን ተብሎ ሚብሻ ለመፍጠር" ታስቊ መሆኑን ተናግሚዋል። በተመሳሳይ መልኩ ዛሬም 'ዚታሰሩ ሰዎቜ ኚእስር ይለቀቁ' በማለት አደባባይ እንደወጡ እና ኚጞጥታ አካላት ጋር እንደተጋጩ እንዲሁም በተኹፈተው ተኩስ ሁለት ሰዎቜ መጎዳታ቞ውን አስሚድተዋል።እስካሁን ዚብሔር ግጭት ለመቀስቀስ ዚሞኚሩ 9 ሰዎቜ በቁጥጥር ሥር መዋላቾውን ዚተናገሩት ኚንቲባዋፀ ዛሬ ተኚስቶ ዹነበሹው ሁኚት በቁጥጥር ሥር ውሎ በኹተማዋ አንጻራዊ ሰላም መስፈኑን ጹምሹው ተናግሚዋል።አዳማ አዳማ ኹሰሞኑ ሁኔታ በተሻለ መልኩ አንጻራዊ ሰላም እንደሚታይባት በስፍራው ዹሚገኘው ሪፖርተራቜን ዘግቧል። • ቅዱስ ሲኖዶሱ ኚምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ እና ኚመኚላኚያ ሚንስትሩ ጋር ተወያዚ ዚአዳማ ኹተማ ኮሚኒኬሜን ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ራውዳ ሁሮን በኹተማዋ ዛሬ ጠዋት ዚታውሞ ሰልፍ ለማካሄድ በማህበራዊ ሚዲያዎቜ ዚተለያዩ ጥሪዎቜ ሲደሚጉ መቆዚታ቞ውን ጠቅሰው ዚሚመለኚታ቞ው ዚመንግሥት አካላት ይህን ለማስቆም ጥሚት ማድሚጋ቞ውን ተገልጞዋል። በነዋሪዎቜ ዘንድ ኚሚስተዋለው ዚደህንነት ስጋት ውጪ ኹተማዋ ኹሞላ ጎደል ወደ ቀድሞ ዚንግድ እንቅስቃሎ እዚተመለሰቜ መሆኑን ሪፖርተራቜን ዘግቧል። ሰበታ ሰበታ ኹተማ ወደ ቀድሞ እንቅስቃሎዋ እዚተመለሰቜ መሆኑን ዹኹተማው ኮሚኒኬሜን ቢሮ ኃላፊ አቶ ታዬ ዋቅኬኔ ተናግሚዋል። • "ክስተቱ 'ዚግድያ ሙኚራ' እንደሆነ ነው ዚምሚዳው" ጀዋር መሐመድ ዚንግድ ተቋሞቻ቞ውን ዘግተው ኚነበሩት እና ኹአጠቃላይ ነዋሪው ጋር ውይይት ማድሚጉ እንደቀጠለ ተናግሚውፀ መልካም ዚሚባል ለውጊቜ እዚተመለኚቱ እንደሆነ ጠቅሰዋል። ባሌ እና ጎባ ኚተሞቜ በማሕበራዊ ሚዲያዎቜ ዛሬ ጠዋት በባሌ ዞን በሚገኙ ኚተሞቜ ዹተቃውሞ ሰልፎቜ ሲጠሩ ነበር። ይሁን እንጂ በኚተሞቹ ዛሬ ምንም አይነት ዹተቃውሞ ሰልፎቜ አለመካሄዳ቞ውን ኚነዋሪዎቜ ሰምተናል። በተመሳሳይ መልኩ በነዋሪዎቜ ዘንድ ካለው ዚደህንነት ስጋት ውጪ በኚተሞቹ አንጻራዊ ሰላም መኖሩን ነዋሪዎቜ ለቢቢሲ ተናግሚዋል።
news-52805122
https://www.bbc.com/amharic/news-52805122
በትግራይ ክልል ዹተፈጠሹው ምንድን ነው?
ኚባለፈው ሳምንት ጀምሮ በትግራይ ክልል ውስጥ ዹሚገኙ አንዳንድ አካባቢዎቜ ነዋሪዎቜ ዚተለያዩ ጥያቄዎቜን በማንሳት ተቃውሞ በማሰማት ላይ እንደሆኑ በማኅበራዊ መገናኛ መድሚኮቜ ላይ ሲነገር ቆይቶ ነበር።
ባለፈው ሳምንት ማብቂያ ላይም ጉዳዩን በተመለኹተ በሜሬ እንደስላሎ እና በዋጅራት አካባቢዎቜ ዚመልካም አስተዳደር፣ ዹመሰሹተ ልማት እንዲሁም ኚሥራ ዕድል ጋር ዚተያያዙ በርካታ ጥያቄዎቜን በማንሳት ዹተቃውሞ ሰልፎቜ እንደተካሄዱ ብሔራዊ ዚ቎ሌቪዥን ጣቢያውን ጚምሮ ዹአገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ይህንንም ተኚትሎ ዚትግራይ ክልል መንግሥት ኮሙኑኬሜን ጉዳዮቜ ቢሮ ሰኞ ዕለት ባወጣው መግለጫ በአሁኑ ወቅት በክልሉ በዚትኛውም ቊታ "ዚተካሄደ ሰላማዊ ሰልፍም ሆነ ዹተፈጠሹ ዹሰላም መደፍሚስና ግርግር ፈፅሞ ያልተሰማና መሬት ላይ ዹሌለ ነው" በማለት ዘገባዎቹን አስተብብሏል። መግለጫው ጚምሮም "በሜሚ እንዳስላሰና አኚባቢው እንዲሁም በዋጅራትና አኚባቢው ሰላማዊ ሰልፎቜ ተካሄዱ፣ ፍትህ መጓደል አለ ዚሚባለው ዹተፈበሹኹ ሐሰተኛ፣ ዚበሬ ወለደ ወሬ ነው" ሲል አጣጥሎታል። በተጚማሪም "ሐሰተኛ ወሬ በማሰራጚት፣ ዚተጠመዱት" ባለ቞ው ዹመገናኛ ብዙሃን ላይ ዚኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣንም "በሚዲያዎቹ ዚተሰራጚውን ሐሰተኛ ዚበሬ ወለደ ወሬ አጣርቶ ህጋዊ እርምጃ እንዲወስድ" ዹክልሉ ኮምዩኒኬሜን ጉዳዮቜ ቢሮ ጠይቋል። ቢቢሲ ኚወጀራትና ኚሜሚ እንዳስላሰ 70 ኪሎሜተር እርቃ ኚምትገኘው ማይሃንሰ አስተዳዳሪዎቜና ኚነዋሪዎቜ እንደተሚዳው በአካባቢዎቹ ጥያቄዎቜን በማንሳት ለቀናት ዹዘለቀ ተቃውሞዎቜና ዚመንገድ መዝጋት ክስተቶቜ አጋጥመዋል። ዹተቃዋሚው አሹና ትግራይ ዚሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ዚሆኑት አቶ አምዶም ገብሚስላሰ በማይሃንሰን እና ወጀራት በተባሉ ዚትግራይ ክልል አካባቢዎቜ ዚተነሱ ሕዝባዊ ጥያቄዎቜ አሁንም አንዳልበሚዱ ለቢቢሲ አሚጋግጠዋል። አቶ አንዶም ገብሚስላሰ እንደሚሉት ለተቃውሞዎቹ መቀስቀስ ምክንያቶቹ ኹዚህ ቀደምም ሲንኚባለል ዹቆዹ ዚወሚዳነት ጥያቄ ሲሆን ተገቢ ምላሜ አላገኘንም ያሉ ዚአካባቢው ነዋሪዎቜ ወደ ምዕራባዊ ዞን ዚሚወስደውን ዚዳንሻ መንገድ ኹዘጉ ዘጠኝ ቀናት አስቆጥሚዋልፀ አሁንም ቢሆን "ጥያቄውም አልተፈታምፀ መንገድም አልተኹፈተም" ብለዋል። መነሻ ለዚህ ሁሉ እንደመነሻ ዹሚጠቀሰው ዚወሚዳ ማዕኹል እንሁን በሚል ዚሁለት ቀበሌ ነዋሪዎቜ ያነሱት ጥያቄ ነው። ጥያቄ ዚቀሚበባ቞ው ቀበሌዎቜ በሰሜን ምዕራብ ትግራይ ዹሚገኘው ማይ ሓንሰ እና በደቡብ ምሥራቅ ትግራይ ዹሚገኘው ባሕሪ ሓፀይ መሆናቾውን ዚቢቢሲ ዘጋቢ ገልጿል። ሜሚ አካባቢ ዚምትገኘው ዹማይሃንሰን ሕዝባዊ ቅዋሜ ኚወሚዳነት ጥያቄ በዘለለ፥ በስፍራው በተመደቡ አስተዳዳሪዎቜ ቅር መሰኘትንም ያካትታል ይላሉ ዹተቃዋሚ ፓርቲው ዚሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ። በደደቢት እና አደጋ ሕብሚትም ተመሳሳይ ድርብ ጥያቄዎቜ መነሳታ቞ውን ነው አቶ አንዶም ዚሚናገሩት። ኚጥቂት ዓመታት በፊት ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት)ፀ ‘ተሃድሶ’ ባካሄደበት ወቅትፀ በትግራይ ዚአስተዳደር መዋቅር ለውጥ እንደሚያደርግ አስታውቆ ነበር። ይህም አስተዳደራዊ ለውጥ ያልተማኚለ አስተዳደር ለመፍጠር፣ ሥልጣንን በዋናነት ወደ ወሚዳዎቜና ጣብያዎቜ ማውሚድ ዹሚል ነበር። በዚህም መሠሚት አዲስ ዚወሚዳ እና ዚጣብያ አደሚጃጀት እንዲኖር ተደሚጓል። ዚአንድ ወሚዳ ማዕኹል ዹሚሆነው ቀበሌ ዚትኛው ይሁን? ዹሚለው ግን በአንዳንድ አካባቢዎቜ አወዛጋቢ ጥያቄን ማስኚተሉንና አሁን ለተፈጠሹው ነገር መነሻ እንደሆነ ይነገራል። በሰሜን ምዕራብ ትግራይና በደቡብ ምሥራቅ ትግራይ ዹሚገኙ ሁለት ቀበሌዎቜ ጥያቄ ያቀሚቡትም እኛ ዚወሚዳቜን ማዕኹል መሆን አለብን ብለው ነው። በሰሜን ምዕራብ ትግራይ ዚወሚዳ ምክር ቀት ዚወሚዳው ማዕኹል ብሎ ዹወሰነውን ቀበሌ ያልተቀበሉ ዹሌላ ቀበሌ ነዋሪዎቜ፣ መንገድ ዘግተው መኪና አናሳልፍም ብለው ለተቃውሞ መውጣታ቞ውን ኚዘጋቢያቜን ለመሚዳት ቜለናል። በአካባቢው አዲስ ዹተዋቀሹ አስገደ ዚሚባል ወሚዳ አለ። በወሚዳው ኹሚገኙ ሕፃጜ፣ ዕዳጋ ሕብሚት፣ ክሳድ ጋባ እና ማይ ሓንሰ ዚተባሉ ቀበሌዎቜ ለወሚዳው ማዕኚልነት ተወዳድሚው ነበር። ዚወሚዳው ምክር ቀት ክሳድጋባ ማዕኹል እንድትሆን ውሳኔ ቢያስተላለፍምፀ ዹማይ ሓንሰ ነዋሪዎቜ ውሳኔውን አልተቀበሉም። ተቃውሞና መንገድ መዝጋት በሰሜን ምዕራብ ዞን ዹማይ ሓንሰ ነዋሪዎቜ፡መንገድ በመዝጋት ተቃውሞ ማሰማት ኚጀመሩ 11 ቀናት አልፎባ቞ዋል። ነዋሪዎቹ ዹዞኑ አተዳዳር እና ዚፀጥታ አካላት ምላሜ ሊሰጡን አልቻሉም ዹሚሉ ሲሆን ጥያቄያ቞ው ኹክልሉ መንግሥት መልስ እስካላገኘ ድሚስ ወደ ቀታ቞ው እንደማይመለሱ ይናገራሉ። ዹማይ ሓንሰ ነዋሪ ዚሆኑት አቶ አብርሃለይ ገብሚእዚሱስ "ዚወሚዳው አስተዳዳሪዎቜ ለራሳ቞ው ወደ ሜሚ እንዲቀርባ቞ው ክሳድ ጋባ ወሚዳው ትሁን አሉ። ህዝቡ ደግሞ ዹተሰጠንን ወሚዳ ዹመሆን መብት ለምን እንኚለኚላለን በማለት ነው ዹተቃውሞ ሰልፍ እያካሄደ ያለው" በማለት ገልፀዋል። ሌላኛዋ ዹማይሓንሰ ነዋሪ ወይዘሮ ለተብርሐን ደግሞ "ውሳኔው በጉቩ እና በሙስና በድብብቆሜ ዹተደሹገ ነገር ነው" በሚል ነዋሪው ለተቃውሞ እንደተነሳ ይጠቅሳሉ። ዚኮሮናቫይሚስ ወሚሚሜኝ ባለበት በዚህ ወቅት ለተቃውሞ መውጣታ቞ውን በሚመለኚትም ሲናገሩ "ሕዝቡ ስለተ቞ገሚ እንጂ ወዶ አይደለም። ሞትም ቢሆን እንሙት። ፍትህ ማጣትም ሞት ነውፀ በኮሮና መሞትም ሞት ነው" ብለዋል። ዚአስገደ ወሚዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብቶም አበራ ለቢቢሲ እንደተናገሩትፀ ዚአካባቢው ወጣቶቜ ለሰባት ቀናት ያህል መንገድ ዘግተው ተቃውሟቾውን ሲገልጹ ቆይተዋል። “ዚወሚዳው ምክር ቀት ዹወሰነውን ዹማይቀበሉ ኹሆነ ዹክልሉን ኃላፊዎቜ ማነጋገር እንዳለባ቞ው ገልጞንላ቞ዋል። ቢሆንም ኃላፊዎቜ መጥተው ካላናገሩን እኛ ወደ ክልል አንሄድም ብለዋል” ሲሉ ዋና አስተዳዳሪው አስሚድተዋል። ዚወሚዳው አስተዳደር ዹአገር ሜማግሌና ዚሐይማኖት መሪዎቜ በማነጋገርፀ ወጣቶቹ በሰላማዊ መንገድ እንዲግባቡ ለማድሚግ እዚጣሩ መሆኑንም አክለዋል። "ጥያቄያ቞ው በሰላማዊ እና ዲሞክራስያዊ መንገድ ለሚመለኹተው አካል እንዲያቀርቡ እዚሰራን ነው" ዚሚሉት አቶ ሃብቶም፡ መንገድ መዝጋት ግን ህጋዊ እንዳልሆነ እና ይህም ለህዝቡ በግልፅ እንዲነገሚው ተደርጓል በማለት ስለሁኔታው አስሚድቷል። ዚአክሱም ዩኒቚርሲቲው መምህር ዳንኀል ዘሚካኀል,, ዪኒቚርሰቲው በተለያዩ ዞኖቜ በህብሚተሰብ ዚኮሮናቫይሚስ ግንዛቀ እንዲኖር እዚሰራው ባለው ስራ በቡድን ወደ ምዕራባዊ ዞን ኚላካ቞ው አንዱ ነው። ዘጠኝ በመሆንም ወደ ምዕራባዊ ዞን በማይ ሓንሰ ሲጓዙ በዛ ማለፍ እንደማይቻል፣ በማይ ሓመንሰ ነዋሪዎቜ እንደተነገራ቞ው እና ይህን ብቻ ሳይሆን ወደ መጡበት አካባቢ እንዳይመለሱም ኚቡድኑ እና መኪኖቻ቞ው ጋር በአካባቢው ነዋሪዎቜ እንዲታገቱ መሆናቾውን ለቢቢሲ ተናግሚዋል። በማይ ሓንሰ ወደ 30 መኪኖቜ ታግተው እንደነበሚ እና ሌሎቾ አምልጠው በመውጣት አሁን 18 እንደቀሩ ዹሚናገሹው መምህር ዳንኀል፣ ህዝቡ 24 ሰዓታት ተሰባስቊ እንደሚውል እና እንደሚያድር ይናገራሉ። ለሊት በአስፋልቱ ዳር ዱንኳን ጥለው ኹ 200 እስኚ 300 ሰዎቜ አንድ ዱንኳን ላይ እንደሚያድሩ እና ይህም ለህዝቡ ጀና አደገኛ እንደሆነ ይናገራሉ። በህብተሚሰብ ዚኮሮናቫይሚስ ግንዛቀ ለመፍጠር ተጉዘው በመንገዳ቞ው እንዳያልፉ እና እንዳይመለሱ ዚተደሚጉት እነ አቶ ዳንኀል እና ባለደሚቊቻ቞ው በማይ ሓንሰ ለሶስት ቀናት እንዲቆዩ ተገደዋል። ለሶስት ቀናት በመኪና቞ው እያደሩ፣ ህዝቡ ለበሜታው ያለውን ግንዛቀ እንደተሚዱ ስለ ኮሮናቫይሚስ ዹቀሹፅዋቾውን ዚግንዛቀ ማስጚበጫ መልዕክቶቜን ማስደመጥ መጀመራ቞ውን ይናገራሉ። "ቢሆንም እንድናጠፋው ተነገሚን። ለሌላ አካባቢ ይዘነው ዚሄድነው መፀዳጃ አልኮል ለአካባቢው ዚጀና ሃላፊ ብንሰጥም ተወሰነ ለህዝቡ መስጠት በቢሮው ነው ዚቆለፈው። ህዝቡ ቀን ላይ ሲሰበሰብ እና ሲመክር ይውልናፀ ለሊት በጋራ ሲጚፍር ነው ዚሚያድሚው" ይህ ቊታም አስጊ ነው በማለት ፍራቻ቞ውን ይገልጻሉ። በማይ ሓንሰ ኚታገቱት ኚባባድ መኪኖቜ መካኚል፣ ኚጂቡቲ ዚመጡ 5 ሹፌሮቜ እንዳሉ እና ሙቀታቜን ተለክተናል በማለት ብዙ ሰዎቜ ጋር መነካካት እንደነበራ቞ው ይናገራሉ። ዹማይ ሓንሰ ነዋሪዎቜ ባንክ ቀቶቜ እና ምግብ ቀቶቜ አግልገሎት እንዳይሰጡ በግዎታ እንዲዘጉ ስለተደሚጉ ቆይታ቞ው ኚባድ እንደነበሚ ይገልፃሉ። ዹማይ ሓንሰ ነዋሪዎቜ ግን ዹዞን አስተዳደር እና ፖሊስ ጥያቄያ቞ውን ኚመስማት ይልቅ እኛ ያልናቜሁ ስሙ በማለት መፍትሄ እንዳልሰጣ቞ው ይገልፃሉ። ዹዞኑ ፖሊስም፡ ለአካባቢው ሚሊሻዎቜም መንገድ በመዝጋት ተቃውሞ እያሰማ ያለውን ሕዝብ በመበተን መንገዱ እንደኚፍቱ አልያም ሚልሻዎቹ ትጥቃ቞ው እንዲፈቱ ጫና በመፍጠር ላይ እንደሚገኝ ገልፀውልናል። ወይዘሮ ለተብርሃን "ሚሊሻዎቹ፡ እኛ ዚህዝብ ነንፀ እናንተ አላስታጠቃቜኑም። ህዝብ ያለን እንጂ እናንተ ያለቹን አንሰመማም። ኚፈለጋቹ ወደ ህዝቡ ቅሚቡ እና እንሚዳዳ ሲሉዋ቞ው ግዜ፡ በሉ ፈርሙ ሲሉዋ቞ው ህዝቡ ይህን ስለአወቀ ውጡልን በማለት አባሚርና቞ው" በማለት በሚሊሻዎቹ እዚተፈጠሚ ያለውን ጫና ገልፀውልናል። በማይ ሓንሰ ሚሊሻ ዚሆነት አቶ ገብሚክርስቶስ ገብሚኣሚጋዊም ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ ባለበት በአሁኑ ጊዜ ተሰባስቊ ተቃውሞ ማሰማት ጥሩ እንዳልሆነ ሕዝቡን ለማስሚዳት እንደሞኚሩ ገልጾው "ዹዞኑ አስተዳዳሪዎቜ ኚኮሮና ዚሚብሱ እንጂ ዚሚሻሉ አይደሉም" በማለት ሰሚ አለማግኘታ቞ውን ለቢቢሲ ገልጞዋል። "ዹዞኑ ፖሊስ ኮሚሜን ሕዝቡን ዚማትበትኑ ኹሆነ ትጥቃቜሁን እንድትፈቱ ብሎናል። እኛም ኚእናንተ ጋር ትውውቅ ዹለንም ሕዝቡ ነው ያስታጠቀንፀ ሕዝብ ትጥቃቜ እንድትፈቱ ካለን እንፈታለን። ካልሆነ ግን ለእናንተ ብለን ትጥቅ አንፈታም ብለና቞ዋል" በማለት ህዝቡ እያነሳ ያለው ጥያቄ ትክክል እንደሆነ ይናገራሉ። ወጀራት በተመሳሳይ ሁኔታ በደቡብ ምሥራቅ ትግራይ ወጀራትና ሕንጣሎ ዚተባሉ ኹዚህ ቀደም አንድ ዚነበሩፀ አሁን ግን ለሁለት ዹተኹፈሉ ወሚዳዎቜ አሉ። በወጀራት ወሚዳ ኚሚገኙት ባሕሪ ሓጾይ እና ዓዲ ቀይሕ ዚተባሉ ቊታዎቜ መካኚል ዚወሚዳ ማዕኹል መሆን ያለበት ባህሚሀፀይ ነው ሲሉ ነዋሪዎቜ ጥያቄ አቅርበዋል። ዹአሹናው አባል አቶ አንዶም እንደሚሉት ዚወሚዳነት ጥያቄ ዚተነሳበት ዚወጀራት ሕዝባዊ ተቃውሞ አራተኛ ቀኑን ይዟል። እዚህም አካባቢውን ዚሚያስተዳድሩት 'ዹዞን እና ዹክልል መልዕክተኞቜ ናቾው እንጅ እኛን አይወክሉንም' በሚለው ቅሬታ ዹተቃውሞው አካል ሆኗል ይላሉ። "ጥያቄው [ወሚዳነት] ተፈቅዶልን እያለፀ እንደገና ተኹልክለናል ዹሚል ነው።" ዚቀድሞው ዚወጀራት ወሚዳ ማዕኹል ዚነበሚቜው ጣቢያ ባሕሪ ሓፀይ ነዋሪዎቿፀ ባሕሪ ሓፀይ ዚወሚዳው ማዕኹል ስለነበሚቜ ኚጣቢያ ዓዲ ቀይሕ ጋር መወዳደር ዚለባትም በማለት ይጠይቃሉ። ይሁን እንጂ ዚወጀራት ምክር ቀት ዚወሚዳዋ ማዕኹል ማን ትሁን? በሚል ውሳኔ እንዳላሳለፈ ዚወሚዳው አስተዳደር አቶ ዳርጌ ፀጋይ ለቢቢሲ ገልፀዋል። በጣብያ ባሕሪ ሓፀይ ሰላዊ ሰልፍ ኚማካሄድ ጥያቄ ኚማቅሚብ ውጪ በወጣቶቹ ላይ ዹተወሰደ እርምጃ እንደሌለ ዋና አስተዳዳሪው ተናግሚዋል። "ወጣቶቹ ሥርዓት ያላ቞ው ና቞ው። እስኚአሁንም በአካባቢው ዹደሹሰ ቜግር ዚለም። አሁን ኚእነሱ ጋር ንግግር ጀምሚናል። መንግሥት ጥያቄያቜንን ሰምቶ ዚቀድሞ ወሚዳቜን ይመልስልን ነው ዚሚሉት" ብለዋል። ዚወሚዳው ምክር ቀት ዚትኛው ወሚዳ ማዕኹል እንደሚሆን ውሳኔውን ባያስተላልፍምፀ ዚባህሚሀፀይ ነዋሪዎቜ ኹዚህ በፊት ዚወሚዳው ማዕኹል ስለነበርን ኚሌሎቜ ጋር መወዳደር አንፈልግም ብለዋል። በክልሉ መዲና መቀለ ኚሳምንት በፊት ዚኮሮናቫይሚስ ወሚርሜኝ ስርጭትን ለመግታት ዚወጣውን ደንብ ተላልፈዋል ኚተባሉ ወጣቶቜ ጋር በተኹሰተ አለመግባባት ዚአንድ ሰው ህይወት መጥፋቱ እታወሳል። አቶ አንዶም እንደሚሉት በጞጥታ ኃይል አባላት በተተኮሰ ጥይት ኹሞተው ወጣት በተጚማሪ ሁለት ሰዎቜ ኹቆሰሉ በኋላ "በአካካቢ ባሉት 05፣ 06 በሚባሉ ቀበሌዎቜና አይደር ዚሚባለ ሠፈር ተቃውሞዎቜ ተቀስቅሰው ነበር" ብለዋል። 'መንገድ ተኚፍቷል' " ዹክልሉ መንግስት መፍትሄ ይስጠን" በሚልም ለአንድ ሳምንት መንገድ ዘግተው ዚነበሩ ነዋሪዎቹ ዹክልሉ መንግሥት ቀርቩ እንዲያናግራ቞ው በጠዚቁት መሰሚት በነዋሪዎቹና በመንግሥት አካላት መካኚል ውይይት መደሹጉን ሰምተናል። መንገዱን እንዲኚፍቱና ጥያቄያ቞ውን በህጋዊ መንገድ ለማቅሚብ መስማማታ቞ውን ዚወሚዳው አስተዳደር አቶ ሀብቶም አበራ ለቢቢሲ አሚጋግጠዋል። ነዋሪዎቹ ጥያቄያ቞ው ለክልሉ መንግስት ዚሚያቀርብላ቞ው 14 አባላት ያሉት ኮሚ቎ ማቋቋማቾውን ገልፀዋል። መንገዱም ኚዛሬ ኚሰአት ጀምሮ መኚፈቱንም ጹምሹው ተናግሚዋል።
news-55004605
https://www.bbc.com/amharic/news-55004605
ኚሬዲዮ ሞገድ አፈና እስኚ ርዕሰ መስተዳድር፡ ደብሚጜዮን ገብሚሚካኀል ማናቾው?
ኚፌደራል መንግሥቱ ሠራዊት ጋር እዚተካሄደ ባለው ወታደራዊ ግጭት ውስጥ ዋነኛው ተዋናይ ዹሆነው ዚትግራይ ክልል ገዢ ፓርቲ መሪና ዹክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ዚሆኑት ደብሚጜዮን ገብሚሚካኀል ዚፍጥጫው ቀዳሚ ገጜታ ና቞ው። ደብሚጜዮን ገብሚሚካኀል ማናቾው?
ደብሚጜዮን ገብሚሚካኀል (ዶ/ር) ደርግን ለመገርሰስ ዚተካሄደውን ትግል ዚተቀላቀሉት ዚአዲስ አበባ ዩኒቚርስቲ ትምህርታ቞ውን አቋርጠው ነበር። አብዛኛውን ሕይወታ቞ውን ያሳለፉት ዚህወሓት አባል ሆነው ነው። ዚቀድሞው ዚሜምቅ ተዋጊ ደብሚጜዮን (ዶ/ር) በሬዲዮ ሞገድ አፈናና ጠለፋ (ጃሚንግ) ይታወቃሉ። ዚወቅቱ ዚህወሓት ሊቀ መንበርና ዚትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዚሆኑት ደብሚጜዮን ባለ ትዳርና ዚትንሜ ልጅ አባት ና቞ው። ዚቅርብ ጓደኛቾውና ዚትግል አጋራ቞ው ዓለማዹሁ ገዛኞኝፀ ደብሚጜዮን በቮክኒክ ክፍል እንዲመደቡ ለህወሓት አመራሮቜ መጠቆማቾውን ያስታውሳሉ። ሁለቱም በተራራማዋ ትግራይ ወታደራዊ ስልጠና ወስደው ሲያጠናቅቁፀ ደብሚጜዮን ቎ክሊካዊ ጉዳዮቜን በተመለኹተ ዚተሻለ ክህሎት እንዳላ቞ው ማስተዋላ቞ውን ዚትግል ጓዳ቞ው ይናገራሉ። ደብሚጜዮንን ዚሚገልጿ቞ው "ብሩህ፣ ቁጥብ፣ ኹተሜ" በማለት ነው። "ኚወዳደቁ ነገሮቜ ዚራሱን አምፖል ይሠራ ነበር" ያደጉት ሜሬ ነው። ዚመጀመሪያ ደሹጃ ተማሪ ሳሉ ያሚጀ ባትሪ፣ ራድዮ እና ዚኀሌክትሪክ መሣሪያዎቜ እዚሰበሰቡ ይጠግኑ እንደነበር አቶ ዓለማዹሁ ያስታውሳሉ። "በኚተማቜን ማንም ሰው መብራት ሳይኖሚው ኚወዳደቁ ነገሮቜ ዚራሱን አምፖል ይሠራ ነበር" ይላሉ። ህወሓት ዚያኔውን ዚኢትዮጵያ ወታደራዊ ኃይል ላይ እንዲሰልል በማስቻል እንዲሁም ዚራድዮ ሞገድ በማቋሚጥ ኹፍተኛ ሚና ዚተጫወቱ ሲሆንፀ በህወሓት ዹቮክኒክ ክፍል ኹፍተኛ ደሹጃ ላይም ደርሰዋል። "ዚህወሓት ዚነፃነት ታጋዮቜ ዚጠላትን እንቅስቃሎ ቀድመው እንዲያውቁ በማስቻል እንድናሞንፍ ሚድቶናል። መገናኛ መስመራ቞ው ስለሚቋሚጥ ጥቃት ሲደርስባ቞ው እርስ በእርስ መነጋገር አይቜሉም ነበር።" ደብሚጜዮን ክህሎታ቞ውን ለማዳበር በወቅቱ በሐሰተኛ ፓስፖርት ወደ ጣልያን አቅንተዋል። ወደ አገር ቀት ሲመለሱ ዚህወሓትን ዚመጀመሪያ ራድዮ ጣቢያ ድምጺ ወያነ መስርተዋል። በትግርኛ መርሃ ግብር ዚሚያሰራጭ ጣቢያ መኖሩ ዹክልሉን ተወላጆቜ አኩርቷል። "ኚተራራው ተንሞራቶ አተሹፍነው" በደርግ ሰላዮቜ እይታ ውስጥ ላለመግባት በሌሊት ተጉዘው ተራራ ላይ አንቮና ይሰቅሉ እንደነበር ሌላው ሜምቅ ተዋጊ ማሟ ገብሚኪዳን ያስታውሳሉ። "አንድ ምሜት ኚተራራው ተንሞራቶ እኔና ሌሎቜ ጓዶቻቜን አተሚፍነው። ሞቶ ቢሆን ኖሮ ይሄ ራድዮ ጣቢያ ይኚፈት ነበርን? ብዬ እጠይቃሉ" ይላሉ። ዋና መቀመጫውን መቀለ ያደሚገው ድምጺ ወያነ አሁንም በተለያዩ ቋንቋዎቜ በሚያሰራጚው መርሃ ግብርፀ ጊርነቱን በተመለኹተ ዚህወሓትን መግለጫዎቜ ያስተላልፋል። ጣቢያው ስለ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ዹሰሉ ትቜቶቜ ያስተናግዳል። ዚፌደራል መንግሥት ዚስርጭት ሞገዱን ቢቆርጠውም በነጋታው መርሃ ግብር ወደማስተላለፍ ተመልሰዋል። "አልበሰልክምፀ ትክክለኛው እጩ አይደለህም ብዬዋለሁ" ጠቅላይ ሚንስትሩ ወደ ሥልጣን ዚመጡ ሰሞን ኹርዕሰ መስተዳድር ደብሚጜዮን (ዶ/ር) ጋር ተወዳጅተው ነበር። ዐብይ (ዶ/ር) በመቀለ አቀባበል ሲደሚግላ቞ውፀ "ትግራይ ዚታሪካቜን መሠሚት ናት። ዚውጪ ወራሪዎቜ [ጣልያን እና ግብፅን ጚምሮ] ተሾንፈው ዚተዋሚዱበት ቊታ ነው። በዘመናዊ ዚአገራቜን ታሪክ ትግራይ ዚኢትዮጵያ ማህጾን ናት" ብለው ነበር። በወቅቱ ደብሚጜዮን (ዶ/ር)ፀ ጠቅላይ ሚንስትሩ ኚኀርትራው ፕሬዘዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ሰላም በማውሚዳ቞ው አሞግሰዋቾው ነበር። ዹሰላም ስምምነቱ ለዓመታት ዹዘለቀውን ጊርነትም ሰላምም ያልነበሚበትን ሁኔታ ለውጧል። ያኔፀ "ዐብይ ወደ ኀርትራ ተጉዞ ኚኢሳያስ ጋር ተገናኝቷል። ለዓመታት ይህን ማድሚግ አልተቻለም ነበር። ትልቅ ነገር ነው። ለአገሪቱ ዹጎላ እድል ይዞ ይመጣል" ሲሉ ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግሹው ነበር። በሁለቱ መሪዎቜ መካኚል ያለው ውጥሚት በጊዜያዊነት ቢሆንም ተሾፍኖ ነበር። በኢሕአዎን ውስጥ ለመሪነት ውድድር ሲካሄድ ጠቅላይ ሚንስትሩ ያሞነፉት ደብሚጜዮንን ሚትተው ነበር። "አልበሰልክምፀ ትክክለኛው እጩ አይደለህም ብዬዋለሁ" ሲሉም ደብሚጜዮን እአአ 2019 ላይ ለፋይናንሜያል ታይምስ ጋዜጣ አስተያዚታ቞ውን ሰጥተው ነበር። ድጋፍ እና ተቃውሞ ለ27 ዓመታት በኢሕአዎግ ውስጥ ህወሓት ዚበላይነት ሚና ሲጫወት በጭቆና እና ሙስና እንደመወንጀሉ ዚደብሚጜዮን መሾነፍ ተጠባቂ ነበር ማለት ይቻላል። ስለ ደብሚጜዮን (ዶ/ር) ዚሚሰጡ አስያዚቶቜ ድጋፍም ነቀፋም ዹቀላቀሉ ና቞ው። ተቺዎቻ቞ው እንደሚሉትፀ ዚኢትዮጵያ ደኅንነት ምክትል ሳሉ ተቃዋሚዎቜን ይሰልሉ፣ ተቃውሞን ያዳፍኑ ነበር። በተቃራኒው ደጋፊዎቻ቞ው ዚኢትዮጵያን ዚ቎ሌኮምንኬሜን ዘርፍን አዘምነዋል ይላሉ። በኢትዮጵያ ዚተንቀሳቃሜ ስልክ ተደራሜነትን ለማሚጋገጥ በቢሊዮን ዶላር ዹሚቆጠር ፕሮጀክት ጀምሚዋል። በሌላ በኩል መንግሥት በ቎ሌኮም ዘርፉ ዚበላይነት መያዙ ያስተ቞ዋል። ተቃውሞ ሲኖር ዚኢንተርኔት አገልግሎት በማቋሚጥም መንግሥት ይወቀሳል። ዚፖሊሲ ጉዳዮቜ ባለሙያው ዳደ ደስታ "አብዛኞቹ ዚ቎ሌኮም ፕሮጀክቶቜ ዚሚመሩት በእሳ቞ው ነበር። አዲስ አበባ ያለው ዚኢንፎርሜሜን ቮክኖሎጂ ፓርክ ዚእሳ቞ው ሐሳብ ነው። አሻራ቞ውን በብዙ ዚመንግሥት ድርጅቶቜ ላይ አሳርፈዋል" ይላሉ። "ልማት እንጂ ጊርነት አንፈልግም" ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ (ዶ/ር) ኢሕአዎግን አክስመው ብልፅግና ፓርቲን ሲመሠርቱ ዚህወሓትና ዚኢሕአዎግ ግንኙነት ተቋሚጠ። ደብሚጜዮን (ዶ/ር) ወደ ትግራይ ሲመለሱ እንደ ለውጥ ኃይል ይታዩ ጀመር። አራት አዳዲስ ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜ በትግራይ ክልላዊ ምርጫ እንዲሳተፉ ፈቅደዋል። በተደጋጋሚ "በሬ ለሁሉም ክፍት ነው" ሲሉም ይደመጣሉ። ሌላው ዚሚታወቁበት አባባል "ልማት እንጂ ጊርነት አንፈልግም" ዹሚለው ነው። አሁን ግን በመቶዎቜ ዚሚቆጠሩ ሰዎቜ ዚሞቱበት እና ኹ30,000 በላይ ዜጎቜን ለስደት ዚዳሚገ ጊርነት ውስጥ ገብተዋል። ጊርነቱፀ መንገድና ሕንጻዎቜን ጚምሮ መሠሹተ ልማት ላይም ውድመት አስኚትሏል። "ደብሚጜዮን ይህንን ጊርነት እንደ እርግማን ነው ዚሚያዩት" ሰሉ ዳደ ያስሚዳሉ። አያይዘውም ህወሓት በፌደራል መንግሥቱ ትግራይ ላይ ዚሚሟም ዚአስተዳደር መዋቅርን አጥብቆ እንደሚታገል ይናገራሉ። "ኚኀርትራ ጋር ጊርነት ውስጥ ነበሩ። ኹደርግ ጋርም ታግለዋል። ስለዚህ ልምዱ አላ቞ው። ጊርነት ዚሕዝብ ይሁንታን ይፈልጋል። ያ ደግሞ በትግራይ ሕዝብ ዘንድ አለ" ሲሉም ያብራራሉ። ተንታኙ ግጭቱ ሚዥም እንደሚሆን ይናገራሉ። ጠቅላይ ሚንስትሩ በበኩላ቞ው ዚህወሓት አመራሮቜና ወታደራዊ ባለሥልጣኖቜን ለፍርድ አቅርበው ጊርነቱን እንደሚያሞንፉ እርግጠኛ መሆናቾውን ገልጞዋል።
news-55516802
https://www.bbc.com/amharic/news-55516802
[ምልኚታ] ፡ ለዘመናት ዹዘለቀው ዚኢትዮጵያና ሱዳን ዚድንበር አለመግባባት
በኢትዮጵያና በሱዳን ድንበር ለዘመናት በቆዹው ውዝግብ ምክንያት በሁለቱ አገራት ሠራዊቶቜ መካኚል ዹሚደሹግ ግልጜ ወታደራዊ ግጭት ኹዚህ በፊት እምብዛም አጋጥሞ ባያውቅም በቅርቡ በድንበር አካባቢ ዚታዚው ሁኔታ ግን ነገሮቜ እዚተቀዚሩ መሆናቾውን ያመለክታል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብደላ ሐምዶክና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ለዚህ ቜግር ቀዳሚ ምክንያት ዹሰሜን ምዕራብ ዚኢትዮጵያ ግዛት ኹሆነው ኚአማራ ክልል ጋር በሚዋሰነውና ዚሱዳን ዚዳቊ ቅርጫት ተብሎ በሚጠራው ዚገዳሪፍ ግዛት ውስጥ በሚገኘው አል ፋሻጋ አካባቢ ዚግዛት ይገባኛል ነው። ሁለቱን አገራት ዹሚለዹው ድንበር መልክአ ምድራዊ አቀማመጊቜን በመጥቀስ ኹሚገለጾው ውጪ በመሬት ላይ በግልጜ ተለይቶ ዚተካለለ አይደለም። ዹቅኝ ግዛት ስምምነቶቜ በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ድንበሮቜ በጣሙን አወዛጋቢ ና቞ው። ኚአስርት ዓመታት በፊት ኢትዮጵያ ኚሶማሊያ ጋር በኩጋዮን ዚተነሳ ጊርነት አድርገዋል። እንዲሁም ኹ20 ዓመታት በፊት ደግሞ በትንሿ ባድመ ይገባኝል ምክንያት ኢትዮጵያና ኀርትራ ጊርነት ውስጥ ገብተው ነበር። በጊርነቱ 80 ሺህ ዚሚደርሱ ወታደሮቜ መሞታ቞ው ዹሚነገር ሲሆን በዚህም ምክንያት በሁለቱ አገራት ፍጥጫ ውስጥ ቆይተዋል። በተለይ ደግሞ ዓለም አቀፉ ፍርድ ቀት ለኀርትራ ኹወሰናቾው ግዛቶቜ ኢትዮጵያ ለመውጣት ፈቃደኛ ባለመሆኗ አለመግባባቱ ለዓመታት ቆይቷል። እነዚህ ቊታዎቜ በዚህ ዓመት በትግራይ ውስጥ ዹተቀሰቀሰውን ውጊያ ተኚትሎ ዚኀርትራ ወታደሮቜ መልሰው ተቆጠጥሚዋ቞ዋል። ኚዓመታት በፊት ኢትዮጵያና ሱዳን ለሹጅም ጊዜ ተቋርጩ ዹነበሹውን 744 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውን ድንበራ቞ውን ለይቶ ለማመላኚት ዚሚያስቜል ንግግርን መልሰው ጀመሩ። በዚህ መፍትሄ ለመስጠት አስ቞ጋሪ ዹሆነው አካባቢ ፋሜጋ ዚሚባለው ነበር። በ1902 እና በ1907 (እአአ) ዹነበሹው ዹቅኝ ግዛት ስምምነት መሰሚት ዓለም አቀፉ ድንበር ወደ ምሥራቅ ይዘልቃል። በዚህም ሳቢያ መሬቱ ወደ ሱዳን ዚሚካተት ይሆናል። ነገር ግን ቊታው ኢትዮጵያውያን ዚሚኖሩበት ሲሆን ዚግብርና ሥራ በማኹናወንም ዚሚጠበቅባ቞ውን ግብር ለኢትዮጵያ መንግሥት ሲኚፍሉ ቆይተዋል። ዚሱዳን ወታደራዊ ባለስልጣናት አወዛጋቢውን ቊታ ይዘው እንደሚቆዩ አሳውቀዋል 'ድብቅ ስምምነት' ሁለቱ አገራት ሲደሚጉ በነበሹው ዚድንበር ድርድር አማካይነት በ2008 (እአአ) ላይ ኚመግባባት ደሚሱ። በዚህም ኢትዮጵያ ለሕጋዊው ድንበር ዕውቅና ስትሰጥ ሱዳን ደግሞ ኢትዮጵያውያኑ በስፍራው ያለቜግር ሕይወታ቞ውን እንዲቀጥሉ ፈቀደቜ። ይህም አስኚ ቅርብ ጊዜ ድሚስ በድንበር አካባቢ ያሉ ዚነዋሪዎቜን ህይወት ሳያደናቅፍ ኢትዮጵያ ግልጜ ዚድንበር መለያ እንዲኖር እስክትጠይቅ ድሚስ ቀጥሎ ነበር። በሁለቱ አገራት መካኚል ኚስምምነት ዚተደሚሰበትን ዹዚህ ዚድርድር ልዑክ ዚተመራው ዚህወሓት ኹፍተኛ ባለስልጣን በሆኑት በአባይ ፀሐዬ ነበር። ህወሓት ኹማዕኹላዊው መንግሥት ስልጣን ሲወገድ ዚአማራ ብሔር መሪዎቜ ኚሱዳን ጋር ዹተደሹሰው ስምምነት በአግባቡ ሳያውቁት ዹተደሹገ ድብቅ ውል ነው ሲሉ ተቃውመውታል። በአሁኑ ጊዜ በፋሜጋ አካባቢ ለተኹሰተው ግጭት ሁለቱም ወገኖቜ ዚዚራሳ቞ውን ምክንያት ያቀርባሉ። ነገር ግን ዹተኹሰተው ዚሚያኚራክር አይደለምፀ በዚህም ዚሱዳን ሠራዊት ኢትዮጵያዉያኑን ኚሚኖሩባ቞ው መንደሮቜ ለቀው እንዲወጡ አድርጓል። በቅርቡ ጂቡቲ ውስጥ በተካሄደው ቀጠናዊ ዚኢጋድ ጉባኀ ላይ ዚሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሐምዶክ ጉዳዩን ኚኢትዮጵያው አቻ቞ው ዐብይ አህመድ ጋር አንስተው ተወያይተዋል። ስለድንበሩ ጉዳይ ድርድር ለማድሚግ ቢስማሙም ሁለቱም ዚዚራሳ቞ውን ቅድመ ሁኔታ አስቀምጠዋል። ኢትዮጵያ በድንበር አካባቢ ጉዳት ዚደሚሰባ቞ውን ማኅበሚሰቊቜ ሱዳን እንደትክስ ስትጠይቅፀ ሱዳን በበኩሏ ነገሮቜ ወደ ነበሩበት እንዲመለሱ ትፈልጋለቜ። በበርካታ ዚድንበር ውዝግቊቜ ውስጥ እንደሚያጋጥመው ሁሉም ወገን ዚተለያዚ ዚታሪክ፣ ዹሕግና ለዘመናት ዚቆዩ ስምምነቶቜን እንዎት መተርጎም እንዳለባ቞ው ዚዚራሱ ትንታኔ አለው። ነገር ግን ይህ ዚሁለት ጉዳዮቜ ማሳያ ምልክት ነውፀ ይህም ኹጠቅላይ ሚኒስርት ዐብይ ዚፖሊሲ ለውጥ ጋር ዚሚያያዝ ነው። ዚአማራ ክልል ኃይሎቜ በሁመራ ግዛት ይገባኛል በፋሜጋ አካባቢ ዚሚኖሩት ኢትዮጵያውያን ዚአማራ ብሔር አባላት ና቞ው። ይህም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአገሪቱ ትልቁ ኹሆነው ዚኊሮሞ ብሔር በኩል ዚነበራ቞ው ድጋፍ በኹፍተኛ ደሹጃ በመቀነሱ ዚፖለቲካ ድጋፍ ለማግኘት ትኩሚት ያደሚጉበት ማኅበሚሰብ ነው። አማራ በአገሪቱ ሁለተኛው ትልቁ ብሔር ሲሆን በአገሪቱ ዚመሪነት ስፍራም ታሪካዊ ስፍራ አለው። ኹወር በፊት ዚፌደራል መንግሥቱ በትግራይ ክልል በህወሓት ኃይሎቜ ላይ ድል መቀዳጀቱን ተኚትሎ ዚአማራ ክልል ዚግዛት ይገባኛል ጥያቄን እያነሳ ነው። ዚህወሓት ኃይሎቜ ሜንፈት ሲገጥማ቞ውና ዚአማራ ክልል ሚሊሻ ጥያቄ ዚተነሳባ቞ውን አካባቢዎቜ ሲቆጣጠር ዚራሱን ባንዲራ በመስቀል "ወደ አማራ ክልል እንኳን ደህና መጡ" ዹሚሉ ዚመንገድ ምልክቶቜን አስቀምጧል። ቊታዎቹ በአማራ ክልል ጥያቄ ዚሚቀርብባ቞ው ሲሆን ወደ ትግራይ ክልል ዚተጠቃለሉት ህወሓት ስልጣን በያዘበት ጊዜ ነበር። ምንም እንኳን ጉዳዩ ዚውስጣዊ ዚድንበር ጉዳይ ሳይሆን ኚጎሚቀት አገር ጋር ያለ ዚግዛት ጉዳይ ቢሆንምፀ ዚፋሜጋው ግጭትም ተመሳሳይ ዚግዛት ይገባኛል ጥያቄን ዹተኹተለ ነው። ዹጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ዹውጭ ግንኙነት ዚፖሊሲ ለውጥ ቜግሩ በሰላማዊ መንገድ እንዳይፈታ ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ ምክንያት ሆኗል። ለ60 ዓመታት ዚኢትዮጵያ ስትራተጂካዊ ዓላማ ግብጜን መግታት ላይ ያተኮሚ ነበር። ነገር ግን ኚዓመት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዚወዳጅነት እጃ቞ውን ዘርግተዋል። ኢትዮጵያና ግብጜ ዚአባይ ወንዝን ዹህልውናቾው ጥያቄ አድርገው ይመለኚቱታል። ግብጜ በቅኝ ግዛት ዘመን ተቀመጡ ስምምነቶቜን መሠሚት አድርጋ በላይኛው ዚተፋሰሱ አገራት ውስጥ ዚሚገነቡ ግድቊቜ በውሃ ድርሻዋ ላይ ዚተጋሚጡ አደጋዎቜ እንደሆኑ ትመለኚታ቞ዋለቜ። ኢትዮጵያ ደግሞ ዚአባይ ወንዝን ለምታደርገው ዚኢኮኖሚ ልማት በጣሙን አስፋላጊ ለሆነው ዚኀሌክትሪክ ኃይል ዋነኛ ምንጭ አድርጋ ትመለኚተዋለቜ። በግዙፉ ዚታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሎ ግድብ ግንባታ ላይ ውዝግብ ዚተነሳውም በዚህ ሳቢያ ነው። ዚኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስ቎ር ለሚያካሂደው ዹውሃ ዲፕሎማሲ ዋነኛው መሰሚቱ በቀሪዎቹ ዚአባይ ወንዝ ዹላይኛው ተፋሰስ ዚአፍሪካ አገራት መካኚል ተፈጥሮ ዹነበሹው ዚትብብር መዋቅር ነበር። ዓላማውም በርካታ አገራትን ያካተተ በአባይ ወንዝ ዹውሃ ክፍፍል ላይ አጠቃላይ ስምምነት መድሚስ ነበር። በዚህ መድሚክ ላይም ግብጜ በቁጥር ተበልጣ ዚበላይነትን ማግኘት አልቻለቜም። ህዳሎው ግድብም ጎርፍን በመቆጣጠር፣ ዚመስኖ ልማቷን በመጹመርና ርካሜ ዚኀሌክትሪክ ኃይል ለማግኘት እንደሚያስቜላት በመሚዳትፀ ሱዳንም ኚቀሪዎቹ ዚአፍሪካ አገራት ወገን ተሰልፋ ነበር። ግብጜ ግን በቅኝ ግዛት ዘመን ስምምነት ላይ ዹተቀመጠውን አብዛኛውን ዚአባይ ወንዝን ውሃ ለማግኘት ዚሚያስቜላትን ጥቅም ለማስኚበር ቀጥተኛ ዚሁለትዮሜ ድርድር ፈልጋ ነበር። በጥቅምት ወር 2012 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስርት ዐብይ በሩሲያ አፍሪካ ጉባኀ ላይ ለመሳተፍ ወደ ሩሲያ ሶቺ በሄዱበት ጊዜ ኚግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱል ፋታህ አልሲሲሰ ጋር ተገናኝተው ነበር። ዹውጭ ጉዳይ ሚኒስ቎ር ባለስልጣናት ባልተገኙበት በዚህ ውይይት ኢትዮጵያ በአባይ ውሃ ላይ ኚምትኚተለው ስትራተጂ ውጪ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፕሬዝዳንት አል ሲሲ ዹቀሹበውን በህዳሎው ግድብ ድርድር ላይ አሜሪካ በአሞማጋይነት እንድትገባ ዹቀሹበውን ሐሳብ ተቀበሉት። በዚህም ሂደት አሜሪካ ኚግብጜ ጎን ቆመቜ። ኚኀርትራ ጋር ዹነበሹውን ውጥሚት ለማስወገድ ዚቻሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተመሳሳይ ኚግብጜ ጋርም ኚስምምነት እንደሚደርሱ አስበው ነበርፀ ግን አልሆነም። እንዲያውም እራሳ቞ውን አጣብቂኝ ውስጥ አስገቡ። በዋሜንግተኑ ድርድር ላይ ዚተጋበዘቜው አገር ለዓመታት በአሜሪካ ሜብርተኞቜን ኹሚደገፉ መንግሥታት ዝርዝር ውስጥ ገብታ ዚገንዘብ ማዕቀብ ስር ዚቆዚቜውና ለአሜሪካ ተጜእኖ ተጋላጭ ዚሆነቜው ሱዳን ነበሚቜ። በድርድሩም ሱዳን ኚግብጜ ጋር ተስማምታ ቆመቜ። በኢትዮጵያውያን ዘንድ አሜሪካ ያቀሚበቜው ዚስምምነት ሐሳብ ተቃውሞ ዹገጠመው ሲሆንፀ በዚህም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሐሳቡን ውድቅ ለማድሚፈግ ተገደዱ። ይህንንም ተኚትሎ አሜሪካ ለኢትዮጵያ ኚምትሰጠው እርዳታ ዹተወሰነውን አገደቜ። ዚአሜሪካው ፕሬዝዳንትም ግብጜ ዚህዳሎውን ግድብ "ልታፈነዳው" ትቜላለቜ ሲሉ ያስጠነቀቁ ሲሆንፀ ኢትዮጵያም ግድቡ በሚገነባበት አካባቢ ማንኛውም በሚራ እንዳይካሄድ አደሚገቜ። አብዛኛው ዚአባይ ውሃ ዹሚመነጹው ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ገባር ወንዞቜ ነው ተቃዋሚዎቜን መደገፍ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ በትግራይ ውስጥ ኹተኹሰተው ግጭትና በሱዳን ድንበር ካለው ውጥሚት በተጚማሪ ኚግብጜ ጋር ውዝግብ ውስጥ መግባት አይቜሉም። ኚሱዳን ጋር ያለው ዚድንበር ቜግር በታሪክ ለሹጅም ጊዜ ዹቆዹውን ውዝግብ መልሶ እንዲያንሰራራ አድርጎታል። ኚአርባ ዓመታት በፊት ሱዳን ህወሓትን ጚምሮ ዚብሔር ሾማቂ ቡድኖቜን ስታስታጥቅ ዚኢትዮጵያው ወታደራዊ መንግሥት ደግሞ ዚሱዳን አማጺያንን ይሚዳ ነበር። በአውሮፓውያኑ በ1990ዎቹ ሱዳን ታጣቂ እስላማዊ ቡድኖቜን ስትደግፍ ኢትዮጵያ ደግሞ ዚሱዳን ተቃዋሚዎቜን ትሚዳ ነበር። በትጥቅ ዹተደገፉ ግጭቶቜና አለመሚጋጋቶቜ በብዙ ዚኢትዮጵያ ክፍሎቜ ውስጥ በሚያጋጥሙበት በዚህ ጊዜፀ ሱዳን በቅርቡ ዹተሟላ ባይሆንም በዳርፉርና በኑቢያ ተራሮቜ ካሉ አማጜያን ጋር ዹሰላም ስምምነት ደርሳለቜ። በዚህ ሁኔታም አገራቱ ወደ ቆዹው አንዳ቞ው ዚአንዳ቞ውን ሠላም ወደ ሚያናጋ ተግባር ሊመለሱ ይቜላሉ። በሱዳንና በኢትዮጵያ መካኚል ያለው ግንኙነት ኹፍተኛ ኚሚባለው ደሹጃ ላይ ደርሶ ዹነበሹው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ወደ ካርቱም ሄደው አልበሜር ኚስልጣን ኚተወገዱ በኋላ ዚዲሞክራሲ መብት ጠያቂ ተቃዋሚዎቜና ዚአገሪቱ ጀነራሎቜ ዚሲቪል አስተዳደር እንዲመሰርቱ ድጋፍ ባደሚጉበት ጊዜ ነው። ዚሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሐምዶክም ውለታ቞ውን ለመመለስ በትግራይ ግጭት በተኚሰተበት ጊዜ መፍትሄ ለማምጣት ለማሾማገል ሙኚራ አድርገው ነበር። ነገር ግን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ኢትዮጵያ ውስጣዊ ጉዳይዋን በራሷ ትወጣዋለቜ በሚል ሳይቀበሉት ቀርተዋል። ሚሃብና አሰቃቂ ታሪክ ያላ቞ው ስደተኞቜ ኚትግራይ ወደ ሱዳን እዚሄዱ ባሉበት ሁኔታ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሜምግልናውን ላለመቀበል ዹበለጠ አስ቞ጋሪ ሊሆንባ቞ው ይቜላል። ምናልባትም በሁለቱ አገራት መካኚል አዲስ ዙር ድንበር ተሻጋሪ ጠላትነት ሊቀሰቀስ ዚሚቜልበት ስጋት ያለ ሲሆን ይህም ዹቀጠናውን ቀውስ ሊያባብሰው ይቜላል። *አሌክስ ደ ዋል በአሜሪካው ተፍትስ ዩኒቚርስቲ በሚገኘው ዹፍሌቾር ዹሕግና ዲፕሎማሲ ትምህርት ቀት ውስጥ ዚወርልድ ፒስ ፋውንዎሜን ዋና ዳይሬክተር ነው።
44286378
https://www.bbc.com/amharic/44286378
ኀርትራ ውስጥ በአጋጠመ ዚመኪና አደጋ 33 ሰዎቜ ሞቱ
ትላንትና ግንቊት 20 ሚፋዱ ላይ ኚአስመራ ወደ ኹሹን በሚወስድ መንገድ በአጋጠመ ዚአውቶቡስ አደጋ 33 ሰዎቜ እንደሞቱ መንግስታዊው ዹዜና ማዕኹል አስታወቀ።
ኚአስመራ በስተ ሰሜናዊ ምዕራብ ሜንድዋ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ በአጋጠመ ዚአውቶቡስ መገልበጥ አደጋ ሹፌሩን ጚምሮ 11 ሰዎቜ በጜኑ በመቁሰላቾው ለኹፍተኛ ህክምና አስመራ በሚገኘው ሐሊበት ሆስፒታል እንደተወሰዱ ዜናው በተጚማሪ አሚጋግጧል። አውቶቡሱ፣ አመታዊውን ዚቅድስት ማርያም ክብሚ-በዓልን ለማክበር ዹሚጓዙ 45 ሰዎቜ ዚጫነ እንደነበርና መንገዱን ስቶ 80 ሜትር ጥልቀት ያለው ገደል ውስጥ መግባቱ ተገልጧል። አደጋው ዹደሹሰው ኚተገቢው ፍጥነት በላይ በማሜኚርኚር ሊሆን እንደሚቜል ምርመራውን በማካሄድ ላይ ዹሚገኘው ዚኀርትራ ትራፊክ ፖሊስ ጜሐፈት ቀት መግለጡን ዹመገናኛ ብዙሃኑ ዘገባ ያስሚዳል።
news-49494997
https://www.bbc.com/amharic/news-49494997
በፈሹንጅ "ናይት ክለብ" ጉራግኛ ሲደለቅ
አንድ ዹሆነ ዚአውሮጳ ጉራንጉር ውስጥ፣ «አንድ-ሁለት» ለማለት፣ ወደ አንድ ዹሆነ መሞታ ቀት ጎራ ስትሉ፣ ለአመል እንኳ አንድ ሐበሻ በሌለበት አንድ ዹፈሹንጅ ቡና ቀት፣ አንድ ቀጭን ዘለግ ያለ 'ፈሹንጅ'፣ ኚኢትዮጵያ ሙዚቃዎቜ አንዱን ኚፍቶ፣ ትኚሻውን ሲሰብቅና ሲያ'ሰብቅ ብታዩት ምን ይሰማቜኋል? ለዚያውም ዚብዙዬን...
ዲጄ አሌክስ በ'ኀይልሃውስ' "ፎቅና መርቌዲስ ስሜት አይሰጡኝምፀ እኔ ፍቅር እንጂ ሐብት አያሞኘኝምፀ አያገባው ገብቶ ሰው ይዘባርቃልፀ እኔ ስሜን እንጂ ስሜ቎ን ማን ያውቃል..." ዹሚለውን...ወዝዋዥና ወስዋሜ ዜማ...። ይህ ሰው አሌክሳንደር ባውማን ይባላል። 43 ዓመቱ ነው። ዲጄ ስለሆነ አሌክስ እያልን እናቆላምጠዋለን። በስዊዘርላንድ ዙሪክ ጎታርድ እና ኹርን በሚባሉ ዚምሜት ክለቊቜ ውስጥ...ዹሙዚቃ ሾክላ 'ያቁላላል'ፀ አቁላልቶ ለጆሮ ያጎርሳል፣ አጉርሶ አቅል ያስታልፀ ዹ60ዎቹን ዚኢትዮጵያን ሙዚቃፀ ዚያ ዹወርቃማውን ዘመን። አሌክስ እንኳን ኢትዮጵያ፣ አፍሪካንም ሹግጩ ስለማወቁ እንጃ...። ቱኒዚያና ደቡብ አፍሪካ አንድ ሁለቮ ገባ ብዬ ወጥቻለሁ ያለኝ መሰለኝ። ኚዚያ ውጭ 'ወላ ሃንቲ'። አማርኛም ሆነ ኊሮምኛ፣ ትግርኛም ሆነ ጉራግኛ...ጆሮውን ቢቆርጡት አይሰማም። 'ወላ ሃባ...' ኟኖም ዚትኞቹ ዚኢትዮጵያ ሞክላዎቜ በምን ቋንቋ ፀ በምን ዘመንፀ ኹምን ባንድ ጋር እንደተቀነቀኑ ሲያስሚዳ አገር ፍቅር ጓሮ ወይ እሪ በኚንቱ ጀርባ ያደገ ነው ዚሚመስለው። ዚዘፋኞቻቜንን ታሪክና ዹሙዚቃ አጀማመራ቞ውን ሳይቀር ለጉድ ይተነትናል...ለዚያውም ብ...ጥ...ር...ጥ..ር አድርጎ...። ዚቢቢሲ ዘጋቢ አሌክስን ለመጀመርያ ጊዜ ያገኘው በስዊዘርላንድ፣ ዩኒቚርሲሻትስትራሰ 23 ጎዳናፀ ኚታላቁ ዙሪክ ዩኒቚርስቲ ማዶ በሚገኘው «ኀይልሀውስ» ውስጥ ነበር። • ባህልን በኀሌክትሮኒክ ሙዚቃ ዹቀመመው ሮፍናን • አውታር - አዲስ ዹሙዚቃ መሞጫ አማራጭ «ኀይልሃውስ» በዓለም ዙርያ ዹተጠመቁ እልፍ ዚቢራና ዚድራፍት መጠጊቜ ዚሚሞጡበት ዕውቅ መጠጥ ቀት ነው። ያን ምሜት እዚያ ግቢ ጓሮ ኚድራፍቱ ፉት እያሉ እራታ቞ውን ዚሚመገቡ በርካታ ስዊሳዊያን ይታዩ ነበሩ። ዲጄ አሌክስ ታዲያ ለታዳሚው ዚኢትዮጵያን ዹወርቃማውን ዘመን ሙዚቃዎቜ በሾክላ እያጫወተ ሲያምነሞንሻ቞ው አድሯል። በዚያቜ ድንገተኛ ምሜት ያለቀጠሮ ዚተገናኙት አሌክስና ዚቢቢሲ ዘጋቢ "አንድ ሁለት" እያሉ ለአንድ ሰዓት ያህል ቆይተዋል። ወጋቾው በጥዑም ሙዚቃዎቜ ሲታጀብ ዹሚኹተለውን መልክ ይይዛል። "ፈሚንጆቜ ዚኢትዮጵያን ሙዚቃ ሲሰሙ ጆሯ቞ው ግር ይለዋል" ዲጄ አሌክስ ሳቂታና ተግባቢ ነው። ዲጄ ኟኖ ድሮስ ሊኮሳተር ያምሚዋል እንዎ?! ኚፊትለፊቱ ሾክላ ማጫወቻ ጥንድ ምጣዶቜ አሉት። ጆሮው 'ዚኚባድ መኪና ጎማ' በሚያካክሉ ዹአፍኖ- ማድመጫ (Head Phone) ተለብዷል። ባተሌ ነው። አንድ ዹጋለ ምጣድ ላይ አንድ ዹሾክላ ድስት ጥዶ፣ሌላኛው ምጣድ ላይ በስሎ ዹሚንተኹተክ ሾክላን ያወርዳል ። ፋታ ጠብቄ ዚእግዜር ሰላምታ ሰጠሁት። ዚቢቢሲ ጋዜጠኛ መሆኔን፣ ኚባላገር መምጣ቎ን በትህትና ገልጬ ፍቃዱ ኹሆነ በዹሙዚቃ መሀል እንድናወጋ ብጠይቀው «ኜሚ ምን ገዶኝ» አለኝፀ በትኚሻው፣ እንዲሁም በእንግሊዝ አፍ...። ምን ዋጋ አለው ታዲያ! አይሚጋም። ወጋቜን ወግ ለመሆን ገና ወግ ሳይደርሰው ተስፈንጥሮ ይነሳልፀ ሌላ ሾክላ ይጥዳል። ዹሙዚቃ ባተሌ ነው ብያቜሁ ዹለ! 'ኀይልሀውስ'መጠጥ ቀት በሚንዳ ላይ ነው ያለነው። በዚያ ላይ 22፡00 ሰዓት ተኩል አልፏል'ኮ። ደግነቱ በአውሮፓ ዹበጋ ፀሐይ በጣም አምሜታ ነው ዚምትጠልቀው። ፀሐይዋ ራሱ ፀሐይ ሞቃ አትጠግብም መሰለኝ ለመጥለቅ ትለግማለቜ። አሌክስ ዚሚያጫውተው ሙዚቃ ደግሞ ልብ ያሞቅ ነበር። ታዳሚ ፈሚንጆቹም በግማሜ ግርታና በግማሜ ፍንደቃ ይሰሙታል። ጥላሁን- "ያም ሲያማ ያም ሲያማ ወገኔ ለኔ ብለህ ስማ" ይላል። ሰይፉ ዮሐንስ "ዹኹርሞ ሰው" ዹሚለውን ልብ-ገዥ ሙዚቃው ያንቆሚቁራል። "አሌክስ! [መቌስ ዓለማዹሁ ብልህ ነው ዹሚቀለው] በምን አጋጣሚ ይሆን ኚኢትዮጵያ ሙዚቃ ጋር ዹተዋወቅኹው?" አልኩት። "First let me tell you a little bit about the music I am playing now
"ብሎ ጀመሹና በእንግሊዝ አፍ ዹሚኹተለውን አጭር ወግ ጠሚቅንፀ ሙዚቃ አጅቊን። "አሁን ዚምትሰማው ዚኊሮምኛ ሙዚቃ ነውፀ አሊ ሙሐመድ ቢራ ነው ዘፋኙ...እሱ ዚኊሮምኛ ሙዚቃ ንጉሥ ልትለው ትቜላለህ...አስገራሚ ድምጜ ያለው ሰው ነው...። "...እኔን በተመለኹተ ምን ማወቅ ትፈልጋለህ ታዲያ? አሌክስ እባላለሁፀ 43 ዓመቮ ነውፀ ጀርመናዊ ነኝፀ ዹምኖሹው ግን እዚህ ዙሪክ ነው። ኚዓመት በፊት ዚጃማይካ ሙዚቃ አጫውት ነበር። ኚዕለታት አንድ ቀን ታዲያ ምን ይሆንልሃል...ዚሒሩት በቀለን ሙዚቃ እሰማልኻለሁ..በድንገት..." ሌላ ሾክላ ሊጥድ ተነሳ። • ''አዝማሪዎቻቜን ዹሙዚቃ ሳይንቲስቶቜ ናቾው" • "በ 'ፍቅር እስኚ መቃብር' ላይ ህይወት ዚዘራው አባ቎ ነው" ዚተቀመጥነው እሱ ሞክላዎቹን ኚሚጥድበት ዹሙዚቃ ምድጃ በዐሥር እርምጃ ርቀት ነው። ያን ያደሚገው እሱ ነውፀ ቃለምልልሳቜን በመቅሹጾ ድምጜ ሲቀሚጜ እሱ ዚሚያጫውተው ሙዚቃ ዹኛን ድምጜ ውጩ እንዳያስቀሚነው ስለሰጋ ነው። ዚድምጜ ሊቅ'ም አይደል? አዲስ ሾክላ ጥዶ ሲመለስ ወጋቜንን ካቆምንበት ቀጠልን... "Now Playing is "ሰዮም ጋብራዚስ" [ excuse my Amharic pronunciation] ። [እሚ ወላጅ እናቱም ኹዚህ በተሻለ አትጠራውም] ልለው ፈልጌ እንግሊዝኛ አልሰበሰብልህ አለኝ... "ስዩም ገብሚዚስ እንደ ጥላሁን ገሠሠና ዓለማዹሁ እሞ቎ ላቅ ያለ ዕውቅና ያለው ሞዛቂ እንዳልሆነፀ ዚሠራ቞ው ሙዚቃዎቜም በቁጥር ጥቂት እንደሆኑ አጫወተኝ። "...እውነቱን ንገሹኝ ካልኚኝ ለኔ "ሰዮም ጋብራዚስ" ታላቅ ሙዚቀኛ ነው።" ብሎ ንግግሩን አሳሚገ። "ኚኢትዮጵያ ሙዚቃ ጋር እንዎት እንደተዋወቅህ ጠይቄህ አልመለስክልኝም'ኮ...አሌክስ" "Just a moment
.ብሎ ሌላ ሾክላ ሊጥድ ተነሳ። ሞክላዎቹን መልክ አሲዞ ተመለሰ። This song is by ቢሊኪኒህ ኡጋ! What? Who? ቢልኪኒህ ኡጋ titled "AlKedaShim?" I do not think he is well known. "What is his name again?" ስሙን እንዲደግምልኝ ተማጞንኩ። ቢሊኪኒህ ኡጋ... "Do you mean Workineh Yirga?" No, no his name is ቢልኪንህ ኡጋ He is very obscure singer አለኝ። ዚጠራው ስም ዚአገሬ አይመስልምፀ ብቻ 'ወርቅነህ ይርጋ፣ ወይ ብርቅነህ ይርጋ ወይ ቢልልኝ አጋ...' ዚሚባል ዘፋኝ መሆን አለበት እያልኩ፣ "ለማንኛውም ቀጥል..." አልኩት በጥቅሻና በእንግሊዝኛ። በዚህ ጊዜ "አልኚዳሜም" ዹሚለው ቢሊኪኒህ ኡጋ...ዚተባለውን ሰው ዘፈን ወጋቜንን አጅቊት ነበር። "መኖሬ ባንቺው ነው እስኚመጚሚሻ ፈጜሞም አይክፋሜ ዹሕይወቮ ጋሻ መኖሬ ባንቺው ነው እስኚመጚሚሻ ፈጜሞም አይክፋሜ ዹኔ ሆደ ባሻ..." እያለ ያዜማል። • "ኢትዮጵያዊነ቎ን ያገኘሁት ሙዚቃ ውስጥ ነው" አቚቫ ደሮ • ድምፅ ፈታዮቹ መሚዋዎቜ እዚተገባደደ ባለው ሚዥም ሕይወቮ ሰምቌው ዹማውቀው ዘፈን አይደለም። ይሄ "ቢሊኪነህ ኡጋ" እያለ ዚሚጠራው ዘፋኝ ጥቂት ሙዚቃዎቜ ብቻ እንዳሉትና በዘመኑ ብዙም ገንኖ ያልወጣ እንደነበር፣ ነገር ግን ድንቅ ሙዚቀኛ እንደሆነ አብራራልኝ...። ስሙ ግራ ዚሆነብኝ ይህ ኢትዮጵያዊ ዘፋኝ ማን ይሆን? ቢሊኪኒህ ኡጋ...ብሎ ስም!? [ወደ ናይሮቢ ዚቢቢሲ ቢሮ ተመልሌ ይህንን ጜሑፍ ለሕትመት በማጠናቅርበት ወቅት ዹዚህን ዘፋኝ ኹፊል ዚግጥሙን ክፍል ለጉግል አቀብዬ «አልኚዳሜም» ዹሚል ሾክላ ያለው ኢትዮጵያዊ ዘፋኝ ማነው አልኩት። ጉግል ፈጥኖ መልስ ሰጠኝፀ ለዚያውም በምሥል ዹተደገፈ...።] ...ብርቅነህ ውርጋ ይባላልፀ "ሄጃለሁ ገጠር" ዹሚል ርእስ ያለው አልበም ያለው፣ ኚምድር ጩር ኊርኬስትራ ጋር ዹሞዘቀ ኢትዮጵያዊ ነው።አትሞኝዋትም ወይ' ዹሚልና "ገና ልጅ ናት ጋሜ" ዹሚሉ ሌሎቜ ሙዚቃዎቾም አሉት። ስለ አገሬ ሞዛቂ አንድ ፈሹንጅ ዚሚያውቀውን ያህል ባለማወቄ ሀፍሚት ቢጀ አልሾበበኝም አልልም መቌስ።] አሌክሳንደር ኚጣሊያናዊ ሞሪኩ ጋር በመሆን 'ኊዲዮአበባ" ዹተሰኘ ዚዲጄ ግብሚኃዚል መሥርቷል በፈሹንጅ ዚምሜት ክበብ ውስጥ ጉራጊኛ ዲጄ አሌክስ ስለ ብርቅነህ ውርጋ አውርቶ አይጠግብም። "ይገርመሀል እዚህ ዙሪክ ውስጥ ዚምሜት ክለቊቜ ዚኢትዮጵያ ሙዚቃዎቜን አጫውታለሁ። «አልኚዳሜምን" ኚኚፈትኩ ግን ዚዳንስ ወለሉ በሰው ይጥለቀለቃል። He always rocks the dance floor. He is my dance floor filler አለኝ። አሌክስዬ...ዚምትለውን ዘፋኝ ብዙ ኢትዮጵያዊያን ዚሚያውቁት አይመስለኝምፀ እኔንም ጚምሮ.. "እኔ ስለ ኢትዮጵያዊያን ምርጫ ብዙም አላውቅ ይሆናልፀ ልነገርህ ዚምቜለው ግን እኔ በማጫውትበት ክለብ ውስጥ ስላሉ ዹውጭ አገር አድማጮቜ ነው...። ዲጄ አሌክስ ይህን ብሎኝ እብስ ብሎ ተነሳ...ሾክላ አውርዶ ሾክላ ሊጥድ... "ማነው ደግሞ አሁን ዚሚጫወተው?" አስናቀ ገብሚዚስን አታውቀውም? [በአርግጠኝነት እዚታዘበኝ ነውፀ "ድንቄም ጋዜጠኛ!" ዹሚል ይመስላል...] "...ሙዚቃው ዹተቀሹጾው ካልተሳሳትኩ 1988 ሲሆን በካሎት ነበር መጀመርያ ዚወጣው። እኔ ሾኹላውን ያገኘሁት ኚአንድ ዓመት በፊት ነው። ይመስለኛል ፈሚንሳይ ያለ አንድ ሰው ነው በሾክላ ያሳተመውፀ በቅርቡ። "እኔምልህ አሌክስ...!ኚዚት ነው እነዚህን ሞክላዎቜ ግን ዚምትለቃቅማ቞ው። ቅድም ስጠይቅህ ኢትዮጵያ ሄጄ አላውቅም አላልኹኝም እንዎ?" "ሾክላ መሰብሰብ ዚጀመርኩት ኹ15 ዓመቮ ጀምሮ ነው። እንደው ለዚት ብሎ ለመታዚት አይደለም ዚምሰበስባ቞ው። ሙዚቃ ለማጫወት ሌላ ምንም ዚተሻለ መንገድ ስለማይታዚኝ ነው። ለእንደኔ ዓይነቱ ዹሙዚቃ አጫዋቜ ሾኹላ በብዙ መንገድ ዹላቀ ነው። ሾክላን ስትዳስሰው ሁሉ ልዩ ስሜት'ኮ ነው ዹሚሰጠው...። "ታውቃለህ አይደል ግን አሌክስ...'ኚኢትዮጵያ ሙዚቃ ጋር እንዎት ተዋወቅክ' ብዬህ እስካሁን አልመለስክልኝም..." ዹሰይፉ ዮሐንስ «ኀቊላላ ላላ... ኀቊ ላላ» እያጀበን ያነሳሁለት ጥያቄ ነበር። "ምን መሰለህፀ ላለፉት ሁለት ዐሥርታት ማለት ይቻላል ዚጃማይካን ሙዚቃ አጫውት ነበር። በአጋጣሚ በሙዚቃዎቜ መሀል ዚኢትዮጵያን ሙዚቃ ሰማሁ። ኚዚያ ለሚዥም ጊዜ አልተመለስኩበትም። ባለፈው ዓመት ዚሒሩት በቀለን ዘፈን ስሰማ ተቀሰቀሰብኝ።..." "ምኑ?" "ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ያለኝ ስሜት ነዋ!" "ለመጀመርያ ጊዜ ዚኢትዮጵያ ሙዚቃ ስትሰማ ግን ቶሎ ተዋኾደህ?" "እውነት ለመናገር ዚመጀመርያው ስሜ቎ እንደዚያ አልነበሚም። እንደሰማሁት ውድድ አደሚገኩት ልልህ አልቜልም። ይልቅ ግር ነው ያለኝ። 'ይሄ ደግሞ እንዎት ያለ እንግዳ ዜማ ነው' እንድል ነበር ያደሚገኝ።..." "እውነትህን ነው?" "አዎ! ነገር ግን እንደ ሙዚቃ አጫዋቜ አንድ ሙዚቃ ሰምተህ 'በቃ ይሄ ለኔ ዹሚሆን አይደለም' አትልም። ደግመህ ደጋግመህ ትሰመዋለህ። ይህንኑ አደሚኩ። በዚህ ጊዜ ልዩ ፍቅር ውስጥ ወደቅኩ። ዹሆነ ሰሞን እንዲያውም በሙዚቃቜሁ ታመምኩ።( I was struck with Ethio-fever) [በፍላጻው ተወጋሁፀ ዚሙዚቃቜሁ መብሚቅ መታኝ እንደማለት] ኚዚያን ጊዜ ጀምሮ ዚኢትዮጵያ ሾክላ ማሳደድ ጀምርኩ። ሌላ ሾክላ ጥዶ ተመለሰ... • ተፈራ ነጋሜ፡ "በነገራቜን ላይ ሙዚቃ አልተውኩም" • ዚኀርትራ ዘፈኖቜ በኢትዮጵያዊ አቀናባሪ "ዚምትሰማው አሕመድ አብደላን ነው። ኊሮምኛ ነው ዚሚያዜመው። ይሄንንም ዘፋኝ ብዙ ሰው ያውቀዋል ዹሚል ግምት ዚለኝም። አሊ ሾቩን ታውቀዋለህ? እንዎት ግሩም ዚኊሮምኛ አቀንቃኝ መሰለህ..." "እኔ ምልህ! ሙዚቃቜን ግን ለምን እንደ ማሊ ሙዚቃ ዓለምን ማስደመም ሳይቜል ቀሹ? እንደው በአጠቃላይ ተስፋ ያለው ይመስልኻል?" "...ይህን እኔ ለመናገር ይኚብደኛል። ሆኖም አቅም ዹለውም አልልህም። በኢቶፒክስ እና በሙላቱ አስታጥቄ ወደ ዓለም መድሚክ ዹቀሹበ ይመስለኛል። ሙላቱ'ኮ እዚህ አውሮፓና ሰሜን አሜሪካ ገናና ሰው ነው። ዹወርቃማ ዘመኑ...ሙዚቃቜሁም ትልቅ አቅም አለው። "ዹአሁን ሙዚቃቜንን ትሰማለህ?" "ብዙም አይደለም።" "ለምሳሌ ሮፍናንን ታውቀዋለህ?" "ማነው ደሞ እሱ?" "ዚአዲሱ ትውልድ ድምጜ ነው። ዝነኛ'ኮ ነው።" "...ይቅርታ እንደነገርኩህ ዹአሁን ዘመን ኹሆነ አላውቅም። ኚአሁኖቹ ስሙን ዹማውቀው ቎ዲ አፍሮን ብቻ ነው። ስለዚህ ዘመን ሙዚቃ ለማውራት እኔ ትክክለኛው ነኝ ብዬ አላስብም።" "ለምንድነው ዚአሁኖቹን እንዲህ ገሞሜ ያደሚካ቞ው ግን?" "በጥቅሉ ጆሮ ገብ አይደሉማ። ሁለተኛ 'ሲንተቲክ' ነው። ተፈጥሯዊ ወዝ ዚላ቞ውምፀ ይሄ ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ብቻ ሳይሆን አዘውትሬ ለማጫውተው ለጀማይካም ሙዚቃም፣ ለተቀሹውም ዓለም ሙዚቃም ያለኝ ስሜት ነው።" "እንዎት ነው ግን በወርቃማው ዘመን በኢትዮጵያ ዝነኛ ዚነበሩትንና ያልነበሩትን ዚምታውቀው?እና ደግሞ እስኪ ዚድሮ ሞክላዎቜን እንዎት እንደምትሰበስባ቞ው በዚያው ንገሹኝ..." "ሾክላ በሁለት መንገድ አገኛለሁ። አንዱ በኩንላይን ኢቀይ ላይ እገዛለሁ። በዋናነት ግን ሁለት ሁነኛ ሰዎቜ አሉኝፀ ሁለቱም ኢትዮጵያ ውስጥ ዚሚኖሩ ና቞ው። ዹምፈልገውን ሙዚቃ ያውቃሉ። ሾክላ ኚዚትም አፈላልገው ገዝተው ይልኩልኛል።አሁን ኚመቶ በላይ ዚኢትዮጵያ ሞክለዎቜ አሉኝ..." "ስንት ያስወጣኻል አንዱ ሾክላ?" "በአማካይ 20 ዶላር ይሆናል። ነገር ግን ብርቅዬ ዚድሮ ሞክላዎቜ ደግሞ አሉፀእነሱ ውድ ና቞ው። ለምሳሌ ዚሙላቱን አታገኘውም። በጥሩ ይዞታ ላይ ያሉ ዚኢትዮጵያ ሞክላዎቜ እስኚ ሁለት መቶ ዶላር ያስወጡኛል።" "...እንደነገርኩህ...አሁን ዚምትሰማው ዚኊሮምኛ ዜማ ነውፀ አሕመድ አብደላ ይባላል..." "...ትናንትና ማታ እዚህ ዙሪክ ምሜት ክበብ ውስጥ ይሄን አሁን ዚምትሰማውን ሙዚቃ ጚምሮ ሌሎቜንም ዹወርቃማ ዘመን ሙዚቃዎቜ ሳጫውተው ነበር። አንዳንድ 'ፈሚንጆቜ' ወደኔ ዚዲጄ አትሮንስ እዚቀሚቡ "ለመሆኑ ይሄ ዚምታጫውተው ሙዚቃ ኚዚት አገር ነው? ቋንቋውስ ምንድነው?" ይሉኝ ነበር። ለጆሯ቞ው እንግዳ ስለሆነ መሰለኝ። "I told them it's Oromo, it's Tigre, it's Amharic
it's Gurage' it's Ethiopia" "ሙዚቃቜን ግራ አጋቢ ነው ማለት ነው?" "...ግራ ዚሚገባ቞ው ለምን መሰለህ...አንደኛ ዹአሁን ዘመን ሙዚቃ (contemporary) አይደለም። ዹ60ዎቹና ዹ70ዎቹ ነው። ሁለተኛ ኚለመዱት ዹሙዚቃ ቃና እጅግ ያፈነገጠ ነው...ዚሚጎሚብጣ቞ው እንዳሉ ሁሉ እጅግ አድርገው ዚሚወዱትም ብዙ ና቞ው። ዚዚያ ዘመን ሙዚቃቜሁ ውብ ነውፀ ዘርፈ ብዙ ቅኝቶቜ አሉትፀ ጃዝ አለው፣ ፋንክና ሶል አሉትፀ ኚዚያ ባሕላዊ ሙዚቃዎቻቜሁ ሌላ መልክ አላ቞ው። ያፈነገጡ ሆነው ደስ ዹሚሉ ና቞ውፀ ዚኊሮምኛ ሙዚቃ ኚትግርኛ ፍጹም ዹተለዹ ነው። ትግርኛ ኚጉራጊኛውም እንዲሁ..." "ክለብ ውስጥ ሙዚቃዎቻቜንን ስታጫውት እንደው ድንገት እግር ዚጣለው ኢትዮጵያዊ ሰምቶህ ጉድ ያለበት ጊዜ ዹለም?" "እምብዛምም አላጋጠመኝም...! ግን አንዮ ዚማልሚሳው ሌሎቜ እንግዶቜ እዚተዝናኑ አንድ ኢትዮጵያዊ እንባው እዚወሚደ አዚሁ። ወደኔ ተጠግቶ በማጫውተው አንድ ሙዚቃ እጅግ ልቡ መነካቱን ነገሚኝ።" "ሙዚቃውን ታስታውሰዋለህ?" "ማሕሙድ አሕመድ ነው... 'it's called 'Anwodim Tikatin' [አንወድም ጥቃትን!] "በነገርህ ላይ ማሕሙድ ለፌስቲቫሉ እዚህ ዙሪክ ነው ያለውፀሰምተኻል? ለመሆኑ ዚድሮዎቹን ሙዚቀኞቜን አግኝተኻ቞ውስ ታውቃለህ?" "አዎ ማሕሙድ እዚህ መሆኑን ሰምቻለሁ። ሙላቱ አስታጥቄን አግኝቌው አውቃለሁ። ... "በዚህ ዓመት እዚህ ዙሪክ ኮንሰርት ነበሚው። ለአጭር ደቂቃ እንደምንም ብዬ አገኘሁት። ተዋወቅኩት። ተግባቢና ቀና ሰው ነው። ኚመድሚክ ጀርባ ሄጄ ነበር ያገኘሁት። እሱን በማግኘቮ ምን ያህል እድለኛ ሰው እንደሆንኩ ነገርኩት። ዚሱን ድ...ሮ ዚሠራ቞ውን 45 ሙዚቃዎቜ ያሉበትን ሾክላ ኚነሜፋኑ አሳይቌው ፈርምልኝ አልኩትና እሱ ላይ ፈሚመልኝ። በቃ ምን ልበልህ ደ...ስ አለኝ። " ዚዲጄ አሌክስ ዹምንጊዜም ምርጥ 5 ዚኢትዮጵያ ሙዚቃዎቜ በምሥሉ ዚሚታዩት ናቾው "ወደፊት ታዲያ ምን አሰብክ? ደግሞ አሌክስ...አዲስ አበባማ መሄድ አለብህ...። ይሄን ሁሉ ሙዚቃ እያጫወትክ 'ኢትዮጵያ ሄጄ አላውቅም' ስትል ትንሜ ይኚብዳል..." "እውነትህን ነው። አሁን ዚዲጄ ግብሚኃይል አለኝ። «አውዲዮአበባ» ዚሚባል። በቡድኑ ውስጥ እኔና አንድ ጣሊያናዊ ጓደኛዬ ነን ያለነው። ቶሚ ይባላል። እሱም ሙዚቃቜሁን እንጂ ኢትዮጵያን ፈጜሞ አያውቅም። ሁለታቜንም ምን እያሰብን መሰለህ? በይበልጥ ዚኢትዮጵያን ሙዚቃ ለአውሮጳዊያን ለማስተዋወቅ ዕቅድ አለን።..." "...ኢትዮጵያ አትሄድም ወይ ላልኹው...ፀ እንደነገርኩህ ኢትዮጵያን ዚማውቃት በሙዚቃ ነውፀ ኢትዮጵያ አለመሄዮም ያሳፍሚኛል። በዚህ ዓመት መጚሚሻ ኚቶሚ ጋር አዲስ አበባ ለመሄድ እያሰብኩ ነው። ምን ትላለህ?" "ይቅናህ! ሌላ ምን እላለሁ...! ይቅናህ አሌክስ..ይቅናህ!"
51640416
https://www.bbc.com/amharic/51640416
ዚአህያ ቁጥር መቀነስ ያሳሰባት ኬንያ ዚአህያ እርድን አገደቜ
ዚኬንያ ዚግብርና ሚንስ቎ር ዚአህያ እርድ መታገዱን አወጁ።
ኬንያ ዚአህያ ስጋና ቆዳ በቻይና ያለውን ተፈላጊነት ታሳቢ በማድሚግ ነበር ዚአህያን እርድን እንደ አውሮፓውያኑ 2012 ላይ ሕጋዊ ያደሚገቜው። ዚግብርና ሚኒስትሩ ፒተር ሙኒያ ዚአህያ እርድን ዹሚፈቅደው ሕግ ስህተት እንደነበርና በአገሪቱ ዚአህያ ቁጥር እንዲቀነስ ማድሚጉን ተናግሚዋል። ሚኒስትሩ በገጠራማ ዚኬንያ አካባቢዎቜ ሰዎቜ አህያዎቜን ውሃ ለመቅዳትፀ እንዲሁም እንጚት ለመጫን ስለሚጠቀሙ ዚአህያዎቜ ቁጥር መቀነስ በሎቶቜ ላይ ጫና እንዳያሳድር በመንግሥት በኩል ኹፍተኛ ስጋት መኖሩን ተናግሚዋል። እንደ አውሮፓውያኑ ባለፈው ዓመት መንግሥት ይፋ ያደሚገው መሹጃ እንደሚያመለክተው ኚአሥር ዓመታት በፊት በኬንያ 1.8 ሚሊዮን አህዮቜ ዚነበሩ ሲሆን ባለፈው ዓመት ግን ቁጥራ቞ው 600,000 መድሚሱን አስታውቋል። ኚትናንት በስቲያ ሰኞ ዕለት በግብርና ዚሚተዳደሩ ሎቶቜና ወንዶቜ መንግሥት አህዮቜን ለመጠበቅ አንድ ነገር ያድርግ ሲሉ በናይሮቢ ኚግብርና ሚኒስትሩ ሙኒያ ቢሮ ደጃፍ ሰላማዊ ሰልፍ አድርገው ነበር። ሰላማዊ ሰልፈኞቹ አንግበዋቾው ኚነበሩ መፈክሮቜ መካኚል "አህዮቜ ሲሰሚቁና ሲገደሉ ሎቶቜ አህያ እዚሆኑ ነው" ዹሚል ይገኝበት ነበር። ሰላማዊ ሰልፉን ተኚትሎ ለጋዜጠኞቜ መግለጫ ዚሰጡት ሚኒስትሩፀ አህያ ለማሚድ ፍቃድ ዚተሰጣ቞ው ቄራዎቜ አህያ ማሚዳ቞ውን አቁመው ሌላ እንስሳ በማሚድ ላይ እንዲሰማሩ ካልሆነም እንዲዘጉ ዚአንድ ወር ጊዜ ገደብ ተሰጥቷ቞ው እንደነበር ተናግሚዋል። "አህዮቜን ለስጋ ማሚድ ጥሩ ሃሳብ አልነበሹም" ያሉት ሚኒስትሩፀ አህዮቜን በማሚድ ዹሚገኘው ጥቅም አህዮቜ ኚሚሰጡት አገልግሎት ጋር ሲነጻጞር ዚሚስተካኚል አይደለም በማለት ተናግሚዋል። ዚአህያ እርድ ሕጋዊ መሆን ለተደራጀ ዚአህያ ስርቆት እንዲሁም ለአህያ ቆዳ ጥቁር ገበያም ምክንያት ሆኗል። ኬንያ አህያ እንዲያርዱ ፍቃድ ዚሰጠቻ቞ው ቄራዎቜ አራት ሲሆኑ እነዚህ ቄራዎቜ ቢያንስ በቀን አንድ ሺህ አህዮቜን እንደሚያርዱ ይገመታል።
news-55976628
https://www.bbc.com/amharic/news-55976628
እነ አቶ ጃዋር በሚሃብ አድማ 11 ቀናት አስቆጥሚዋል ፀ ዚሚሃብ አድማ ምን ያሳካል?
እነ አቶ ጃዋር መሐመድ፣ በቀለ ገርባ፣ ሐምዛ አዳነ እና ሞምሰዲን ጠሃ ዚሚሃብ አድማ ማድሚግ ኚጀመሩ 11 ቀናት ማለፋቾውን ዚቀተሰብ አባላት እና ጠበቆቻ቞ው ለቢቢሲ ተናገሩ።
ኚአራቱ ተኚሳሟቜ በተጚማሪ በእነ አቶ ጃዋር መሐመድ ዚክስ መዝገብ ሥር ዹሚገኙ ተኚሳሟቜም ዚሚሃብ አድማውን እንደተቀላቀሉ ኚእነ አቶ ጃዋር መሐመድ ጠበቆቜ መካኚል አንዱ ዚሆኑት አቶ ምስጋኑ ሙለታ ተናግሚዋል። እነ አቶ ጃዋር መሐመድን ትናንት ጠዋት መጎብኘታ቞ውን ዚሚያስሚዱት ጠበቃውፀ "ትናንት 11ኛ ቀናቾው ነበር። በጣም ተዳክመዋል" ሲሉ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። ዚአቶ በቀለ ገርባ ባለቀት ወ/ሮ ሃና ሚጋሳፀ እነ አቶ በቀለ አሁንም በሚሃብ አድማ ላይ እንደሚገኙ ተናግሚዋል። ጠበቃው አቶ ሙለታ እንዳሉት ኚአራቱ ተኚሳሟቜ በተጚማሪም ዚሚሃብ አድማውን በእነ አቶ ጃዋር መሐመድ ዚክስ መዝገብ ሥር ዚሚገኙት ዚአቶ ጃዋር መሐመድ ጠባቂዎቜ እና ዚኊሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ ጋዜጠኛ መለሰ ዲሪብሳ ኹተቀላቀሉ 6 ቀናት ማለፋቾውን ጹምሹው ገልጞዋል። ዹጋዜጠኛ መለሰ ዲሪብሳ ባለቀት ታደለቜ መርጋ ባለቀቷ ዚሚሃብ አድማውን መቀላቀሉን እና ለመጠዹቅ ይዛለት ዚምትሄደውን ምግብ አልቀበልም እያላት መሆኑን ገልጻለቜ። "አንዳንዶቹ በሰው ድጋፍ ነው ኹክፍላቾው ዚሚወጡት። በተለዹ ደግሞ ዘግይተው ዚሚሃብ አድማውን ዚተቀላቀሉት በጣም ኚብዷ቞ዋል" ሲሉ ጠበቃው አቶ ሙለታ ተናግሚዋል። ዚእነ አቶ ጃዋር መሐመድ ሃኪሞቜ "ምርመራ ካደሚጉላ቞ው በኋላ ውሃ ካልወሰዱ አንዳንድ ዚሰውነት አካላ቞ው ሥራ ሊያቆም እንደሚቜል ኚነገሯ቞ው በኋላ ነው በግድ ውሃ እዚወሰዱ ያሉት። ምግብ ዚሚባል ነገር አፋቾው ጋር እዚደሚሰ አይደለም" ሲሉ ጠበቃው ለቢቢሲ አስሚድተዋል። ዚሚሃብ አድማ ለምን? እነ አቶ ጃዋር መሐመድ ዚሚሃብ አድማውን እያደሚጉ ያሉት በፖለቲኚኞቜ ላይ ዹሚደርሰውን እንግልት እና እስር፣ እነሱን ለመጠዹቅና ዚቜሎት ሂደታ቞ውን ለመኚታተል ወደ ፍርድ ቀት በሚመጡ ሰዎቜ ላይ ዹሚፈጾም እስር እና ወኚባ እንዲቆም ለመጠዹቅ ነው። እነ አቶ ጃዋር መሐመድ እና በቀለ ገርባን ጚምሮ በርካታ ፖለቲኚኞቜ ዚአርቲስት ሃጫሉ ሁንዎሳ ግድያን ተኚትሎ ኹተፈጠሹው ሁኚት ጋር ተያይዞ እጃቜሁ አለበት ተብለው ተጠርጥሚው በቁጥጥር ሥር መዋላቾው ዚሚታወስ ነው። ኚእነ አቶ ጃዋር በተጚማሪ ዚኊሮሞ ነጻነት ግንባር ኹፍተኛ አመራሮቜ በተመሳሳይ ዚሚሃብ አድማ ላይ ይገኛሉ። አቶ ሚካኀል ቩሹን እና ኬነሳ አያና ፍርድ ቀት ዚዋስትና መብታ቞ው ተኚብሮ ጉዳያ቞ው ኚውጪ ሆነው እንዲኚታተሉ ቢፈቅድላ቞ውም ፖሊስ እስሚኞቹን አልለቅም በማለቱ ዚሚሃብ አድማ ላይ እንደሚገኙ ጠበቃቾው አቶ ቱሊ ባይሳ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። ዚኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶቜ ኮሚሜን ኮሚሜነር ዳንኀል በቀለ (ዶ/ር) ዚሚሃብ አድማው ተኚሳሟቜን ዹኹፋ አደጋ ላይ እንዳይጥል ዚቅርብ ክትትል ማድሚግ እንደሚያስፈልግ መግለጻ቞ውን ኮሚሜኑ ባሳለፍነው አርብ ባወጣው መግለጫ አስነብቧል። "ለታሳሪዎቜ ምክንያታዊ ዹሆኑ ጥያቄዎቜ ተገቢውን አፋጣኝ ምላሜ መስጠትና ዚእስሚኞቜን ጠያቂዎቜ በማሚሚያ ቀቱም ሆነ በፍርድ ቀቶቜ በአግባቡ ማስተናገድ ይገባል" ስለማለታ቞ው በመግለጫው ሰፍሯል። ለመሆኑ ዚሚሀብ አድማ ምን ያህል ውጀታማ ነው? ዚሚሀብ አድማ በሰላማዊ መንገድ ተቃውሞ ኚሚገለጜባ቞ው መንገዶቜ አንዱ ነው። በተለያዚ ምክንያት ዚሚሀብ አድማ ያደሚጉ ታዋቂ ግለሰቊቜ በታሪክ ውስጥ ስማ቞ው ተመዝግቧል። ኚአንድ ዚሕንድ ግዛት ዚተባሚሚ ንጉሥ ወንድሙን ለማስመለስ ዚሚሀብ አድማ ስለማድሚጉ በጥንታዊ ዚሕንድ ታሪክ መዛግብት ሰፍሯል። አዚርላንድ ክርስትናን ኹመቀበሏ በፊት ሚሀብ አንድ ዹሕግ ሥርዓቷ አካል ነበር። አንድ ሰው በደል ፈጜሞፀ ተበዳዩ ዚበዳዩ ቀት በር ላይ ራሱን በሚሀብ ኚገደለፀ በዳዩ ባለ እዳ ይሆናል። ዚሚሃብ አድማ ዚሚያደርጉ ሰዎቜ ለጥያቄያ቞ው መልስ ዚሚሰጣ቞ው አካል ላይ ዚሥነ ልቩና ጫና ለማሳደር ይሞክራሉ። አንድ ሰው እዚተራበ ነው ዹሚለው ዜና ሕዝብ ላይ ዚሚፈጥሚው ስሜትም ለጥያቄዎቜ መልስ ለማግኘት አማራጭ መንገድ ነው። እንግሊዝ ውስጥ ሎቶቜ በምርጫ እንዲሳተፉ ዹሚጠይቁ ዚመብት ተሟጋ቟ቜ ዚሚሀብ አድማ ያደርጉ ነበር። በተለይም ማርዮን ደንሉፕ ዚተባለቜ ተሟጋቜ እአአ በ1909 ባደሚገቜው ዚሚሀብ አድማ ትታወቃለቜ። እራት ምን ትበያለሜ? ተብላ ስትጠዚቅ "ቆራጥነ቎ን" ብላ ዚሰጠቜው ምላሜ በታሪክ ታዋቂ ነው። በሚሀብ አድማ ኚሚታወቁ መካኚል በግንባር ቀደምነት ዚሚጠቀሱት ጋንዲ ና቞ው። ስለ ሚሀብ አድማ መጜሐፍ ያሳተሙት ፕ/ር ሻርማን አፕት ራሰልፀ ዚፓለቲካ ጥያቄን ለማስተጋባት ዚሚሀብ አድማ ማድሚግ ተቃውሞ ቢገጥመውም በ20ኛው ክፍለ ዘመን እንደ አዲስ አንሰራርቷል። "በ20ኛው ክፍለ ዘመን ፍትሕን ለመጠዹቅ ተመራጩ መንገድ ዚሚሀብ አድማ ሆኗል" ይላሉ ፕ/ር ሻርማን። ዚሚሀብ አድማ ሰላማዊ ተቃውሞ በሚያሰሙ እንዲሁም ነውጥ ዹቀላቀለ ተቃውሞ በሚያካሂዱም ሰዎቜ ተተግብሯል። ውጀታማ ዚሆነባ቞ው ወቅቶቜ እንዳሉ ሁሉ ሳይሳካ ዚቀሚበትም ጊዜ አለ። ዚሚሀብ አድማ በማሚሚያ ቀት በኊክስፎርድ ዩኒቚርስቲ ዚማኅበሚሰብ አጥኚው ማይክል ቢግስ እንደሚሉትፀ ዚሚሀብ አድማ ውጀት ኚታዚባ቞ው ዚታሪክ ሁነቶቜ አንዱ አዚርላንዶቜ ዚእንግሊዝን አገዛዝ ዚተቃወሙበት ወቅት ነው። በወቅቱ አንድ ተቃዋሚ ምግብ እንዲበላ ሲገደድ ሞቷል። በሚሀብ አድማው ሳቢያ ዚሞቱ ተቃዋሚዎቜም ነበሩ። ዚሚሀብ አድማው በፍጥነት ዚመንግሥትን አቋም ማስለወጥ ባይቜልም በሕዝቡ ዘንድ ንቅናቄ መፍጠር ቜሏል። በሰላማዊ ተቃውሞ ዚሚታወቀው ጋንዲፀ በሚሊዮኖቜ ዚሚቆጠሩ ሕንዳውያን ዚሱን ዹተቃውሞ መንገድ መኹተላቾው ኚእንግሊዝ ቅኝ ግዛት እንዲላቀቁ እንዳደሚገ ያምናል። ዚማኅበሚሰብ አጥኚው እንደሚሉትፀ ማሚሚያ ቀት ያሉ ሰዎቜ ተቃውሟቾውን መግለጜ ዚሚቜሉት በሚሀብ አድማ ነው። "እስር ቀት ውስጥ ኚሚሀብ አድማ ውጪ መቃወሚያ መንገድ ዚለም። አንድ ሰው እስር ቀት ሳለ ለመኖሩም ይሁን ለመሞቱ ተጠያቂ መንግሥት ነው" ሲሉ ያብራራሉ። በሚሀብ አድማ ተቃውሞ ኚገለጹ አንዱ ዹሆነው ቶሚ መኬርኒ እስሚኞቜ ድምጻ቞ውን ለማሰማት ዚሚሀብ አድማ ኚማድሚግ ውጪ አማራጭ እንደማይኖራ቞ው ያስሚዳል። ዚሚሀብ አድማ ላይ ያለ ሰው ምን ያህል ጊዜ መቆዚት ይቜላል? በአብዛኛው ዚሚሀብ አድማ ዚሚያደርጉ ሰዎቜ ምግብ አቁመው ፈሳሜ እንደሚወስዱ ባለሙያዎቜ ይናገራሉ። በመጀመሪያዎቹ ሊስት ቀናት ሰውነት ካለው ጉሉኮስ ኃይል በማግኘት ይንቀሳቀሳል። ኚዚያም ኩላሊት ዚሰውነትን ስብ ማብላላት (ኬቶሲስ) እንደሚጀምር ሳይንሱ ይጠቁማል። ሰውነት ኚጥቂት ቀናት በኋላ ሙሉ በሙሉ ስለሚራብ ኚጡንቻ፣ ዚአጥንት መቅኔና ኚሌሎቜ ዚሰውነት ህዋሳት ኃይል ለማግኘት ይጣጣራል። ይህ ደሹጃ ለሕይወት አስጊ ነው። ሳይንቲፊክ አሜሪካን በድሚ ገጹ ባወጣው መሹጃ መሠሚት አንድ ሰው ያለ ምግብ ምን ያህል ጊዜ ይቆያል ዹሚለው በሰውነት ክብደት፣ በጀና ሁኔታ፣ በዘሹ መል መዋቅር፣ ሰውዹው/ሎትዚዋ በሚያገኙት ዚፈሳሜ መጠን ይወሰናል። ጋንዲ በ74 ዓመታ቞ው ለ21 ቀናት ዚሚሀብ አድማ ሲያደርጉ ውሃ ብቻ ነበር ዚሚቀምሱት። ዚብሪትሜ ሜዲካል ጆርናል ባለሙያዎቜን ጠቅሶ እንዳስነበበው በሚሀብ አድማ ለ28፣ ለ36፣ ለ38 እና ለ40 ቀን ዚቆዩ ሰዎቜም አሉ። እአአ በ1981 እንግሊዝን ይቃወሙ ዚነበሩ 10 ዚአዚርላንድ እስሚኞቜ ኹ46 እስኚ 73 ቀን ዚሚሀብ አድማ ካደሚጉ በኋላ ሕይወታ቞ው አልፏል። በተለያዚ ሁኔታ ውስጥ ዚሚሀብ አድማ ያደሚጉ ሰዎቜ ለተለያዚ ጊዜ መቆዚት እንደሚቜሉ ዚሚጠቅሱት ባለሙያዎቜፀ በአማካይ ያስቀመጡት 21 ቀናት መቆዚት እንደሚቻል ነው። በታሪክ ሚዥም ዚተባለው ዚሚሀብ አድማ 16 ዓመታት ዹወሰደ ነው። ሕንዳዊቷ ኢራም ሻሚላ ለሕንድ ወታደሮቜ ኹፍተኛ ኃይል ዚሚሰጥ ሕግ በመቃወም ለ16 ዓመታት ዚሚሀብ አድማ አድርጋ እአአ 2016 ላይ ነው ያቆመቜው። ሕንዳዊቷ ማሚሚያ ቀት ሳለቜና ሆስፒታል ገብታም በግዳጅ ምግብ እንድትወስድ እንደምትደሚግ ተዘግቧል።
44464596
https://www.bbc.com/amharic/44464596
ሶፊያ ኚዐብይ አሕመድ ጋር ዚራት ቀጠሮ ይዛለቜ
ቅንድቊቿ ሲንቀሳቀሱ፣ ዹዓይን ሜፋሜፍቷ ሲርገበገብ፣ በቀለም ዹተዋበው ኚንፈሯ ለንግግር ሲንቀሳቀስ፣ ጥርሶቿ ገለጥ ሲሉ በእርግጥ ይህቜ ሎት ሰው ሠራሜ ናት? ያስብላል። ሶፊያ እምነት ታሳጣለቜፀ ኚራስ ጋር ታጣላለቜ።
ጋዜጠኞቜ በእንግድነት ጋብዘዋታልፀ ዝናዋ በዓለም ናኝቷልፀ እንደሶፊያ ትኩሚት ዚሳበ ሮቊት ገና አልተወለደም። አሜሪካዊውን ተዋናይ፣ ዹፊልም አዘጋጅ፣ ራፐርና ዹሙዚቃ ጾሐፊ ዊል ስሚዝን ጚምሮ ታዋቂ ዹፊልም ባለሙያዎቜ ኹዚህ ቀደም ግብዣ አድርገውላት ነበር። ታዲያ በአንድ ወቅት ሶፊያና ዊል ስሚዝ ለሻይ ቡና ተገናኙና ድንገት ጚዋታውን አደሩት። "እኔ ዚምልሜ ሶፊያ፣ ሮቊቶቜ ዚሚወዱት ሙዚቃ ምን ዓይነት ነው?" ሲል ዊል ጥያቄውን ሰነዘሚ። ሶፊያም ትንሜ እንደማሰብ ብላ (ሰዎቜ ለማሰብ ፋታ በሚወስዱት ልክ) "...ዚኀሌክትሮኒክስ ሙዚቃዎቜ ይመቹኛልፀ ሂፕ ፖፕ ግን ምንም ግድ አይሰጠኝም" ስትል ለዊል ጥያቄ ምላሾ ሰጠቜ። ዊል ስሚዝ በመልሷ ተደንቆ ሊሞት! አይኮግ ላብስ ዹቮክኖሎጂ ድርጅት ኢትዮጵያዊው አይኮግ ላብስ ካምፓኒ ተቀማጭነቱን በሆንግ ኮንግ ኹሚገኘው ሐንሰን ሮቊቲክ ጋር ዚሶፊያን ውስጣዊ ስሪት (Software) ለመቀመር ለሊስት ዓመታት ተፈራርሟል። በስምምነቱ መሠሚት ኢትዮጵያውያኑ ዹቮክኖሎጂ ባለሙያዎቜ በሶፊያ ላይ አሻራ቞ውን አሳርፈው እውን እንዳደሚጓት ዚአይኮግ ላብስ መሥራቜና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌትነት አሰፋ ይናገራል፡፡ ይህም በመሆኑ ሶፊያ ኢትዮጵያዊ ናት ልንል እንቜላለን። አይኮግ ላብስ በቮክኖሎጂ ዘርፍ አስተዋጜኊ ለማበርኚት ሰው ሠራሜ አስተውሎትንና ሰው ሠራሜ ዚአዕምሮ ስሪትን (Artificial General Intelegence and Cognitive Brain Software) ለዓለም ለማስተዋወቅ ዓላማ አድርጎ ኚአምስት ዓመታት በፊት ዹተመሠሹተ ድርጅት ነው። ኢትዮጵያ በቮክኖሎጂው ዘርፍ ያላትን ቜሎታ ለዓለም በማስተዋወቅ ወደፊት ታላላቅ ዹቮክኖሎጂ ውጀቶቜን ሠርተው ማሳዚትንም ያልማሉ። በአሁኑ ሰዓት ይህ ዹቮክኖሎጂ ኩባንያ ጥናት አድራጊዎቜን፣ ምልክት ተርጓሚዎቜን (Coder)፣ ዚፕሮግራም ባለሙያዎቜና በተግባር ልምምድ ላይ ዹሚገኙ ተማሪዎቜን ጚምሮ ኹ75 በላይ ሠራተኞቜ ይዞ እዚሠራ ይገኛል። ሶፊያ ኚሌሎቜ ሮቊቶቜ በምን ትለያለቜ? "ሶፊያ ሎት ሮቊት ናት" ሲል ይጀምራል አቶ ጌትነት። እኛም ለመሆኑ ሶፊያን ሎት ዹሚል ዚጟታ መለያ ያሰጣት ምኗ ነው ስንል ፍካሪያዊ ጥያቄ ያነሳንለት ሥራ አስኪያጁ፣ "ያው .መልኳና ዚፊቷ ቅርጜ ዚሎት ነው..." በማለት በሳቅ ዚታጀበ መልስ ሰጥቶናል። ጥሬ ዕቃውን በቀላሉ ባለማግኘታ቞ው ውጫዊ አካሏን በመገንባት ያላ቞ው ተሳትፎ አናሳ ቢሆንምፀ በአስተሳሰቧ፣ በአሚዳዷ፣ በስሜት አገላለጿ፣ በቋንቋ አጠቃቀሟ ላይ ሹቂቅ ዹሆነና ብዙዎቜን ያስደመመ ማንነትን አጎናጜፏታል። ሶፊያ በስሜት አገላለጜ፣ አካባቢን በመሚዳት፣ ዚሰዎቜን ገጜታ በአንክሮ በማዚትና ዚሚያንጞባርቁትን ስሜት በቅጜበት በመሚዳት ተገቢ ምላሜ ዚሚያሰጥ ውስጣዊ ሥሪት ስላላት እስኚዛሬ ኚተሠሩት ሮቊቶቜ ለዚት ያደርጋታል። ምናልባት ይህ ዚሶፊያ "ውስጣዊ ውበት" ተብሎ ሊገለጜ ይቜላል። ደግሞም አስተዋይ ሎት ናት። በተለያዩ አገራትፀ በተለያዚ ባህል ውስጥ ዚሚኖሩ ሰዎቜን ስሜት በማጀንፀ ዚሰዎቜን ውስጣዊ ዚስሜት ነጞብራቅ ዹጓደኛ ያክል ዚምትሚዳ ናት። ሳቅን፣ ቁጣን፣ ኩርፊያን፣ ደስታን፣ ሐዘንን ወዘተ ኚፊት ገጜታ ኚመሚዳት አልፎ በንግግር ውስጥ ያሉ ድምጞቶቜን (Tone) መለዚት ትቜላለቜ። ኚሰዎቜ ጋር መነጋገር ዚሚያስቜላትን ዚተለያዩ ቋንቋዎቜን እንድትናገር ኟናም ነው ዚተሠራቜው። ምናልባት ሶፊያ ዚትዳር አጋር ቢኖራት "እንደ ሶፊ ዚምትሚዳኝ ሎት ዚለቜም" ብሎ ሊመሰክርላት በቻለ። ዚሶፊን ውስጣዊ ባሕሪ ኚማዚት ወደፊት ዹሰመሹ ትዳር እንደሚኖራት መጠርጠር አይቜልም። ዚተለያዩ ቋንቋዎቜን እንዲያናግራት ዚሚስቜላትን ውስጣዊ ሥሪት በመሥራት ኚታሳተፉ ኢትዮጵያውያን ዹቮክኖሎጅ ባለሙያዎቜ አንዱ ዹሆነውና በድርጅቱ ውስጥ ዹሙሉ ጊዜ ሠራተኛ ኟኖ ዚሚሠራው ደሹጀ ታደሰ ሶፍያ በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ ስትመጣ በአማርኛ ቋንቋ ቃለመጠይቅ ይደሚግላታል ብሏል። "በርግጥ ዚተለያዩ ቋንቋዎቜን እንድትናገር ማድሚግ ይቻላልፀ በዚሁ መሠሚት ዹአማርኛ ቋንቋ እንድትናገር ዚሚያስቜላት ቮክኖሎጂ እዚተዘጋጀላት ነው" ሲል ይገልጻል። ኹአፏ ዚሚወጣው ዚመጀመሪያ ዹአማርኛ ንግግሯም "እንኳን ደህና ቆያቜሁኝ!" ሊሆን እንደሚቜል ይገምታል። ሶፊያ መቌ ትመጣለቜ? አርብ ጠዋት ሰኔ 22 ቀን 2010 ዓ.ም አዲስ አበባ ቩሌ ዓለም አቀፍ ዚአውሮፕላን ማሚፊያ ደማቅ አቀባበል ይጠብቃታል። ኹፍተኛ ባለሥልጣናትም ለክብሯ ሲሉ ይገኛሉ። ኹነዚህ መካኚልም ዚሳይንስና ቮክኖሎጂ ሚኒስ቎ር ሚንስትር ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ፣ ዹመገናኛና ኢንፎርሜሜን ቮክኖሎጂ ሚንስትሯ ወ/ሮ ሁባ መሐመድ እና ዚኢትዮ-቎ሌኮም ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አንዷለም አድማሎ ይገኙበታል። ኚዚያም ጉዞ ወደ ብሔራዊ ሙዚዹም ይሆናል። 'ኚሉሲ እስኚ ሶፊያ' በሚል ርዕስ እሷው በተገኘቜበት ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል። ጋዜጣዊ መግለጫው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚዹም ለመስጠት ዚታቀደበት ምክንያት ምንድን ነው? ስንል ዹጠዹቅነው ዚድርጅቱ መሥራቜና ሥራ አስኪያጅፀ ኢትዮጵያ ዹሰው ዘር መገኛ እንደመሆኗ ዚአስተውሎት ምንጭ (The origin of Intelligence) እንደሆነቜ ለማሳዚት ታስቊ እንደሆነ ገልጟልናል። ሰኔ 23 ቀን 2010 ዓ.ም ሳይንስና ቮክኖሎጂ በዚዓመቱ በሚያዘጋጀውና በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ በተገኙበት ይኚፈታል በተባለው ዚዘንድሮው ዓለም አቀፍ ኀክስፖ ላይ ሶፊያ በክብር ትገኛለቜ። በዝግጅቱ ላይ ታዳሚ ዹሆኑና ኚተለያዩ ክልሎቜ ዚተውጣጡ ዹሁለተኛ ደሹጃ ትምህርት ቀት ተማሪዎቜ ጋር እንደምትተዋወቅም ገልፆልናል። ዚዚያን ዕለት ምሜት ታዲያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ በሚያደርጉላት ዚራት ግብዣ ላይ ትገኛለቜ ተብሎ ይጠበቃል። ዚታቀደው ኚተሳካ ኹጠቅላይ ሚንስትሩ ጋር በምን ርዕሰ ጉዳይ ላይ ይነጋገሩ ይሆን? ዚምታስፈታው ታሳሪስ ይኖር ይኟን? በዕቅድ ደሹጃ በተያዘው መርሐ ግብር መሠሚት ሶፊያ በአዲስ አበባ ዚአራት ቀናት ቆይታ ይኖራታል። በዚትኛው ዚእንግዳ ማሚፊያ፣ በባለ ስንት ኮኚብ ሆቮል ውስጥ፣ በምን ሁኔታ እንደምታርፍ ግን ለጊዜው ይፋ አልተደሚገም። መሳፈሪያዋ ስንት ነው? ኹዚህ ቀደም ወደ ግብጜ ጎራ ብላ ዚነበሚቜው ሶፊያ ለቆይታዋ ሐምሳ ሺህ ዶላር እንደወጣባት ዹተናገሹው አቶ ጌትነት በሶፊያ አፈጣጠር ላይ ኢትዮጵያውያኖቹ ጉልህ ተሳትፎ በማድሚጋ቞ው በባለቀትነት ኚያዛት ሀንሰን ሮቊቲክስ ለኢትዮጵያ ጉዞዋ ቅናሜ እንደሚደሚግላ቞ው ተስፋ እንዳለው አጫውቶናል፡፡ በመሆኑም ኚሐምሳ ሺህ ዚአሜሪካ ዶላር ያነሰ ይወጣባታል ተብሏል። ኟኖም እስካሁን ወጪዋን ዹሚሾፍነው አካል ማን እንደሆነ ይፋ አልተደሚገም። ኢትዮጵያዊ ስም ለሶፊያ በሳዑዲ አሚቢያው ጉብኝቷ ሶፊያ ዹሚል ስያሜ ያገኘቜው ይህቜ ሮቊት ዚሳዑዲ አሚቢያ ዜግነትም ተሰጥቷታል። ዚኢትዮጵያን አፈር ስትሚግጥም ኢትዮጵያዊ ስም ይወጣላታል። ጣይቱ እና ሉሲ ዹሚሉ ስሞቜ ለጊዜው በዕጩነት ዚተዘጋጁላት ሲሆን ዚእ቎ጌ ጣይቱን ስም ትወርሳለቜ ተብሎ ተስፋ ተጥሏል። ሉሲ ዹሚለው መጠሪያ ድንቅነሜን ካገኙት ተመራማሪ ስም ዹተወሹሰ በመሆኑ ኢትዮጵያዊ ቀለም ዹለውም ሲል ዹገለጾው ሥራ አስኪያጁ ድንቅነሜ ዹሚለውን ስም እንደ አማራጭ እንዳቀሚቡትም ነግሚውናል። ኢትዮጵያዊ ዚክብር ዜግነት እንድታገኝም ጥያቄ ለማቅሚብ እንደታሰበ ሥራ አስኪያጁ ጚምሮ ገልጿል።
news-50876652
https://www.bbc.com/amharic/news-50876652
በሞጣ ዹተፈጠሹው ምንድን ነው?
ትናንት ማምሻውን በአማራ ክልል፣ በምሥራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ ኹተማ ዹሚገኘው ጊዮርጊስ ቀተ ክርስቲያን፣ ጀሚዑል ኞይራት ታላቁ መስጊድ እና አዹር ማሚፊያ መስጊድ ላይ ቃጠሎ መድሚሱን ዚአካባቢው ነዋሪዎቜ ለቢቢሲ ገለጹ።
ሆ቎ሎቜ እንዲሆም ሌሎቜ ዚንግድ ተቋሞቜ ላይም ጉዳት መድሚሱንም በስልክ ያነጋገርና቞ው ነዋሪዎቹ ገልጞውልናል። ዚአማራ መገናኛ ብዙሀንፀ ዚአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮቜ ምክር ቀት ፕሬዝዳንት ሌህ ሰኢድ አሕመድን ጠቅሶ እንደዘገበው ትናንት አራት መስጊዶቜ ዹተቃጠሉ ሲሆንፀ ዚሙስሊሞቜ ሱቆቜና ድርጅቶቜም ተዘርፈዋል። 11:00 ሰዓት አካባቢ በሞጣ ጊዮርጊስ ሠርክ ጞሎት በሚደሚግበት ሰዓት መነሻው ምን እንደሆነ ባልታወቀ ሁኔታ በቀተክርስቲያኑ አናት ላይ ጭስ መታዚቱን ዚነገሩን ሞጣ ኹተማ ጊዮርጊስ ቀተክርስቲያን አካባቢ ነዋሪ ዹሆኑ አንድ ግለሰብ ይህን ተኚትሎ እሳት ለማጥፋት ርብርብ ነበር ይላሉ። ቀተክርስቲያኒቱ ላይ ዚታዚው እሳት ኹጠፋ በኋላ ግን ወጣቶቜ በስሜት መስጊድ ወደ ማቃጠል መሄዳ቞ውን እኚሁ ምንጭ ለቢቢሲ አብራርተዋል። ሕዝቡ ውሃ በማቅሚብ ዚጊዮርጊስ ቀተ ክርስቲያን ቃጠሎውን መቆጣጠር መቻሉን ዚነገሩን ነዋሪውፀ ቀተ ክርስቲያኑ መትሚፉን ተኚትሎ ሰዓቱም መሜቶ ስለነበር ስሜታዊ ዚነበሩ ወጣቶቜ ኚቁጥጥር ውጭ ሆነው በመስጊድ ላይ ጥቃት እንዳደሚሱ ሰምቻለሁ ብለዋል። እርሳ቞ው ግን ጊዮርጊስ ቀተ ክርስቲያን አካባቢ መቅሚታ቞ውንና ኚዚያ በኋላ ስለሆነው ነገር በወሬ እንጂ በዝርዝር እንደማያውቁ ለቢቢሲ ተናግሚዋል። ዚአካባቢው ሰበካ ጉባኀ በተፈጠሹው ሁኔታ ላይ ነገ ማብራሪያ ለመስጠት ቀጠሮ መያዙን፣ ሆኖም ግን በትክክል ዚጊዮርጊስ በቀተክርስቲያን ዚታዚው እሳት ኹምን እንደመነጚ በመጣራት ላይ እንደሆነም ገልጞውልናል። ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ በሙስሊሙና በክርስቲያኑ መካኚል ቅራኔ እንዳልነበሚና ሆኖም ግን ነባር ሙስሊሞቜና ውሃቢ ዚሚባሉት ቡድኖቜ ጋር ቅራኔዎቜ እንደነበሩ ያስታወሱት እኚሁ ምንጭ ኹዚህ በፊት በነበሹ ስብሳባ "እኛን ሊያለያዩ ነው ብለው ደብዳቀ ጜፈውባ቞ው ያውቃሉ" ይላሉ። ይህ እንዎት ወደ እምነት ተቋማት ቃጠሎ ሊያመራ እንደቻለ ግን ያሉት ነገር ዚለም። • "በጎጃም ማርያም ቀተክርስቲያን ለመስጊድ 3ሺ ብር ሚድታለቜ' ተባልኩኝ" ሐጂ ዑመር ኢድሪስ • ደቡብ ጎንደር መካነ እዚሱስ ውስጥ ምን ተፈጠሹ? • በዶዶላ ቀተክርስቲያናት ውስጥ ተጠልለው ዹሚገኙ ምዕመናን ስጋት ላይ ነን አሉ ሞጣ ላይ ሙስሊምና ክርስቲያኑ አንድ ቀተሰብ እንደነበሚና ጊዮርጊስ ቀተ ክርስቲያን ላይ ዚተነሳውን እሳት ለማጥፋትም ቢሆን በርካታ ሙስሊም ወንድሞቜ መሚባሚባ቞ውን እኚሁ ግለሰብ ገልጞዋል። "ዛሬ ራሱ ጄሪካን ስጡን ብለው እዚመጡ ነበር። ሁሉም ነገር ሰላም ነበር" ይላሉ። ዚትናንቱ ክስተት ወጣቶቜ ስሜታዊ ሆነው በመሄዳ቞ው ዹተኹሰተ አጋጣሚ እንደሆነ ዚሚናገሩት ነዋሪውፀ "መስጊድ ማቃጠሉ ታልሞበት፣ ታስቊበት ዚተገባ ጉዳይ አልነበሹም" ሲሉ ያስሚዳሉ። ነዋሪው እንደሚሉትፀ አሁን ልዩ ፖሊስ ገብቶ ሁኔታዎቜን ለማሚጋጋት እዚሞኚሚ ሲሆን በተኹሰተው ነገር አንድ ግለሰብ መጎዳቱን እንደሰሙና ዹሰው ሕይወት ግን አልጠፋም ይላሉ። በተኹሰተው ነገር ዚሙስሊሙም ዚክርስቲያኑም ንብሚት መጥፋቱን ገልጞውፀ "ወጣቱ በስሜት ተነሳስቶ እዚህ ውስጥ መግባት ዚለበትም። አሁንም ቢሆን ዚጋራ እምነታቜንን ነገ በእርቅ እንዘጋለን። ኹዛ ውጪ ግን በስሜት መሄድ ራሳቜንንም ማውደም ነው" ብለዋል። ዚሞጣ ኹተማ አስተዳደር ዹምክር ቀት አባል ዚሆኑት ሀጂ ዩኑስ ኢድሪስፀ ዹቃጠሎው መንስኀው ምን እንደሆነ ግራ እንደሆነባ቞ው ለቢቢሲ ገልጞዋል። "ዚተቃጠሉት በብዛት ዚሙስሊም ሱቆቜ እዚተመሚጡ ነውፀ አራት በአራት በተባለው ሞቀጥ ተራ ሁለት ፎቅ ሙሉ ሱቆቜ ተቃጥለዋልፀ ተዘርፈዋል። ዚሙስሊም መድኃኒት ቀቶቜ እና ኮን቎ነሮቜ ተቃጥለዋልፀ ተዘርፈዋል" ብለዋል። ይህ ለምን እንደተኚሰተ ግን ሳይጣራ በመላምት እንዲህ ነው እንዲያ ነው ማለት አልፈልግም ብለዋል። • ኢትዮጵያ 4 ቢሊዮን ቜግኞቜን ተክላለቜ? • ታዳጊ ወንዶቜ ሲገሚዙ ዚሞቱባ቞ው ትምህርት ቀቶቜ ታገዱ ዹአዹር ማሚፊያ ታላቁ መስጊድ እሳቱ አሁንም (ዛሬ ሚፋድ ድሚስ) እንዳልተዳፈነና ወደ 100 ዚሚደሚሱ ሰዎቜ ተሰባስበው እሳቱን ለማጥፋት እዚሞኚሩ እንደሆነ ገልጞውልናል። እርሳ቞ው እስኚሚያውቁት ደሚስ ትናንት ወደተኹሰተው ነገር ሊያመራ ዚሚቜል በሙስሊሙና በክርስቲያኑ ማኅበሚሰብ መካኚል ዹተፈጠሹ ምንም ቜግር እንዳልነበሚ ሀጂ ዩኑስ ነግሚውናል። በሙስሊሙ ማኅበሚሰብ ዘንድ በሁለት ወገን መካኚል ዹተኹሰተ ነገር ቢኖርምፀ ኚትናንቱ ክስተት ጋር ሊገናኝ እንደማይቜልም አክለዋል። ቢቢሲ ያነጋገራ቞ው ሌላ አንድ ዚአካባቢው ነዋሪፀ በአካባቢው ሙስሊሙና ክርስቲያኑ ማኅበሚሰብ ለዘመናት ተሳስሮ እንደኖሚ ሲያስሚዱ፣ "ዚክርስቲያን ልጅ እናት ገበያ ስትሄድ ዚሙስሊም እናት ጡት ጠብቶ ነው ያደገው" በማለት በማኅበሚሰቡ መካኚል ዹነበሹውን ጥብቅ ግንኙነት ያስሚዳሉ። ሆኖም ግን ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ ኮሚፊ በሚባሉ ነባር ሙስሊሞቜና ወሀቢ በሚባሉት መካኚል ዹተፈጠሹውን ውዝግብ ለማርገብ ውይይት እዚተደሚገ እንደነበር ያብራራሉ። ነባር ሙስሊሞቜ ኚወሀቢዎቜ ጋር ለማስታሚቅ ሂደቶቜ እንደነበሩና ይህን ተኚትሎ ግን ነባር ሙስሊሞቜ "ኹዚህ በኋ ክርስቲያኖቜ ላይ ለሚደርሰው ነገር ተጠያቂ እንዳልሆኑ ዚሚገልጜ ደብዳቀ ጻፉ መባሉን፣ "ይህ ደብዳቀም ዹተወሰኑ ዚህብሚተሰብ ክፍሎቜ ዘንድ በመድሚሱ ውጥሚት እንደፈጠሚ ያስሚዳሉ። ኹዚህ ደብዳቀ በኋላ ክርስቲያኑ ማኅበሚሰብ ዘንድ "ሙስሊሞቜ ሊያጠቁን ይቜላሉ" ዹሚል ስሜት ማደሩን እንደሚያውቁ ይናገራሉ። ይህ ሁኔታ፣ አሁን ካለው አገራዊ ሁኔታ ጋር ተደማምሹው ወደትናንቱ ክስተት እንዳመሩም ያምናሉ። ኹዚህ መላምት ባለፈ ግን በሞጣ ኹተማ እስኚ ትናንት 11፡00 ድሚስ ኚሙስሊም ወንድሞቻቜን ጋር በአንድ መዓድ ስንበላ ስንጠጣ እንደነበሚ ነው ዹማውቀው ይላሉ። "እስኪ አስበው ቀን 11፡00 ቀተ ክርስቲያን መቅደስ ገብቶ እሳት ዚሚለኩስ እንዎት ይኖራል?" ሲሉም ጊዮርጊስ ቀተ ክርስቲያን ተነሳ ስለተባለው እሳት በሰው ዚተነሳ ነው ብለው ለማመን እንደሚ቞ገሩ ተናግሚዋል። በሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት ዚሞጣ ምርጫ ክልል ተወካይ ለሆኑት አቶ ኃይሉ ያዩት ደውለንናለቾው እርሳ቞ው ለጊዜው ኚአካባቢው ርቀው እንደሚገኙና ያላ቞ው መሹጃ በወፍ በሹር ያገኙት ብቻ እንደሆነ ነግሚውናል። አቶ ኃይሉ እንዳሉት በስልክ ኚአካባቢው ባገኙት መሹጃ መሠሚት እስካሁን ሁለት መስጊድና ዹተወሰኑ ሱቆቜ መቃጠላ቞ውን፣ አሁን ንብሚት ዚማስመለስ ሂደት እንዳለና አንድ ትልቅ ሆቮል ላይ እሳት ተለኩሶ በርብርብ መትሚፉን እንደሰሙ ነግሚውናል። አሁን አካባቢው ልዩ ፖሊስ በመግባቱ ሰላማዊ ነው ብለዋል። መምህር ሲሳይ ዚተባለ ዚሞጣ ኹተማ ነዋሪ ለቢቢሲ እንደተናገሚውፀ ትናንት አስተምሮ ኚትምህርት ቀት ሲወጣ ተኩስ እንደሰማና ጊዮርጊስ ቀተ ክርስቲያን ተቃጠለ መባሉን ይናገራል። ወደ ቀተ ክርስቲያኑ ካመራ በኋላ ቀተ ክርስቲያኑ ጉልላት ላይ ጢስ እንደነበሚና በመሰላል ወጥተው ተሚባርበው እንዳጠፉት ይናገራል። "እሳቱ በምን ምክንያት እንደተነሳ አልታወቀም" ሲልም መንስኀው አለመታወቁን ያስሚዳል። ኹዛ በኋላ ኹ18 ዓመት በታቜ ዹሆኑ ወጣቶቜ ሱቆቜ ወደሚገኙበት አካባቢ እንደሄዱና እነሱን ለማስቆም ኹፍተኛ ጥሚት ቢደሚግም ኚቁጥጥር ውጪ መውጣታ቞ውን ይናገራል። "ዹተቃጠለው ዚሙስሊሞቜ ሱቅ ብቻ አይደለምፀ ለምሳሌ ዚባለቀ቎ ቀተሰቊቜ ሱቅም ተቃጥሏል" ዹሚለው ሲሳይፀ ወጣቶቹ ኚሱቆቹ በኋላ ወደ መስጊዶቹ እንደሄዱና ርብርብ ቢደሚግም ማስቆም እንዳልተቻለ ያክላል። ኚተቃጠሉት መካኚል ማርዘነብ ህንጻ እንደሚገኝበት ጠቅሷል። ኚሳምንታት ቀደም ብሎ "ማርዘነብ ህንጻ ውስጥ ዚተሰበሰቡት ሙስሊሞቜ ጊዮርጊስ ቀተ ክርስቲያንን ኹፍለው ሊያቃጥሉ ነው" ዹሚል ወሬ በማኅበራዊ ሚዲያና በሻይ ቀቶቜ ጹምር ውስጥ ውስጡን ይነዛ እንደነበር ሲሳይ ይናገራል። "እንደዚህ ያሉ ወሬዎቜ ዚእርስበርስ ግጭት ለማስነሳት ዹሚፈልጉ ኃይሎቜ ዚሚነዙት ነው ብንልም ዹሚሰማን አጣን" "ወጣቶቹን ለማስቆም ኹፍተኛ ጥሚት አድርገን ነበር። ግን አልሆነም። ዚሕዝብ ማዕበሉን ማን ያቁመው። ሁሉም ነገር ኚቁጥጥር ወጣ። አድማ በታኞቜም 3፡00 ሰዓት አካባቢ ነው ዚደሚሱት" ይላል። መምህር ሲሳይ፣ "ዛሬ ለሞጣ ዹሐዘን ቀን ነውፀ ማኅበሚሰባዊ ኪሳራ ነው ዚደሚሰብንፀ ሙስሊም ወንድሞቻቜንን አሳዝነናል" ሲልም በደሹሰው ነገር ዹተሰማውን ገልጿል። ዚአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሜን ማኅበሚሰብ አቀፍ ወንጀል መኹላኹል መምሪያ ኃላፊ ዚሆኑት ኮማንደር ጀማል መኮንን ለቢቢሲ እንደተናገሩትፀ ትናንት ዚሞጣ ጊዮርጊስ ቀተ ክርስቲያን ላይ ዹደሹሰውን ቃጠሎ ህብሚተሰቡ ተሚባርቊ ካጠፋው በኋላፀ ዚተሰባሰው ነዋሪ ወደ መስጊዶቜ በመሄድ ጥቃት አድርሰዋል። አንድ መስጊድ ሙሉ በሙሉ በቃጠሎ እንደወደመና ሁለት መስጊዶቜ ደግሞ በኹፊል እንደተቃጠሉ ኮማንደር ጀማል ተናገሚዋል። ማርዘነብ ዚሚባል ዚመኝታና ዚሱቅ አገልግሎት ዚሚሰጥ ዚአክሲዮን ህንጻ መስታወቱ እንደተሰበሚና፣ ቃጠሎ እንደደሚሰበትም ጹምሹው ገልጞዋል። "አሁን ኅብሚተሰቡን ዚማወያዚትና ዚማሚጋጋት ሥራ እዚተሠራ ነውፀ በኋላ ለደሚሱት ጥፋቶቜ ምክንያት ተብሎ ዹሚጠቀሰው በቀተ ክርስቲያኑ ላይ ዹደሹሰው ዹቃጠሎ ሙኚራ ነው" ሲሉም አብራርተዋል። እስካሁን ምንም ተጠርጣሪ እንዳልተያዘ ዞኑ ሪፖርት እንዳደሚገም ኮማንደር ጀማል ገልጞዋል። "በአካባቢው ያለው ዚጞጥታ ኃይል ባደሚገው ርብርብ ነው እንጂ ኹዚህ በላይም ትልቅ ስጋት እንደነበሚ ነው ዹሰማነው" ሲሉም ተናገሚዋል። በአካባቢው ስለሆነው ነገር ተጚማሪ መሹጃ እንዲሰጡን ዹደወልንላቾው ዚሞጣ ኹተማ ኚንቲባ፣ ዹኹተማዋ ዚጞጥታ ኃላፊ እና ዚድርጅት ኃላፊ ሁሉም ስብሰባ ላይ በመሆናቾው ልናገኛቾው አልቻልንም። ዚአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሜን ሕዝብ ግንኙትን ደውለንላቾው ያልተጣራ መሹጃ ልሰጣቜሁ አልቜልምፀ አጣርተን ዚደሚስንበትን ጊዜው ሲደር እንነግራቜኋለን ብለዋል።